uz
Feedback
ASTU Muslim Students Jeme'a

ASTU Muslim Students Jeme'a

Kanalga Telegram’da o‘tish

The aim of this Channel is to broadcast information and to assist muslim students in ASTU by sharing info about Qur'an and kitab derses,remembering others.So,please share it to muslim students For any questions,comment use this bot @ASTU_MSJ_Bot

Ko'proq ko'rsatish
2 195
Obunachilar
-324 soatlar
-77 kunlar
-3830 kunlar
Postlar arxiv
🌙 Ergaa Xumuraa Bara 1447 Yaa ilma Adam, kan Rabbiin waan uume hunda caalaa kabaja sitti godhee hoo! Obboleewwan Kee kan biyya duniyaa waliin dhuftan baay'ee dha. Garuu ammoo obbolaan kee kan ati beektu baay'een turtii yeroo isaaniif kennamee xumuruun gara ganda lammaffaa godaananii jiru. 🤔 Ati hoo hanga yoom ganda duniyaa kana turta laata? Gaafii kanaaf deebii hin qabdu. Kanaaf baallamni deemsa keetii osoo hin gahin, galaa gaafa galaa qopheeffadhu. ⏳ Kana gochuuf ammoo yeroo amma caalu goonkumaa hin argattu; kanaaf ammumarraa jalqabii galaa Kee sassaabbadhu. 📌 Lubbuu Kee gamaggami 📌 Balleessaa keef araara gaafadhu 📌 Dogongoroota kee sirreeffadhu 📌 Hojii gaarii baay'isi 📌 Amala kee bareechi 📌 Rabbii keetti dhiyaadhu 🌱 Bara hijraa 1447ffaa kana haala kanaan xumurii, miira haarawaan bara haarawa simadhu. 🤲 Rabbi si haa gargaaru. https://t.me/ASTU_MSJ

🌙 የ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የመጨረሻ መልዕክት የአደም ልጅ ሆይ! አላህ ከፈጠራቸው ሁሉ በላይ ክብር የሰጠህ ሆይ! ከአንተ ጋር ወደዚህ የዱንያ ሀገር የመጡ ወንድሞችህ ብዙ ናቸው። ነገር ግን ከምታውቃቸው ወንድሞችህ ብዙዎቹ የተሰጣቸውን ጊዜ ጨርሰው ወደ ሁለተኛው መንደር ተሰደው ሄደዋል። 🤔 አንተስ በዚህ የዱንያ መንደር እስከ መቼ ትቆያለህ? ለዚህ ጥያቄ መልስ የለህም። ስለዚህ የጉዞህ ቀጠሮ ሳይደርስ፣ የጉዞ ስንቅህን አዘጋጅ። ⏳ ይህን ለማድረግ ደግሞ ከአሁን የተሻለ ጊዜ የለህም፤ ስለዚህ ከአሁኗ ሰዓት ጀምረህ ስንቅህን ሰብስብ። 📌 ራስህን መርምር 📌 ለወንጀሎችህ ይቅርታ ጠይቅ 📌 ስህተቶችህን አርም 📌 መልካም ሥራህን አብዛ 📌 ባህሪህን አሳምር 📌 ወደ አላህ ቅረብ 🌱 ይህንን 1447ኛ የሂጅራ ዓመት በዚህ መልኩ አጠናቅቀህ፣ አዲሱን ዓመት በአዲስ መንፈስ ተቀበል። 🤲 አላህ ይርዳህ! https://t.me/ASTU_MSJ

LAST MESSAGE OF THE YEAR
LAST MESSAGE OF THE YEAR

እጅግ አስቸኳይ መረጃ! የነገው ፕሮግራም እንዲሰረዝ ተደርጓል❗ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በረያን መስጂድ በነገው እለት ሊያዘጋጀው የነበረው የፓናል ውይይት እንዲሰረዝ ተደርጓል። ለዚህም በዋነኝነት የተሰጠው ምክንያት "የመንግስት አካላት ፕሮግራሙ እንዳይካሄድ ክልከላ አድርገዋል" የሚል ነው። ህብረታችንም ሙስሊሙን ማህበረሰብ የሚወክለው መጅሊስ እና ሌሎችም የሚመለከታቸው አካላት የዜጎችን ህገ-መንግስታዊ እና ተፈጥሯዊ መብት ከማስከበር አኳያ ከጎናችን በመቆም መፍትሄ ያመጣሉ ብለን ተስፋ አድርገን የነበረ ቢሆንም፤ በሚያሳዝን ሁኔታ ተገቢውን ከለላ፣ ድጋፍ እና መፍትሄ ማግኘት አልተቻለም። ፕሮግራሙን ለመታደም ከተለያየ ዩኒቨርስቲ መጥታችሁ አዲስ አበባ ያደራችሁ የጀመዓ አሚሮች፤ አላህ (ሱ.ወ) ጥረታችሁን በጀነት ይመንዳችሁ። ጁምዓ በየመስጂዱ ጥሪ ሲደረግ በእምባ ታጅባችሁ ዱዓ በማድረግ ጭምር እንደምትመጡ የነገራችሁን እናት አባቶች፤ አላህ ዱዓችሁን ይቀበልልን። ከተለያየ ሀይስኩል፣ ኮሌጅ እና መድረሳዎች ለመምጣት የተሰናዳችሁ እህት ወንድሞቻችን፣ የሚዲያ ሽፋን ለመስጠት የተሰናዳችሁ ቲቪዎች፣ ኡስታዞች፣ መሻይኾች እና የክብር እንግዶቻችን፤ ኒያችሁን አላህ ያሳምርላችሁ። መስጂድ የሁሉም ሙስሊም የጋራ ቤት ነው። በሰላማዊ መንገድ መሰባሰብ እና ስለጋራ ጉዳያችን መወያየት በማንም ሊገፈፍ የማይችል ሕገ-መንግስታዊ መብታችን ነው። የሚዳፈንም ሆነ ወደኋላ የሚጎተት ጥያቄ የለንም። መብታችንን ለማስከበር የምናደርገው ጉዞ በህግ፣ በስርአት እና በኢስላማዊ አዳብ የታነፀ ሆኖ ይቀጥላል። ይህ መልእክት በጊዜው ያልደረሳቸው እና ለፕሮግራሙ በነገው እለት ወደ መስጂዱ የሚመጡ በርካታ ወንድም እና እህቶች ሊኖሩ ስለሚችሉ፤ ይህንን ፕሮግራም ያገዳችሁ አካላት፣ ቢያንስ እንኳን ይህን አላዋቂ እንግዳ በእንግድነቱ ልክ በክብር በማስተናገድ እና በጥሩ ቃል በመመለስ ከሚጠበቅባችሁ ትንሹን እንድታደርጉ እናሳስባለን። ቀጣዩን አቅጣጫችንን በቅርቡ እስከምናሳውቅ ድረስ በዱዓ፣ በሰብር እና በፅናት ጠብቁን። "በእርግጥም የአላህ እርዳታ ሁሌም ቅርብ ነው።" (አል-በቀራህ 214) ©aaumsu @AAU6kilojemea

📢 የStory Challenge! የነገውን ፕሮግራም ለብዙ ተማሪዎች እንዲደርስ ይህን ፖስተር በTelegram, WhatsApp, Instagram እንዲሁም Facebook Story ላይ ያጋሩ። አንድ St
📢 የStory Challenge! የነገውን ፕሮግራም ለብዙ ተማሪዎች እንዲደርስ ይህን ፖስተር በTelegram, WhatsApp, Instagram እንዲሁም Facebook Story ላይ ያጋሩ። አንድ Story ማድረግ ብቻ ብዙ ሰዎችን ፕሮግራሙ ላይ እንዲገኙ ሊያነቃቃ ይችላል። ጓደኞቻችሁም story እንዲያደርጉት ጋብዟቸው! 📌 ርዕስ፦ "የሙስሊም ተማሪዎች መብት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት!" ⏰ እሁድ ከጠዋቱ 2:30 📍 ጦርሀይሎች ረያን መስጅድ 3ኛ ፎቅ #StoryChallenge #ShareAndInvite #NiqabIssue #panelDiscussion @AAU6kilojemea

ውድና የተከበራችሁ የ6ኪሎ ሙስሊም ተማሪዎች፤ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስንገባ አላማችን ተምሮ ፤ ዕውቀት ጨብጦ ራስን፣ ቤተሰብን እንዲሁም ሀገርን መጥቀም ነው። ሆኖም ግን ይህ ጉዞ ለብዙዎቻችን የአልጋ በአልጋ እንዳልሆነ ይታወቃል። በተለይም ማንነታችንን የሚገልጸው ሂጃባችንን እና ኒቃባችንን በአንዳንድ ተቋማት ውስጥ እንደ ስጋት ተቆጥሮ፣ እንደ ኋላ ቀርነት ታይቶ ወይም በ"ህግና መመሪያ" ስም ሲገፋና ሲጨቆን ማየት የየዕለቱ ህመም ሆኗል። እህቴ ሆይ! ሂጃብሽ የግል ምርጫሽ ብቻ ሳይሆን ሐይማኖታዊ ግዴታሽና የማንነትሽ መገለጫ ነው። በግቢ ውስጥ በኒቃብሽ ምክንያት የሚደርስብሽ መገለል፣ የሚሰነዘርብሽ አድሏዊ አመለካከትና "አውልቂ" የሚሉ የጫና ድምፆች መብትሽን ካለማወቅ የሚመነጩ ናቸው። በሐገሪቱ ህገ-መንግስትም ሆነ በትምህርት ተቋማቱ መመሪያ መሰረት፣ ማንም ሰው በሐይማኖታዊ አለባበሱ ምክንያት ሊገለልም ሆነ ትምህርት ሊከለከል አይገባም! ወንድሜ ሆይ! የእህቶችህ መገፋት ያንተም የዲንህ መከበርና የቋሚነትህ ጉዳይ ነው። መብቱን የማያውቅ ተማሪ መብቱን ማስከበር አይችልም። የነገው ምሁርነትህ እና ታላቅነትህ ትርጉም የሚኖረው ዛሬ በግቢ ውስጥ ያለህን መብት በብልሃትና በህግ አግባብ ማስከበር ስትችል ነው። ነገስ ለምን እንገናኛለን? ነገ “ የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች” በሚል ርዕስ የሚኖረን የፓናል ውይይት ስለ መብቶቻችንን በዝርዝር የምንረዳበት ትልቅ መድረክ ይሆናል ። • በሂጃብ ላይ የሚደርሱ ጫናዎችን በህግ አግባብ እንዴት መጋፈጥ እንችላለን? • በተቋማቱ ውስጥ ያለን መብት እስከ የት ድረስ ነው? • ጭቆና ሲደርስብን በምን መልኩ ድምፃችንን እናሰማ? ለእነዚህ እና ሌሎችም ጥያቄዎች ምሁራንና የህግ ባለሙያዎች ምላሽ ይዘው ይጠብቁሃል/ሻል። አንተ/ቺ ካልመጣህ/ሽ... አንድ ትልቅ ድምፅ ይጎድላል! ዝምታ ጭቆናን ያባብሳል፤ በአንድነት መታገል ግን ነፃ ያወጣል። ዛሬ ለመብታችን መከበር ካልቆምን ነገ ለሚመጣው ትውልድ የምናስረክበው ዩኒቨርሲቲ የጭቆና ተቋም ይሆናል። ስለዚህ ነገ እሁድ ካለንበት ቦታ ሁሉ ወጣ ብለን ስለ መብታችን ለመወያየት ዝግጅታችንን እናጠናቅ! 📌 ርዕስ ፦ "የሙስሊም ተማሪዎች መብት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት!" 📍ቦታ፦  ጦርሀይሎ ረያን መስጅድ 3ኛ ፎቅ ⏰ ቀን፦ ነገ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ ለጓደኞቻችሁ ሼር ማድረግ አትዘንጉ! @AAU6kilojemea

ነገ አይቀርም! እኔ አልቀርም ... እርስዎስ?! ሙሐመድአሚን ካሳው ... የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፕሬዚዳንት ! ! ! © aaumsu @AAU6kilojemea

​✊ "ፍትሕ እስኪሰፍን መደረግ ያለበትን ሁሉ እናደርጋለን!" ​በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት የ ሁላችንም ህመም ነው። የነቢዩ (ﷺ) ኡማ የትም ቦታ ለሚበደል አካል ድምፅ መሆን ግዴታው ነው። ​የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (ASTU) ሙስሊም ተማሪዎችም ከወንድሞቻችን ጎን ነን! ​📍 በአካል መገኘት የምትችሉ፡ በመጪው እሁድ ሰኔ 07 ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ ጦርኃይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ በመገኘት የፕሮግራሙ ተሳታፊ ይሁኑ ። ​#ፍትሕ_ለሙስሊም_ተማሪዎች #ASTUMSJ #AAUMSU #አንድነት

አንድ ቀን ብቻ ቀርቷል __ ለታሪካዊው ቀን ... ከላይ ያለው ምስል ስቶሪ ይደረግ ... ከፕሮፋይልም ይቀመጥ ! ! ! ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ከ100 በላይ ኪሎሜትሮችን ተጉዘው ሊታደሙ የሚመጡ አሉ
አንድ ቀን ብቻ ቀርቷል __ ለታሪካዊው ቀን ... ከላይ ያለው ምስል ስቶሪ ይደረግ ... ከፕሮፋይልም ይቀመጥ ! ! ! ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ከ100 በላይ ኪሎሜትሮችን ተጉዘው ሊታደሙ የሚመጡ አሉ። በአዲስ አበባ ዙሪያ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች በፕሮግራሙ ለመታደም ይመጣሉ። የመድረሳ ተማሪዎች፤ የሀይስኩል ተማሪዎች፤ የኮሌጅ ተማሪዎች፤ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፤ እናት አባቶቻችን፤ እህት ወንድሞቻችን፤ ኡስታዞቻችን፣ መሾይኾች፣ ሁሉም ስለአንድ አላማ በአንድ መድረክ ይሰባሰባሉ። የታሪክ ምሁሩ አብዱልጀሊል በታሪክ ውስጥ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የደረሰውን ያብራራል ... የሕግ ፕሮፌሰሩ ዘላለም እየተጣሱ ስላሉት መብቶች ከሕግ አንፃር ያለውን እውነታ ያስቃኛል ... ኡስታዝ ሺሃቡዲን ሸህ ኑራም በእንዲህ አይነት ሁኔታዎች ውስጥ የእኛ ሚና ምን መሆን እንዳለበት ያስቀምጣሉ። ስለ አሁኑ እና ስለወደፊቱ ከተማሪዎች በኩል ያለውንም እናደምጣለን። ሰኔ 07 / 2018 ዓ.ል እሁድ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ ከላይ ያለውን ምስል ስቶሪ አድርጉ ... ከፕሮፋይላችሁ ላይም አስቀምጡት ! ! ! የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች © aaumsu @AAU6kilojemea

ከፓናሊስቶቻችን 3 - ኡስታዝ ሺሐቡዲን ሸይኽ ኑራ! የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በባህርዳር ዩኒቨርስቲ በሰሩበት ወቅት የጀመዓው አሚር ነበሩ። የዚያኔ ስለሙስሊም ተማሪዎች የታገሉ ሲሆን ደማቅ አሻራን አሳ
ከፓናሊስቶቻችን 3 - ኡስታዝ ሺሐቡዲን ሸይኽ ኑራ! የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በባህርዳር ዩኒቨርስቲ በሰሩበት ወቅት የጀመዓው አሚር ነበሩ። የዚያኔ ስለሙስሊም ተማሪዎች የታገሉ ሲሆን ደማቅ አሻራን አሳርፈው አልፈዋል። ወደ ሌሎች ዩኒቨርስቲዎች በማምራትም የተለያዩ ድግሪዎችን ሰርተዋል። በአራት የተለያዩ ዲፓርትመንቶች የማስተርስ ዲግሪ አላቸው። በአሁኑ ሰዓትም የPHD ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ነው። ከዚህም ባሻገር የአዲስ አበባ መጅሊስን በምክትል ፕሬዚዳንትነት፤ ኢምፓክት ሜከርስ ፋውንዴሽንን በዳይሬክተርነት እየመሩ ጉልህ አስተዋፅዕ በማበርከት ላይ ናቸው። ለተለያዩ ተቋማትም የአመራርነት ስልጠናን በመስጠት ብቁ መሪዎች ይኖሩ ዘንድ ተግተው እየሰሩ ነው። ኡስታዝ ሺሐቡዲን ሸህ ኑራ የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች በሚል ርዕስ በመጪው እሁድ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ በተዘጋጀው የፓናል ውይይት ላይ ፓናሊስት ናቸው። ቀጠሯችንን ከዚያው እናድርግ። በሰዓቱ እንገኝ! ለተሻለ ነገ መሠረት የምንጥልበትን ዛሬ እንያዝ!! ዝግጁ ?! የኢማም አሕመድ ልጆች ዝግጁ?! የጦልሓ ጀዕፈር ምትኮች ዝግጁ?! የኡሙአይመን ልጆች _ ዝግጁ?!!! © aaumsu @AAU6kilojemea

የፓናሉ መሪ _ ዲኑ ዓሊ ! የሚዲያ ባለሙያ ነው። በሙስሊሞች ላይ አንዳች የመብት ጥሰት ሲፈፀም ከፊት ለፊት ይገኛል። ኸይር ፈላጊ የሚልን ተቋም አቋቁሞ ማህበረሰቡን በማስተባበር ብዙ መስጂዶችን እና
የፓናሉ መሪ _ ዲኑ ዓሊ !   የሚዲያ ባለሙያ ነው። በሙስሊሞች ላይ አንዳች የመብት ጥሰት ሲፈፀም ከፊት ለፊት ይገኛል። ኸይር ፈላጊ የሚልን ተቋም አቋቁሞ ማህበረሰቡን በማስተባበር ብዙ መስጂዶችን እና መድረሳዎችን ገንብቷል። በርካታ የውሐ ጉድጓዶችንም በገጠሩ የሀገራችን ክፍል በማስቆፈር ለብዙዎች ደርሷል።    ከዚህም ባሻገር በተለያዩ ኸይር ስራዎች ተፅዕኖ ሲፈጥር ይታወቃል። "የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች!" - በሚል ርዕስ ያዘጋጀነው የፓናል ውይይት ላይ የፓናሉ መሪ ሆኖ ቀርቧል። እሁድ ሰኔ 7 / 2018 ዓ.ል ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ በሚካሄደው ፕሮግራም ላይ ማለት ነው። በሰዓቱ እንገኝ! ከቀደምቶች የሚገኝን ልምድ በመቅሰም ስለአሁኑ በደንቡን የምንሰራበትን ስንቅ እንሸምት ዘንድ። በዳዮችን በመጋፈጥ ረገድ ሊያገለግለን የሚችልን እውቀት እንይዝ ዘንድ። ፍትሕ እንዲሰፍን በምናደርገው ትግል ውስጥ የሚጠቅመንን ነገር እናገኝ ዘንድ። ዝግጁ? ያኡመተ-ሙሐመድ! የሱመያ ልጆች ... የቢላል ወራሾች _ ዝግጁ?! © aaumsu @AAU6kilojemea

ከፓናሊስቶቻችን 2 - አብዱልጀሊል ሸህ ዓሊ ካሳ ! የመጀመሪያ ዲግሪውን ከሀረማያ ዩኒቨርስቲ ወስዷል። ሁለተኛ ዲግሪውን ባህር ማዶ ተሻግሮ በጣሊያን ሰርቷል። ኪነት-ያገነነው አፄ፤ ተምኔታዊት ደሴት
ከፓናሊስቶቻችን 2 - አብዱልጀሊል ሸህ ዓሊ ካሳ ! የመጀመሪያ ዲግሪውን ከሀረማያ ዩኒቨርስቲ ወስዷል። ሁለተኛ ዲግሪውን ባህር ማዶ ተሻግሮ በጣሊያን ሰርቷል። ኪነት-ያገነነው አፄ፤ ተምኔታዊት ደሴት እና እስልምና በኢትዮጵያ ከቅድመ ክርስቶስ እስከ ዛሬ የሚሉ ዘመን ተሻጋሪ መፅሐፍትን ለማህበረሰቡ በማበርከት ጉልህ አስተዋፅዖ አበርክተዋል። ከዚህ ባሻገር በተለያዩ የሚዲያ ፕላትፎርሞች ላይ ሕዝበ ሙስሊሙን በማንቃት ይታወቃሉ። "የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች!" - በሚል ርዕስ በመጪው እሁድ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ ያዘጋጀነው የፓናል ውይይት ላይ ከፓናሊስቶች መካከል ሲሆኑ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ እና አሁናዊ መፍትሔ ጥልቅ እይታቸውን ያጋሩናል። በሰዓቱ እንገኝ ... ታሪክን ከማወቅ ባሻገር ታሪክ እየሰሩ ካሉ ምሁራን ትላንታችንን እንወቅ፤ ዛሬያችንን እንረዳ፤ ስለነጋችን እናልም። የትላንቶቹ የሰሩትን እውቅና በመስጠት ዛሬን በመስራት ልናልፍ ቃልኪዳን አለንና ቃላችንን እንሞላ ዘንድ ከሚያሰባስበን መድረክ እንክተም። ሁሉም ይገኝ ... ከሀይስኩል እስከ ኮሌጅ ... ከመድረሳ እስከ ዩኒቨርስቲ ተማሪ ይገኝ ... የተማሪ ወላጅም ይገኝ ... ወላጅ ያልሆነም ይገኝ ... ሁሉም ይገኝ! ስለጋራ አጀንዳችን በጋራ ተሰባስበን በጋራ እንምከር!!! ዝግጁ?! ©aaumsu @AAU6kilojemea

ከፓናሊስቶቻችን ! - 1 በሕግ ትምህርት ረዳት ፕሮፌሰር ናቸው። በሕገ-መንግስታዊ ሕጎች ዙሪያ አሉ ከሚባሉ ምሁራን ነው። በወሎ ዩኒቨርስቲ ሕግን እያስተማሩ ከመሆናቸው ባሻገር በፕሪቶሪያ ዩኒቨርስቲ
ከፓናሊስቶቻችን ! - 1 በሕግ ትምህርት ረዳት ፕሮፌሰር ናቸው። በሕገ-መንግስታዊ ሕጎች ዙሪያ አሉ ከሚባሉ ምሁራን ነው። በወሎ ዩኒቨርስቲ ሕግን እያስተማሩ ከመሆናቸው ባሻገር በፕሪቶሪያ ዩኒቨርስቲ እጩ የሕግ ዶክተር ናቸው። በ Ethiopian Civil Society Organizations Council ፖሊሲ ዳይሬክተር በመሆን እያገለገሉ ነው። ፕሮፌሰር ዘላለም እሸቱ ... በተለያየ መድረክ በተለይም  በሴኩላሪዝም እና መሠል ርዕሶች ዙሪያ ጥልቅ የሕግ እውነታዎችን በማቅረብ ይታወቃሉ። "የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች!" - በሚል ርዕስ በመጪው እሁድ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ ያዘጋጀነው የፓናል ውይይት ላይ ከፓናሊስቶች መካከል ሲሆኑ መሠረት የሚሆኑንን ምልከታዎች ያጋሩናል። ለመገኘት፣ ለመማር፣ ለመጠየቅ ዝግጁ ናችሁ? ደግሞም እርሳቸው ብቻ አይደሉም። ሌሎች ምሁራንም ተጋብዘዋል። የምናሳውቅ ይሆናል። የሀይስኩል ተማሪዎች ዝግጁ? የAAU እንቁዎች ዝግጁ?! የኮሌጅ ተማሪዎች ዝግጁ?!! ያኡመተ-ሙሐመድ ዝግጁ?!!! እንሰባሰብ፣ ድምፃችንን እናዋህድ፤ ስለአንድ አላማ በአንድነት እንሰለፍ፤ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ታሪክ እናድርግ!!! ©aaumsu @AAU6kilojemea

ታሪካዊው መድረክ ጥቂት ቀናት ቀርተውታል! ቅስቀሳው ቀጥሏል፤ ዝግጅቱም ደምቋል! በመጪው እሁድ ሰኔ 07/2018 ዓ.ል በጦር ኃይሎች ረያን መስጂድ የሚካሄደው ታላቅ የፓናል ውይይት እንደተጠበቀ ነው።
ታሪካዊው መድረክ ጥቂት ቀናት ቀርተውታል! ቅስቀሳው ቀጥሏል፤ ዝግጅቱም ደምቋል! በመጪው እሁድ ሰኔ 07/2018 ዓ.ል በጦር ኃይሎች ረያን መስጂድ የሚካሄደው ታላቅ የፓናል ውይይት እንደተጠበቀ ነው። ይህ መድረክ የሙስሊም ተማሪዎች ሕገ-መንግስታዊ መብቶች የሚከበሩበትን፣ እንደ ኒቃብና ሒጃብ ያሉ የእምነትና የማንነት መገለጫዎች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች በሕጋዊ መንገድ የሚመከቱበትንና ዘላቂ መፍትሔ የሚቀመጥበትን አቅጣጫ የሚያሳይ ነው። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ (ትራንስፖርት በተዘጋጀላቸው ካምፓሶች) ጀምሮ በከተማዋ የምትገኙ የከፍተኛ ትምህርት፣ የኮሌጅና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በሙሉ የዚህ ታሪክ አካል እንድትሆኑ ጥሪያችን የፀና ነው። እምነታችን፣ መብታችንና ምርጫችን ይከበር ዘንድ፣ ሰኔ 7 ከጧቱ 2፡30 ጀምሮ ልባችንና አቅጣጫችን ወደ ረያን መስጂድ ይሁን። ሁላችንም ለአንድ ዓላማ በአንድነት እንሰባሰብ። ዝግጁ ናችሁ?!👍🫡 © aaumsu @AAU6kilojemea

በባለቤቱ የተበደለ ፈረስ እያነባ ለነቢ ስሞታ አቀረበ ... እርሳቸውም ዝም አላሉትም ... ፍትሕ ይሰፍን ዘንድ ከባለቤቱ በመሄድ መደረግ ያለበትን አደረጉ --- የእኛ ነብይ እንዲህ ናቸው ... ከሰው ዘር አልፈው ለተበደሉ እንስሳት ጥብቅና የሚቆሙ ... ፍትሕ እንዲሰፍንላቸው የሚተጉ ነብይ ነበሩ ... በደልን እንድንፀየፍ አስተማሩን ከበዳይ ፊት ሐቅን መናገር ከጂሐድ እንደሆነ አስተማሩን ፍትሕ ይሰፍን ዘንድ በአንድነት እንድንሰባሰብ አስተማሩን በእርሳቸው ላይ ሰለዋት አውርዱ አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሙሐመድ !😍! የእርሳቸው ኡማ እንደመሆናችን በትምህርት ተቋማት ውስጥ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ዝም አንልም። ፍትሕ እስኪሰፍን እንጠይቃለን ... ፍትሕ እስኪሰፍን እንሰራለን ... ፍትሕ እስኪሰፍን እንሰባሰባለን ... ፍትሕ እስኪሰፍን መደረግ ያለበትን ሁሉ እናደርጋለን!! በመጪው እሁድ ሰኔ 07 / 2018 ዓ.ል ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ እንገናኝ ! ! @aaumsu

Repost from N/a
📢 Oduu Gammachiisaa: Galmeen marsariitii(pilaatfoormii) Akaadaamii Afrikaa banameera 💫  Barattoota Keenna kabajamoo Baniinsa Galmee marsariitii Akkaadaamii Afrikaa fi gara Marsariitii (Pilaatfoormii) barnootaa Akkaadaamii keenyaa seenuun herrega (akkawuntii) keessan akka  jalqabsiistan isin beeksisuu keenyaaf gammachuu guddaatu nutti dhaga'ama. 🔗 Linkii Marsariitii (Pilaatfoormii) Seensaa: https://orm.africaacademy.com Viidiyoon asiin gadii tarkaanfii akkaataa galmee gadi-fageenyaan isiniif ibsa: Barruu isaa wajjiin sirritti ilaalaa! - Karaa galmee seensaa herreega  (Akkaawuntii) Telegraama fayyadamanii. - Karaa galmee  seensaa herrega (Akkaawuntii) Google fayyadamanii. 💡 Yeroo seensaa fi galmee dhimmi rakkoo teekinikaa yoo isin mudate, gara duubatti osoo hin jedhin garee deeggarsa teekinikaa keenya quunnamuu dandeessu 🔗 Linkii Deeggarsa Teekinikaa Akkaadaamii: @AfricaacademyOromo Imala barnootaa gammachiisaa, kan milkaa'inaa fi badhaadhinaan guutame isiniif hawwina!

Chaanaaliin kun kan Akkaadaamii Afriikaa Afaan Oromoo Sagantaa Dippiloomaa Marsaa tokkoffaati - Baruumsi fedhii Rabbiitin yeroo dhiyootti ni eegala. https://t.me/AkaadaamiiAfrikaa

📢የምስራች! በአፍሪካ አካዳሚ ዌብሳይት ምዝገባና መግቢያ ተከፍቷል 💫 ውድ ተማሪዎቻችን በዌብሳይት (ድረ-ገጻችን) ላይ ለመመዝገብና ለመግባት ዝግጅቱ መጠናቀቁን እየገለፅን ከታች በሚለቀቅላችሁ ቪዲዮ መሰረት ሊንኩን ተጠቅማችሁ ዌብሳይታችን ላይ አካውንት መክፈትና መግባት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን። 🔗 መግቢያ ሊንክ (Link) https://am.africaacademy.com/course/view.php?id=3 በቪዲዮው ላይ በሁለት መልኩ መመዝገብ የምትችሉ ሲሆን 1. በቴሌግራም (Telegram) አካውንት በመጠቀም የመመዝገቢያ እና የመግቢያ መንገድ 2. በጉግል (Google) አካውንት በመጠቀም የመመዝገቢያ እና የመግቢያ መንገድ 💡 በሚገቡበት ጊዜ ማንኛውም ቴክኒካዊ ችግር ካጋጠማችሁ፣ እባካችሁ የቴክኒክ ድጋፍ ቡድናችንን ያናግሩ 🔗 አካዳሚው የቴክኒክ ድጋፍ ሊንክ @Ethio_africaacademy አስደሳች፣ በስኬትና በማሸነፍ የተሞላ የትምህርት ዘመን እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!

ታላቁ መድረክ ደረሰ .... የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች! እንደ ሙስሊም ተማሪ ስላሉን ሕገ-መንግስታዊ መብቶች በተጋባዥ ምሁራን በጥልቀት ይዳሰሳል።
ታላቁ መድረክ ደረሰ .... የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች! እንደ ሙስሊም ተማሪ ስላሉን ሕገ-መንግስታዊ መብቶች በተጋባዥ ምሁራን በጥልቀት ይዳሰሳል። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጀምሮ ድሮም ዛሬም መመሪያ በማውጣትም ሆነ እንደ ግል ሒጃብን በመከልከል ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርት ስለሚያሰናክሉ ተቋማት እና ግለሰቦች ፍላጎት እና አንደምታ ብሎም ዘላቂ መፍትሔ በፓናሊስቶች ይብራራል። የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ የእኛ ትውልድ ሀላፊነት ነው ብለን የገባነውን ቃል እናድሳለን፤ ቀጣይ የቤት ስራዎቻችንም ግልፅ ይደረጋሉ። የሁሉም ካምፓስ ተማሪዎች (ትራንስፖርት ተመቻችቷል) የዚህ ታሪካዊ ፕሮግራም አካል ትሆኑ ዘንድ ተጋብዛችሗል። አዲስ አበባ ውስጥ ያላችሁ ሀይስኩል እና ኮሌጅ ተማሪዎች የዚህ ታሪክ አካል ትሆኑ ዘንድ በክብር ተጠርታችሗል። ሁላችንም የሁላችንም አጀንዳ በሆነው ጉዳይ ዙሪያ እንሰባሰብ ዘንድ ግድ ሆኗል። መታደልም ነው! ቦታ፦ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ ቀን፦ በመጪው እሁድ ሰኔ 07 / 2018 ዓ.ል ሰዓት፦ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ አዘጋጁ፦ የእናንተው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ነው። ለጓደኞቻችን፣ ለቤተሰቦቻችን፣ ለእህት ወንድሞቻችን ማሰራጨት ግዴታ ነው። @aaumsu