ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
Open in Telegram
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
Show more3 309
Subscribers
-224 hours
-97 days
-3630 days
Posts Archive
«ሰው የሚፈልገውን ከፈጸመ የሚጠብቀው ሞቱን ነው !»
【ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ】
#ሐምሌ ፳፪ ቀን ፲፱፻፹፪ ዓ.ም. ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ተኩል በመቂ ደብረ አሚን ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ለሚገኙ ምእመናን ትምህርተ ወንጌል ለመስጠት ሲሔዱ በዚህች ቀን በድንገተኛ የመኪና አደጋ አለፉ፡፡😭 ገና በ፶ ዓመታቸው! ከጊዜ ጋር የነበራቸው መሽቀዳደም ተገታ፡፡ ጥድፊያው፣ ችኮላው፣ ከሀገር ሀገር መራወጡ፣ ትውልድ ማሰባሰቡ ለዚህ ኖሯል። ያ በርቀት የተያዘ ዕቅድ በአጭር ተቀጨ ያ ዕረፍት አልባ ሩጫ በሞት ተገደበ ፤ #ያ ተወርዋሪ ኮከብ ብልጭ ብሎ ወገግታውን ሰጥቶ ጠፋ፡፡ ለተልዕኮ የመጣ ነውና በተልዕኮ አለፈ፡፡ የዕድሜን፣ የመኖርን፣ አጭር ጊዜ ኖሮ ሕያውና ዘላቂ ሥራ መሥራትን በሕይወቱ ተርጕሞልን ተጠራ፡፡
አባታችን ለሞት የተጠሩበት ዕድሜ በጳጳሳት ደረጃ ሲታይ እጅግ ልብ ሰባሪ የሚባል ነው፡፡ የሞታቸውን ዜና የዘገበው ዜና ቤተ ክርስቲያን ጋዜጣ በፊት ለፊት ገጹ የተጠሩበትን ዕድሜ አጉልቶ “በ፶ ዓመታቸው አርፈዋል” ያለው ጥሪው ቢያሰቅቀው ነው፡፡ ከአባታችን ጋር ለአገልግሎት አብረው ሔደው የነበሩት ዲያቆን ጳውሎስ በቀለና የመኪናው አሽከርካሪ ዲያቆን ኤፍሬም ዘውዴም በደረሰው ድንገተኛ አደጋ ገና በለጋ ዕድሜያቸው አልፈዋል።
ስምከ ሕያው ዘኢይመውት
[ ከ፲፱፻፴፪ - ፲፱፻፹፪ ዓ.ም ]
#እኛም እንጂ ታሪካቸውን ብሎም ስራዎቻውን በማንበብ እንዘክራቸው ዘንድ #አዲሱን የብጹዕነታቸውን መጽሐፍ ለዛሬ በልዩ ቅናሽ አዘጋጅተናል!
[ታላቁ አቡነ ጎርጎርዮስ በዛሬው ዕለት ነው ያረፉት በጸሎታቸው ያስቡን !]
📚ግዮን መጻሕፍት
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
🎤ሰቆቃወ ጴጥሮስ
በሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን [በ1961 ዓ.ም]
ታላቁ ኢትዮጵያዊ ሰማዕት አቡነ ጴጥሮስ
† ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ምንም እንኳ ለሃገራቸውና ሃይማኖታቸው ያን ያህል ዋጋ ቢከፍሉም ትውልዱም : መንግስቱም : ራሷ ቤተ ክርስቲያናችንም ተገቢውን ክብር ሰጥተው እያሰቧቸው አይደለም:: እስኪ እንዲያው ቢያንስ እንደ ክርስቲያን : አንድም እንደ ኢትዮጵያዊ እነዚህ ነገሮቻቸውን እናስብ::
ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ከልጅነታቸው ጀምረው ትምሕርት : ትሕርምትና ደግነት ወዳጅ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ወቅቱ ኢትዮጵያ የራሷን ጳጳሳት የምትሻበት ጊዜ ነበርና በፈቃደ እግዚአብሔር ለመጀመሪያ ጊዜ የሃገራችን አራት አባቶች ጵጵስናን ተሾሙ::
እነርሱም ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ እና አበው አባ ሚካኤል: አባ አብርሃም እና አባ ይስሐቅ ናቸው:: የተሾሙትም ግንቦት 18 ቀን 1921 ዓ/ም ነው:: አቡነ ጴጥሮስ ከተሾሙ በኋላ በሐዋርያዊ አገልግሎትና በጸሎት ተግተው ኑረዋል::
በ፲፱፻፳፰/1928 ዓ/ም ፋሺስት ጣልያን ሃገራችንን በወረረች ጊዜ ቆራጡ ጳጳስ በዱር በገደል ለመሔድ ተነሱ:: በየበርሃው እየሔዱ አርበኞችን ሲያጽናኑ : ሲናዝዙ : ሲባርኩም ቆይተዋል:: ለሃገራቸውና ለሃይማኖታቸው ረሃብ : ጥም : እንግልትን ታግሰዋል::
በተያዙባት በዚያች ሌሊትም በጣልያኖች ለሮም እምነትና ለአገዛዙ እንዲያጐበድዱ ተጠየቁ:: ቆራጡ ሰው ግን እንቢ ቢሉ የሚደርስባቸውን እያወቁ "አይደረግም" አሉ:: በማግስቱ በአደባባይ መትረየስ ተደግኖባቸው አሁንም ጥያቄ ቀረበላቸው::
አቡነ ጴጥሮስ አፋቸውን ከፍተው ሊናገሩ ጀመሩ:- "የሃገሬ ሕዝብ ሆይ! ለሃገርህ : ለሃይማኖትህ ባትጋደል ትውልድ ይፋረድህ:: ለጣልያን ግን እንኳን ሰው ዛፍ ቅጠሉ መሬቱ እንዳይገዛለት አውግዣለሁ" አሉ:: በደቂቃዎች ልዩነት በግራዚያኒ ትዕዛዝ የመትረየስ ጥይት ዘነበባቸው::
አካላቸው ተበሳስቶ በሰንሰለት እንደ ታሠሩ መሬት ላይ ወደቁ:: አንዱ ወታደር ቀርቦ ቢመለከት ትንሽ ትንፋሽ ነበረቻቸው:: "ይሔ ቄስ አልሞተም" ብሎ ጭንቅላታቸው ላይ ተኮሰባቸው::
አቡነ ጴጥሮስ ለሃገራቸውና ሃይማኖታቸው ተሠው:: ነገሩ በአርበኞች ዘንድ ሲሰማ ትግሉ ተቀጣጠለ:: ይሄ የተደረገው ሐምሌ ፳፪ [22] ቀን በ፲፱፻፳፰/1928 ዓ/ም ነው:: አቡነ ጴጥሮስም በተ/መ/ድ [UN] የሺህ ዓመቱ ምርጥ ሰማዕት [MARTYR OF THE MILLENIUM] በመባል ይታወቃሉ::
💧#ሐምሌ_22 ቀን ቅዱስ ዑራኤል ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበትና ለነብዩ ዕዝራ ሱቱኤል የእውቀትን ጽዋ ያጠጣበት ዓመታዊ በዓለ ንግሱ ነው ።
#እንኳን_አደረሰን@GhionBookStore1623
፨በዓሉን ምክንያት በማድረግ ዛሬ ለምትመጡ ደንበኞች ድርሳነ ዑራኤል በልዩ ቅናሽ አዘጋጅተናል ።
ከቦታ አንጻር እግዚአብሔርን የሚሸከም ዓለም የለም። እርሱ ከዓለማት ኹሉ በላይ ስለኾነ። አንዲት ዓለም ከእኛ ዘንድ ተገኘች። በዓለም ውስጥ ያለች ከዓለማት የሰፋች። ከዓለማት በላይ የኾነውን ይኽች ድንቅ ዓለም በልዩነት ተሸከመች። በመንፈሳዊ ዐይን ለተመለከታት እርሷ ከዓለማት የምታልፍ ሰፊ ናት። እግዚአብሔርን መሸከም ላቃታቸው ዓለማት ኹሉ በመሻል ቤዛ የኾነች ድንግል ማርያም ናት።
እነዚያ አልቻሉትም እርሷ ግን ከመሸከም አልፋ ከሥጋና ከደሟ ይነሣ ዘንድ ወደደች ፈቀደች። ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ይነሣ ዘንድ በቅታ ተገኘች። ለተዋሕዶ ተመረጠች። ሠራዒ መጋቢው ወተት ለመናት። አጠባችው።
#ቤዛዊተ_ዓለም
#በግዮን_መጻሕፍት_መደብር
ነባር እና ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍትን
ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኛሉ
አድራሻ ፦ፒያሳ መናገሻ ገነተ ጽጌ
ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን
ማህበረ በኵር ሰንበቴ ፊት ለፊት
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDeliveryሀ አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
👇
https://t.me/GhionBookStore1623
…………ለ9ኛ ጊዜ የታተመ
"እንደ ኦርቶዶክሳውያን ወላጆች፥ ዓላማችን ፍጹማን ወላጆች መኾን አይደለም። ይህ የማይቻል ነውና። ... ልጆች የሚፈልጉት [እና የሚያስፈልጋቸው] እንደ እነርሱ የሚሳሳቱና [ከስሕተታቸው እየተማሩ] የሚያድጉ ወላጆችን ነው።"
#ትንሿ_ቤተክርስቲያን፥ ገጽ 447
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
በእንተ ሥጋዌ
ለተማሪዎቹ የሚያስብ ርኀሩህ አስተማሪ አንዳንዶቹ ተማሪዎቹ ረቀቅና መጠቅ ያለው ትምህርት እንዳልገባቸው ሲያይ ወደ እነርሱ ደረጃ ዝቅ ብሎ እነርሱ በሚገባቸው በማንኛውም ሁኔታ እንደሚያስተምራቸው ሁሉ የእግዚአብሔር ቃልም እንዲሁ አደረገ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም እንዲህ እንዳለ፡- በእግዚአብሔር ጥበብ ምክንያት ዓለም እግዚአብሔርን በጥበብዋ ስላላወቀች በስብከት ሞኝነት የሚያምኑትን ሊያድን የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ሆኗልና፡፡»"
#ቅዱስ_አትናቴዎስ_ሐዋርያዊ_ህይወቱና_ትምህርቱ
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
ሐምሌ_19_መልአኩ_ቅዱስ_ገብርኤል።
እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!
ታላቁ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ዛሬ ሐምሌ ፲፱ ቀን ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ቅዱስ ቂርቆስን ከእሳት ጋንና ከብዙ መከራዎች ያዳነበት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓላቸው ነው።
የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነትና ምልጃ በረከት ከእኛ ጋር ይሁን። አሜን!
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
ጸሎት
#ጸሎት በሕይወታችን ውስጥ ደንብና መደበኛ ልምምድ መሆን አለበት ፤ ይህም በጽድቅና በአክብሮታዊ አቋቋም እንዲሁም ፍጹም በሆነ ትኩረት ሊከናወን ያስፈልጋል። በጸሎት ጊዜ ከእግዚአብሔር ጋር ስንነጋገር ለእርሱ የሚገባውን ተገቢ ክብር መስጠት አለብን የጸሎትን ታላቅ ጥቅም ማወቅ አለብን። በግላችንም የተለየ ምላሽ መኖራቸውን መገንዘብ አለብን። ጸሎት ከእግዚአብሔር ጋር በእውነት የመነጋገር ያህል የሆነለት ሰው #ምድራዊ_መልአክ ሆኖ ተለውጧል ማለት ነው።
እግዚአብሔር አምላክ ከእርሱ ጋር ስንነጋገር የተዋቡ ቃላትን እንድንጠቀም አይጠይቀንም። ይሁን እንጂ የምንነጋገራቸው ቃላት ከተዋበ ነፍሳችም ተፈንጥቀው መውጣት አለባቸው ጸሎት በተለመደበት ሰዓት ሲቀርብ ሽምጋዮችን፤ስርዐቶችን ወይም ቀጠሮዎችን አይሻም። የእግዚአብሔር ደጆች ዘወትር ክፍት ስለሆኑ እርሱ እኛን ይጠብቀናል እራሳችንን ከእግዚአብሔር የምናገል ወይም የምናርቅ ከሆንን ሙሉ በሙሉ በራሳችን ሀሳብ መደገፍ ይጀምራል ማለት ነው። እርሱ ዘወትር ቅርብ ነው። በተለየ ሁኔታ አንደበተ እርቱ መሆን አያስፈልገንም። እኛ የተፈለገውን ያህል ድምጻችንን ዝግ አድርገን ብንናገር እንኳን እርሱ ይሰማናል። በጸሎት ጥበብ ውስጥ የተራዘመን መመሪያዎችን ማስቅመጥ አስፈላጊ አይደለም። ለመጸለይ መፈለጋችን በራሱ በቂ ነው።
በቂው ነገር የጸሎት ዘዴ ነው እኛ መጸለይ ያለብንን ከልባችን ሆነን መንፈዊዊ ዕድገት የሚሻ ጸጸት ውስጥ ሆነን ሌሎች ሰዎችን ይቅር ለማለት የእርሱን ይቅርታ መጠየቅ እንዲሁም የእውነት ትሁት ሰው መሆን ነው። እግዚአብሔር እንደሚፈልገን ሆነን የምንጸልይ ከሆነ። ጸሎታችን ባለ መታከት የምናቀርብ ከሆነ፤ በጸሎታችን ውስጥ ለእኛም ሆነ ለሌሎች ነፍሳት ጥቅም ጉዳይ ላይ የምናተኩር ከሆንን ጸሎታችን አድማጭ ተቀባይ ያገኛል።
በምንጸልይበት ጊዜ ጸሎታችን መጋነን የለበትም ፤ ጥረቶቻችን ሙሉ ለሙሉ በመቀበል ሐሳብ ላይ ብቻ ማተኮር የለባቸውም። ዋናው አላማችንና አስፈላጊ ነገር ነፍሳችንን የተሻለ ማድረግ ነው ፣ ይህም ሊሆን የሚችለው በጸሎት አማካኝነት ነው። ይህን ጉዳይ አላማው አድርጎ የሚጸልይ ሰው ከዓለማዊ ነገሮች ኃይል ይበልጥ ብርቱ ይሆናል ከእርሱ ጋር በላይም ከፍ ብሎ ሊከናወንለት ይችላል።
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
✨#ዜና_መጽሐፍ 💧
📖#የቤተ-ክርስቲያን ታሪክ📖
❝ እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ ሰው ሥራ ሰጥቶታል ፣ ያንን መስራት የእሱ ፈንታ ነው፡፡ ቢቻለው አሱን ማገድ የዲያቢሎስ ሥራ ነው፡፡ በእርግጥ ሥራው እግዚአብሔር እንደሰጠህ ያህል ሠይጣን ሊያግድህ ይጥራል፡፡ ሌላ ነገር በበለጠ ደስ የሚያሰኝ ሊያቀርብልህ ይጥራል፡፡ በዓለማዊ ተስፋዎች ያባብልሃል፡፡ የሐሜት ጐርፍ ያስወርድብሃል፡፡ #ደራሲያን እንዲጠይቁህ እጅግ ስመጥር ሰዎችም በክፉ እንዲናገሩብህ ይጠቀምባቸዋል፡፡ ...❞
[#ብጹዕነታቸው አቡነ ጎርጎርዮስ ]
#ቀ'ደ'ም በኹለት ክፍል ተዘጋጅቶ የነበረው -የቤተክርስቲያን ታሪክ በዓለም መድረክ እና -የቤተክርስቲያን ታሪክ በኢትዮጵያ መጽሐፍ ፥አኹን በአንድ ጥራዝ #በብጹዕነታቸው አቡነ ጎርጎርዮስ ጥዑም ታሪክና፤ተግሳጻት ታጅቦ ብቅ ብሏል እንዳያመልጠን....!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDeliveryሀ አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
👇
https://t.me/GhionBookStore1623
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
በእንተ ሥጋዌ
ለተማሪዎቹ የሚያስብ ርኀሩህ አስተማሪ አንዳንዶቹ ተማሪዎቹ ረቀቅና መጠቅ ያለው ትምህርት እንዳልገባቸው ሲያይ ወደ እነርሱ ደረጃ ዝቅ ብሎ እነርሱ በሚገባቸው በማንኛውም ሁኔታ እንደሚያስተምራቸው ሁሉ የእግዚአብሔር ቃልም እንዲሁ አደረገ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም እንዲህ እንዳለ፡- በእግዚአብሔር ጥበብ ምክንያት ዓለም እግዚአብሔርን በጥበብዋ ስላላወቀች በስብከት ሞኝነት የሚያምኑትን ሊያድን የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ሆኗልና፡፡»"
#ቅዱስ_አትናቴዎስ_ሐዋርያዊ_ህይወቱና_ትምህርቱ
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
📖#እስከማዕዜኑ📖
የደስታ ቀናት አንደ ሰማይ ሲርቁ... ክፉ ቀናት አንደ አጀብ ሲከቡን... የተጠበቀው ቀርቶ ያልተጠበቀው ሲሆን... ሞት አንድ አማራጭ ሆኖ ሲቀርብ... ውስጣዊ ሰላማችን ሲረበሽ... እርጋታ ፈጽሞ ሲጠፋ....
...ያን ጊዜ “ጌታ ሆይ እስከመቼ?'' አንላለን፡፡ ደግሞም በልጅነት ሰቆቃ በአባቶቻችን አንደበት “እስከማዕዜኑ?'' እንላለን። እንባችን እንደ መጠጥ፣ ሀዘናችንሞ እንደ መብል ይሆንብናል። የቀናት ጠንሳሽ የሆነው አባታችን እግዚአብሔር ግን “ታገስ፣ የመጠበቅን ፍሬ ትበላለህ” ማለቱን ይቀጥላል፤ እኛም “አምላኬ ሆይ፣ እንዴት ልታገስ? እስከመቼስ ልጠብቅ?” አንላለን። ከዚያም ቃሉን ያስታውሰናል፣ የቀደሙ ቅዱሳነኘ አብነት ይዘክርልናል።
“እንደ ልጄ እንደ ዳዊት ቀና ሁን፣ እንደ ታላቁ ታጋሽ እንደ ኢዮብ ሁንልኝ፣ የቀጠርኩልህ ቀን ሲደርስ የመከራህን ቀናት አስረሳሃለሁ! እንደ ተወዳጁ ልጄ እንደ ወልድ ትንሳኤህ አስኪገለጥ አርጋታን ገንዘብህ አድርግ!'' ይለናል፡፡ በቅዱስ ቃሉ ያባብለናል፡፡
የህማማት ቀናቶቻችን አንደ ግዮን ወንዝ የረዘሙ ሲመስሉ፣ የህዝባችን እፎይታ፣ የሀገራችን ሰላምና መረጋጋት እንደ ጌታችን መምጫ ቀን ሲርቁበን፣ ህይወት ከንቱ፣ መኖርም ምናምንቴ መስሎ ሲታይ... የምድረ በዳው መንከራተት ከንዓናችንን ሊያስረሳን ሲደርስ፣ መራርነት ተስፋችንን ሊያስጥለን ሲተጋ፣ የስጋ ድካሞ ከዘለዓለማዊው አጣ ፈንታችን ሊያናጥበን ሲል... ያን ጊዜ የታላላቅ አባቶች ሞክር፣ የቅዱሳን ጥበብ፣ የታጋሾች ሞስክርነት ያስፈልገናል።
እነዚህ የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ ስብስብ ደቂቅ መጻሕፍት የተጻፉትም ለዚሁ ዓላማ ነው። በጥሞና አንበባችሁ ትጠቀሙ ዘንድ እነሆ ከብዙ ጥንቀቄ ጋር ወደ አማርኛ ተርጉመን አቅርበንላችኋል።
መልካም ንባብ!!
ዘወትር ከግዮን ቅናሽ ጋር እንጠብቅዎታለን
Repost from ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
የሰብአዊ ድጋፍ ጥሪ!
+++
ማኅበረ ቅዱሳን በሀገራችን ኢትዮጵያ በማኅበራዊ ቀውሶች ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ እያሰባሰበ በማድረስ ላይ ይገኛል።
እርስዎም ድጋፍ በማድረግ ኃላፊነትዎችን እንዲወጡ ተጋብዘዋል።
ድጋፍ ለማድረግም፡-
በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
(Mahiber kidusan social support and rehabilitation accounts )
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በአዋሽ ባንክ 01329817420400
መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
💦#ዜና_መጽሐፍ
📖የአባ_ዘራስ_ምክር📖
✨[ከእማኾይ_እኅተ_ማርያም_ይፍሩ_ዘደብረ _ወገግ]
📝ከእማኾይ ጋር ምንም እንኳ-#በገድለ_ምንኲስና ብንተዋወቅም #የበረሃው_ምስጢር በተሰኘው ክታብ ልቡ ተሳፍሮ ከቅዱሳኑ በረሃ ያልገባ #ፍቅረ_እግዚአብሔር ግዚአብሔርን እንዲሁም ወደር አልባ ምሕረቱን በማሰብ ድንቂያ ያልወዘወዘው፤ የልቡናውን አውታር በቅዱሳኑ ታሪክ ያላለዘበ የለም ብንል ሐሰት አይመስለኝም! -ታድያ አኹን ደግሞ ከ፬ዓመታት በኋላ #የአባ_ዘራስ_ምክር በተሰኘ አጓጊ መጽሐፍ መተውልናል እነኾ .....!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
👇
https://t.me/GhionBookStore1623
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
በእንተ ሥጋዌ
ለተማሪዎቹ የሚያስብ ርኀሩህ አስተማሪ አንዳንዶቹ ተማሪዎቹ ረቀቅና መጠቅ ያለው ትምህርት እንዳልገባቸው ሲያይ ወደ እነርሱ ደረጃ ዝቅ ብሎ እነርሱ በሚገባቸው በማንኛውም ሁኔታ እንደሚያስተምራቸው ሁሉ የእግዚአብሔር ቃልም እንዲሁ አደረገ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም እንዲህ እንዳለ፡- በእግዚአብሔር ጥበብ ምክንያት ዓለም እግዚአብሔርን በጥበብዋ ስላላወቀች በስብከት ሞኝነት የሚያምኑትን ሊያድን የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ሆኗልና፡፡»"
#ቅዱስ_አትናቴዎስ_ሐዋርያዊ_ህይወቱና_ትምህርቱ
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
💧💧💧💧💧💧💧
📖#የጽድቅ_ሕይወት📖
አልፎ አልፎ አንዳንድ ሰዎች “ለጸሎት ጊዜ የለንም!” በማለት ይቅርታ ሲጠይቁ ይደመጣሉ፡፡ እኔ ምንጊዜም ቢሆን እንደዚህ ያለውን ምክንያት ፈጽሞ አልቀበለውም፡ ዋና ምክንያት አድርጌም አልቆጥረውም፡፡ በመሆኑም እንደዚህ ዓይነቶቹን ሰዎች እንዲህ እላቸዋለሁ፡ “ጸሎታችሁንና ተመስጦአችሁን ቅድሚያ ከምትሰጧቸው ፍላጎቶቻችሁ በላይ አድርጋችሁ የምታስቀምጧቸው ከሆነ ለእነርሱ የሚሆነውን ጊዜ ማግኘት ትችላላችሁ በአገልግሎት መስክ ውስጥና ብዛት ባላቸው አገልጋዮች ሕይወት ውስጥ ስላለው ጸሎትም ተመሳሳይ ነገር መናገር እንችላለን ፡፡ እነርሱ ራሳቸውን በመንፈሳዊነት ለማዘጋጀት ከሚወስዱት ጊዜ የበለጠ ትምህርቱን ለማዘጋጀት ለሚወስዱት ጊዜ ነው ትኩረት የሚሰጡት፡፡ እነርሱ የሚጨነቁት ለአገልግሎታቸው ጊዜ፡ ለአገልግሎቱ ለሚደረጉ ስብሰባዎች፡ ለፎቶግራፎች፡ ለስጦታዎች፡ ለቤተመጻሕፍት፡ ለስብከቶች፡ ለጉዞዎችና ለሌሎች ተመሳሳይ እንቅስቃሴዎች ነው፡፡
[ከመጽሐፉ የተወሰደ]
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
👇
https://t.me/GhionBookStore1623
"❝ነፍስ ድኅንት ወነፍስ ርህብት እንተ ጸግበት ተአኩተከ❞።ምሳሌ ሰሎ፡ ፴፯:፯#ረድኤተ_እግዚአብሔር ለተራበች ሰውነት የመረረው
#ቅምሻ
#ነገር_ግን እግዚአብሔር ከደማስቆ አፋፍ ላይ ሆኖ ይጣራል፤ ተው ተመለሱ ይለናል፡፡
የጳውሎስ አምላክ የእኛም አምላክ ነው፡፡ እርሱን ፈልጎ በደማስቆ መንገድ ያገኘው እና ምርጥ ዕቃው ያደረገው ጌታ እኛን የማይፈልግበት ምክንያት የለም፡፡ ግን የሚጣራውን የእግዚአብሔርን ደምፅ እንዴት ነው መስማት የምንፈልገው? በሕልም ወይስ በሌላ ዓይነት ተአምራዊ መንገድ? እኛን ፈልጎ የሚጣራው መለኮታዊ ድምፅ ያለው በእጃችን የጨበጥነው #መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ነው፡፡
ሳውል ወደ ክርስትና እምነት ተመልሶ
በሰማዕትነት ካረፈ ይኸው _ ከሁለት ሺህ ዓመታት በላይ ተቆጠሩ፡፡ በሐዋርያት ሥራ የተጻፈው ‹‹ለምን ታሳድደኛለህ? የሚለው ቃል ግን ያልተመለስነውን _ ሳውሎች ለማንቃት አሁንም ድረስ በታላቅ ድምፅ
ይጣራል፡፡
ቀደም ብለን እንዳነሣነው ቅዱስ ሉቃስ ስለዚህ መገለጥ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፉ ሦስት ጊዜ የጻፈ ቢሆንም እርሱ ስለ ሁኔታው በተረከው እና የታሪኩ ባለቤት ቅዱስ ጳውሎስ በተናገራቸው መካከል ግን የተወሰነ ልዩነት ያለ መስሎ እንዲሰማን የሚያደርጉ ንባቦች አሉ፡፡ በተለይ ደግሞ ከላይ በጥሬው ለሚያነብ ሰው ‹‹ከሳውል ጋር የነበሩት ሰዎች የክርስቶስን ድምፅ _ ሰምተዋል ወይስ አልሰሙም በሚለው ጥያቄ ዙሪያ ጸሐፊው ቀድሞ...
ከ ገጽ【109】
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
