ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
Open in Telegram
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
Show more3 275
Subscribers
No data24 hours
-207 days
-5830 days
Posts Archive
"ተክለሃይማኖት" ማለት ‹‹ተክለ አብ፣ ተክለ ወልድ፣ ተክለ መንፈስ ቅዱስ›› ማለት ነው፡፡ውልደታቸው በቡልጋ ደብረ ጽላሎሽ ነው። አባታቸው ቅዱስ ጸጋ ዘአብ፤ እናታቸው እግዚእ ኀርያ ይባላሉ። ቅዱሳን ከሆኑት ጸጋ ዘአብ እና እግዚእ ኃርያ ቅዱስ ጋብቻ አቡነ ተክለ ሐይማኖት መጋቢት 29 ተፀንሰው ታህሳስ 24 ተወለዱ። በወላጆቻቸው ፍስሐ ጽዮን ተብለው ነበር የተሰየሙት፤ትርጓሜውም የጽዮን ደስታ፣ ተድላ ማለት ነው፤ ኋላ ነው ተክለሀሃይማኖት የተባሉት። አባታችን ጻድቁ ተክለሃይማኖት ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር ሃያ አምስተኛ ሆነው የእግዚአብሔርን መንበር አሐዱ አብ ቅዱስ፣አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ብለው አጥነዋል። የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ምልጃና ጸሎት አይለየን። 23/10/2017 ዓ.ም!
ስለ እርሱ አንብቡ
"እግዚአብሔር በአሳባችሁ ውስጥ እንዲኖር ስለ እርሱ አብዝታችሁ "አንብቡ ።
እርሱን ለማወቅ ስለ እርሱ "አንብቡ ። እርሱን ካላወቃችሁት እንዴት እርሱን ልትወዱት ትችላላችሁ ?
ስለ እርሱ "አንብቡ ስታነቡ ግን በሳይንሳዊ ወይም በፍልስፍና ጠባይ አታንብቡ ወይም ደግሞ ስለ እርሱ ጥናታዊ ጽሑፍ ወይም ትምህርት ለመስጠት አታንብቡ ። ነገር ግን ወደ እርሱ ጥልቀት ለመግባት ወይም እርሱ ወደ እናንተ ጥልቀት እንዲገባ "አንብቡ። ለነፍሳችሁ ውድ የሆኑትን የእርሱን ባሕርያት ለማወቅ ስትሉ "አንብቡ ይህ እውቀት አሳባችሁ ከእርሱ ጋር እንዲጣበቅና ፍቅሩ ከእናንተ ልብ ጋር እንዲቀናጅ ያደርግላችኋልና ። ስለ ስምምነቱ ስትሉም "አንብቡ ። ከወደዱት ሰዎች ጋር ስላለው ግንኙነት በጠላቶቹ ላይ ስላለው አቋም ስትሉ "አንብቡ !
"እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነ ቀምሳችሁ ታዩ ዘንድ ስለ እርሱ "አንብቡ ። ታዲያ ንባባችሁ ለልባችሁ ምግብ እንዲሆን እንጂ እንዲሁ ተራ ንባብ እንዲሆን አትፍቀዱ ።
ስለ እግዚአብሔር ብዙ ካነበባችሁ በእርሱ ዘንድ ያለውን ፍጹምነት በሙሉ ታገኛላችሁ ።
ከወደዳችሁት ስለ እርሱ ማንበባችሁን ትቀጥላላችሁ ። እግዚአብሔር ስለ እርሱ የሚያነቡትን ስለ እርሱ ዜና የሚጠይቁትን ከእርሱ ታሪኮች መካከል አንዱን ለማወቅ የሚናፍቁትንና እርሱን የሚያደንቁትን ሰዎች ይወዳቸዋል ። ስለ እርሱ ከመጽሐፍ ቅዱስ ወይም ከአባቶች ብሒሎች ወይም ከቤተክርስቲያንና ከቅዱሳን ታሪክ ልታነቡ ትችላላችሁ ። በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ የእግዚአብሔር እጅ ለመዳሰስ ስትሞክሩ በጥበቡ በኃይሉና በርኅራኄው ውስጥ እንደምትወዱት ታውቃላችሁ ።
- አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
📖#ትምህርት_በእንተ_ምክንያተ_ሐውልታት📖
.....ገብረ እግዚአብሔር ኪደን የማመሰግነው ይህን ሊቅ በራሳችን ቋንቋና ዘይቤ ዳግም እንዳውቀው ስላደረገኝ ነው፡፡ የትርጓሜው ወደረኛ ቋንቋና ውበት ሊቁን የራሳችን ትውፊትና የሕይወት ዘይቤ አካል አድርገን እንድንቈጥር ይጠቁመናል ሳይኾን ያስገድደናል፤ እኔ ተገድጄበታለሁ!
➮ይህን መጽሐፍ አንብቦ ትውፊቱን ከጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ለማነጻጸር፣ ሕይወቱን፣ ነባራዊውን የአገራችንን አኗኗር፣ የአገሩን ካህናት አገራዊ ሚና፣ ክርስቲያናዊ ምግባሩን ... ለመፈተሸ የማይገደድ አንባቢ ካለ ከሸንጎ ፊት ያቅርበኝ!በማለት የመጽሐፉን ግሩምነት የመሰከሩት #ደብተራና የሕግ ባለሞያ የኾኑት በአማን ነጸረ እኛም አንብበን ተጠቃሚዎች እነኾን ዘንድ ብሎም ራሳችንን እንድንፈትሽበት ያሳሰቡ ሲኾን #በግዮን_መጻሕፍት ደግሞ በልዩ ቅናሽ የተዘጋጀ ሲሆን ግዜ ሳንሰጥ መጽፏን ገዝተን ብንመገባት መልካም ነው እንላለን!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL ,በEMS እንዲሁም የ delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
https://t.me/GhionBookStore1623
#ሕንጸተ_ቤተ ክርስቲያን ዘእግዝእትነ ማርያም። #ሰኔ_21
.... ✍#ጌታችን በዐረገ በስምንተኛው ዓመት ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስ ወደ ፊልጵስዩስ ገብተው በክርስቶስ ስም አሳምነው ብዙ አሕዛብን ካጠመቁ በኋላ ቤተ ክርስቲያን ሊሠሩላቸው ወደዱ፡፡
በዚህ ጊዜ ርእሰ ሐዋርያት እያለ እኛ መሥራት አይገባንም ብለው በሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ መልእክት ላኩበት፡፡ እርሱም ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር መጥቶ ከቅዱስ ጳውሎስ እና ቅዱስ በርናባስ ጋር በኢየሩሳሌም ተገናከጽንት
በዚያም በአንድነት ሱባዔ ይዘው ከቆዩ በኋላ ጌታችን የሞቱትን አስነሥቶ፣ ያሉትንም ጠርቶ ቅዱሳን ሐዋርያትን #በፊልጵስዩስ አገር ሰብስቦ ‹‹በእናቴ በድንግል ማርያም ስም ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚሠራዉን የአብያተ ክርስቲያናት ሥራ ላሳያችሁ፤ ሥርዓቱንም ላስተምራችሁ ሰብስቤአችኋለሁ›› ብሎ ወደ ምሥራቅ ይዟቸው ወጣ፡፡
#በዚያም_ሥፍራ የነበሩትን ሦስት ድንጋዮችንም የተራራቁትን አቀራርቦ፣ ጥቃቅኑን ታላላቅ አድርጎ ቁመቱን በ፳፬፤ ወርዱን በ፲፪ ክንድ ለክቶ ለቅዱሳን ሐዋርያት ሰጣቸው፡፡
ከዚህ በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያት ሰም እሳት ሲያገኘው እንዲለመልም፣ ድንጋዩ በእጃቸው ላይ እየተሳበላቸው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑን ሠርተው ፈጽመዉታል፡፡
#ሕንጻ_ቤተ_ክርስቲያኑ የተሠራዉም ጌታችን በዐረገ በ፲፱ኛው ፤ እመቤታችን በዐረገች በ፬ኛው ዓመት ሰኔ ፳ ቀን ሲኾን፣ በ፳፩ኛው ቀን (በማግሥቱ) ኅብስት ሰማያዊ፣ ጽዋዕ ሰማያዊ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ወረደ፡፡ ጌታችንም ከእመቤታችን ጋር ከሰማየ ሰማያት መጥቶ እመቤታችንን ታቦት፤ ሐዋርያትን ልዑካን አድርጎ፣ እርሱ ሠራዒ ካህን ኾኖ ቀድሶ ካቈረባቸው በኋላ “ከዛሬ ጀምሮ እናንተም እንደዚህ አድርጉ “ ብሎ አዝዟቸው በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡
[መጽሐፈ ስንክሳር]
#እንኳን አደረሰን🙏🙏
+1
📚📚📚
📖#የበረሃው_ምሥጢር
📖#ገድለ_ምንኩስና
ውድ #ግዮናውያን እነዚህ ኹለት ተወዳጅ መጻሕፍት ስጠይቁን የነበራችኹ ጥቂት ፍሬ ተገኝተዋል....!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
+1
📚📚📚
📖#የበረሃው_ምሥጢር
📖#ገድለ_ምንኩስና
ውድ '#ግዮናውያን' እነዚህ ኹለት ተወዳጅ መጻሕፍት ስጠይቁን የነበራችኹ ውስን ፍሬዎች ብቻ አግኝተናል እንዳያልቅባችኹ....!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
" ስለ እኛ የሚማልደው ....."
👉 " ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ " ምን ማለት ነው?
👉 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሮሜ 8፥34ን ምን ብሎ ተረጎመው
👉 "መካከለኛ" የተባለበት ምክኒያት
👉 የቅዱሳን አማላጅነት ትምህርት የኢየሱስ ክርስቶስን መካከለኛነት ይቃወማል/ይጋፋል ?
+++++++++++++~~~++++++++++
ታዲያ እንዲህ ከአብ ጋር በከሃሊነትና በሥልጣን አንድ የሆነ እርሱ እኛን ለመርዳት ማላጅ መሆን እንዴት ያስፈልገዋል? እንዴት እርሱ አማላጅ ይሆናል? እንዴት ይማልዳል ይባላል? የተፈረደባቸውንና የተኮነኑትን ነጻ ያወጣቸውና ያዳናቸው እርሱ፣ ከሞት ፍርድና ከኩነኔ ነጻ ያወጣና ያዳነ እርሱ፣ ጻድቃንና ልጆች ያደረጋቸው እና እጅግ ከፍ ወዳለ ክብር ያወጣቸው እርሱ፣ ይህን ሁሉ ከፈጸመና ካከናወነ በኋላ፣ ባሕርያችንን በየማነ አብ በዘባነ ኪሩብ ካስቀመጠው በኋላ፣ በጣም ቀላል ስለሆኑት ነገሮች ማላጅ መሆን እንዴት ያስፈልገዋል? ሲዖልን በሥልጣኑ የበዘበዘ፣ ሞትን በኃይሉ የሻረ፣ ልጅነትንና ትንሣኤን የሰጠ፣ ባሕርያችንን ከራሱ ባሕርይ ጋር አዋሕዶ በሰማያት በንጉሡ ዙፋን ላይ ያስቀመጠው እርሱ፣ ስለ ጥቃቅን ነገሮች ለምን ለማኝ ማላጅ ይሆናል?
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፣ ትርጓሜ መልእክተ ሮሜ)
#መድሎተ_ጽድቅ
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
📖ሥርዓተ ቅዳሴና ሚስጥራዊ ማብራሪያው📖
......#በቅዳሴ ጊዜ የሚስቅ የሚሳለቅ ቢኖር ካህን ቢሆን ተቀብሎ ውጥቶ አንድ ሱባኤ (ሰባት)ቀን ይጹም ይስገድ ሕዝባዊ ቢሆን ግን ሳይቀበል ፈጥኖ ሊወጣ ይገባል።
**ካህኑ ተቀብሎ ይውጣ የተባለ አብነት ስለሆነ ቅዳሴውን ንቆት ወጣ ብለው ምእመናን እንዳይሰናከሉ እንዳይጠራጠሩ ነው። ሕዝባዊ ግን የወጣበትን ምስጢር ስለሚያውቁ ወጥቶ ሲሄድ እገሌ ቢስቅ ቢሳለቅ ቢናገር አስወጥተው ሰደዱት እኛንም እንደሱ አስወጥተው ይሰዱናል ብለው መቀጣጫ ያደርጉታልና ስለዚህ ነው።
#ይህ ሥርዓተ ቅዳሴና ሚስጥራዊ ማብራሪያው የተሰኘው ግሩም መጽሐፍ በመደብራችን በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
እመቤቴ ሆይ
“መብረቅ ሲጮህ ሰው ሁሉ እንደሚደነግጥ የአንቺን ስም ሲሰማ ዲያቢሎስ ይደነግጣል
አንቺ ከተወለድሽ ጀምሮ እረፍት አላገኘምና ነው፤ በአንቺ ታመመ፤ በልጅሽ መስቀል ተሰቃየ፤ ስለሆነም ከፍጥረት ሁሉ አንቺን ይጠላል”
ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
https://t.me/GhionBookStore1623
📖#ኃጢኣቷን_የቀበረችው_ማርያም📖
.....ማርያም ኀጥእት ማናት?
በማቴዎስ ወንጌል ስለ ጌታችን ሽቱ መቀባት የተመዘገበውን የታሪክ ክፍል መነሻ በማድረግ በጊዜ ቅደም ተከተል ሽቱ የተቀባበትን መቼት አብራርቶ የነገረን ቅዱስ ቄርሎስ፡ ማርያም ኀጥእት፡ ኹለተኛ ሽቱ የቀባችበትን ዕለት ሐሙስ ጌታችን ረቡዕ ምሽት ስለተቀባ፡ዕለቱን ሐሙስ ብሎታል] ከማለቱ በቀር በዮሐንስ ወንጌል የግእዝና አማርኛ ትርጓሜ ላይ......
#ከውስጥ ገጽ የተቆረሰ
#የተወሰነ_ቅጂ_ቀርቷል_እንዳያመልጥዎ...!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
+1
✨#ቅዱስ_ሚካኤል_፭ት_ነገሮችን_የፈጸመበት_እለት_ነው! እነርሱም...
፠፩. በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ ሚካኤል፤
፠፪. ባሕራንን ያዳነበት፤
፠፫. የአስተራኒቆስ ሚስት ቅድስት አፎምያን ያዳነበት፤ በዓለ እረፍቷም በዚሁ እለት ነው፤
፠፬. በግብፅ ሃገር ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ ቅዳሴ ቤቱን ያከበረበት፤
፠፭. ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ነጥቆ ወስዶ ያሳየበት፤
ት.ዳንኤል 12 ¹ በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል፤ ሕዝብም ከሆነ ጀምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ እንደ እርሱ ያለ ያልሆነ የመከራ ዘመን ይሆናል፤ በዚያም ዘመን በመጽሐፉ ተጽፎ የተገኘው ሕዝብህ ሁሉ እያንዳንዱ ይድናል። #እንኳን_አደረሳችሁ !🙏
💧#ዜና-መጽሐፍ
📖#ሄርማ_ኖላዊ📖
➮#በሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ረፋዱ ላይ ሄርማ በተባለ ሰው የተጻፈ ሄርማ ኖላዊ" የተሰኘው መጽሐፍ በየአገራቱ ለንባብ ይዘዋወር ነበር። ይህም መጽሐፍ በአንዳንድ አብያተ ክርስቲያን ዘንድ በጉባኤ ወይም በህዝብ አገልግሎት ጊዜ የሚነበብ እና ልክ የሐዲስ ኪዳን የቀኖና መጻሕፍትን ያህል ተቀባይነት ነበረው።
✨#በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው ይህ በ#መጋቤ ምስጢር ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ
የቅኔና የመጻሕፍት ትርጓሜ መምህር የተዘጋጀውን "ሄርማ ኖላዊ" እነኾ..!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
📖#በርዮድስ📖
....ተድባበ ማርያም በየጊዜው ስመ ስርጋዌ ተሰጥቷታል። ጥንት ተድባበ ጽዮን፣ ኋላ ተድባበ ማርያም፣ አሁን ደግሞ “ርእሰ አድባራት ወገዳማት ተድባበ ማርያም” ትባላለች፡፡ ቀዳሚው ቤተ ክርስቲያን በአርብሃ ወአጽብሃ ተመሠረተ። ተድባበ ማርያምም ከዐራቱ መናብርተ ጽዮን አንዷ ናት፡፡
“ተድባበ ማርያም በሥዕሎቿ ጭምር ርእሰ አድባራት ወገዳማት ናት፡፡ ሥዕሎቿ በመጋረጃ የተጋረዱ ሲሆኑ ከስቅለት እስከ ዕርገት መጋረጃው ይጠቀለላል። ሥዕሎቿ ይገለጣሉ፡፡ ከስቅለት እስከ ዕርገት የመጣ ሰው በሥዕሎቿ አይቶ የሥዕል ጥበብ ተምሮ ይመለሳል። ሥዕሎቿ የተሣሉት በኢትዮጵያ የዕፀዋት ቀለም ነው። ቀለማቱ ከዓመት ዓመት እየቦኩ ሥዕሎቿ እየፈኩ እየፈኩ ይሄዳሉ፡፡ የስቅለት ዕለት የመጣ ሰው መጋረጃው ሲገለጥ .......
ከገጽ 278 - 279
#በሐሽማል ስለምታውቋቸው ስለ ሊቁ ማዕበል ፈጠነ መጽሐፍ ምንም ልል ስለማልችል ዝም በሉና ገዝታችኹ አንብቡት !
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
✨✨✨#በድጋሚ_ለአራተኛ_ጊዜ_ታተመ 💦ጠፍቶ በውድድ ሲሸጥ የነበረው በጉጉት ስንጠብቀው የከረምነው..........
📖📖📖📖#መሠረታዊ_የመጽሐፍ_ቅዱስ_አጠናን_ዘዴ ➮#በመምህር_ቸርነት
..✍️የመጽሐፉ ግብ፡- እያንዳንዱ መጽሐፍ ከባለቤቱ ከመንፈስ ቅዱስና ከጸሐፊዎቹ ቅዱሳን ማንነት ጋር እያስማሙ፣ ብሉዩን ከብሉይ፣ ብሉዩን ከሐዲስ፣ ሐዱሱን ከሐዲስ ኪዳኑ እያገናዘቡ ሙሉ ሥዕሉን በመያዝና ዐውዱን መረዳት ያስፈልጋል። በእውነት ቤተ ክርስቲያናችን ብሉይን ከሐዲስ እያቀናጁ፤ እያመሳጠሩ፣ እያታረኩ፣ እያዋደዱ ወዘተ ማስተማርና መጻፍ የሚችሉ አያሌ ሊቃውንት አሏት፡፡ እኔም ይኽችን መጽሐፍ ለዚህ ትውልድ ስጽፍ ሊቃውንቱ ከጥልቅ ዕውቀታቸው በማፍለቅ በተባ ብዕራቸው እንጻፉት ኹሉ ሌሎችን ለማነሣሣትና የመንደርደሪያ ሐሳብ እንዲሆን እንዲሁም በነጻ ላስተማረችኝ ቤተ ክርስቲያን ውለታዋን መክፈል ባልችልም በዘርፉ ካለው ክፍተት አንጻር የድርሻዬን በመወጣት መጠነኛ አስተዋጽዖ ለማበርከት ነው፡፡
#መጽሐፉ_ሰባት_ምዕራፎች_አሉት᎓᎓ ➮የመጀመሪያው ምዕራፍ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናትን ምንነት ይገልጻል፤ ➮ኹለተኛው ምዕራፍ ስለመጽሐፍ ቅዱስ ትውፊት ያስረዳል፤ ➮ምዕራፍ ሦስት ስለ ቀኖና ቅዱሳት መጻሕፍት፣
➮ምዕራፍ አራት #የ81 ቅዱሳት መጻሕፍት ዋና እና ዝርዝር መረጃዎች በስፋት ያስገነዝባል፣ ➮ምዕራፍ አምስት ስለ መጽሐፍ ቅዱስና አዋልድ መጻሕፍት ግንኙነት፣ ➮ምዕራፍ ስድስት የቅዱሳት መጻሕፍት አተረጓጎምና አረዳድ ዘዴ፣ ➮ምዕራፍ ሰባት የመጽሐፍ ቅዱስ አጠቃላይ አጠናን ስልት ምን መምሰል እንዳለበት ያስረዳል። #ለዚህ የአራተኛ እትም አስተያየቶቻችሁን ተቀብዬ መጠነኛ ለውጦች ለማድረግ ሞክሬአለሁ። ብለውናል #አዘጋጁ.......!
📚#ግዮን_መጻሕፍት
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
📖#ጸያሔ_ፍኖት📖
[መንገድ ጠራጊ]
....✍️#የብሉያትና_የሐዲሳት_ሊቅ_የሆኑት_አባታችን_አባ_ገብረ_ኪዳን ለጌታችን ቆርጠው ሊመሰክሩ መሻታቸውን እንደ አባቶቻችን ሰለዮሐንስ በመመስከር አሐዱ ብለው የጀመሩ ይመስላል። በርግጥም ዮሐንስን የተከተሉ ከጌታ ሳይደርሱየቀሩ የሉም!
➮ይህ መጽሐፍም፡- ቤተ ከርስቲያን ስለዮሐንስ የያዘችውን እውነት ግልጽ አድርጎ ያወጣ አዘጋጁን አባታችንም የእውነት ምስክር የሚያሰኝ ነው፡፡ #እንዲያውም_ቅዱስ_ያሬድ_ስለቅዱስ_ዮሐንስ
ውንቱ አንነ ኣብል በእንተ ዮሐንስ እና ከርስ አው እግዚኡ አእመረ፣ በዕለት ጥፉ ኢኀደረት ነፍሱ ዲበ ምድርእንዳለው ስለዚህ መጽሐፍ ጠቀሜታ እኔም ብዙ ላለመናገር ብመርጥ መልካም ሳይሆን አይቀርም፡፡ በርግጥ መጽሐፉ አባታችንም የቅዱስ ያሬድ ልጅ መሆናቸውን የሚመሰከር ንዜኑ ንዜኑ የሚያስብል መጽሐፍ መሆኑን ላለመመስከር ልላቀቅ አልችልም። #ጌታን የሚያገኝ ዮሐንስ ቀድሞ ያስፈልገዋልና : አባታችንም ቀድመው ዮሐንስን ይዘው ስለመጡ የጌታን ነገር ሊያስከትሉ ነው ብዬ እንድገምት ማድረጉንም ልደብቅ አልችልም፡፡ እንግዲያውስ አንደ አነርሱ: አመጣጥ ከስድስት ወር ልዩነት ሳያስበልጡ ቶሎ ይዘውልን ይምጡ አያልኩ መማጸኔን ማሳወቅ ክፉ አልመሰለኝም፡፡ #ዲያቆን_ብርሃኑ_አድማስ 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
ሳይንስ እና ሃይማኖት
..✍ሳይንስ የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን አዕምሮ ተጠቅሞ ያስገኘውና በዚህ ዓለም ያለውን የኑሮ ድካም ማቅለያው የዕውቀት ዘርፍ ሲሆን ሃይማኖት ደግሞ ከአምላኩ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኘው መንገድ ነው። ነገር ግን የሳይንስን ውሱንነት ያልተረዱ ሰዎች ሃይማኖትን በሳይንሳዊ ዕውቀት ለመተንተን ሲሞክሩና ወደ ተሳሳተ ግንዛቤ ሲያመሩ ይስተዋላል። በሌላ መልኩ ደግሞ ሳይንስ ለመንፈሳዊ ሰዎች እርባና የሌለው ነው ብለው የሚያምኑም አሉ።
ይህንን በተመለከተ ለሚነሱ ጥያቄዎችና ፍልስፍናዊ አስተያየቶች፣ ጸሐፊው መምህር ያረጋል አበጋዝ፣ በዚህ መጽሐፉ ከሳይንስና ከሃይማኖት ጋር በተገናኙ ፍልስፍናዊ አስተሳሰቦች ዙሪያ ሰፊ ጥናት በማድረግ ከጥልቅ ትንታኔ ጋር አቅርቦልናል። ስለሆነም መጽሐፉን አንብበን የተሻለ ግንዛቤ እንድናገኝና እንድንጠቀምበት እየጠየቅኩ፣ ለመምህር ያረጋል ዕድሜና ጤናን ለእናንተ ለአንባብያን ደግሞ መልካም ንባብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
ቀሲስ ሰሙ ምትኩ (ፕሮፌሰር)
ቦትስዋና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንተርናሽናል ዩኒቨርሲቲ
ይህ መንፈሳዊ እና ሳይንሳዊ እሳቤዎችን የተነተነ በግሩማን ሐሳቦች የታጨቀው [የተሞላው] በመምህረ ቤተክርስትያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የቀረበ ጥዑም ማዕድ[መጽሐፍ ] ለ ሁለተኛ ጊዜ ታተሞ እያለቀ ስለሆ ውስን ቅጅዎች ስላሉን ይጎብኙን በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍትን ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኛሉ።
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
#ውድ_አንባብያን ! ከቤተክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆቿ መካከል አንዱና ዋነኛ ከኾኑት #ከመምህር_ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ ዘመን ተሻጋሪ ፤ አንጀት አርስ ስራዎች ጥቂት እንጠቁምዎ ፦
፩፡#መድሎተ_ጽድቅ_፩_፪_እና_፫ ፦ ስለ መጽሐፉ መናገር አይቻልም።ለእኛ የእምነት ሚዛን ብቻ ሳይኾን መሠረት ጭምር ነው። ለመናፍቃን ደግሞ እንደ ሰም እያቀለጠ እንደ መዶሻ እየቀጠቀጠ መድረሻ የሚያሳጣ ረቂቅ ና ግሩም መጽሐፍ...
፪#የቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_ሕይወቱና_ትምህርቱ ፦
ስለ ቅዱሱ ሕይወት ከውልደቱ በመጀመር በትምህርቱ እያሳለጠ እስከ ሕይወቱ ፍጻሜ ፍንትው አድርጎ በሚያስደምም ኹኔታ የሚገልጽ...
፫#የቅዱስ_አትናቴዎስ_ሐዋርያሕይወቱና_ትምህርቱ ፦
ስለቅዱሱ ማወቅ በራሱ መታደል ነው ለዚህም ከዚህ የተሻለ መጽሐፍ አይገኝም ብንል ማጋነን አይኾንም....
፬፡#ኦሪት_ዘፍጥረት ፦ ታላቁን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የመጀመሪያዎቹን አስር ምዕራፎች አንድ በአንድ እያብራራ የሚያስረዳ ሲኾን ክፍል ኹለት ይቀጥላል ተብለናል...
፭ ፡#ሳይንስ_እና_ሃይማኖት ፦ ለዚህ ማለትም ሳይንስና ሃይማኖት ተምታቶበት እየዋተተ ላለው ትውልድ አይነተኛ መፍትሔ ይህ መጽሐፍ እንደኾነ ጥርጥር የለውም....
፮#ከበረሐውያን_ሕይወት_እና_አንደበት፦ከቅዱሳኑ ሕይወት በማጣቀስ ሕይወት የሚዘሩ የቅዱሳኑን ቢሂል የያዘ ብሎም የነርሱን አሰረ ፍኖት ተከትለን ወደ ቅድስናው ማማ ከፍ እንድንል የሚረዳ ነው....
❝#ውድ አፍቃርያነ ንባብ ታድያ መጻሕፍቱ እጅግ አስፈላጊ እንደመኾናቸው #በግዮን_መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ አዘጋጅተናል ።
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
http://t.me/GhionBookStore1623
#ውድ_አንባብያን ! ከቤተክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆቿ መካከል አንዱና ዋነኛ ከኾኑት #ከመምህር_ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ ዘመን ተሻጋሪ ፤ አንጀት አርስ ስራዎች ጥቂት እንጠቁምዎ ፦
፩፡#መድሎተ_ጽድቅ_፩_፪_እና_፫ ፦ ስለ መጽሐፉ መናገር አይቻልም።ለእኛ የእምነት ሚዛን ብቻ ሳይኾን መሠረት ጭምር ነው። ለመናፍቃን ደግሞ እንደ ሰም እያቀለጠ እንደ መዶሻ እየቀጠቀጠ መድረሻ የሚያሳጣ ረቂቅ ና ግሩም መጽሐፍ...
፪#የቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_ሕይወቱና_ትምህርቱ ፦
ስለ ቅዱሱ ሕይወት ከውልደቱ በመጀመር በትምህርቱ እያሳለጠ እስከ ሕይወቱ ፍጻሜ ፍንትው አድርጎ በሚያስደምም ኹኔታ የሚገልጽ...
፫#የቅዱስ_አትናቴዎስ_ሐዋርያሕይወቱና_ትምህርቱ ፦
ስለቅዱሱ ማወቅ በራሱ መታደል ነው ለዚህም ከዚህ የተሻለ መጽሐፍ አይገኝም ብንል ማጋነን አይኾንም....
፬፡#ኦሪት_ዘፍጥረት ፦ ታላቁን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የመጀመሪያዎቹን አስር ምዕራፎች አንድ በአንድ እያብራራ የሚያስረዳ ሲኾን ክፍል ኹለት ይቀጥላል ተብለናል...
፭ ፡#ሳይንስ_እና_ሃይማኖት ፦ ለዚህ ማለትም ሳይንስና ሃይማኖት ተምታቶበት እየዋተተ ላለው ትውልድ አይነተኛ መፍትሔ ይህ መጽሐፍ እንደኾነ ጥርጥር የለውም....
፮#ከበረሐውያን_ሕይወት_እና_አንደበት፦ከቅዱሳኑ ሕይወት በማጣቀስ ሕይወት የሚዘሩ የቅዱሳኑን ቢሂል የያዘ ብሎም የነርሱን አሰረ ፍኖት ተከትለን ወደ ቅድስናው ማማ ከፍ እንድንል የሚረዳ ነው....
❝#ውድ አፍቃርያነ ንባብ ታድያ መጻሕፍቱ እጅግ አስፈላጊ እንደመኾናቸው #በግዮን_መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ አዘጋጅተናል ።
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
📱ይደውሉልን ፦0913083816
http://t.me/GhionBookStore1623
"እራስህን የተበሳጨህ ሆነህ ካገኘኸው ነርቮችህን ተቆጣጠር ፣ ምላስህን ተቆጣጠር፣የፊትህን ስሜት ተቆጣጠር እና እንቅስቃሴህን ተቆጣጠር እና ምንም ያህል ቢበድሉህም ሌላውን ለመበደል አትፍቀድ"
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
https://t.me/GhionBookStore1623
#ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘስዋስው_ምዕራግና_ድርሳን
"ዮሐንስ ዘሰዋስው በምሥራቁ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ እንዲያውም በገዳማዊ ሕይወት ውስጥ ከወንጌል ቀጥሎ ተጠቃሹና ተሰሚነት ያለው መጽሐፍ ይህ መጽሐፍ መሆኑ በስፋት የተነገረለት ነው፡፡ እስከ ዛሬ ወደ እኛ ባለመምጣቱ የቀረብንን ይኸው ዛሬ መጽሐፉ ተተርጉሞ በመቅረቡ አንድ ጉድለት ተሸፍኗል፡፡ መጽሐፉ የክርስትና ሕይወትን ምንነት በአግባቡ ለመረዳትና ለመኖር በሚሹ ዘንድ ሁሉ የሚፈለግና የሚጠቅም መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ይህ እንዳለ ሆኖ በተለይ ደግሞ እግዚአብሔር አምላካቸውን በገዳማዊ ሕይወት ለሚያገለግሉ ጠቀሜታው እጅግ የጎላ ነው፡፡"
ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
#📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
