ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
Open in Telegram
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
Show more3 309
Subscribers
-224 hours
-97 days
-3630 days
Posts Archive
📖“ድርሳን ዘሄርማን ነቢይ ንባብና ትርጓሜው”፡
✨ተወዳጆች ከዚህ ቀደም "መጽሐፈ ምሥጢር ዘአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ" በተሰኘ የትርጉም ሥራቸው የምናውቃቸው ➮ አባ ኅሩይ ኤርምያስ (ዶ/ር) ከዚህ በፊት ያዘጋጇቸው መጻሕፍት እና የምርምር ሥራዎች መካከል መዝገበ ታሪክ ቁጥር 1፣መዝገበ ታሪክ ቁጥር 2፣መልካም ዜጋ ማነው?፣ገድለ ቂርቆስ ትርጉም ፣ገድለ ፋሲለደስ - ትርጉም፣ ገድለ አቡነ ቀውስጦስ - ትርጉም፣ ገድለ አቡነ ታዴዎስ - ትርጉም፣ ገድለ አቡነ አፍጼ - ትርጉም፣ መጻሕፍትን መርምሩ፣መርኆ ምሥጢር፣ መጽሐፈ ምሥጢር ዘአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ- ትርጉም፣ቅዳሴ ወቁርባን፣ እንዲኹም መዐዛ ቅዳሴ ንባቡና ትርጓሜው - አንድምታ........ ተጠቃሽ ናቸው።
👉አኹንም ይህን “ድርሳን ዘሄርማን ነቢይ ንባብና ትርጓሜው”፡ ከተዘጋጀ ቢቆይም ሀገር ውስጥ ማግኘት አለመቻላችንን ከግምት በማስገባት እዚኹ ተዘጋጅቶ ቀርቦልናል....
💧መጽሐፉም እኛው ዘንድ በልዩ በቅናሽ ይገኛል ....!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
#እግዚአብሔርስ እግዚአብሔር ነውና መግለጫም ማመስገኛም ቃል ብናጣ አያስደንቅም። ከአእምሮ በላይ ከዐቅማችን በላይ ነው ብለን መደበቂያ ዋሻ እናገኛለን።
👉🏾የተቸገርነው በእኛ ተፈጥሮ የተፈጠረችውን የክብርን ማዕርጋት ኹሉ ሰብስባ የከበረችውን ድንግል ማርያምንም ማመስገኛ እና መግለጫ ቃላት በማጣታችን ነው። የጸጋ እና የክብር ሁሉ እልፍኝ የኾነችበት ባዕለ ጸግነቷ እኛን ደሃ አደረገን። ገና አላመሰገንናትም ገናም አልተረጎምናትም እኮ!
የእመቤታችን ፍቅሯን በልቡናችን ጣዕሟን በአንደበታችን ያኑርልን!🙏🙏 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
📖ውዳሴ ማርያምና ቅዳሴ ማርያም
ጸሎተ ሃይማኖትና አቡነ ዘበሰማያት
አንድምታ ትርጓሜ
#ውዳሴ ማርያምንና ቅዳሴ ማርያምንና የጸለዩ አባቶች ከፍ ያለ ክብርና ከፈጣሪያቸው ባለሟልነትን ተቀብለዋል። እኛም በጸሎቱ ተጠቅመን ከሰይጣን ሥራ ከሥጋ ፈተና ተጠብቀንበት በአምላካችን ዘንድ ክብር እንድናገኝ ያድርገን፤ ለቅዱስ ኤፍሬምና ለቅዱስ ሕርያቆስ ምሥጢሩን ጥበቡን የገለጠች እመቤት ለእኛም ጥበቡን ማስተዋሉን ትግለጥልን፤ ከነዚህ ቅዱሳን በረከት ረድኤት ያሳትፈን፤ አሜን፡፡
#በታላቁ የበዓታው ሊቅ መጋቤ ሐዲስ ደምጸ አንበርብር የተዘጋጀው ይህ የእመቤታችንን ውዳሴዋን ቅዳሴዋን ከአቡነ ዘበሰማያትናጸሎተ ሃይማኖት ጋር የያዘ አንድምታ ነው! ማብራሪያውና ታሪኩማ ልዩ ነው !!
➮በያዝነው ጾም ደግሞ አስፈላጊነቱ የማያጠያይቅ ነው!
©መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
1. ጾም በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት
2. የጾም አስፈላጊነትና ጠቀሜታ
3. ጾም የታወቀ ጊዜ ያለው መሆኑ
4. በጾም ወቅት የማይበሉ ምግቦች ስለ መኖራቸው
5. ጾም በእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋ ያለው ስለ መሆኑ
6. ጾም በቅዱሳን አባቶች ትምህርት
በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም መልኳ እንደ አምላክ መልክ ነው!
ፍጹም እውነት ነውና እንድታርፍ ልብህን ደግፈህ ስማው። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ለመወለዱ ምድራዊ አባት የለውም።
በዚህ ዓለም በታወቀው ሥርዓተ ልደት ለመፅነስ ዘር ከወንድም ከሴትም መከፈል አለበት። ሲወለድም አባቱን ወይ እናቱን ይመስላል ለማለት መነሻ ምክንያት አለ። ከኹለቱ የተገኘ ነውና።
እመቤታችን ግን ያለ ዘርዐ ብእሲ በኅቱም ድንግልና ነው የወለደችው። ስለዚህ የጌታችን መልኩ የሚመስለው እናቱን ብቻ ነው። አባቱን ይመስላል እንዳንል ምድራዊ አባት የለውምና እናቱን መምሰሉ አያጠራጥርም። እናም የጌታችን መልኩ እንደ እናቱ ማርያም ነው ከማለት የሚያደናቅፈን የለም።
ነገር ግን ስለ ትሕትና አነጋገር እርሱ እርሷን ይመስላል ከማለት የእርሷ መልክ እንደ አምላክ መልክ ነው እንላለን።
አዕምሮውን ለብዎውን ሳይብን አሳድሪብን። ሰአሊ ለነ ቅድስት!
📖#አንቀጸ_ብርሃን_ትርጓሜ📖
#ቅዱስ_ኤፍሬም_ሶርያዊ ቅዱሳት መጻሕፍትን እንዲህ ገልጿቸው ነበር ✍️"ቅዱሳት መጻሕፍት ተቀድቶ እንደማያልቅ ጥልቅ የውኃ ጉድጓድ ናቸው፡፡ ማንም : ሰው : የፈለገውንና የቻለውን ያህል ጠጥቶ መርካትና ቀድቶ መውሰድ ይችላል፣ የውኃ ጉድጓዱን ግን አይጨርሰውም። ከእርሱ በኋላ የሚመጡ ሌሎችም እንዲሁ መጠጣትና መቅዳት ይችላሉ፡፡ የቀደመው ለኋለኛው፤ ያም ከእርሱ በኋላ ለሚመጣው አይጨርስበትም፡፡"
.. ይህም ማለት ቅዱሳት መጻሕፍትን ሊቃውንት በየዘመናቱ ይመሰጡባቸዋል፤ ይመገቧቸዋል፤ ይተረጕሟቸዋል፣ ያም ሆኖ ግን እነርሱ የተገለጠላቸውንና የቻሉትን ያህል ተረድተውና አስረድተው ያልፋሉ እንጂ ምሥጢሩን ግን አይጨርሱትም።
#መምህራችን መምህር ኃይለ ማርያም ዘውዱ እስከ ዛሬ ሐሳቡ ሳይፍታታና ሳይተረጐም በገጸ ንባብ ብቻ የነበረውን አንቀጸ ብርሃን የተባለውን የቅዱስ ያሬድን ድርሰት በአንድምታ ትርጓሜ ተርጉመው አቅርበውልናል።
#የኔታ ኃይለ ማርያም ዘውዱ በዚህ የጀመረው አስተማሪ የሆኑ ሌሎች መጻሕፍትንም ብዕራቸው ወደፊትም እንደሚያስነብበን ተስፋ በማድረግ፤ እርሳቸውን እንዲጠብቅልን እኛንም #አንብበን እንድንጠቀም #እግዚአብሔር ይርዳን እላለሁ፡፡
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL ,በEMS እንዲሁም የ delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
https://t.me/GhionBookStore1623
በሱባዔ፣ በምሕላ፣ በምጽዋት፣ በጸሎት፣ በስግደት በመትጋት መዋዕለ ጾሙን በየገዳማቱ ካሉት አባቶቻችንና እናቶቻችን ጋር እንተባበር ዘንድ የፈቀደልን የጊዜ ባለቤት ልዑል እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን!!!
የአምላክ እናት ክብርት እመቤታችን ዕርገቷን ለማየት ታብቃን! የቤተ ክርስቲያናችንን እና የሀገራችንንም ትንሣኤ ታሳየን።
መልካም ሱባኤ!!!
እመቤታችን እምላክን ወለደች ሲባል ያልደነቃቸው ሰዎች በልጇ ኃይል ከሞት ተነሥታለች ዐርጋለች ሲባሉ በጣም ይከፋሉ። ለምን? ካልን ለእርሷ የኾነውን ኹሉ ሊኾኑት ስለማይችሉ በቅናት ነበልባል እስኪጨነቁ ድረስ እየተቃጠሉ።
ለእመቤታችን የተሰጣት ኹሉ የቱንም ያኽል ቢያስደንቅ የአምላክ እናት ከመኾኗ የሚደርስ የለም። ትንሣኤዋ እጅግ እጅግ በጣም ያስደንቀን እንጅ እመ አምላክነቷ ይበልጥ ያስደንቀናል።
እንኳን ለጾመ ፍልሰታ አደረሳችሁ!!!
+3
#ውድ_የግዮን_ቤተሰቦቻችን
# እንኳን ለጾመ ማርያም [ጾመ ፍልሰታ ለእግዝእትነ] አደረሰን..!
..ለተወጃ ጾም ማሳለጫ ይኾኑ ዘንድ እኒህን መረጥንላችኹ👇
📜ነገረ ማርያም በሶርያ አባቶች ፦በጣም ግሩም መጣጥፍ ነው!#በመምህር ሽመልስ መርጊያ ፦ በጥቅሉ ስለ ቅድስቷ ደስ በሚል አጻጻፍ የተዘጋጀ...እንደምትወዱት አልጠራጠርም !
📖ፍና ቅዱሳን ፦ ቀሲስ ታምራት ውቤ ...እድሜዎትን ያርዝምልን ..! ይህ ከቅዱሳኑ መንገድ እንዴት እንደምንደርስ ቆንጠጥ በግሩማን መካሪ ቃላት ጓደኛ የሚኾን መጽሐፍ !ይያዝ!
🗞ሕይወተ ማርያም ድንግል ፦ከሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ የተበረከተ...ስለዚህ መጽሐፍ ማውራት ይከብዳል ከጥፍጥናው የተነሳ ከእጃችን ባንለየውሳ ያሰኛል....! ለዚህ ጾም ደግሞ የግድድድድ መነበብ አለበት!
📝ከበረሀውያን ሕይወት እና አንደበት ፦መምህረ መምህራን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ እቅበተ እምነት ብቻ አይደለም እንዲህ ወደ ቅድስና የሚያንደረድር መሳጭ መጽሐፍ ! አደራ ይነበብ!
👉#እኛም ጥቆማ ብቻ ሳይኾን ጾሙን በማስመልከት ታላቅ ቅናሽ ከዘጋጅተናል!
📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
📖ኰኲሐ ሃይማኖት
【ወጣት ተመልከት እንዳትሳሳት】
✍️...በል ደኅና ኹን! አንተ፤ ዕውሩን ዐይናማ ነህ ቢሉት ዐይናማ ላይሆን፣ የተሰበረውንም ደኅና ነህ ቢሉት ደኅና ላይሆን፣ የንብላውን ሕግ እውነተኛ ለማስመሰል በጻፍከው ስሕተት የምእመናንን ልቡና ይሆንን? አይሆንን? ከሚል ጥርጥር ላይ ስለጣልከው እኔም “ይነግረው ያጣ ያሙኝ አይመስለውም” እንደሚባለው ተረት ዝም ብንልህ ጥፋትህ እየቀጠልክ ስለሔድክ ለምእመናን ነገርህ እውነት ይመስላቸዋል በማለት “ገሥጽ ወተዛለፍ” ያለው ቃል እያጽናናኝ (፪ጢሞ. ፬÷፪) መልሱን ስጽፍልህ ያመላለሱ ዘዴ እያስገደደኝ በማደርገው ንግግር አንዳንድ ላይ “ባርክዎሙ ለእለ ይረግሙክሙ” የተባለው ትእዛዝ ሳይፈርስብኝ የቀረ አይመስለኝምና የሰውን መዳኑን እንጂ መጎዳቱን የማይወድ ቸሩ አምላክ ኹላችንንም ይቅር ብሎ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ያገናኝን፡፡ አሜን፡፡
[ከመጽሐፉ የውስጥ ገጾች የተወሰደ]
🫧መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ ሊቅ ረቂቅ የሃይማኖት አርበኛ መኾናቸው ዛሬም በመጻሕፍቶቻቸው፤ ሲወሳ፤ ሲመሰከር ፤ትውልድ ሲሻገር ይኖራል። በእቅበተ እምነት ዙሪያም ይኽ ነው የማይባል አሻራ አኑረውልናል ።ከድንቅና ዘመን ተሻጋሪ ስራዎቻቸው መካከል ለኘሮቴስታንቱ ዘመንፈስ ቅዱስ አብርሃ ምላሽ የሰጡበት ኰኲሐ ሃይማኖት የተሰኘው መጽሐፋቸው በትህትና የተለበጠ በእውቀት የተጠረዘ መጽሐፍ መኾኑ መስካሪ የማያሻው እንዲኹም በዚኽ ዘመን ላለው የኑፋቄ ትምህርት እና ግርታ ውስጥ እየወደቀ ላለው ወጣት አይነተኛ መፍትሔ ይኽ መጽሐፍ እንደኾነ መገንዘብ አይከብድም።
©መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
#📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
ክህነት በሀዲስ ኪዳን
* የተለየ ክህነት
* አዲስ ክርስቲያን ካህን መሆን ይችላል?
* ሽማግሌ ወይስ ካህን ?
++++++++++~~~~~+++++++++
ኃጢአትን ይቅር የማለትን ሥልጣን ለራሱ ለእግዚአብሔር ብቻ የሚገባ ሥልጣን ስለሆነ ይህን ለሌላ ለማንም አንሰጥም በማለት፣ እግዚአብሔርን ታላቅ በሆነ አክብሮት እናከብረዋለን ይላሉ። ሆኖም ግን እርሱ በግልጽ የተናገረውን ትእዛዙን እንደሚሽሩትና ለካህናት የሰጠውን ሥልጣን አንቀበልም እንደሚሉት እንደ እነርሱ አድርጎ የሚያቃልለው ሌላ ማንም የለም። ራሱ ጌታችን “መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ፣ ኃጢአታቸውን ይቅር ያላችኋቸው ሁሉ ይቀርላቸዋል፤ የያዛችሁባቸው ተይዞባቸዋል” ያላቸው ከሆነ፣ እግዚአብሔርን የሚያከብረው የእርሱን ትእዛዝ ተቀብሎ የሚታዘዘው ነው? ወይስ ትእዛዙን አልቀበልም የሚለው? .. " (ቅዱስ አምብሮስ በእንተ ንስሐ፣ መጽሐፍ 1፡6-7)
#መድሎተ_ጽድቅ
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
❝ ስሙ የጣፈጠ መድኃኒታችን እሱ የምሥጋና ወይን ነው እናቱ የድኅነት ጽዋ ናት መስቀሉም የመላእክት ጉጠት ምሳሌ ዕርፈ መስቀል ነው።❞
ድርሳነ መድኃኔ ዓለም ዘእሑድ
ምዕራፍ ፲፩፥፯
መልካም ዕለተ #?ሰንበት ወ በዓለ #መድኃኔዓለም !!
🙏🙏🙏
✨
📖መጽሐፈ ሳዊሮስ ዘእስሙናይን📖
#ይህ መጽሐፍ ጥንታዊው #ኦርቶዶክሳዊ_የቤተ_ክርስቲያ፣ አስተምህሮ ከዘመነኛው ተግዳሮት (በተለይ እስላማዊው የአስተምህሮ ትችት) አንጻር ቃኝቶ ያዘጋጀው ድርሰቱ ነው:: ምሥጢረ ሥላሴን በአብዛኛው በኩነታት አጓጻር ሲያብራራ እናገኘዋለ። ይህም ለእስላማዊው ትችት የተሻለ የሚሆነው በኩነታት ላይ የተመሠረተው ሐተታ በመሆኑ ነው::
👉ይህ መጽሐፍ በሳዊሮስ እና በሌሎች አረብ~ክርስቲያ፣ ሊቃውንት ድርሳናት በተለመደ መልኩ ጥልቅ እና ረቂቅ የሆኑ ተመስጦአዊ ሐተታዎች፣ የያዘ መጽሐፍ ነው። ልዩ የሚያደርገው ደግሞ ነገረ~ሃይማኖታዊ ሐተታዎች፣ ብቻ ሳይሆን ጥልቅ የሆኑ የመንፈሳዊ ሕይወት መመሪያዎች፣ እና ተሞክሮዎች የያዘ እጅግ ጠቃሚ መጽሐፍ መሆኑ ነው::
#መምህር_ኤፍሬም ክንዱ ይህን በቀላሉ የማይገኝ ውድ መጽሐፍትን ከግእዝ ወደ አማርኛ ተርጉመው ለአንባብያን ማብቃታቸው በእጅጉ የሚያስመሰግን ነው:: #ለመምህር _ኤፍሬም #እግዚአብሔር ብዙ የሚያገለግሉበት፣ ጸጋ ያድልልኝ!!
ዲ/ን በረከት አዝመራው
©መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
✨
📖መጽሐፈ ሳዊሮስ ዘእስሙናይን📖
#ይህ መጽሐፍ ጥንታዊው #ኦርቶዶክሳዊ_የቤተ_ክርስቲያ፣ አስተምህሮ ከዘመነኛው ተግዳሮት (በተለይ እስላማዊው የአስተምህሮ ትችት) አንጻር ቃኝቶ ያዘጋጀው ድርሰቱ ነው:: ምሥጢረ ሥላሴን በአብዛኛው በኩነታት አጓጻር ሲያብራራ እናገኘዋለ። ይህም ለእስላማዊው ትችት የተሻለ የሚሆነው በኩነታት ላይ የተመሠረተው ሐተታ በመሆኑ ነው::
👉ይህ መጽሐፍ በሳዊሮስ እና በሌሎች አረብ~ክርስቲያ፣ ሊቃውንት ድርሳናት በተለመደ መልኩ ጥልቅ እና ረቂቅ የሆኑ ተመስጦአዊ ሐተታዎች፣ የያዘ መጽሐፍ ነው። ልዩ የሚያደርገው ደግሞ ነገረ~ሃይማኖታዊ ሐተታዎች፣ ብቻ ሳይሆን ጥልቅ የሆኑ የመንፈሳዊ ሕይወት መመሪያዎች፣ እና ተሞክሮዎች የያዘ እጅግ ጠቃሚ መጽሐፍ መሆኑ ነው::
#መምህር_ኤፍሬም ክንዱ ይህን በቀላሉ የማይገኝ ውድ መጽሐፍትን ከግእዝ ወደ አማርኛ ተርጉመው ለአንባብያን ማብቃታቸው በእጅጉ የሚያስመሰግን ነው:: #ለመምህር _ኤፍሬም #እግዚአብሔር ብዙ የሚያገለግሉበት፣ ጸጋ ያድልልኝ!!
ዲ/ን በረከት አዝመራው
©መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
+2
🫧መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ
.....🤔እናንተዬ ጊዜው ይነጉዳል የዛሬ 55ዓመት ገደማ መኾኑ ነው#መልአከ_ብርሃናት_አድማሱ_ጀንበሬ የኢትዮጵያን ሊቃውንት ታሪካቸውንና ቅኔያቸውን አሰባስበው ለኅትመት እያዘጋጁ በነበሩበት ወቅት ነበር በወርኃ ሐምሌ 24 ቀን1962 ዓ.ም ኅልፈት የገታቸው .....
የ20ኛው ክፍለ ዘመን መብራት እንቁ ሊቅ ረቂቅ የሃይማኖት አርበኛ መኾናቸው ዛሬም መጻሕፍቶቻቸውን ያነበበ በሙሉ የዃሊት መለስ ብሎ በአድናቆት የሚመሰክረው እውታ ነው።
💧 በእቅበተ እምነት ዙሪያም ይኽ ነው የማይባል አሻራ አኑረውልናል ።ከድንቅና ዘመን ተሻጋሪ ስራዎቻቸው መካከል መድሎተ አሚን[ሰው ኾይ!!] እና ኰኲሐ ሃይማኖት የተሰኙት መጻሕፍት በቀዳሚነት የሚጠቀሱ ናቸው ።
የሚደንቀው እያንዳንዱን መጽሐፍ በትህትና ለብጠው በእውቀት ጠርዘው እንዳዘጋጁት መጻሕፍቱ ምስክር ናቸው ለዚያም በየዘመኑ የሚነሱ ዛሬም ድረስ ያሉ አሉን የምንላቸው እውቅ ጸሐፍት በየክታቦቻቸው የእሳቸውን መጽሐፍ ሳያጣቅሱልን አያልፉም ።
ለእናት ቤተክርስትያንም ግጻዌ እና መሰል መገልገያዎች ያበረከቱ ፤ የቅኔ ማዕበል የኾኑ ታላቅ ሊቅ......!
[በረከታቸው ትድረሰን!]
#📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
Repost from N/a
የቤተክርስቲያናችን የኻያኛው ክፍለ ዘመን ሊቅ!
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
ታሪካቸው ዘመን ተናክሶ ሲነሣ መነሻውን 1885 ዓ.ም ያደርጋል። የተወለዱት ከአቶ ጀንበሬ አዲሱ እና ከእናታቸው ወ/ሮ ወለተ ማርያም ኃይሉ በሀገረ ድማኅ/ዲማ #ቅዱስ_ጊዮርጊስ አጥቢያ ከላይ በተጠቀሰው ዓመተ-ምሕረት ነሐሴ አንድ ቀን ነው። እናታቸው ገና በአራስነታቸው ወደ ቤታቸው በመጡ ለአምላካቸው ባደሩ አንድ ባሕታዊ፦
ይኽ ሕፃን #እግዚአብሔርን እንዲያገለግለው የመረጠው ነውና በጥንቃቄ አሳድጊው ፤ በሰዓቱም ወደ ትምህርት ቤት አስገቢው።የሚል መመሪያ ተቀብለዋል ፤ በዚያው የልጃቸውን ስምም "ያለው" አሉት። #እግዚአብሔር ያለው/የፈቀደው ይኹን ማለተቸው ነበር። ወላጅ አባት ግን አድማሱ አሉት። ከቤተሰቦቻቸው እስኪለያዩ 19 ዓመታቸው ድረስ በእናታቸው በወጣላቸው ስም ይጠሩ ነበር። በኋላ ለትምህርት ከሀገራቸው ከወጡ በኋላ በመላ ዘመናቸው በአባታቸው በወጣላቸው ስም ሲጠሩ ኑረዋል! ትምህርትን የጀመሩት ከአጥቢያቸው ከነበሩ አባ ወንድሙ ከተባሉ ባሕታዊ ነው። ከዚያ በኋላማ የትምህርት አበባን ለመቅሰም ያልበረሩበትን ሀገር መጥቀስ ይቀላል። ጾመ ድጓን ፣ ምዕራፍን ፣ ድጓን ፣ ዝማሬ መዋሥዕትን ፣ ቅኔን እና ከትርጓሜ መጻሕፍት ቤት የተወሰኑ ጉባኤያትን ከአጥቢያቸው ከቀሰሙ በኋላ በደብረ ሊባኖስ አድርገው አዲስ አበባ በመግባት "የቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን" የብሉይ መምህር ከነበሩት ከወልደ ሥላሴ የብሉይ ትርጓሜያትን ተምረዋል። ከዚያ እንደ ገና ወደ አጥቢያቸው በመመለስ ቅኔን አጥብቀዋል። አኹንም ወደ ደሴ በመሻገር ፍትሐ ነገሥትን ከተማሩ በኋላ ከታላቁ ሊቅ /የቀለም ቀንድ/ ከመምህር አካለ ወልድ ደግሞ መጻሕፍተ ሐዲሳትንና መጻሕፍተ ሊቃውንትን ተምረዋል። በዚኽ መቼ ያርፉና አኹንም ወደ ጎጃም በመሻገር ብሉያትን አጠንክረው በዚያው ቅኔ አስመስክረው ወደ ሀገረ ሙላዳቸው ዲማ በመመለስ የቅኔ ጉባኤ ገብተው ቅኔ ማስተማር ጀመሩ። ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ወደ ሸዋ ተሻግረዋል ወደ ሸዋ ሲመጡ በእጃቸው በብራና ጽፈው ይዘው ከመጧቸው መጻሕፍት መካከል ኹለቱ አኹንም ድረስ "መንበረ መንግሥት ገብርኤል ቤተክርስቲያን" ይገኛሉ። አዲስ አበባ እያሉ መጋቤ ምሥጢር ተብለው ተጠሩ - ይኽ ስም ለመጠሪያነት ሲውል የመጀመሪያው ነበርና ከእሳቸው ይልቅ ዕድለኛው ስያሜው ነው ተብሎላቸዋል። በኋላ "ሊቀ ጠበብት" ተብለው ተሹመው ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። ቅኔ እያስተማሩ ባሉበት ሰዓት ኢጣልያ ሀገራችንን ወርራ ስለነበር እሳቸውም ሕዝቡን ለጸሎት እየቀሰቀሱ የአርበኞች አባል በመኾኑ ሞራል በመስጠት ለሀገራቸው የሚችሉትን ኹሉ አድርገዋል። በኋላ ኢጣልያና በኢትዮጵያ አርበኞች በእግዚአብሔር ቸርነት ተሸንፎ ከሀገር ሲወጣ - "ሊቀ ጠበብት አድማሱ ጀንበሬ" ላደረጉት አስተዋጽኦ ባለ ሦስት ዘንባባ ሚዳሊያ ከንጉሠ ነገሥቱ ተበርክቶላቸዋል። በዚያ ዓመት (1935 ዓ.ም) ራስ ወርቅ አስረው "መልአከ ብርሃኑ" ተብለው ተሾሙ። ከዚያ በኋላ ፈላጊያቸው ስለበዛ አዲስ አበባ መጥተው በጠቅላይ ቤተክህነት ሲያገለግሉ ኑረዋል!! የድርሰት ክፍል ሹም ፣ የሊቃውንት ጉባኤ ፕሬዝዳንት ፣ በመኾን በሙሉ አቅማቸው ቤተክርስቲያንን አገልግለዋል ፣ ቤተክርስቲያናችንም በራሷ ልጆች ሲኖዶስ መሥራት መተዳደር እንዳለባት በብርቱ ሞግተዋል። ለጊዜው የሐሳባቸው ተጋሪ ቢያጡም በኋላ ግን ድካማቸው በጊዜው ጊዜ ፍሬ አፍርቶ ቤተክርስቲያን በራሷ ልጆች መመራት ችላለች። በንጉሠ ነገሥቱ በ1949 ዓ.ም የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ኹነው በመሾም ሀገራቸውን አገልግለዋል። በዚኽ ኹሉ ኃላፊነት የተወጠሩ ቢኾንም አንባቢ ተመራማሪ ጠያቂ ፣ ለዎችም ያወቁትን ማስረዳት ነፍሳቸው ነበርና ከንባብ ጎን ለጎን እስከ አኹን ተወዳጅነታቸው እንደቀጠለ ያለላቸውን ኹለቱን መጻሕፍቶቻቸውን ያዘጋጇቸው [ #ኰኵሐ_ሃይማኖትንና #መድሎተ_አሚንን ] በዚኽ ወቅት ነበር። ከፍርድ ቤት ጡረታ ሲወጡ ቀጥታ ሙሉ ጊዜያቸውን ቤተክርስቲያንን ለማገልገል ተጠቅመውበታል። ቅዳሳት መጻሕፍት ትርጉም ሐተታ ላይ እየተሳተፉ አንዳንድ አሻሚ ገጸ ንባባትን በተሰጣቸው ሀብተ ትርጓሜ ሐተታ ይሠሩላቸው ነበር። ታላቁ ሊቅ አለቃ ጌታው ኅሩይ በጉባኤያቸው ትርጓሜ ሲያስተምሩ እንደ ስርዋጽ "መልአክ ብርሃን" እንደተረጎሙት እያሉ አብነት ይጠቅሷቸው እንደነበር ይነገራል። እረፍት የማያውቁት እኒኽ ሊቅ የኢትዮጵያን ሊቃውንት ታሪካቸውንና ቅኔያቸውን አሰባስበው ለኅትመት እያዘጋጁ ባሉበት ሰዓት ደከሙ አዎ ደከሙ ሰው አይደሉ.... በንባብ በምርምር በኃሠሣ አእምሮአቸው ደከመ (ስትሮክ) እና ታላቁ ሊቅ ሐምሌ 24 1962 ዓ.ም ከድካመ ሥጋ አረፉ.....!! [ታሪካቸው እንዲኹ በቀላሉ ተነግሮ የሚያልቅ ባይኾንም - የተወሰነ ታሪካቸውንና ስለመጻሕፍቶቻቸው በክፍል ኹለት በአጭሩ እንመለስበታለን] ─━━━━⊱✿⊰━━━━─ ኢትዮጵያዊው አትናቴዎስ! ኢትዮጵያዊው ዮሐንስ አፈወርቅ! ኢትዮጵያዊው ዓምደ ሃይማኖት ቄርሎስ! #መልአከ_ብርሃናት_አድማሱ_ጀንበሬ!! [ቅድስት በረከታቸው ትረፍብን]
# የልዳው ቅዱስ ጊዮርጊስ ኾይ ለአንተ ሰላምታ ይገባል። #ፈረሰኛው ቅዱስ ጊዮርጊስ ኾይ ሰላምታ ይገባሃል። #የተወደደው የልጅዋ የኢየሱስ ክርስቶስና የድንግል ማርያም እውነተኛ ምስክር ሆይ ሰላምታ ይገባሃል።#የጥበብ መገኛዋ አዳራሽ ኾይ ሰላምታ ይገባሃል።
#መልክአ_ጊዮርጊስ
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDeliveryሀ አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
