1 083
Subscribers
+924 hours
+207 days
+1530 days
Posts Archive
በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የከተማና መሠረተ ልማት ሚንስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሣኒ የተመራ ልዑክ በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር የሚገኙ በአለም ባንክ ድጋፍ የተደረገባቸውን ፕሮጀክቶች የስራ አፈጻጸም ጉብኝት አደረገ።
በዚህ የጉብኝት መርሃግብር በአስተዳደሩ ወረዳ 3 ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎ የተገነባውን የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ እና ለአገልግሎት መስጫ አስፈላጊ የሆኑ ግብዓት ተሟልተው ለህብረተሰቡ እየሰጡ ያለውን አገልግሎት በስፍራው በመገኘት ተመልክተዋል።
በተያያዘ "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ቢሮው ከአስተዳደሩ የኢንዱስትሪዎች ጋር በፈጠረው መግባባት ብዙ ወጣቶችን ተጠቃሚ መሆናቸው ይታወቃል ይህንንም በስራ ላይ የሚገኙ ወጣቶችንና ቅጥር የፈጸሙ ኢንዱስትሪዎችን ጎብኝተዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሐምሌ 11/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአስተዳደሩ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞችን ከጊዜው ጋር በሚራመድ የስርአት ማዕቀፍ ውስጥ እንዲመሩ የሚያስችል ስራዎችን በመስራት ላይ እንገኛለን፡፡
አቶ ሙሉጌታ ኃ/ማርያም
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር
ኢንተርፕራይዞች የሚገጥማቸውን የገበያ ተደራሸነትን ለመቅረፍ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በሚመራው የኢትዬጵያ ሥራ ገበያ መረጃ ስርአት ፕሮጀክት ለምቶ ተግባራዊ የሆነው መተግበሪያና ድህረገፅ ላይ በሰፊው እንዲመዘገቡ የንቅናቄ መርሃግብር መጀመሩ ተገለጸ፡፡
ይህም የንቅናቄ ዘመቻ በአስተዳደሩ 01 ወረዳ የተጀመረ ሲሆን በሁሉም ወረዳዎች ላይ በተመሳሳይ የሚቀጥል ይሆናል ምዝገባውን እያካሄደ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ኃ/ማርያም እንደተናገሩት ኢንተርፕራይዞች ምርታቸውን ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ሀገራት ኦንላይን በማስተዋወቅ የሚሸጡበትና ክፍያ የሚቀበሉበት መሆኑን በማንሳት ሁሉም ኢንተርፕራይዞች በመመዝገብ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሐምሌ 10/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በ2016 ዓ.ም ለሁለተኛ ዙር እየተተገበረ የሚገኘው "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም የስራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄደ፡፡
በመድረኩም የቢሮውና በአስተዳደሩ የሚገኙ አንድ ማዕከላት አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በግምገማ መድረኩም አንድ ማዕከላት አሁን ላይ እስከ ደረሱበት የወጣቶቹ በኢንዱስትሪዎች የስራ ላይ ልምምድ ሶስተኛ ወራቸው ያለውን የሥራ አፈጻጸም አቅርበው ባቀረቡት አፈጻጸም ላይ በመነሳት ሀሳብ አስተያየት ተሰጥቶ ያለባቸውን ክፍተትም ለማሟላት ያግዝ ዘንድ የቀጣይ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በመድረኩ ተገኝተው በቀጣይ በተለይ የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ወጣቶች በአግባቡ እና ያለማቆራረጥ የስራ ላይ ልምምዱን እያደረጉ እንደሚገኝ ክትትልና ድጋፉ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና ልምምዱን በሚቀጥሉት ሶስት ወራት ሲያጠናቅቁ ከስራ ጋር የሚተሳሰሩበትን ሁኔታ የማመቻቸት ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሐምሌ 10/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በማዕድናት፣ በፈጠራዎች፣ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አይ ሲ ቲ ዘርፍ ላይ እየሰራችሁ ላላችሁ ኢንተርፕራይዞች በ3ኛው ዓመታዊ የመካከለኛ አነስተኛ እና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ/MSME/ መድረክ ላይ በመገኘት ልምድና ተሞክሮአችሁን እንዲሁም ሥራችሁን ለማጋራት ትልቅ ዕድል ተመቻችቶላችኋል ፡፡
በማዕድናት፣ በፈጠራዎች፣ በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ እና አይ ሲቲ ዘርፍ የተለያዩ ሥራዎችን በመስራት ሁለት ዓመትና በላይ የቆያችሁ ኢንተርፕራይዞች ይህ ዕድል እንዳያመልጣችሁ፡፡
ፎረሙ የሚካሄደው በአፍሪካ ናሚቢያ ሲሆን መስፈርቱን የምታሟሉ ኢንተርፕራይዞች በፍጥነት ከዚህ በታች በተቀመጠው ሊንክ በመግባት መመዝገብ ትችላላችሁ ፡፡
ሊንክ https://msmeforum.africa/
የዚህ የአፍሪካ ኢንተርፕራይዞች አውታረ መረብ ስብስብ ፕሮግራም አባል መሆንም ትልቅ ዕድል ነው፡፡
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+9
የድሬዳዋ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሳተላይት ካንፓስ፥ በተለያዩ የሞያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ሠልጣኝ ተማሪዎችን በዛሬው እለት በጋራ በመሆን አስመረቁ።
በምረቃ ስነ-ስርአቱ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር አቶ ሃርቢ ቡህ እንደገለጹት የአንድ አገር ኢኮኖሚና ማህበራዊ እድገት የሚወሰነው በትምህርት የሰለጠነ የሰው ሃይል የዳበረ እውቀትና ክህሎት ባላቸው ዜጓቿ በመሆኑ በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል።
ምክትል ከንቲባው አክለውም ድሬዳዋ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመገንባት በምታደርገው ጥረት ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ተመርቀው የሚወጡ ተማሪዎች ያልተቆጠበ ተሣትፎ ቀዳሚውን ድርሻ የሚይዝ ብለዋል።
በዚህ የምርቃት ስነ -ስርአት ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር አቶ ሃርቢ ቡህ፣ ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ፣ የሁለቱም ኮሌጆች ዲኖችና ም/ዲኖች እንዲሁም መምህራን እና ተመራቂዎችና የተመራቂ ቤተሠቦች ተገኝተዋል ።
በምረቃ ስነ-ስርአቱ ላይ ከድሬዳዋ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሳተላይት ካንፓስ ጋርመንት ቴክኖሎጂ ትምህርት ክፍል ተማሪ የሆኑት ሲሳይ ዘውዱ እና በእምነት ጠብቀው 3.91 እኩል ነጥብ በማምጣት የወርቅ ሜዳሊያ እና የዋንጫ ተሸላሚ ሲሆኑ፥ ከኢትዮ ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሳተላይት ካንፓስ ተማሪ ኤርሚያስ ከፍያለው 3.95 በማምጣት የወርቅ ሜዳሊያና የዋንጫ ተሸላሚ በመሆን አጠናቋል።
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ሀምሌ6/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ከኔዘርላንድ የልማት ድርጅት (SNV) RAYEE ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ለተደራጁ 50 ኢንተርፕራይዞች የኢንተርፕሩነርሺፕና የህይወት ክህሎት ስልጠና እንዲወስዱ በማድረግ የሥራ መነሻ ድጋፍ "start up support" ግምቱ 3,869,715 ብር የሚገመት ድጋፍ ተደረገ፤
የድጋፍ ርክክብ ስነ ስርዓቱ ላይ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተገኝተው ባደረጉት ንግግር የአስተዳደሩ ካቢኔ ባስቀመጠው ውሳኔ የከተማና የገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራዎች በአንድ ላይ እንዲመሩ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ቢሮው የተለያዩ ሥራዎችን በመስራት ላይ እንደሚገኝ አንስተው በተለይ ከአጋር አካላት ጋር በመቀናጀት የገጠሩን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ ከኔዘርላንድ የልማት ድርጅት (ኤስ ኤን ቪ) ጋር በመሆን በዛሬው ዕለት የተደረገው የሥራ ማስጀመሪያ ድጋፍ ለተደራጁ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለራሳቸውና ለሌሎች እንዲፈጥሩ የሚያስችል ማሳያ ሆኖ የሚቀርብ ነው ብለዋል፡፡
የSNV ድርጅት ተወካይ አቶ ኃይለየሱስ ለምለም በበኩላቸው ድርጅታቸው ከቢሮው ጋር በመተባበር ሥራ የሌላቸው ሴቶችና ወጣቶችን በገጠርና በከተማ በማደራጀት በተለያዩ ርዕስ ጉዳዮዎች በተለይ በኢንተርፕሩነርሺፕና በህይወት ክህሎት ስልጠናዎችን በመስጠት እና ተደራጅተው በሚሰማሩበት ሥራ ዘርፍ ላይ አሰፈላጊው ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ጠቅሰው የዛሬው ድጋፍ 41 በገጠር እና 9 በከተማ ለተደራጁ 71 ሴቶች እና 4 ወንዶች በአጠቃላይ 74 ወጣቶች ከሶስት ነጥብ ስምንት ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል ፡፡
በመቀጠል ድጋፍ የተደረገላቸው ተጠቃሚ የተደራጁ ወጣቶች እንደተናሩት በሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮና በSNV የጋራ ትብብር ለተሰጣቸው ስልጠና እና የአይነት ድጋፍ በማመስገን ለበለጠ ሥራ ለመሥራት እንደሚያነሳሳቸው ተናግረው ከዚህ በፊት በዚሁ የዶሮ እርባታ ላይ በአነስተኛ አቅምና እውቀት የጀመሩትን አስፍተውና አጠናክረው ለመስራትም መነሳሳት የፈጠረላቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በድጋፍ ርክክብ ሥነ ስርዓቱ ላይ የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ፣ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን እንዲሁም የገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራ አመራሮችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሐምሌ 5/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+1
የሥራ ማስታወቂያ
****
Ethiopian Airlines
መረጃውን ሼር በማድረግ ለወጣቶቻችን ተደራሽ እናድርግ!!
#ዜና | በድሬዳዋ ስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የተዘጋጀ፥ አሰሪ እና ሰራተኛ የሚያገናኝ ዓውደ ርዕይ ተካሄደ።
በአስተዳደሩ ያለውን ስራ አጥነትን መቅረፍ አላማው ያደረገው ይህ ዓውደ ርዕይ፥ በተለያዩ የትምህርት መስኮች የተመረቁ ስራ ፈላጊዎችን ከአሰሪዎች ጋር በማገናኘት እንዲቀጠሩ ማድረግ ዋነኛ ግቡ መሆኑ ተገልጿል።
በአውደ ርዕዩ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ፥ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው፥ ለዜጎች ምቹና ዘላቂ የስራ እድል መፍጠር እንደ አስተዳደር ትኩረት ከሚሰጣቸው ዓበይት ተግባራት መካከል አንዱ መሆኑን ተናግረዋል።
አቶ ሮቤል አክለዉም ሥራ ፈላጊዎችን በማደራጀት፥ አሰሪ እና ሰራተኞች የሚገናኙበትን መድረክ በማመቻቸት እንዲሁም በውጭ ሀገር ሥምሪት ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚቻልባቸው መንገዶች መሆናቸውን ጠቅሰው፥ እነዚህን አማራጮች በመጠቀም የስራ አጥነት ቁጥርን ለመቀነስ እየሰራን ነዉ ብለዋል።
የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው በስራ ፈላጊነት የተመዘገቡ 15 ሺህ ወጣቶች እንደሚገኙ አስታውቀው፥ ቢሯቸው አብዛኛዎቹን ወደ ስራ ማስገባት መቻሉን ገልጸዋል።
የድሬዳዋ ነፃ ንግድ ቀጠና እና ኢንደስትሪ መንደር ሰፊ የሰዉ ሀይል እንደሚፈልጉ ይታወቃል ያሉት ወ/ሮ ፈጡም በየጊዜው ግንዛቤን በማዳበር አሰሪዎችን እና ወጣቱን በማገናኘት፣ የድሬዳዋን ልማት የምናፋጥንበት ጊዜው አሁን ነዉ ብለዋል።
ስራ ፈላጊ ወጣቶች በበኩላቸው ከማስታወቂያ ሰሌዳዎች ላይ ቀጣሪ ተቋማትን በመፈለግ ሳንደክም፥ ከአሰሪዎች ጋር ፊት ለፊት እንድናገኝ እና በተማርነው የትምህርት መስክ ስራ እንድናገኝ አውደ ርዕዩ ጥሩ እድል ፈጥሮልናል ብለዋል።
በአውደ ርዕዩ ላይ 13 ቀጣሪ ድርጅቶች እንዲሁም 2 ኮሌጆችን ጨምሮ ስራ እና ሰራተኛ አገናኝ ፌዴሬሽኖች ተሳትፈዋል።
©️ Dire Tv
በድሬዳዋ ከተማ አሸዋ የገበያ ስፍራ በተከሰተው የእሳት አደጋ ጉዳቱ የደረሰባቸውን የንግዱን ማህበረሰብ መልሶ ለመማቋቋም ሁሉም የበኩሉን አስተዋፆ እንዲያበረክት ከታች በተዘረዘሩት የባንክ የሒሳብ ቁጥር ሁሉም ማህበረሰብ የአቅሙን ድጋፍ በማድረግ እንረባረብ።
Via Robel Getachew
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ከፍተኛ የሥራ አጥነት ቁጥር መቀነስን መነሻ በማድረግ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በመቋቋሙ በሀገሪቱ ውስጥ ከፍተኛ ለውጥ ማስመዝገብ ተችሏል፡፡
በበጀት ዓመቱ ለ3.8 ሚሊዮን ዜጎች ሥራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡
ከዚህ ቁጥር ውስጥ 3.4 ሚሊዮን ያህሉ በአገር ውስጥ የተፈጠረ ሲሆን በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ደግሞ 332 ሺ የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡
ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦https://t.me/fdre_mols
ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official
የ2017 የፌዴራል በጀት 971.2 ቢሊዮን ብር ሆኖ ፀደቀ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ2017 በጀት ዓመት የፌደራል መንግስት በጀትን 971.2 ቢሊዮን ብር አድርጎ አፀደቀ።
©️ etv
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
