uz
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

Kanalga Telegram’da o‘tish

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

Ko'proq ko'rsatish
3 285
Obunachilar
-324 soatlar
-197 kunlar
-4130 kunlar
Postlar arxiv
📖ሥርዓተ ቅዳሴና ሚስጥራዊ ማብራሪያው📖 ......#በቅዳሴ ጊዜ የሚስቅ የሚሳለቅ ቢኖር ካህን ቢሆን ተቀብሎ ውጥቶ አንድ ሱባኤ (ሰባት)ቀን ይጹም ይስገድ ሕዝባዊ ቢሆን ግን ሳይቀበል ፈጥኖ ሊወጣ
📖ሥርዓተ ቅዳሴና ሚስጥራዊ ማብራሪያው📖 ......#በቅዳሴ ጊዜ የሚስቅ የሚሳለቅ ቢኖር ካህን ቢሆን ተቀብሎ ውጥቶ አንድ ሱባኤ (ሰባት)ቀን ይጹም ይስገድ ሕዝባዊ ቢሆን ግን ሳይቀበል ፈጥኖ ሊወጣ ይገባል። **ካህኑ ተቀብሎ ይውጣ የተባለ አብነት ስለሆነ ቅዳሴውን ንቆት ወጣ ብለው ምእመናን እንዳይሰናከሉ እንዳይጠራጠሩ ነው። ሕዝባዊ ግን የወጣበትን ምስጢር ስለሚያውቁ ወጥቶ ሲሄድ እገሌ ቢስቅ ቢሳለቅ ቢናገር አስወጥተው ሰደዱት እኛንም እንደሱ አስወጥተው ይሰዱናል ብለው መቀጣጫ ያደርጉታልና ስለዚህ ነው። #ይህ ሥርዓተ ቅዳሴና ሚስጥራዊ ማብራሪያው የተሰኘው ግሩም መጽሐፍ በመደብራችን በልዩ ቅናሽ ያገኙታል። 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

እመቤቴ ሆይ “መብረቅ ሲጮህ ሰው ሁሉ እንደሚደነግጥ የአንቺን ስም ሲሰማ ዲያቢሎስ ይደነግጣል አንቺ ከተወለድሽ ጀምሮ እረፍት አላገኘምና ነው፤ በአንቺ ታመመ፤ በልጅሽ መስቀል ተሰቃየ፤ ስለሆነም ከፍጥ
እመቤቴ ሆይ “መብረቅ ሲጮህ ሰው ሁሉ እንደሚደነግጥ የአንቺን ስም ሲሰማ ዲያቢሎስ ይደነግጣል አንቺ ከተወለድሽ ጀምሮ እረፍት አላገኘምና ነው፤ በአንቺ ታመመ፤ በልጅሽ መስቀል ተሰቃየ፤ ስለሆነም ከፍጥረት ሁሉ አንቺን ይጠላል”    ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ https://t.me/GhionBookStore1623

📖#ኃጢኣቷን_የቀበረችው_ማርያም📖 .....ማርያም ኀጥእት ማናት? በማቴዎስ ወንጌል ስለ ጌታችን ሽቱ መቀባት የተመዘገበውን የታሪክ ክፍል መነሻ በማድረግ በጊዜ ቅደም ተከተል ሽቱ የተቀባበትን መቼት
📖#ኃጢኣቷን_የቀበረችው_ማርያም📖 .....ማርያም ኀጥእት ማናት? በማቴዎስ ወንጌል ስለ ጌታችን ሽቱ መቀባት የተመዘገበውን የታሪክ ክፍል መነሻ በማድረግ በጊዜ ቅደም ተከተል ሽቱ የተቀባበትን መቼት አብራርቶ የነገረን ቅዱስ ቄርሎስ፡ ማርያም ኀጥእት፡ ኹለተኛ ሽቱ የቀባችበትን ዕለት ሐሙስ ጌታችን ረቡዕ ምሽት ስለተቀባ፡ዕለቱን ሐሙስ ብሎታል] ከማለቱ በቀር በዮሐንስ ወንጌል የግእዝና አማርኛ ትርጓሜ ላይ...... #ከውስጥ ገጽ የተቆረሰ #የተወሰነ_ቅጂ_ቀርቷል_እንዳያመልጥዎ...! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

✨#ቅዱስ_ሚካኤል_፭ት_ነገሮችን_የፈጸመበት_እለት_ነው! እነርሱም... ፠፩. በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ ሚካኤል፤ ፠፪. ባሕራንን ያዳነበት፤ ፠፫. የአስተራኒቆስ ሚስት ቅድስት አፎምያን ያዳነበት፤ በዓለ እረ
+1
#ቅዱስ_ሚካኤል_፭ት_ነገሮችን_የፈጸመበት_እለት_ነው!  እነርሱም...    ፠፩. በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ ሚካኤል፤ ፠፪. ባሕራንን ያዳነበት፤ ፠፫. የአስተራኒቆስ ሚስት ቅድስት አፎምያን ያዳነበት፤ በዓለ እረፍቷም በዚሁ እለት ነው፤ ፠፬. በግብፅ ሃገር ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ ቅዳሴ ቤቱን ያከበረበት፤ ፠፭. ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ነጥቆ ወስዶ ያሳየበት፤
ት.ዳንኤል 12 ¹ በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል፤ ሕዝብም ከሆነ ጀምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ እንደ እርሱ ያለ ያልሆነ የመከራ ዘመን ይሆናል፤ በዚያም ዘመን በመጽሐፉ ተጽፎ የተገኘው ሕዝብህ ሁሉ እያንዳንዱ ይድናል።
            #እንኳን_አደረሳችሁ !🙏  

💧#ዜና-መጽሐፍ 📖#ሄርማ_ኖላዊ📖 ➮#በሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ረፋዱ ላይ ሄርማ በተባለ ሰው የተጻፈ ሄርማ ኖላዊ" የተሰኘው መጽሐፍ በየአገራቱ ለንባብ ይዘዋወር ነበር። ይህም መጽሐፍ
💧#ዜና-መጽሐፍ 📖#ሄርማ_ኖላዊ📖 ➮#በሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ረፋዱ ላይ ሄርማ በተባለ ሰው የተጻፈ ሄርማ ኖላዊ" የተሰኘው መጽሐፍ በየአገራቱ ለንባብ ይዘዋወር ነበር። ይህም መጽሐፍ በአንዳንድ አብያተ ክርስቲያን ዘንድ በጉባኤ ወይም በህዝብ አገልግሎት ጊዜ የሚነበብ እና ልክ የሐዲስ ኪዳን የቀኖና መጻሕፍትን ያህል ተቀባይነት ነበረው። ✨#በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው ይህ በ#መጋቤ ምስጢር ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ የቅኔና የመጻሕፍት ትርጓሜ መምህር የተዘጋጀውን "ሄርማ ኖላዊ" እነኾ..! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖#በርዮድስ📖 ....ተድባበ ማርያም በየጊዜው ስመ ስርጋዌ ተሰጥቷታል። ጥንት ተድባበ ጽዮን፣ ኋላ ተድባበ ማርያም፣ አሁን ደግሞ “ርእሰ አድባራት ወገዳማት ተድባበ ማርያም” ትባላለች፡፡ ቀዳሚው ቤ
📖#በርዮድስ📖 ....ተድባበ ማርያም በየጊዜው ስመ ስርጋዌ ተሰጥቷታል። ጥንት ተድባበ ጽዮን፣ ኋላ ተድባበ ማርያም፣ አሁን ደግሞ “ርእሰ አድባራት ወገዳማት ተድባበ ማርያም” ትባላለች፡፡ ቀዳሚው ቤተ ክርስቲያን በአርብሃ ወአጽብሃ ተመሠረተ። ተድባበ ማርያምም ከዐራቱ መናብርተ ጽዮን አንዷ ናት፡፡ “ተድባበ ማርያም በሥዕሎቿ ጭምር ርእሰ አድባራት ወገዳማት ናት፡፡ ሥዕሎቿ በመጋረጃ የተጋረዱ ሲሆኑ ከስቅለት እስከ ዕርገት መጋረጃው ይጠቀለላል። ሥዕሎቿ ይገለጣሉ፡፡ ከስቅለት እስከ ዕርገት የመጣ ሰው በሥዕሎቿ አይቶ የሥዕል ጥበብ ተምሮ ይመለሳል። ሥዕሎቿ የተሣሉት በኢትዮጵያ የዕፀዋት ቀለም ነው። ቀለማቱ ከዓመት ዓመት እየቦኩ ሥዕሎቿ እየፈኩ እየፈኩ ይሄዳሉ፡፡ የስቅለት ዕለት የመጣ ሰው መጋረጃው ሲገለጥ ....... ከገጽ 278 - 279 #በሐሽማል ስለምታውቋቸው ስለ ሊቁ ማዕበል ፈጠነ መጽሐፍ ምንም ልል ስለማልችል ዝም በሉና ገዝታችኹ አንብቡት ! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

✨✨✨#በድጋሚ_ለአራተኛ_ጊዜ_ታተመ 💦ጠፍቶ በውድድ ሲሸጥ የነበረው በጉጉት ስንጠብቀው የከረምነው.......... 📖📖📖📖#መሠረታዊ_የመጽሐፍ_ቅዱስ_አጠናን_ዘዴ ➮#በመምህር_ቸርነት ..✍️የመጽ
✨✨✨#በድጋሚ_ለአራተኛ_ጊዜ_ታተመ 💦ጠፍቶ በውድድ ሲሸጥ የነበረው በጉጉት ስንጠብቀው የከረምነው.......... 📖📖📖📖#መሠረታዊ_የመጽሐፍ_ቅዱስ_አጠናን_ዘዴ#በመምህር_ቸርነት ..✍️የመጽሐፉ ግብ፡- እያንዳንዱ መጽሐፍ ከባለቤቱ ከመንፈስ ቅዱስና ከጸሐፊዎቹ ቅዱሳን ማንነት ጋር እያስማሙ፣ ብሉዩን ከብሉይ፣ ብሉዩን ከሐዲስ፣ ሐዱሱን ከሐዲስ ኪዳኑ እያገናዘቡ ሙሉ ሥዕሉን በመያዝና ዐውዱን መረዳት ያስፈልጋል። በእውነት ቤተ ክርስቲያናችን ብሉይን ከሐዲስ እያቀናጁ፤ እያመሳጠሩ፣ እያታረኩ፣ እያዋደዱ ወዘተ ማስተማርና መጻፍ የሚችሉ አያሌ ሊቃውንት አሏት፡፡ እኔም ይኽችን መጽሐፍ ለዚህ ትውልድ ስጽፍ ሊቃውንቱ ከጥልቅ ዕውቀታቸው በማፍለቅ በተባ ብዕራቸው እንጻፉት ኹሉ ሌሎችን ለማነሣሣትና የመንደርደሪያ ሐሳብ እንዲሆን እንዲሁም በነጻ ላስተማረችኝ ቤተ ክርስቲያን ውለታዋን መክፈል ባልችልም በዘርፉ ካለው ክፍተት አንጻር የድርሻዬን በመወጣት መጠነኛ አስተዋጽዖ ለማበርከት ነው፡፡ #መጽሐፉ_ሰባት_ምዕራፎች_አሉት᎓᎓ ➮የመጀመሪያው ምዕራፍ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናትን ምንነት ይገልጻል፤ ➮ኹለተኛው ምዕራፍ ስለመጽሐፍ ቅዱስ ትውፊት ያስረዳል፤ ➮ምዕራፍ ሦስት ስለ ቀኖና ቅዱሳት መጻሕፍት፣ ➮ምዕራፍ አራት #የ81 ቅዱሳት መጻሕፍት ዋና እና ዝርዝር መረጃዎች በስፋት ያስገነዝባል፣ ➮ምዕራፍ አምስት ስለ መጽሐፍ ቅዱስና አዋልድ መጻሕፍት ግንኙነት፣ ➮ምዕራፍ ስድስት የቅዱሳት መጻሕፍት አተረጓጎምና አረዳድ ዘዴ፣ ➮ምዕራፍ ሰባት የመጽሐፍ ቅዱስ አጠቃላይ አጠናን ስልት ምን መምሰል እንዳለበት ያስረዳል። #ለዚህ የአራተኛ እትም አስተያየቶቻችሁን ተቀብዬ መጠነኛ ለውጦች ለማድረግ ሞክሬአለሁ። ብለውናል #አዘጋጁ.......! 📚#ግዮን_መጻሕፍት ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖#ጸያሔ_ፍኖት📖 [መንገድ ጠራጊ] ....✍️#የብሉያትና_የሐዲሳት_ሊቅ_የሆኑት_አባታችን_አባ_ገብረ_ኪዳን ለጌታችን ቆርጠው ሊመሰክሩ መሻታቸውን እንደ አባቶቻችን ሰለዮሐንስ በመመስከር አሐዱ ብለው
📖#ጸያሔ_ፍኖት📖 [መንገድ ጠራጊ] ....✍️#የብሉያትና_የሐዲሳት_ሊቅ_የሆኑት_አባታችን_አባ_ገብረ_ኪዳን ለጌታችን ቆርጠው ሊመሰክሩ መሻታቸውን እንደ አባቶቻችን ሰለዮሐንስ በመመስከር አሐዱ ብለው የጀመሩ ይመስላል። በርግጥም ዮሐንስን የተከተሉ ከጌታ ሳይደርሱየቀሩ የሉም!  ➮ይህ መጽሐፍም፡- ቤተ ከርስቲያን ስለዮሐንስ የያዘችውን እውነት ግልጽ አድርጎ ያወጣ አዘጋጁን አባታችንም የእውነት ምስክር የሚያሰኝ ነው፡፡ #እንዲያውም_ቅዱስ_ያሬድ_ስለቅዱስ_ዮሐንስ
ውንቱ አንነ ኣብል በእንተ ዮሐንስ እና ከርስ አው እግዚኡ አእመረ፣ በዕለት ጥፉ ኢኀደረት ነፍሱ ዲበ ምድር
እንዳለው ስለዚህ መጽሐፍ ጠቀሜታ እኔም ብዙ ላለመናገር ብመርጥ መልካም ሳይሆን አይቀርም፡፡ በርግጥ መጽሐፉ አባታችንም የቅዱስ ያሬድ ልጅ መሆናቸውን የሚመሰከር ንዜኑ ንዜኑ የሚያስብል መጽሐፍ መሆኑን ላለመመስከር ልላቀቅ አልችልም። #ጌታን የሚያገኝ ዮሐንስ ቀድሞ ያስፈልገዋልና : አባታችንም ቀድመው ዮሐንስን ይዘው ስለመጡ የጌታን ነገር ሊያስከትሉ ነው ብዬ እንድገምት ማድረጉንም ልደብቅ አልችልም፡፡ እንግዲያውስ አንደ አነርሱ: አመጣጥ ከስድስት ወር ልዩነት ሳያስበልጡ ቶሎ ይዘውልን ይምጡ አያልኩ መማጸኔን ማሳወቅ ክፉ አልመሰለኝም፡፡ #ዲያቆን_ብርሃኑ_አድማስ 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

ሳይንስ እና ሃይማኖት ..✍ሳይንስ የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን አዕምሮ ተጠቅሞ ያስገኘውና በዚህ ዓለም ያለውን የኑሮ ድካም ማቅለያው የዕውቀት ዘርፍ ሲሆን ሃይማኖት ደግሞ ከአምላኩ ከእግዚአብ
ሳይንስ እና ሃይማኖት ..✍ሳይንስ የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን አዕምሮ ተጠቅሞ ያስገኘውና በዚህ ዓለም ያለውን የኑሮ ድካም ማቅለያው የዕውቀት ዘርፍ ሲሆን ሃይማኖት ደግሞ ከአምላኩ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኘው መንገድ ነው። ነገር ግን የሳይንስን ውሱንነት ያልተረዱ ሰዎች ሃይማኖትን በሳይንሳዊ ዕውቀት ለመተንተን ሲሞክሩና ወደ ተሳሳተ ግንዛቤ ሲያመሩ ይስተዋላል። በሌላ መልኩ ደግሞ ሳይንስ ለመንፈሳዊ ሰዎች እርባና የሌለው ነው ብለው የሚያምኑም አሉ። ይህንን በተመለከተ ለሚነሱ ጥያቄዎችና ፍልስፍናዊ አስተያየቶች፣ ጸሐፊው መምህር ያረጋል አበጋዝ፣ በዚህ መጽሐፉ ከሳይንስና ከሃይማኖት ጋር በተገናኙ ፍልስፍናዊ አስተሳሰቦች ዙሪያ ሰፊ ጥናት በማድረግ ከጥልቅ ትንታኔ ጋር አቅርቦልናል። ስለሆነም መጽሐፉን አንብበን የተሻለ ግንዛቤ እንድናገኝና እንድንጠቀምበት እየጠየቅኩ፣ ለመምህር ያረጋል ዕድሜና ጤናን ለእናንተ ለአንባብያን ደግሞ መልካም ንባብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ። ቀሲስ ሰሙ ምትኩ (ፕሮፌሰር) ቦትስዋና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንተርናሽናል ዩኒቨርሲቲ   ይህ መንፈሳዊ እና ሳይንሳዊ እሳቤዎችን የተነተነ በግሩማን ሐሳቦች የታጨቀው [የተሞላው]  በመምህረ ቤተክርስትያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የቀረበ ጥዑም ማዕድ[መጽሐፍ ]  ለ ሁለተኛ ጊዜ ታተሞ እያለቀ ስለሆ ውስን ቅጅዎች ስላሉን ይጎብኙን በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍትን ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኛሉ። 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816    https://t.me/GhionBookStore1623

#ውድ_አንባብያን ! ከቤተክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆቿ መካከል አንዱና ዋነኛ ከኾኑት #ከመምህር_ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ ዘመን ተሻጋሪ ፤ አንጀት አርስ ስራዎች ጥቂት እንጠቁምዎ ፦ ፩፡#መድሎተ_ጽድቅ
#ውድ_አንባብያን ! ከቤተክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆቿ መካከል አንዱና ዋነኛ ከኾኑት #ከመምህር_ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ ዘመን ተሻጋሪ ፤ አንጀት አርስ ስራዎች ጥቂት እንጠቁምዎ ፦ ፩፡#መድሎተ_ጽድቅ_፩_፪_እና_፫ ፦ ስለ መጽሐፉ መናገር አይቻልም።ለእኛ የእምነት ሚዛን ብቻ ሳይኾን መሠረት ጭምር ነው። ለመናፍቃን ደግሞ እንደ ሰም እያቀለጠ እንደ መዶሻ እየቀጠቀጠ መድረሻ የሚያሳጣ ረቂቅ ና ግሩም መጽሐፍ... #የቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_ሕይወቱና_ትምህርቱ ስለ ቅዱሱ ሕይወት ከውልደቱ በመጀመር በትምህርቱ እያሳለጠ እስከ ሕይወቱ ፍጻሜ ፍንትው አድርጎ በሚያስደምም ኹኔታ የሚገልጽ... #የቅዱስ_አትናቴዎስ_ሐዋርያሕይወቱና_ትምህርቱ ስለቅዱሱ ማወቅ በራሱ መታደል ነው ለዚህም ከዚህ የተሻለ መጽሐፍ አይገኝም ብንል ማጋነን አይኾንም.... ፬፡#ኦሪት_ዘፍጥረት ታላቁን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የመጀመሪያዎቹን አስር ምዕራፎች አንድ በአንድ እያብራራ የሚያስረዳ ሲኾን ክፍል ኹለት ይቀጥላል ተብለናል... ፭ ፡#ሳይንስ_እና_ሃይማኖት ለዚህ ማለትም ሳይንስና ሃይማኖት ተምታቶበት እየዋተተ ላለው ትውልድ አይነተኛ መፍትሔ ይህ መጽሐፍ እንደኾነ ጥርጥር የለውም.... #ከበረሐውያን_ሕይወት_እና_አንደበት፦ከቅዱሳኑ ሕይወት በማጣቀስ ሕይወት የሚዘሩ የቅዱሳኑን ቢሂል የያዘ ብሎም የነርሱን አሰረ ፍኖት ተከትለን ወደ ቅድስናው ማማ ከፍ እንድንል የሚረዳ ነው.... #ውድ አፍቃርያነ ንባብ ታድያ መጻሕፍቱ እጅግ አስፈላጊ እንደመኾናቸው #በግዮን_መጻሕፍት  ዘወትር በልዩ ቅናሽ አዘጋጅተናል ። 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። 📱ይደውሉልን ፦0913083816 http://t.me/GhionBookStore1623

#ውድ_አንባብያን ! ከቤተክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆቿ መካከል አንዱና ዋነኛ ከኾኑት #ከመምህር_ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ ዘመን ተሻጋሪ ፤ አንጀት አርስ ስራዎች ጥቂት እንጠቁምዎ ፦ ፩፡#መድሎተ_ጽድቅ
#ውድ_አንባብያን ! ከቤተክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆቿ መካከል አንዱና ዋነኛ ከኾኑት #ከመምህር_ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ ዘመን ተሻጋሪ ፤ አንጀት አርስ ስራዎች ጥቂት እንጠቁምዎ ፦ ፩፡#መድሎተ_ጽድቅ_፩_፪_እና_፫ ፦ ስለ መጽሐፉ መናገር አይቻልም።ለእኛ የእምነት ሚዛን ብቻ ሳይኾን መሠረት ጭምር ነው። ለመናፍቃን ደግሞ እንደ ሰም እያቀለጠ እንደ መዶሻ እየቀጠቀጠ መድረሻ የሚያሳጣ ረቂቅ ና ግሩም መጽሐፍ... #የቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_ሕይወቱና_ትምህርቱ ስለ ቅዱሱ ሕይወት ከውልደቱ በመጀመር በትምህርቱ እያሳለጠ እስከ ሕይወቱ ፍጻሜ ፍንትው አድርጎ በሚያስደምም ኹኔታ የሚገልጽ... #የቅዱስ_አትናቴዎስ_ሐዋርያሕይወቱና_ትምህርቱ ስለቅዱሱ ማወቅ በራሱ መታደል ነው ለዚህም ከዚህ የተሻለ መጽሐፍ አይገኝም ብንል ማጋነን አይኾንም.... ፬፡#ኦሪት_ዘፍጥረት ታላቁን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የመጀመሪያዎቹን አስር ምዕራፎች አንድ በአንድ እያብራራ የሚያስረዳ ሲኾን ክፍል ኹለት ይቀጥላል ተብለናል... ፭ ፡#ሳይንስ_እና_ሃይማኖት ለዚህ ማለትም ሳይንስና ሃይማኖት ተምታቶበት እየዋተተ ላለው ትውልድ አይነተኛ መፍትሔ ይህ መጽሐፍ እንደኾነ ጥርጥር የለውም.... #ከበረሐውያን_ሕይወት_እና_አንደበት፦ከቅዱሳኑ ሕይወት በማጣቀስ ሕይወት የሚዘሩ የቅዱሳኑን ቢሂል የያዘ ብሎም የነርሱን አሰረ ፍኖት ተከትለን ወደ ቅድስናው ማማ ከፍ እንድንል የሚረዳ ነው.... #ውድ አፍቃርያነ ንባብ ታድያ መጻሕፍቱ እጅግ አስፈላጊ እንደመኾናቸው #በግዮን_መጻሕፍት  ዘወትር በልዩ ቅናሽ አዘጋጅተናል ። 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። 📱ይደውሉልን ፦0913083816 http://t.me/GhionBookStore1623

"እራስህን የተበሳጨህ ሆነህ ካገኘኸው ነርቮችህን ተቆጣጠር ፣ ምላስህን ተቆጣጠር፣የፊትህን ስሜት ተቆጣጠር እና እንቅስቃሴህን ተቆጣጠር እና ምንም ያህል ቢበድሉህም ሌላውን ለመበደል አትፍቀድ" አቡነ
"እራስህን የተበሳጨህ ሆነህ ካገኘኸው ነርቮችህን ተቆጣጠር ፣ ምላስህን ተቆጣጠር፣የፊትህን ስሜት ተቆጣጠር እና እንቅስቃሴህን ተቆጣጠር እና ምንም ያህል ቢበድሉህም ሌላውን ለመበደል አትፍቀድ" አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ     ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥ https://t.me/GhionBookStore1623

#ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘስዋስው_ምዕራግና_ድርሳን "ዮሐንስ ዘሰዋስው በምሥራቁ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ እንዲያውም በገዳማዊ ሕይወት ውስጥ ከወንጌል
#ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘስዋስው_ምዕራግና_ድርሳን "ዮሐንስ ዘሰዋስው በምሥራቁ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ እንዲያውም በገዳማዊ ሕይወት ውስጥ ከወንጌል ቀጥሎ ተጠቃሹና ተሰሚነት ያለው መጽሐፍ ይህ መጽሐፍ መሆኑ በስፋት የተነገረለት ነው፡፡ እስከ ዛሬ ወደ እኛ ባለመምጣቱ የቀረብንን ይኸው ዛሬ መጽሐፉ ተተርጉሞ በመቅረቡ አንድ ጉድለት ተሸፍኗል፡፡ መጽሐፉ የክርስትና ሕይወትን ምንነት በአግባቡ ለመረዳትና ለመኖር በሚሹ ዘንድ ሁሉ የሚፈለግና የሚጠቅም መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ይህ እንዳለ ሆኖ በተለይ ደግሞ እግዚአብሔር አምላካቸውን በገዳማዊ ሕይወት ለሚያገለግሉ ጠቀሜታው እጅግ የጎላ ነው፡፡"             ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ #📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

ሸሽተህ አምልጥ «ወደ ሜዳም ካወጡአቸው በኋላ እንዲህ አለው ራስህን አድን ወደ ኋላህ አትይ በዚህም ዙሪያ ሁሉ ኣትቁም እንዳትጠፋ ወደ ተራራው ሸሽተህ አመልጥ» /ዘፍ.19፥17/ አንዳንድ ሰዎች ባለማ
ሸሽተህ አምልጥ «ወደ ሜዳም ካወጡአቸው በኋላ እንዲህ አለው ራስህን አድን ወደ ኋላህ አትይ በዚህም ዙሪያ ሁሉ ኣትቁም እንዳትጠፋ ወደ ተራራው ሸሽተህ አመልጥ» /ዘፍ.19፥17/ አንዳንድ ሰዎች ባለማወቅ ብቻ ሳይሆን ውጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል እያወቁ እንኳ ጉዳት ከሚያስከትልባቸው ነገር ሽሽቶ ማምለጥ ያቅታቸዋል፡፡ ሽሽት ራስን የማዳኛ መንገድ ነው:: አንድ ክርስቲያን በሕይወቱ ኃጢአትን በሁለት መንገድ ሊያሽንፍ ይችላል። ይህም ሊከናወን የሚችለው ከኃጢአቱ ባሕርይ ኣኳያ ተነሥተን እንጂ እንዲያው በደፈናው አይደለም:: ምክንያቱም በትግል የምናሽነፈው ኃጢኣት እንዳለ ሁሉ በሽሽትም የምና ሽንፈው ኃጢአት አለ:: በሽሽት ማመለጥ ያለብን ኃጢአት ራሴን አውቃለሁ አልሽነፍም በሚል ትምክህት ለምታገል መሞከር ያለብን ኃጢአት ራሴን አውቃለሁ ውጤቱ አደገኛ ሊሆን ይችላል ።ለምሳሌ በአንድ ትልቅ ፓርቲ ላይ ተገኝቶ ብዙዎች እየበሉና እየጠጡ ተነሥተውም እየጨፈሩና እየደነሱ ባሉበት ሁኔታ ይህን ከመሸሽ ይልቅ በመካከላቸው በታዛቢነት ተቀምጬ አያቸዋለሁ እንጂ ምንም አልሆንም በአይኔ የማየው ዳንሳቸው በጆሮዬ የምሰማው ዘፈናቸው በዙሪያዬ የሚከናወነው ትርምሳቸው ሁሉ ለእኔ የሚታየኝ እንደ ምንም ነው ማለቱ ከከንቱ ትምክህት የሚመነጭ ነው ከዚህ ይልቅ ውጤታማ የሚያደርግ በዚያ ዙሪያ ሁሉ አለመቆሙ የሕሊናና የመንፈስ መሰረቅ እንዳያጋጥመን ሸሽቶ ማምለጡ አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው፡፡ ለቅዱስ ቁርባን እንድንበቃ ምን ላድርግ ገጽ 84 #📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

የመዳን ትምህርት በዘመናት ሂደት ውስጥ - አጭር ዳሰሳ * የነገረ ድኅነት ትምህርት በምዕራቡ አለም * ስኮላስቲሲዝም (scholasticism) * የትሬንት ጉባኤ * የፕሮቴስታንቶች አጸፌታ * ኦርቶዶክሳዊ የመዳን ትምህርት ++++++++ ~ +++++++ መዳን ከኃጢአት ይቅርታ ባሻገር ብዙ ነገሮችን የያዘ ሰፊና ጥልቅ ነገር ነው፡፡ ስለዚህም አንደኛውንና የመጀመሪያውን ሥጦታ (የኃጢአትን ይቅርታ ማግኘትን) ብቻ ሌላውን እስከሚያስረሳ ድረስ ማጉላትና ከዚያ ያለፈ ነገር የሌለ ማስመሰል እግዚአብሔር የሰጠውን ጸጋ ማሳነስና የተጠራንበትን ከፍ ያለውን የእግዚአብሔርን ጥሪ ማስረሳት ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱሳዊውና በአበው ቀደምት አስተምህሮ መሠረት መዳን ስንል ሥርየተ ኃጢአት ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔርን ማወቅን፣ ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት ማግኘትን፣ ብርሃናዊነትን ገንዘብ ማድረግን፣ ከባርነት ነጻ መውጣትን፣ አዲስ ተፈጥሮንና የጸጋ አምላክነትን ገንዘብ ማድረግን ሁሉ የሚጨምር ሰፊና ጥልቅ ነው:: ++++++++ ~ ++++++++ ኦርቶዶክሳውያን አባቶቻችን የጸጋው ሥጦታ ነጻ (እንዲሁ) የሚሰጥ መሆኑን በአንድ በኩል፣ የሰውን ነጻ ፈቃድ (ነጻነት) ደግሞ በሌላ በኩል አስተባብረው በመያዝ ለሰው መዳን የሁለቱ መስተጋብር (በግሪኩ Synergy) አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት ያስተምራሉ፡፡ ይህም በቅዱስ ጳውሎስ “ከእርሱ ጋር አብረን የምንሠራ ነንና” ተብሎ የተገለጸው ነው፡፡ 1 ቆሮ. 3:9 #መድሎተ_ጽድቅ #ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ

📖#ገድለ_ቅዱስ _ፊቅጦር📖 ✍️ #እርሱ ባለቤቱ የሠራዊት ጌታ አምካችን እግዚአብሔር በዐወቀ ለወዳጆቹ ቅዱሳን የሰጣቸው ሌላም ትንቢታዊ ዕሤተ ጸጋ አለ ። እውነት ነው :: የእርሱ ቸርነታዊ ጸጋ እ
📖#ገድለ_ቅዱስ _ፊቅጦር📖 ✍️ #እርሱ ባለቤቱ የሠራዊት ጌታ አምካችን እግዚአብሔር በዐወቀ ለወዳጆቹ ቅዱሳን የሰጣቸው ሌላም ትንቢታዊ ዕሤተ ጸጋ አለ ። እውነት ነው :: የእርሱ ቸርነታዊ ጸጋ እጅግ ብዙ ነው።
ቅዱስ መጽሐፍም ይኽንኑ ሲያረጋግጥ “ወብክሙ ጸጋ
<"እግዚአብሔር--------ከአምላካችሁ እግዚአብሔር የተሰጣችሁ ልዩ ልዩ ጸጋ አላችሁ...">ይላል ። #ከእነዚኽም ጸጋዎች አንዱ ሀብተ ትንቢት #ለሰማዕቱ_ቅዱስ_ፊቅጦር ተሰጥቶት ከአንፆኪያ እስከ እለእስክንድርያ ምድር ይልቁንም ባርቆን ድረስ በስደት ተግዞ በተቀበለው ፀዋትወ መከራ ውስጥ ሳለ በዚኽ የመጨረሻው ዘመን ስለሚከሠተውና ስለሚኾነው ነገር ስለ #ኢትዮጵያም ኹሉ ግልጥ ትንቢትን ተናግሯል፡፡ ➮ይኽን ትንቢቱንም በዚኹ መጽሐፈገድል ውስጥ እንደምናነበው በዚኽ በአለንበት ዘመን እየታየ ያለውን አስከፊና አስደንጋጭ የጭንቅ ኩነትና በመጨረሻም መልካም ዘመን እንደሚመጣ ደግ ንጉሥ ቴዎድሮስ እንደሚነሣ ይናገራል ፡፡ በተጨማሪም “...በዚያ ዘመን ሰዎች እርስ በእርሳቸው ይጠላላሉ ። አንዱ አንዱን ለሞት አሳልፎ ይሰጠዋል ይገድለዋል ። ሐሰተኞች ነቢያትና ሐሰተኞች መምህራን ይነሣሉ ፡ ብዙ ሰዎችን ያስታሉ.........እያለ በዚህ ገድል ሰፋ አድርጎ የተገለጸለትን ያትተዋል። #ገድላትን በማንበብ ከበረከታቸው ሱቱፋን እንኾን ዘንድ ይገባናል !ታድያ ጽሩይይይ በኾነ መልኩ ተተርጉሞና ተሻሽሎ እንዲኹም ለአይን ምቹ ይኾን ዘንድ ሽሮ ከለር ኾኖ ቀደሞ ከ88 በላይ ገድላት እና ድርሳናትን ከግእዝ ወደ አማርኛ በመተርጎም ያበረከቱልን ሊቁ አኹን ደግሞ የዚህን #ታላቅ_ሰማእት_ማር_ቅዱስ_ፊቅጦር ገድል አበርክተውልናል! 📚ግዮን መጻሕፍት✨ 📖 📱ይደውሉልን ፦0913083816 Telegram https://t.me/GhionBookStore162

📖ኰኲሐ ሃይማኖት 【ወጣት ተመልከት እንዳትሳሳት】 ✍️...በል ደኅና ኹን! አንተ፤ ዕውሩን ዐይናማ ነህ ቢሉት ዐይናማ ላይሆን፣ የተሰበረውንም ደኅና ነህ ቢሉት ደኅና ላይሆን፣ የንብላውን ሕግ እውነተ
📖ኰኲሐ ሃይማኖትወጣት ተመልከት እንዳትሳሳት】 ✍️...በል ደኅና ኹን! አንተ፤ ዕውሩን ዐይናማ ነህ ቢሉት ዐይናማ ላይሆን፣ የተሰበረውንም ደኅና ነህ ቢሉት ደኅና ላይሆን፣ የንብላውን ሕግ እውነተኛ ለማስመሰል በጻፍከው ስሕተት የምእመናንን ልቡና ይሆንን? አይሆንን? ከሚል ጥርጥር ላይ ስለጣልከው እኔም “ይነግረው ያጣ ያሙኝ አይመስለውም” እንደሚባለው ተረት ዝም ብንልህ ጥፋትህ እየቀጠልክ ስለሔድክ ለምእመናን ነገርህ እውነት ይመስላቸዋል በማለት “ገሥጽ ወተዛለፍ” ያለው ቃል እያጽናናኝ (፪ጢሞ. ፬÷፪) መልሱን ስጽፍልህ ያመላለሱ ዘዴ እያስገደደኝ በማደርገው ንግግር አንዳንድ ላይ “ባርክዎሙ ለእለ ይረግሙክሙ” የተባለው ትእዛዝ ሳይፈርስብኝ የቀረ አይመስለኝምና የሰውን መዳኑን እንጂ መጎዳቱን የማይወድ ቸሩ አምላክ ኹላችንንም ይቅር ብሎ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ያገናኝን፡፡ አሜን፡፡ [ከመጽሐፉ የውስጥ ገጾች የተወሰደ] 🫧መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ ሊቅ ረቂቅ የሃይማኖት አርበኛ መኾናቸው ዛሬም በመጻሕፍቶቻቸው፤ ሲወሳ፤ ሲመሰከር ፤ትውልድ ሲሻገር ይኖራል። በእቅበተ እምነት ዙሪያም ይኽ ነው የማይባል አሻራ አኑረውልናል ።ከድንቅና ዘመን ተሻጋሪ ስራዎቻቸው መካከል ለኘሮቴስታንቱ ዘመንፈስ ቅዱስ አብርሃ  ምላሽ የሰጡበት ኰኲሐ ሃይማኖት የተሰኘው መጽሐፋቸው በትህትና የተለበጠ በእውቀት የተጠረዘ መጽሐፍ መኾኑ መስካሪ የማያሻው እንዲኹም በዚኽ ዘመን ላለው የኑፋቄ ትምህርት እና ግርታ ውስጥ እየወደቀ ላለው ወጣት አይነተኛ መፍትሔ ይኽ መጽሐፍ እንደኾነ መገንዘብ አይከብድም። ©መጽሐፉን በግዮን መጻሕፍት  በልዩ ቅናሽ ያገኙታል። #📚 ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖📖📖 #የቅዱስ_ጳውሎስ_14ቱ_መልእክታት ..፲፱ወይትዐወቅ ምግባሩ ለሥጋ የሥጋም ሥራው ይህ ነው፤ ዝሙት፡ዝሙት፤፳ርኲስ፡ኃጢአት ወምርዓት፡መዳራት፤አጣዕዎ፡በጣኦት ማምለክ ፤ሥራይ፡ሥራይ ማድረግ ፤
📖📖📖 #የቅዱስ_ጳውሎስ_14ቱ_መልእክታት ..፲፱ወይትዐወቅ ምግባሩ ለሥጋ የሥጋም ሥራው ይህ ነው፤ ዝሙት፡ዝሙት፤፳ርኲስ፡ኃጢአት ወምርዓት፡መዳራት፤አጣዕዎ፡በጣኦት ማምለክ ፤ሥራይ፡ሥራይ ማድረግ ፤ ጸልእ፡ፀብዕ፤ትዝኅርት፡ትዕቢት፤ትውዝፍት፡የምንዝር ጌጥ፤ቅንአት፡ቅንአት፤መዓት፡በቁሙቁጣ፤ኑፋቄ፡ጥርጥር፤ተቃሕዎ፡ፉክክር፤ተሓምሞ፡ምቀኝነት፤ተቃትሎ፡ነፍስመ መግደል፤ ስክረት፡ያለመጠን ጠጥቶ መስከር   ፳፪/ ወፍሬሁሰ ለመንፈስ ቅዱስ የነፍስ የሠራ ግን 【#ተፋቅሮ፤ ፍቅር፤#ፍሥሓ፤ተስፋ ደስታ ልጅነት#ሰላም፤አንድነት #ትዕግሥት ፡በነገር በመከራ መታገሥ፤ #ምጽዋት፣ መስጠት፣#ኂሩት፤ ቸርነት #ሃይማኖት ሃይማኖት፤ #የውሃት ኃዲገ በቀል፤ #ኢዘምዎትንጽሕና 】ነው፡፡ ፳፫/ #አልቦ ዘይኄይስ እምዝ ሕግ፡፡ ከዚህ ሥራ የሚበልጥ የለም፤   ፳፬/ ወእለሰ በኢየሱስ ክርስቶስ ስቀሉ ሥጋሆሙ ምስለ ፍትወት ወምስለ ኃጢአት፡፡ በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው ከ፲፭ቱፈቃዳተ ሥጋ  ጋር ከፍትወት ከኃጢአት ሰውነታቸውን የለዩ ሰዎች ይገብሩ ፱ኙን ፈቃዳተ ነፍስ ይሠራሉ፡፡ #አንድም በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው ፱ኙን ፈቃደተ ነፍስ የሚሠሩ ሰዎች ከፍትወት ከኃጢአት ጋር ከ፲፭ቱ ፈቃዳተ ሥጋ ሰውነታቸውን ይለያሉ፡፡ ፳፭/ ወይእዜሰ በመንፈስ ንሕየው አሆንም በፈቃደ ነፍስ እንኑር፤ ወዘመንፈስ ንግበር፡፡ ፈቃደ ነፍሳችነን እንሥራ፡፡ ፳፮/ ወኢንኩን ዝኁራነ፤ ትዕቢተኞች አንሁን፡፡ [ከገላትያ ምዕራፍ ፭ የተቀነጨበ ] ✨መሰል ብስል ተግሳጻትን ብሎም ህግጋትን ኸረ ምኑ......ያጨቀውን የምርጥ እቃው የጳውሎስን 14ቱን መልእክታት አንድምታ ብቻ ሳይኾን ማብራሪያም ጭምር የያዘው በሊቁ #መጋቤ ሐዲስ ቃለ ሕይወት በዛ  የተዘጋጀልንን ይህን ግሩም ክታብ እነኾ። 📚ግዮን መጻሕፍት 📱ይደውሉልን ፦0913083816

❝እምነት ማለት ያላየውን ነገር ማመን ነው ፣ ሽልማቱ ደግሞ ያመንከውን ማየት ነው።❞ ◍ሊቁ "ቅዱስ" አውግስጢኖስ
እምነት ማለት ያላየውን ነገር ማመን ነው ፣ ሽልማቱ ደግሞ ያመንከውን ማየት ነው።❞        ◍ሊቁ  "ቅዱስ"  አውግስጢኖስ

#የተባረከች_አይን የእግዚሐብሔርን ቃል በማንበብ ትጠመዳለች #የተባረከች_ጆሮ የንስሀ መዝሙር በመስማት እራሷን ታንጻለች #የተባረከ_ጉሮሮ ላይ የተቀደሰ ውሀ ይንቆረቆርበታል #የተባረከች_ምላስ የአምላ
#የተባረከች_አይን የእግዚሐብሔርን ቃል በማንበብ ትጠመዳለች #የተባረከች_ጆሮ የንስሀ መዝሙር በመስማት እራሷን ታንጻለች #የተባረከ_ጉሮሮ ላይ የተቀደሰ ውሀ ይንቆረቆርበታል #የተባረከች_ምላስ የአምላኳን ስጋና ደምን ትቀበላለች #የተባረከ_አንደበት ላይ እግዚሐብሔር ይመስገን የሚል ቃል አይጠፋበትም #የተባረከች_አንገት የአምልኮ ደም የፈሰሰበትን ቅዱስ መስቀል ትሸከማለች #የተባረከች_ልብ ኢየሱስን እስከ እናቱ አንግሳ በፍቅር ትሞላለች #የተባረከች_እጅ የቀረበላትን ምግብ በአምልኮ ስም ትባርካለች #የተባረከች_እግር ጠዋትና ማታ የአምላኳን መቅደስ ትረግጣለች "እኔ እግዚሐብኤር አምላካቹ ነኝና ሰውነታችሁን ቀድሱ ቅዱስም ሁኑ እኔ ቅዱስ ነኝና" ዘሌ. 11፥44 #አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ