en
Feedback
ASTU Muslim Students Jeme'a

ASTU Muslim Students Jeme'a

Open in Telegram

The aim of this Channel is to broadcast information and to assist muslim students in ASTU by sharing info about Qur'an and kitab derses,remembering others.So,please share it to muslim students For any questions,comment use this bot @ASTU_MSJ_Bot

Show more
2 211
Subscribers
-124 hours
-107 days
+830 days
Posts Archive
📢 ማስታወስ 🔶 ዛሬ ማታ በአላህ ፈቃድ በቀጥታ ስርጭት በቴሌግራም እና በዩቱብ ኪታብ ደርስ ይኖረናል።       📚 المستوى التمهيدي - الأذكار والآداب 📚 አል-ሙስተዋ አል-ተምሂዲ - አል-አዝካር ወል-አዳብ (የመግቢያ ደረጃ - ዚክሮች እና ስነ-ምግባራት)    •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• 🗓  ሰኞ ሙሐረም 21/1447 ሂጅሪ, (ሰኔ 29,2018), ⏰ ሰዐት: ማታ 3፡00 (በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር)። 🕌 ቦታ: ቀጥታ ስርጭት በቴሌግራም (Telegram) እና በዩቱብ (YouTube)             •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• 🎙 الأُسْتَاذُ أَبُو مُسْلِمٍ عُمَرُ بنُ حَسَنٍ الْعَرُوسَيّ 🎙 በኡስታዝ አቡ ሙስሊም ኡመር ሐሰን  አልአሩሲ አል-አይመሮ (ሀፊዘሁላህ) 📌 ትምህርቱን ለመከታተል ይህን ቻናል ይቀላቀሉ 👇👇👇 🌐 https://t.me/AbumuslimAlarsi

📢 ማስታወስ 🔶 ዛሬ ማታ በአላህ ፈቃድ በቀጥታ ስርጭት በቴሌግራም እና በዩቱብ ኪታብ ደርስ ይኖረናል።       📚 المستوى التمهيدي - الأذكار والآداب 📚 አል-ሙስተዋ አል-ተምሂዲ - አል-አዝካር ወል-አዳብ (የመግቢያ ደረጃ - ዚክሮች እና ስነ-ምግባራት)    •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• 🗓  ቅዳሜ ሙሐረም 19/1447 ሂጅሪ, (ሰኔ 27,2018), ⏰ ሰዐት: ማታ 3፡00 (በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር)። 🕌 ቦታ: ቀጥታ ስርጭት በቴሌግራም (Telegram) እና በዩቱብ (YouTube)             •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• 🎙 الأُسْتَاذُ أَبُو مُسْلِمٍ عُمَرُ بنُ حَسَنٍ الْعَرُوسَيّ 🎙 በኡስታዝ አቡ ሙስሊም ኡመር ሐሰን  አልአሩሲ አል-አይመሮ (ሀፊዘሁላህ) 📌 ትምህርቱን ለመከታተል ይህን ቻናል ይቀላቀሉ 👇👇👇 🌐 https://t.me/AbumuslimAlarsi

🔖 አዲስ የክረምት Online ደርስ ማስታወቂያ >○ የምንቀራው ኪታብ 📚 ኹላሰቱ ኑሪል የቂን ፊ ሲረቲ ሰዪዱል ሙርሰሊን >○ የኪታቡ ይዘት 🔹 ኪታቡ የነቢያችንን ﷺ የሕይወት ታሪክ ከውልደታቸው
🔖 አዲስ የክረምት Online ደርስ ማስታወቂያ >○ የምንቀራው ኪታብ 📚 ኹላሰቱ ኑሪል የቂን ፊ ሲረቲ ሰዪዱል ሙርሰሊን >○ የኪታቡ ይዘት 🔹 ኪታቡ የነቢያችንን ﷺ የሕይወት ታሪክ ከውልደታቸው ጀምሮ ፣ የነቢይነት መጀመሪያቸውን፣ በመካና በመዲና የነበራቸውን ቆይታ፣ ያደረጓቸውን ውጊያዎች፣ የሰሃባዎችን ሁኔታና የዕለተ ሞታቸውን ታሪክ በዝርዝር በክፍል በክፍል ይተርካል። 🔹 ኪታቡ የተዘጋጀው: በሙአሊፍ ዑመር አብዱልጀባር ረሒመሁሏህ ነው። >○ የኪታቡ ጠቀሜታ 🔹 የነቢዩን ﷺ ሕይወት በዝርዝር ማወቅ በልብ ውስጥ ያላቸውን ቦታ ከፍ በማድረግ፣ የእርሳቸውን ፈለግ ለመከተል ከፍተኛ መነሳሳትን ይሰጣል። የእርሳቸውን የላቀ ሥነ-ምግባር፣ ትዕግስትን፣ ለሰዎች ማዘንና የነበራቸውን ስብእና በመማር የራስን ሕይወት ለማነጽም ይረዳል። ~ ⏳ ቀን: ዘወትር ማክሰኞና ሐሙስ ⏱ ሰአት: ከመግሪብ እስከ ዒሻ 👤 በኡስታዝ ኢብራሒም ኸይረዲን 📎 የሚተላለፍበት ቻናል: ቂርዓት_ቻነል @qireat6k

ምሽት 3:00 ሰዓት አይቀርም! ሰርፕራይዞች አሉን። በሰዓቱ እንገናኝ!! https://www.tiktok.com/@aaumsu ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! © aaumsu @AAU6kilojemea

ውድ ወንድሞች እና እህቶች በቅድሚያ የአላህ ሰላምና እዝነት ብናንተ ላይ ይስፈን። በመቀጠልም የASTUMSJ አባላት እና ወዳጆች በሙሉ በዚህ ልዩ በሆነው የAddis Ababa University Muslim Students Union (AAUMSU) ወንድሞቻችን በTikTok ላይ ባዘጋጁት ታላቅ የpannel discussion በንቃት እንድትሳተፉ ስንጋብዛቹ እንደምትሳተፉ ተስፋ በማድረግ ነው። ነገ ምሽት ከ3 ሰዓት ጀምሮ ለመሳተፍ የሚከተለውን የTikTok Account Link በመጫን ይግቡ፣ እግረ መንገድዎን follow ያድርጉ። https://www.tiktok.com/@aaumsu جزاكم الله خيرا.

ታላቁ የቲክቶክ መድረክ ደረሰ _ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ! ! ! ስለኒቃብ መጠየቅ በምርቃት ቀን እስከ ማሳሰር ከመድረሱ በፊት ጀምሮ ስላለው የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ
ታላቁ የቲክቶክ መድረክ ደረሰ _ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ! ! ! ስለኒቃብ መጠየቅ በምርቃት ቀን እስከ ማሳሰር ከመድረሱ በፊት ጀምሮ ስላለው የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ በሰፊው ይዳሰሳል። ሕገ- መንግስቱን ጥሰው ስለሚጥሱት መብት ሕጋዊ ቦታ በሰፊው ይተነተናል። ከእኛ ስለሚጠበቀው ነገርም በደንቡን ውይይት ይደረጋል። ሙባረክ አደም፦ በድምፃችን ይሰማ የመብት ትግል እንቅስቃሴ ፈርቀዳጅ ታጋይ፤ አክቲቪስት፤ ቲክቶከር፤ ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕና፤ የሂባ ፋውንዴሽን መስራች ነው። ፕሮግራማችንን በመድረክ መሪነት የሚያስተናብርልን ይሆናል። ሙስጠፋ ሺፋ፦በድምፃችን ይሰማ የመብት ትግል እንቅስቃሴ ወቅት ለታሰሩት ጠበቃ ሆኖ አገልግሏል፤ አሁንም በጥብቃና ሙያው አንቱታን ካተረፉ ባለሙያዎች መካከል ነው። ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ሕጋዊ መሠረት ያብራራልናል። የሕያ ኢብኑ ኑሕ፦የንፅፅር ትምህርት መምህር፤ የሒዳያ ኢስላማዊ ማህበር መስራች እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕና ነው። ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ ያብራራልናል። ሁሴን ዩሱፍ፦የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፀሐፊ ሲሆን ከማን ምን ይጠበቃል የሚለውን በዝርዝር ያስቀምጣል። መቅረት አይታሰብም። ጀመዓዎች በቻናሎቻችሁ ላይ አሰራጩት። ሁሉም ለሁሉም ያድርስ። በአንድነት በአንድ መድረክ ተሰባስበን ስለመብቶቻችን እውቀትን እንጨብጥ። 🗓 ቀን፡ ሰኞ፣ ሰኔ 22 ⏰ ሰዓት፡ ከምሽቱ 03፡00 ሰዓት እውቀትን መፈለግ መብት ነው፤ እምነትንም በክብር መተግበር እንዲሁ! የቲክቶክ ገፃችንን Follow በማድረግ ዝግጅቱን ይጠብቁ፦ https://www.tiktok.com/@aaumsu ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! © aaumsu @AAU6kilojemea

AS WR WB! ዛሬ ምሽት ኢንሻአላህ። እንዳይቀሩ ተጋዘዋል፣ ለሌሎችም በማጋራት ያግዙን፡ እናመሰግናለን! Harra Galgala Inshaa'allaah. Akka hinhafne, affeeramtanii
AS WR WB! ዛሬ ምሽት ኢንሻአላህ። እንዳይቀሩ ተጋዘዋል፣ ለሌሎችም በማጋራት ያግዙን፡ እናመሰግናለን! Harra Galgala Inshaa'allaah. Akka hinhafne, affeeramtanii jirtu; Namoota biroos affeeruun nu gargaaraa: Galatoomaa!

“Ramadan booda sooma hundarra caalu” kan jedhameef soomni ji’a Muharram — Ashuuraan — kunoo gaheera. Imaamu Muslim hadiisa Ab
“Ramadan booda sooma hundarra caalu” kan jedhameef soomni ji’a Muharram — Ashuuraan — kunoo gaheera. Imaamu Muslim hadiisa Abu Hureyraa (رضي الله عنه) irraa gabaafame jechuun dabarsaniin dabarsaniin, Ergamaan Rabbii ﷺ «Ramadan booda soomni hundarra caalu sooma ji’a Muharram, -ji’a Rabbii-, ti.» jedhaniiru. Dhugumatti, soomni kabajamaan kun guyyaa Kamisa (Waxabajjii 16 / June 25) irra kan oolu ta'a. Kanaaf carraa warqee kana akka hin dhabneef, soomuun akka dabarsinu isin yaadachiisuu barbaanne. Dabalataanis, qajeelfama Nabiyyii keenya ﷺ kan “Yahuudota faallessaa” jedhu hojiirra oolchuuf, guyyaa tokko isa dura yookaan guyyaa tokko isa booda dabalannee akka soomnu yaadachiisuun ergaa keenya arraa xumurre. Rabbiin kheyrii hunda nuu haa qunnamsiisu. https://t.me/ASTU_MSJ

“ከረመዳን በኋላ ከሁሉ በላጩ ጾም” የተባለለት የሙሀረም -ዓሹራዕ- ፆም እነሆ ደርሷል። ኢማሙ ሙስሊም ከአቡ ሑረይራ (رضي الله عنه) በመጣ ዘገባ ባስተላለፉት ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ ﷺ «ከ
“ከረመዳን በኋላ ከሁሉ በላጩ ጾም” የተባለለት የሙሀረም -ዓሹራዕ- ፆም እነሆ ደርሷል። ኢማሙ ሙስሊም ከአቡ ሑረይራ (رضي الله عنه) በመጣ ዘገባ ባስተላለፉት ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ ﷺ «ከረመዳን በኋላ ከሁሉ የተሻለው ጾም የአላህ ወር የሆነው ሙሐረም ወር ጾም ነው» ብለዋል። እነሆ ይህ የተከበረ ፆም ቀን በእለተ ሐሙስ (ሰኔ 16 / June 25) ላይ ይውላል። በመሆኑም ይህን ወርቃማ እድል እንዳናስመልጥ በፆም እናሳልፈው ስንል ልናስታውሳችሁ ወደድን። በተጨማሪም «አይሁዶችን ተቃረኑ» የሚለውን የነብያችን መርሆኧዊ አስተምህሮት እንተገብር ዘንድ አንድ ቀን ቀደም ብለን ወይም አንድ ቀን አስከትለን እንፁም የሚለውን የዛሬው መልዕክታችን ማሳረግያ አደረግን። አላህ ኸይሩን ሁሉ ይግጠመን። https://t.me/ASTU_MSJ

" قَالَ كَلَّا إِنَّ مَعَيَ رَبِّي سَيَهْدِينِ " " [Muusaan] ni jedhe: “lakkisaa! Dhugumatti, Gooftaan kiyya na wajjin jira,
" قَالَ كَلَّا إِنَّ مَعَيَ رَبِّي سَيَهْدِينِ " " [Muusaan] ni jedhe: “lakkisaa! Dhugumatti, Gooftaan kiyya na wajjin jira, Inni [furmaatatti] na qajeelcha.” Yeroo Fira'oonii fi loltoonni isaa duubaan isaan ari’an, fuuldura isaaniitiin immoo garbi dambali’u sun jiru... yeroo dhiphinnaa sanatti Amantiin Nabiyyii Muusaa (A.S) Rabbitti qaban hin raafamne ture . Guyyaan Rabbiin garba addaan baasee Isaa fi ummata isaa bilisa baase, dhugaan (Haqni) soba (Baaxila) irratti injifannoo argate kun — Guyyaa Ashuraati! ​Seenaa injifannoo guddaa kanaa fi Sunnaa sooma Raasulaa (S.A.W) ilaalchisee Jama'aan Barattoota Musliimaa ASTU Muhaadaraa Live addaa ta’e isiniif qopheesseera. ​🎤 Keessummaa Addaa: Sheek Mas'uud ​🎙️ Keessummeessaa (Host): Ramadaan Urgeessoo ​🗓️ Guyyaa: Roobii, Waxabajjii 17, ​⏰ Sa'aatii: Galgala sa'aatii 3:00 (LT) irraa eegalee ​Humni amantiinii fi iccitiin injifannoo maal akka ta'e waliin kan barannu ta'a. ​Hordofuuf qophiidhaa? Sa'aatii jedhametti Toora Telegraama keenyaan nu eegaa! 👉@ASTU_MSJ

" قَالَ كَلَّا إِنَّ مَعَيَ رَبِّي سَيَهْدِينِ " " (ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡ " ​ፈርዖንና ሰራዊቱ ከበስተጀርባ ሲያባርሯቸው
" قَالَ كَلَّا إِنَّ مَعَيَ رَبِّي سَيَهْدِينِ " " (ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡ " ​ፈርዖንና ሰራዊቱ ከበስተጀርባ ሲያባርሯቸው፣ በፊታቸው ደግሞ ማዕበሉ የሚናወጠው ባህር በነበረበት በዚያ አስጨናቂ ቅጽበት... ነቢዩ ሙሳ (ዐ.ሰ) በአላህ ላይ የነበራቸው እምነት ፍጹም አልተናወጠም ነበር። አላህም ባህሩን ከፍሎ እርሳቸውንና ህዝቦቻቸውን ነፃ ያወጣበት፣ ሀቅ ባጢልን ያሸነፈበት ታላቅ ቀን — የአሹራ ቀን ነው! ​ይህንን ታላቅ የድል ታሪክና የረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) የፆም ሱና አስመልክቶ የ ASTU ሙስሊም ተማሪዎች ጀምዓ ልዩ የላይቭ ሙሀደራ አዘጋጅቶላችኋል። ​🎤 ልዩ እንግዳ፦ ሼኽ መስዑድ ​🎙️ አስተናጋጅ (Host)፦ ረመዳን ኡርጌሶ ​🗓️ ቀን፦ ረቡዕ፣ ሰኔ 17 ​⏰ ሰዓት፦ ከምሽቱ 3፡00 (LT) ጀምሮ ​የእምነትን ኃይልና የድልን ሚስጥር አብረን የምንማርበት ልዩ ምሽት ይሆንልናል። ​ለመከታተል ዝግጁ ናችሁ? በሰዓቱ በቴሌግራም ቻናላችን ይጠብቁን! 👉 @ASTU_MSJ

Assalamu Alaikum Warahmatullahi Wabarakatuh, 🎓✨ Congratulations to our beloved ASTUMSJ graduating members! ✨🎓 I would like
Assalamu Alaikum Warahmatullahi Wabarakatuh, 🎓✨ Congratulations to our beloved ASTUMSJ graduating members! ✨🎓 I would like to extend my heartfelt congratulations to all our brothers and sisters who are graduating from Adama Science and Technology University (ASTU). On behalf of Adama Science and Technology University Muslim Students Jemea (ASTUMSJ), we are proud of your achievement and celebrate this important milestone with you. Your success is a reflection of your hard work, patience, and dedication. We also sincerely appreciate and thank all members who have contributed to ASTUMSJ throughout the years, especially those who took leadership roles, organized activities, and actively participated in serving and strengthening our Jemea. May Allah reward you all abundantly and make your knowledge beneficial for Ummah. May Allah bless your next journey, open doors of success. Congratulations once again, dear graduates! 🎉🤍 Sebonsa Ahmed Ali General Amir — ASTUMSJ

USTAZ AMMAAR SHEIKH AMIN URJILEE_DACHII 2

🌙 Ergaa Xumuraa Bara 1447 Yaa ilma Adam, kan Rabbiin waan uume hunda caalaa kabaja sitti godhee hoo! Obboleewwan Kee kan biyya duniyaa waliin dhuftan baay'ee dha. Garuu ammoo obbolaan kee kan ati beektu baay'een turtii yeroo isaaniif kennamee xumuruun gara ganda lammaffaa godaananii jiru. 🤔 Ati hoo hanga yoom ganda duniyaa kana turta laata? Gaafii kanaaf deebii hin qabdu. Kanaaf baallamni deemsa keetii osoo hin gahin, galaa gaafa galaa qopheeffadhu. ⏳ Kana gochuuf ammoo yeroo amma caalu goonkumaa hin argattu; kanaaf ammumarraa jalqabii galaa Kee sassaabbadhu. 📌 Lubbuu Kee gamaggami 📌 Balleessaa keef araara gaafadhu 📌 Dogongoroota kee sirreeffadhu 📌 Hojii gaarii baay'isi 📌 Amala kee bareechi 📌 Rabbii keetti dhiyaadhu 🌱 Bara hijraa 1447ffaa kana haala kanaan xumurii, miira haarawaan bara haarawa simadhu. 🤲 Rabbi si haa gargaaru. https://t.me/ASTU_MSJ

🌙 የ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የመጨረሻ መልዕክት የአደም ልጅ ሆይ! አላህ ከፈጠራቸው ሁሉ በላይ ክብር የሰጠህ ሆይ! ከአንተ ጋር ወደዚህ የዱንያ ሀገር የመጡ ወንድሞችህ ብዙ ናቸው። ነገር ግን ከምታውቃቸው ወንድሞችህ ብዙዎቹ የተሰጣቸውን ጊዜ ጨርሰው ወደ ሁለተኛው መንደር ተሰደው ሄደዋል። 🤔 አንተስ በዚህ የዱንያ መንደር እስከ መቼ ትቆያለህ? ለዚህ ጥያቄ መልስ የለህም። ስለዚህ የጉዞህ ቀጠሮ ሳይደርስ፣ የጉዞ ስንቅህን አዘጋጅ። ⏳ ይህን ለማድረግ ደግሞ ከአሁን የተሻለ ጊዜ የለህም፤ ስለዚህ ከአሁኗ ሰዓት ጀምረህ ስንቅህን ሰብስብ። 📌 ራስህን መርምር 📌 ለወንጀሎችህ ይቅርታ ጠይቅ 📌 ስህተቶችህን አርም 📌 መልካም ሥራህን አብዛ 📌 ባህሪህን አሳምር 📌 ወደ አላህ ቅረብ 🌱 ይህንን 1447ኛ የሂጅራ ዓመት በዚህ መልኩ አጠናቅቀህ፣ አዲሱን ዓመት በአዲስ መንፈስ ተቀበል። 🤲 አላህ ይርዳህ! https://t.me/ASTU_MSJ

LAST MESSAGE OF THE YEAR
LAST MESSAGE OF THE YEAR

እጅግ አስቸኳይ መረጃ! የነገው ፕሮግራም እንዲሰረዝ ተደርጓል❗ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በረያን መስጂድ በነገው እለት ሊያዘጋጀው የነበረው የፓናል ውይይት እንዲሰረዝ ተደርጓል። ለዚህም በዋነኝነት የተሰጠው ምክንያት "የመንግስት አካላት ፕሮግራሙ እንዳይካሄድ ክልከላ አድርገዋል" የሚል ነው። ህብረታችንም ሙስሊሙን ማህበረሰብ የሚወክለው መጅሊስ እና ሌሎችም የሚመለከታቸው አካላት የዜጎችን ህገ-መንግስታዊ እና ተፈጥሯዊ መብት ከማስከበር አኳያ ከጎናችን በመቆም መፍትሄ ያመጣሉ ብለን ተስፋ አድርገን የነበረ ቢሆንም፤ በሚያሳዝን ሁኔታ ተገቢውን ከለላ፣ ድጋፍ እና መፍትሄ ማግኘት አልተቻለም። ፕሮግራሙን ለመታደም ከተለያየ ዩኒቨርስቲ መጥታችሁ አዲስ አበባ ያደራችሁ የጀመዓ አሚሮች፤ አላህ (ሱ.ወ) ጥረታችሁን በጀነት ይመንዳችሁ። ጁምዓ በየመስጂዱ ጥሪ ሲደረግ በእምባ ታጅባችሁ ዱዓ በማድረግ ጭምር እንደምትመጡ የነገራችሁን እናት አባቶች፤ አላህ ዱዓችሁን ይቀበልልን። ከተለያየ ሀይስኩል፣ ኮሌጅ እና መድረሳዎች ለመምጣት የተሰናዳችሁ እህት ወንድሞቻችን፣ የሚዲያ ሽፋን ለመስጠት የተሰናዳችሁ ቲቪዎች፣ ኡስታዞች፣ መሻይኾች እና የክብር እንግዶቻችን፤ ኒያችሁን አላህ ያሳምርላችሁ። መስጂድ የሁሉም ሙስሊም የጋራ ቤት ነው። በሰላማዊ መንገድ መሰባሰብ እና ስለጋራ ጉዳያችን መወያየት በማንም ሊገፈፍ የማይችል ሕገ-መንግስታዊ መብታችን ነው። የሚዳፈንም ሆነ ወደኋላ የሚጎተት ጥያቄ የለንም። መብታችንን ለማስከበር የምናደርገው ጉዞ በህግ፣ በስርአት እና በኢስላማዊ አዳብ የታነፀ ሆኖ ይቀጥላል። ይህ መልእክት በጊዜው ያልደረሳቸው እና ለፕሮግራሙ በነገው እለት ወደ መስጂዱ የሚመጡ በርካታ ወንድም እና እህቶች ሊኖሩ ስለሚችሉ፤ ይህንን ፕሮግራም ያገዳችሁ አካላት፣ ቢያንስ እንኳን ይህን አላዋቂ እንግዳ በእንግድነቱ ልክ በክብር በማስተናገድ እና በጥሩ ቃል በመመለስ ከሚጠበቅባችሁ ትንሹን እንድታደርጉ እናሳስባለን። ቀጣዩን አቅጣጫችንን በቅርቡ እስከምናሳውቅ ድረስ በዱዓ፣ በሰብር እና በፅናት ጠብቁን። "በእርግጥም የአላህ እርዳታ ሁሌም ቅርብ ነው።" (አል-በቀራህ 214) ©aaumsu @AAU6kilojemea

📢 የStory Challenge! የነገውን ፕሮግራም ለብዙ ተማሪዎች እንዲደርስ ይህን ፖስተር በTelegram, WhatsApp, Instagram እንዲሁም Facebook Story ላይ ያጋሩ። አንድ St
📢 የStory Challenge! የነገውን ፕሮግራም ለብዙ ተማሪዎች እንዲደርስ ይህን ፖስተር በTelegram, WhatsApp, Instagram እንዲሁም Facebook Story ላይ ያጋሩ። አንድ Story ማድረግ ብቻ ብዙ ሰዎችን ፕሮግራሙ ላይ እንዲገኙ ሊያነቃቃ ይችላል። ጓደኞቻችሁም story እንዲያደርጉት ጋብዟቸው! 📌 ርዕስ፦ "የሙስሊም ተማሪዎች መብት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት!" ⏰ እሁድ ከጠዋቱ 2:30 📍 ጦርሀይሎች ረያን መስጅድ 3ኛ ፎቅ #StoryChallenge #ShareAndInvite #NiqabIssue #panelDiscussion @AAU6kilojemea

ውድና የተከበራችሁ የ6ኪሎ ሙስሊም ተማሪዎች፤ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስንገባ አላማችን ተምሮ ፤ ዕውቀት ጨብጦ ራስን፣ ቤተሰብን እንዲሁም ሀገርን መጥቀም ነው። ሆኖም ግን ይህ ጉዞ ለብዙዎቻችን የአልጋ በአልጋ እንዳልሆነ ይታወቃል። በተለይም ማንነታችንን የሚገልጸው ሂጃባችንን እና ኒቃባችንን በአንዳንድ ተቋማት ውስጥ እንደ ስጋት ተቆጥሮ፣ እንደ ኋላ ቀርነት ታይቶ ወይም በ"ህግና መመሪያ" ስም ሲገፋና ሲጨቆን ማየት የየዕለቱ ህመም ሆኗል። እህቴ ሆይ! ሂጃብሽ የግል ምርጫሽ ብቻ ሳይሆን ሐይማኖታዊ ግዴታሽና የማንነትሽ መገለጫ ነው። በግቢ ውስጥ በኒቃብሽ ምክንያት የሚደርስብሽ መገለል፣ የሚሰነዘርብሽ አድሏዊ አመለካከትና "አውልቂ" የሚሉ የጫና ድምፆች መብትሽን ካለማወቅ የሚመነጩ ናቸው። በሐገሪቱ ህገ-መንግስትም ሆነ በትምህርት ተቋማቱ መመሪያ መሰረት፣ ማንም ሰው በሐይማኖታዊ አለባበሱ ምክንያት ሊገለልም ሆነ ትምህርት ሊከለከል አይገባም! ወንድሜ ሆይ! የእህቶችህ መገፋት ያንተም የዲንህ መከበርና የቋሚነትህ ጉዳይ ነው። መብቱን የማያውቅ ተማሪ መብቱን ማስከበር አይችልም። የነገው ምሁርነትህ እና ታላቅነትህ ትርጉም የሚኖረው ዛሬ በግቢ ውስጥ ያለህን መብት በብልሃትና በህግ አግባብ ማስከበር ስትችል ነው። ነገስ ለምን እንገናኛለን? ነገ “ የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች” በሚል ርዕስ የሚኖረን የፓናል ውይይት ስለ መብቶቻችንን በዝርዝር የምንረዳበት ትልቅ መድረክ ይሆናል ። • በሂጃብ ላይ የሚደርሱ ጫናዎችን በህግ አግባብ እንዴት መጋፈጥ እንችላለን? • በተቋማቱ ውስጥ ያለን መብት እስከ የት ድረስ ነው? • ጭቆና ሲደርስብን በምን መልኩ ድምፃችንን እናሰማ? ለእነዚህ እና ሌሎችም ጥያቄዎች ምሁራንና የህግ ባለሙያዎች ምላሽ ይዘው ይጠብቁሃል/ሻል። አንተ/ቺ ካልመጣህ/ሽ... አንድ ትልቅ ድምፅ ይጎድላል! ዝምታ ጭቆናን ያባብሳል፤ በአንድነት መታገል ግን ነፃ ያወጣል። ዛሬ ለመብታችን መከበር ካልቆምን ነገ ለሚመጣው ትውልድ የምናስረክበው ዩኒቨርሲቲ የጭቆና ተቋም ይሆናል። ስለዚህ ነገ እሁድ ካለንበት ቦታ ሁሉ ወጣ ብለን ስለ መብታችን ለመወያየት ዝግጅታችንን እናጠናቅ! 📌 ርዕስ ፦ "የሙስሊም ተማሪዎች መብት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት!" 📍ቦታ፦  ጦርሀይሎ ረያን መስጅድ 3ኛ ፎቅ ⏰ ቀን፦ ነገ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ ለጓደኞቻችሁ ሼር ማድረግ አትዘንጉ! @AAU6kilojemea