ሙስተጃብ ፋሪስ አሊት አባልቾ (አቡ ጁለይቢብ)
የተለያዩ የሱና መሸይኾችና ዑስታዞች ምክሮች እና ፈታዋዎች የሚቀርቡበት ቻናል ቀን 1 12 2015
Show more202
Subscribers
No data24 hours
+17 days
-130 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
Repost from ዛዱል ኸይር Zadul Kheir
የ«ተቅሊድ» ምርኮኛ አትሁን፤ በ«ተቅሊድ» እንጂ (ሌላ) ካቃተህ፣ በተከተልከው ነገር ሌላን አታስገድድ።
ሸይኽ ኢሊያስ አሕመድ
3200
Repost from ☀ሁዳ መልቲሚዲያ |HUDA MULTIMEDIA
አዲስ ጥንቅር በሸይኽ ኢልያስ አህመድ
ርዕስ:-
جواب عن بعض مسائل الجرح والتعديل
በጀርህና ተዕዲል ዙሪያ ለሚነሱ አንዳንድ ጥያቄዎች ምላሽ
ዝግጅት ሸይኽ ኢልያስ አህመድ
2910
Repost from አህመድ ፈንታቢል
ግዴታ ሶላት የሚሰግዱ ሁለት ሰዎች ብቻ ከሆኑ
እኩኩል ትዩዩ ሁነዉ መስገድ ያለባቸዉ
አንዳድ ፉቅሃዎች አማሙ ቀደም ማለት አለበት ያሉ አሉ ይሄ ትክክል አይደለም
👇👇👇
ፎሎዉ አድርጉኝ ያላደረጋቹሁ
ሊንኩ ተጫኑ👇👇👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=61555445233071&mibextid=ZbWKwL
3400
Repost from የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)
ለምንድ ነው ሰለፎች ቂሳ ከሚያበዙ ቀሳሶች ያስጠነቀቁት?!
“ከቀሳሶች(ተራኪዎች) ተጠንቀቁ! ማለትም ሰባኪዎች… ምክንያቱም ብዙ ጊዜ በሰዎች ላይ ተጽእኖ ማሳደር ስለሚፈልጉ ተረቶቹን እና ቂሳዎችን አያረጋግጡም፣ ስለሆነም ያነበቡትን ሁሉ ሳያረጋግጡ ያመጣሉ፣ የተቀጠፉ ወይም ደካማ ሊሆኑ የሚችሉ ሀዲሶችን ይጠቅሳሉ፣ አያረጋግጡም። ምክኒያቱም ጭንቀታቸው በሰዎች ላይ ተጽእኖ ማሳደር ነው፣ ለዚህም ነው የቀደሙት ሰለፎች "ቀሳሶች”ን ማድመጥ የከለከሉት፣ ምክንያቱ ሐዲሶችን ሳያረጋግጡ ስለሚናገሩ ነው….. አዎን።”
ሸይኽ ሷሊህ አል ፈውዛን - አላህ ይጠብቃቸውና
።
https://t.me/sultan_542800
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
በአይነቱ ልዩ የሆነ ኢስላማዊ ኮንፈረንስና የመልቲሚዲያ ማስጀመሪያ ፕሮግራም
እነሆ በዘመናዊው የዲጂታል አለም ላይ እንገኛለን፣ በዚህ መድረክ ላይ ኢስላማዊ ዳዕዋ ወሳኝ አሻራውን የሚያሳርፍበት ጊዜ አሁን ነው በማለት፤ በመሻኢኾችና በኡስታዞች የተደራጀው " ሐኒፍ መልቲሚዲያ" ዘመናዊ ስቱዲዮ በመገንባት በ10 የተለያዩ የማህበራዊ ሚድያ ፕላትፎርሞች ኢስላማዊ ዳዕዋን ለማህበረሰባችን ለማድረስ ዝግጅቱን አጠናቆ የብስራት ዜና ለማሰማት አብሮነታችሁ ከእኛ ጋር እንዲሆን ስንጋብዛችሁ በታላቅ ደስታ ነው።
ቦታ: አዲስ አበባ ስታዲየም በሚገኘው ኦሮሚያ ባህል ማዕከል
ቀንና ሰአት: እሁድ ጥር 26፣ 2016 ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ
☑️YouTube
🔗https://www.youtube.com/@HanifMultimedia
☑️TikTok
🔗https://tiktok.com/@HanifMultimedia
☑️Telegram
🔗https://t.me/HanifMultimedia
☑️Facebook
🔗https://www.facebook.com/HanifMultimedia
☑️ X(twitter)
🔗https://x.com/HanifMultimedia
☑️Ummalife
🔗https://ummalife.com/HanifMultimedia
☑️Linkedin
🔗https://www.linkedin.com/in/HanifMultimedia
☑️Threads
🔗https://www.threads.net/@HanifMultimedia
☑️Instagram
https://www.instagram.com/HanifMultimedia
☑️Whatsapp
🔗https://whatsapp.com/channel/0029VaL8R3hEVccEYgBgbd0W
" የዲን ጉዳይ ሀላፊነቱ የሁሉም ሙስሊም ነው"
" ሐኒፍ የከፍታዎ ማዕቀፍ"
2200
Repost from የአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን የመማማሪያ መድረክ
🔹ኢኽ^ዋንን በጨረፍታ፣ በዑለማዎች እይታ
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
ልብ በሉ! የማቀርበው የዑለማኦችን ንግግር እንጂ የራሴን አይደለም። ይህንን የማሳስበው ኢኽዋን ሲነካ ደርሰው አራስ ነብር ለሚሆኑ አካላት ለአፍታ ቆም ብለው ጉዳዩን እንዲያጤኑት ለማስታወስ ነው። አብዛኞቹ ኢኽዋን ሲነካ የሚንጨረጨሩ ወገኖቻችን በተሳሳተ ስብከት ስለተሞሉ እንጂ ለሐቅ ጥላቻ ኖሯቸው አይደለም። ስለዚህ ጉዳዩን ከተለያዩ አቅጣጫዎች እንዲመለከቱ በማገዝ ከሰመመናቸው እንዲነቁ መስራት ያስፈልጋል። ከነዚህ መንገዶች ውስጥ አንዱ ደግሞ የዑለማእ ንግግሮችን ማሳየት ነው። በኢኽዋን ክፉ ስብከት ተበክለው ዑለማኦችን እስከመወንጀል የደረሱ ቢኖሩም ዛሬም ድረስ ለታላላቅ የሱና ዑለማኦች ክብር ያላቸው ወገኖቻችን ቀላል አይደሉም። ወደ ዑለማኦቹ ንግግር አልፋለሁ።
1. አሕመድ ሻኪር (ግብፃዊ)፡-
“የሸይኽ ሐሰን አልበና እና የሙስሊም ወንድማማቾቹ ንቅናቄ የኢስላማዊ ደዕዋን ወደ አፍራሽ የጥፋት ደዕዋ የገለበጡ ናቸው። ኮሙኒስቶች እና አይሁዳውያን እንደሚረዱት በተጨባጭ እናውቃለን።” [ሹኡኑ ተዕሊም ወልቀዷእ፡ 48]
2. ኢብኑ ባዝ፡-
“አላህ መልካም ይዋልልዎትና ህዝቦቼ ወደ 73 ቡድኖች ይከፋፈላሉ። አንዷ ስትቀር ሁሉም የእሳት ነው የሚለውን የነብዩ ﷺ ሐዲሥ መሰረት በማድረግ ሺርካ ሺርክና ቢድዐዎች ያለባቸው የተብሊግ ቡድን እና ቡድንተኝነትና በመሪዎች ላይ በማመፅ ሰሚና ታዛዥ ባለመሆን ልዩነት የሚፈጥሩት ኢኽዋነል ሙስሊሚን እነዚህ ሁለት አንጃዎች ከጠፊዎቹ አንጃዎች ውስጥ ይካተታሉን?”
መልስ፡- ከ72ቱ ውስጥ ይገባሉ። የአህሉ ሱናን ዐቂዳ የጣሰ ከ72ቱ ውስጥ ይገባል። “ህዝቦቼ” ሲሉ የተፈለገው ለጥሪያቸው አዎንታዊ መልስ የሰጡትና እሳቸውን መከተልን ያንጸባረቁትን ነው። እነዚህም 73 ናቸው። የምትድነዋ ያቺ የተከተለቻቸውና በዲናቸውም ላይ የፀናችው ናት። በ72ቱ ውስጥ ግን ከ ሃ ዲም ይኖራል፤ ወንጀለኛ ይኖራል። ሙብተዲዕም ይኖራል። ብዙ ክፍል ነው።
ጠያቂ፡- ስለዚህ እነዚህ ሁለት አንጃዎች ከ72ቱ (ጠፊ አንጃዎች) ውስጥ ይገባሉ ማለተ ነው?”
ኢብኑ ባዝ፡- አዎ! ከ72ቱ ውስጥ ናቸው።” [ሸርሑል ሙንተቃ የካሴት ቅጂ]
ይሄ ፈትዋ ከመሞታቸው ሁለት አመት ወይም ከዚያ ባነሰ ጊዜ ጧኢፍ ውስጥ የተናገሩት ነው።
3. ሸይኽ ሙቅቢል አልዋዲዒይ (የመናዊ)፡-
ጥያቄ፡- በዘመናችን የሚገኙት የሱሩሪያና የኢኽ^ዋን ቡድኖች ከሱና ከሚወጡ ቡድኖች ውስጥ ናቸውን?”
መልስ፡- ከአህሉ ሱና አይቆጠሩም። ክብረ ቢስ ናቸው። የሚቀረው በተናጠል አባላቶቻቸው ላይ ብይን መስጠት ነው። አባሎቻቸው ላይ በተናጠል ብይን መስጠት አንችልም። ምክንያቱም አላዋቂ መሀይም ሊሆን ይችላልና። የኢኽ^ዋንና የሱሩሪያን ሰበካ የሚያውቅ ወደዚያ የሚጣራና ለነሱ በጭፍን የሚሞግት የሆነው ቁንጮ ግን እሱ ከምትድነዋ አንጃ ውስጥ አይደለም ልንል ይቻለናል።” [ቱሕፈቱል ሙጂብ፡ 10]
ጥያቄ፡- ከኢኽ^ዋን አልሙስሊሚን አንፃር የአህሉ ሱና ወልጀማዐ አቋም ምን ሊሆን ይገባል?”
መልስ፡- ከኢኽ^ዋን አልሙስሊሚን አንፃር የአህሉ ሱና ወልጀማዓ አቋም መንገዳቸው የፈጠራ መንገድ እንደሆነ ይፈርዳሉ። በተናጠል አባላቱ ዘንድ ስንመጣ መንገዱን ካወቀ በኋላ የሚፀናበትም እንዲሁ ሙብተዲዕ ነው። መንገዱን ሳያውቅ እንዲሁ ኢስላምንና ሙስሊሞችን እረዳለሁ ብሎ የሚያስብ ግን እንደ ስህተተኛ ይቆጠራል።” [ቱሕፈቱል ሙጂብ፡ 10]
ሐሰን አልበና እና ሰይድ ቁጥብ ወደ አላህ በሚደረገው ጥሪ ላይ ኢማሞች (መሪዎች) ናቸው የሚል አለ” ተብለው ሲጠየቁ “አዎ ኢማሞች ናቸው። ነገር ግን ኢማምነታቸው ለቢድዐ ባለቤቶች ነው…” ብለው ነው የመለሱት።
4. ሸይኽ ፈውዛን
ጥያቄ፡- እነዚህ አንጃዎች ከ72ቱ ጠፊ አንጃዎች ውስጥ ይገባሉን?
መልስ፡- አዎ። ወደ ኢስላም ራሱን ከሚያስጠጋ ውስጥ በደዕዋ ወይም በዐቂዳ ወይም በሆነ የኢማን መሰረቶች ውስጥ የአህሉ ሱና ወልጀማዐን ዐቂዳ የሚጣረስ ሁሉ ከ72ቱ አንጃዎች ውስጥ ይገባል። ዛቻውም ይመለከተዋል። በተቃርኖው ልክ ውግዘትና ዛቻም ይኖረዋል።” [አልአጅዊባ]
5. ሸይኽ ዐብዱል ሙሕሲን አልዐባድ
ስለተብሊግና ኢኽ^ዋን ቡድኖች ሲጠየቁ እንዲህ ብለው መልሰዋል፡-
እነዚህ የተለያዩ አዳዲስ ቡድኖች መጤዎች ናቸው። በ14ኛው ክ/ዘመን ነው የተወለዱት። … ለምሳሌ የኢኽዋን ቡድን ከነሱ ዘንድ የገባ ወዳጃቸው ነው። ይወዳጁታል። ከነሱ ያልሆነን ከሱ ተቃራኒ ይሆናሉ። ከነሱ ጋር ከሆነ ግን ቆሻሻ ከሆኑ የአላህ ፍጡሮች ቢሆንም፣ ራ*ፊ*ዳ (ሺዐ) ቢሆንም ወንድማቸው ወዳጃቸው ነው። ለዚህም ነው አካሄዳቸው ያለፈ ያገደመን የሚሰበስበው። ሶሐባን የሚጠላ ራ*ፊ*ዲ ለምን አይሆንም?!...” [ፈታወል ዑለማእ ፊልጀማዓት ወአሠሪሃ ፊ ቢላዲል ሐረመይን]
6. ሷሊሕ ኣሊ ሸይኽ
የኢኽ^ዋን አልሙስሊሚን ቡድንን በተመለከተ ጎላ ካሉ መታወቂያዎቻቸው ውስጥ አንዱ ትክክለኛ ማንነታቸውን መደበቅ፣ መለዋወጥ፣ ይጠቅመናል ብለው የሚያስቡት ዘንድ መቀራረብ፣ ትክክለኛ ገፅታቸውን ግልፅ አለማውጣት ነው። ማለትም በሆነ በኩል ሲታይ ባ*ጢ*ኒ*ያ ናቸው።…
ሌላኛው ኢኽዋኖችን ከሌሎች የሚለያቸው እነሱ ሱናን አያከብሩም። የሱና ሰዎችንም አይወዱም። ምንም እንኳን ይህንን አደባባይ ባያወጡትም። ግና በተጨባጭ ሱናን አይወዱም። ወደሱና ሰዎችም አይጣሩም። ..” [ፈታወል ዑለማእ ፊልጀማዓት ወአሠሪሃ ፊ ቢላዲል ሐረመይን] የቻለ ሙሉውን ይስማ።
ይህንን እንደ ሰደድ እሳት የተሰራጨ ብልሹ አስተሳሰብ የዑለማዎችን ፈትዋዎች በማጣቀስ፣ የኢኽ^ዋኖች ከባባድ የዐቂዳ ጥፋቶችን ሚዛናዊ የሆነና ለዐቂዳው ዋጋ የሚሰጥ ሰው አይቶ እንዲፈርድ በማቅረብ ማጋለጥ ያስፈልጋል። አቡበክር ብኑ ዐያሽ ረሒመሁላህ “ሱኒይ ማነው?” ተብለው ሲጠየቁ ሱኒይ ማለት “ስሜቶች (ቢድዐዎች) ሲወሱ (ሲጋለጡ) ለየትኛዋም ወግኖ የማይቆጣ ነው” ይላሉ። [አሸሪዐህ፡ ቁ.፡ 2112]
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ የካቲት 02/2009)
T.me/dawudyassin
የአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን የመማማሪያ መድረክ
نفهم الكتاب والسنة بفهم سلفنا الصالح ቁርአንና ሐዲስን በሰለፎች ግንዛቤ እንገንዘብ
4100