ru
Feedback
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

Открыть в Telegram

# ቁልፍ እሴቶች 1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣ 2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣ 3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣ 4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

Канал FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት (@fdredefenseforc) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 42 469 подписчиков, занимая 6 068 место в категории Новости и СМИ и 768 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 42 469 подписчиков.

Согласно последним данным от 12 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 70, а за последние 24 часа — -3, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 11.40%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 8.29% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 840 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 3 520 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 36.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
# ቁልፍ እሴቶች 1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣ 2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣ 3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣ 4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 13 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Новости и СМИ.

42 469
Подписчики
-324 часа
-227 дней
+7030 день
Архив постов
በጅማ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የእግር ኳስ ውድድር በማዕከላዊ ዕዝ አሸናፊነት ተጠናቀቀ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም የጅማ ከተማ ስፖርት ፅህፈት ቤት ያዘጋጀውና በአስር የግልና የመንግስት ተቋማትን በማሳተፍ ሲካሄድ የቆየው የጤና ስፖርት የእግርኳስ ውድድር በማዕከላዊ ዕዝ ጤና ስፖርት ቡድን አሸናፊነት ተጠናቋል ። ውድድሩ በሁለት ምድቦች ተከፍሎ ለወራት የተካሄደ ሲሆን ሠራዊቱን የወከለው የዕዙ ጤና ስፖርት ቡድን በየዙሩ ካደረጋቸው ጨዋታዎች በአንዱ ብቻ አቻ ተለያይቶ ቀሪ ጨዋታዎችን በሰፊ የጎል ልዩነት እያሸነፈ የመጣ ሲሆን የፍፃሜ ጨዋታውን በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል። በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው የዋንጫና ሰርተ-ፊኬት ሽልማቱን ያበረከቱት የጅማ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት ሃላፊ ኢንጅነር መሃመድ ሳኒ የህዝብ መከታና የሀገር ወዳድነት ምሳሌ የሆነው ሠራዊታችንን የወከለው የዕዙ ስፖርት በድን በፍፁም ስፖርታዊ ጨዋነትና ዲሲፕሊን ከውድድሩ ጅማሮ እስከ ፍፃሜው ድረስ ላሳየው አርዓያነት የላቀ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል። የማዕከላዊ ዕዝ ስፖርት ከፍል ሃላፊ ሻለቃ ኤልያስ ታፈሰ ውድድሩን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት ይህን መሰል ስፖርታዊ መድረክ ፈጥሮ ውድድሩ እንዲካሄድ ላደረገው የከተማው ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት ምስጋና አቅርበው በውጤቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል። የፍፃሜ ጨዋታውን ከቀዩ ፊትነስ ስፖርት ቡድን ጋር ያደረገው የዕዙ ጤና ስፖርት ቡድን መደበኛ የጨዋታ ጊዜውን አንድ አቻ አጠናቆ በመለያ ምት 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፎ የውድድሩን ዋንጫ ወስዷል። ዘጋቢ ዮሴፍ ጉርቢያው ፎቶግራፍ ሚኪያስ እስክንድር የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አስከብሮ ለማስቀጠል ሀገራዊ ኢኮኖሚን እና ወታደራዊ አቅምን ማጠናከር ያስፈልጋል፦     አቶ ጌታቸው ኃይለ ማሪያም የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና ሥራ አሥፈፃሚ አቶ ጌታቸው ኃይለማሪያም ኢንዱስትሪው ከተቋሙ በተሰጠው የተልዕኮ አቅጣጫ መሰረት የሰራዊታችንን የማድረግ አቅም ለማጠናከር ወታደራዊ ትጥቆችን በማምረት በማደሥና በማዘመን ሀገር የሚያኮራ ሥራ መሠራቱን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የአለም የፍትህ ሚዛን በጉልበተኞች እጅ በወደቀበት ሰዓት ወታደራዊ አቅምን ማሳደግ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የጠቆሙት ዋና ሥራ አሥፈፃሚው ለዚህ ይረዳ ዘንድ ኢንዱስትሪው ዘመኑን የሚመጥኑ የተለያዩ ወታደራዊ ትጥቆችን እየመረተ እንደሚገኝ አብራርተዋል። በበጀት ዓመቱ ለሰው ሀይል የአቅም ግንባታ ስራ ትኩረት ተሰጥቶ መሠራቱ አሁን ለተገኘው ሁሉን አቀፍ ውጤት አሥተዋፅኦው ከፍ እንዲል ያሥቻለ መሆኑ እና ከነባር የማምረቻ ፋሲሊቲዎች በተጨማሪ አዳዲስ የወታደራዊ ትጥቆች ማምረቻ ግንባታዎች በትኩረት የተሰሩበት ዓመት እንደነበር በሪፖርቱ ተመላክቷል። ይህ ሥኬትም ዘመኑን የዋጁ የጦር መሳሪያዎችን እንድናመርት ከማድረጉ ባሻገር  ጦርነትን በሩቁ ለማስቀረትና ጠላቶቻችን ቆም ብለው እንዲያሰቡ የሚያደርግ መሆኑን አንስተዋል። የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ውጤታማነትና ጥንካሬ የሚለካው ከመንግሰት በሚያገኘው በጀት ብቻ ሳይሆን የራሱን የገቢ አማራጮች በማፈላለግ ኢኮኖሚያዊ አቅሙን ለማሳደግ በሚያደርገው ጥረትም ነው። በዚህም ከአፍሪካ ሀገሮች ጋር ውል በመፈፀም ወታደራዊ ትጥቆቻቸውን በመጠገንና አምርቶ በመሸጥ ገቢን ማሣደግ ተችሏል። አቶ ጌታቸው ኃይለ ማሪያም ግሩፑ እያሥመዘገበ ላለው ውጤት ጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር አብይ አህመድና የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ሚናቸው የጎላ እንደነበር አንስተዋል። የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዳስትሪ ግሩፕ ምክትል ስራ አስፈፃሚና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ብርጋዲየር ጀነራል ዮሃንስ ትኬሳ ኢንዱስትሪ ግሩፑ ዋናውን ተልዕኮ ከመወጣት ባሻገር ለተለያዬ አገልግሎት የሚውሉ የኮሜርሻል ምርቶች ማለትም የህዝብ መጓጓዣ አውቶብሶችን ፣ የተለያዬ ሞዴል ያላቸው መኪናዎችን በማምረት ገቢውን እያሳደገ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል። በአጠቃላይ ኢንዱስትሪ ግሩፑ ወታደራዊ ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬን ገቢ በማስገኘት ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ደጋፊ መሆን እንደቻለም ብርጋዲየር ጄኔራል ዮሃንስ ትኬሳ ገልፀዋል።  በዓመታዊ የሥራ አፈፃፀም ውይይት ላይ የተሳተፉት አመራሮች በበኩላቸው በተገኘው ውጤት ደስ መሰኘታቸውን ገልፀው በቀጣይ የስራ ዘመን የግሩፑን ፍላጎት ለማርካትና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ፈጠራና የቴክኖሎጅ ዝማኔ ላይ ትኩረት አድርገን እንሰራለን ብለዋል። በመጨረሻም በ2019 በጀት ዓመት የሥራ እቅድ ላይ ወይይት ተደርጎ የአፈፃፀም አቅጣጫ ተቀምጧል። ዘጋቢ ማሩ ግርማይ ፎቶግራፍ ፉራ አብደላ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

ፅንፈኛው ካምፕ አድርጎት የነበረው የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም የፅንፈኛው ቡድን ማረፊያ ካምፕ አድርጎት የነበረውን የደብረ ማርቆስ ንጉሥ ተክለ ሐይማኖት አውሮፕላን ማረፊያን ከጠላት በማፅዳት ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መቻሉን ሜጄር ጄነራል ብርሃኑ ጥላሁን ገልፀዋል። አውሮፕላን ማረፊያው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድን (ዶክተር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች፣ ጄኔራል መኮንኖች እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል። ከ30 ዓመታት በፊት ተቋርጦ የነበረው አውሮፕላን ማረፊያው በዘመናዊ መልክ ግንባታው ተጀምሮ የነበረ ቢሆንም ባለፉት አራት ዓመታት በፀጥታ ችግር ምክንያት ግንባታው ተቋርጦ ቆይቷል። ነገር ግን መከላከያ ሠራዊቱ የልማት አደናቃፊ የሆነውን ፅንፈኛ ቡድን በማፅዳት አካባቢውን ሠላም በማድረጉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። ይህ የአውሮፕላን ማረፊያ እውን እንዲሆን ሠራዊቱ ታላቅ መስዋዕትነት የከፈለበት ነው ያሉት የ6ኛ ዕዝ አዛዥ ሜጄር ጄኔራል ብርሃኑ ጥላሁን ቦታው ከዓመታት በፊት ጠላት ማረፊያ ካምፑ አድርጎት እንነደነበረና ቦታውን ሠራዊቱ ተዋግቶ ያፀዳበት ሁኔታ እንዳለ አሥረድተዋል። 6ኛ ዕዝ ተሠማርቶ በሚገኝበት ቀጠና ሁሉ የተላላኪዎችን የሽብር ተልዕኮ መና እያደረገ ሕብረተሰቡ በሠላም ወጥቶ እንዲገባ እየሠራ እንደሚገኝ የገለፁት አዛዡ ልማት ጠል የሆነው ፅንፈኛው ቡድን መሠረተ ልማቶች እንዳይለሙ ሙኩራ ቢያደርግም የሕዝብ ልጅ የሆነው መከላከያ ግን ልማት እንዲቀጥል ማድረጉን ተናግረዋል። ዕዙ በምሥራቅ ጎጃምና አካባቢው ከተሠማራ ወዲህ የጥፋት ቡድኑ ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመሆን የከፈተውን ውጊያ ማምከን የቻለ ሲሆን የጠላት ምኞትም ህልም ሆኖ መቅረቱን ገልፀዋል። ሠራዊቱ ባይኖር ኖር ደብረ ማርቆስና አካባቢው የሠላምን አየር አይተነፍሱም ነበር ያሉት የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተሾመ ዋለ መከላከያ ባስገኘልን ሠላም ፊታችንን ወደ ልማት አዙረናል ብለዋል። ሕብረተሰቡም ለዓመታት በጉጉት ሲጠብቀው የነበረው የአየር ትራንስፖርት እውን ሆኖ በማየቱ ደስታውን የገለፀ ሲሆን ለዚህ ስኬትና ሠላም መረጋገጥ ትልቁን ድርሻ ለተወጣው መከላከያ ሠራዊት ያላቸውን ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል። ዘጋቢ ውብሸት አንበሴ ፎቶግራፍ ገነት አወቀ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የሜካናይዝድ ዕዝ በተለያዬ የውጊያ ድጋፍ ሙያ የሠለጠኑ ሙያተኞችን አሥመረቀ፡፡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም የሜካናይዝድ ዕዝ በተለያዬ ሙያ ያሰለጠናቸውን ሙያተኞች የሠራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት  አስመርቋል፡፡ በስልጠናው መርሃ ግብር ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የሜካናይዝድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጀነራል ከፍያለው አምዴ የዕዙን ሠራዊት ለማዘመን ከተለመደው አሰራር ለመውጣት ዘመኑ ያፈራቸውን ቴክኖሎጂዎች መጠቀም እና ዕቅድ በመንደፍ ዝግጁነትን የማጠናከር ሥራ እየተሠራ ነው። ኢትዮጵያ የረጅም ዘመን ታሪክና ሥርዓተ መንግስት ያላት፣ ነፃነቷንና ሉዓላዊነቷን አስጠብቃ የኖረች ሀገር መሆኗን የጠቀሱት አዛዡ ታሪካዊ ጠላቶቻችን ኢትዮጵያ በራሷ በተፈጥሮ ሀብቷ ሰርታ እዳትለወጥ ያለ እረፍት ቢሰሩም ሴራቸውን ለማክሸፍ ዝግጁነታችን  ከምንጊዜም በላይ አጠናክረን እንቀጥላለንም ብለዋል፡፡ ጀግኖች አባቶቻችን በመሥዋዕትነት ያፀኗትን እና ከነ ሙሉ ክብሯ ያስረከቡንን ታላቅ ሀገር ለትውልድ ጠብቃችሁ በክብር ማሻገር ይጠበቅባችኋል ሲሉ ለተመራቂዎች አሥገንዝበዋል። የማሰልጠኛ ማዕከሉ አዛዥ ኮሎኔል አየለ ወልደ ጊዮርጊስ በበኩላቸው ዕዙ እንደ ዕዝ ራሱን ካደራጀ ማግስት ጀምሮ ሀገርና ህዝብን በሚመጥን መልኩ የሚሰጠውን ተልዕኮ በአስተማማኝ ብቃት ሊፈፅም  የሚችል የሀገር ኩራት የሆነ የሜካናይዝድ ድጋፍ ሰጪ ሙያተኛ እያፈራ መሆኑን ተናግረዋል። ዘገባው የዕዙ የሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ ነው፡፡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

ሠላም አስከባሪ ሻለቃው የደቡብ ሡዳን አስራ አምስተኛ አመት የነፃነት ቀንን አከበረ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም ‎ ‎በዌስተርን ኢኳቶርያ ያምቢዮ ካምፕ በተከበረው የደቡብ ሱዳን አሥራ አምስተኛ ዓመት ክብረ በዓል አከባበር የተገኙት የካምፑ ፊልድ ኦፊሰር ቡዱን መሪ ሚስተር  ጆዎፌሪ የደቡብ ሡዳን ሠላም ለማፅናት በቀጠናው የተሠማራው የ21ኛ ሞተራይዝድ ሠላም አስከባሪ ሻለቃ ተልዕኮውን በአስተማማኝ እየተወጣ መሆኑን ገልፀዋል። ‎ ‎የ21ኛ ሞተራይዝድ ሠላም አስከባሪ ሻለቃ አዛዥ ኮሎኔል እንዳለ እሸቱ ሠላም አስከባሪ ሠራዊት ከተልዕኮው ባሻገር ከአካባቢው የፀጥታ አካላት እና ከሕብረተሠቡ ጋር እጅ እና ጓንት ሆኖ በመስራት የቀጠናውን ሠላም ለማረጋገጥ የሚያኮራ ግዳጅ መፈፀሙን ተናግረዋል። ‎ ‎አሁን ላይ የ21ኛ ሞተራይዝድ ሠላም አስከባሪ ሠራዊት በሴክተር ሳውዝ ጁባ እና በዌስተርን ኢኳቶርያ ሰፊ ቀጠና ሸፍኖ ተዕኮውን እየተወጣ ይገኛል። በደቡብ ሱዳን የነፃነት ቀን በዓል የተለያዩ የኪነ ጥበብ ስራዎች የቀረቡ ሲሆን የደቡብ ሡዳን የባህል ቡድን የኪነ ጥበብ ስራዎችን አቅርቧል። ‎ ‎ዘጋቢ ፍፁም ተካ ‎ፎቶ ግራፍ ግርማቸው አብረሀ ‎ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

በስልጠና የተገነባ ሠራዊት የድል ባለቤት መሆኑ አያጠያይቅም።                  የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም የምዕራብ ዕዝ ህዳሴ ኮር ከማሰልጠኛ ተመድበው የመጡ መሰረታዊ ወታደሮችን ለሁለት ወራት ወታደራዊ ሥልጠና በመሥጠት አስመርቋል። በስነ - ስርዓቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የምዕራብ ዕዝ ህዳሴ ኮር አዛዥ ብርጋዲየር ጀነራል ንጉሴ ለውጤ ፤  ሠራዊቱ የሸኔ ሽብር ቡድንን እና ፅንፈኛውን ቡድን ከቀጠናው በማፅዳት ለህዝባችን አስተማማኝ ሰላም ለማስፈን በሚያደርገው ስኬታማ የግዳጅ አፈፃፀም የወታደራዊ ስልጠናዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑን አመላክተዋል። ኮሩ እየሰለጠኑ መዋጋት እየተዋጉ መሰልጠን የሚለውን መርህ በመከተል በተሰማራባቸው የግዳጅ ቀጠናዎች ባስመዘገባቸው አኩሪ ድሎች የፀረ-ሰላም ሀይሎችን አቅም በከፍተኛ ሁኔታ በማዳከም ሀገራዊ ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ይገኛል ሲሉ ገልፀዋል። ኮሩ የተሰጠውን ተልዕኮ በድል በመፈፀም መስዋዕትነት ከፍሎ ታላቁ የህዳሴ ግድብ በስኬት እንዲጠናቀቅ አሥተዋፅኦ ማበርከቱን የተናገሩት ጀኔራል መኮንኑ ሠራዊቱ እንደ ሁልጊዜው ሁሉ ማንኛውንም ግዳጅ በብቃት የመወጣት ተግባሩን አጠናክሮ መቀጠል አለበት ነው ያሉት። ተመራቂዎችም በወሰዱት ወታደራዊ ሳይንስና ጥበብ በተከተለ ስልጠና መሰረት ከመሰረታዊ ውትድርና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ካገኙት እውቀት ላይ ተጨማሪ አቅም በመፍጠር ተልዕኳቸውን በጀግንነት በመፈፀም ተቋሙን እና የኢትዮጵያን ህዝብ የሚያኮራ ስራ የማከናወን ሃላፊነት እንዳለባቸው ተናግረዋል ። የስልጠናውን ሪፖርት ያቀረቡት የኮሩ ዘመቻ ሃላፊ ሌተናል ኮሎነል ወንደወሰን ብርሃኑ ሰልጣኞች በቆይታቸው ኮሩ ባዘጋጀው የስልጠና መርሃ ግብር መሰረት የሚሰጣቸውን ግዳጅ በድል መወጣት የሚያስችል የወታደራዊ አቅም ማጎልበቻ ስልጠና መውሰዳቸውን ገልፀዋል። የዘገበው ጋብዘው ዳና ነው። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

በአሸባሪው ሸኔ ላይ ያነጣጠረ እርምጃ መውሰዳቸውን ክፍሎች አሥታወቁ። ‎ ‎የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም ‎ ‎የ6ኛ ዕዝ አንድ ኮር ተሰማርቶ በሚገኝበት ምዕራብ ሸዋ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች እና በመተከል ዞን ድባጤ ወረዳ የሚገኘው የንስር ክፍለ ጦር በአሸባሪው ሸኔ ላይ የተጠናከረ እርምጃ መውሰዳቸውን አሥታውቀዋል። የ6ኛ ዕዝ ኮር ሠራዊት ማንኛውንም አስቸጋሪ ሁኔታ በመቋቋም በሽብር ቡድኑ ላይ ተገቢውን እርምጃ በመውሰድ ሸኔን የመደምሰስ የመማረክ እና ትጥቅና መሣሪያን በቁጥጥር ሥር ማዋል እየተቻለ ሥለመሆኑ የኮሩ አዛዥ ብርጋዲየር ጀኔራል ሃብታሙ ምህረቴ  ገልፀዋል። የሽብር ቡድኑ ይጠቀምባቸው የነበሩ ስናይፐር ፣ ክላሽ፣ ቦንብ፣ የተለያዩ ዓይነት ተተኳሾች ተይዘዋል። በተመሳሳይ በመተከል ዞን ድባጤ ወረዳ ቆርካ ቀበሌ የሚገኘው የንስር ክፍለ ጦር ሬጅመንት፣ አሸባሪው ሸኔ ለጥፋት ኃይሉ ሲጠቀምበት የቆየውን በርካታ መሣሪያ መያዙን በምዕራብ ዕዝ የንስር ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል ባምላኩ ሰንደቁ ገልፀዋል። የክፍለጦሩ አዛዥ አሸባሪው ሸኔ ለጥፋት ሲጠቀምበት የቆየውን 27 መሣሪያ በአሰሳና ፍተሻ ከነታጣቂዎች  መያዙን ጠቅሰው፣ የክፍለጦሩ ሠራዊት ስልታዊ ጥበብን በመጠቀም መረጃ ሰጪ የሸኔ ተላላኪ ሴሎችን በመያዝ መሣሪያዎች የተደበቁባቸውን ስፍራዎች በመለየት ግዳጁን በብቃት እየፈጸመ መሆኑን ተናግረዋል። ዘገባው የክፍሎች ነው። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

ግዳጅን በብቃት ለመፈፀም በወታደራዊ ስልጠና አቅምን መገንባት እንደሚገባ ተገለፀ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም ግዳጅን በአስተማማኝ ብቃት ለመፈፀም በወታደራዊ ስልጠና አቅምን መገንባት እንደሚገባ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ተናገሩ። በመቅደላ ክፍለጦር የስልጠና ማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሀኑ በቀለ አገራችን በሉዓላዊነታቸው የማይደራደሩ የእልፍ ጀግኖች መኖሪያና መፍለቂያ መሆኗን ገልፀዋል። ኢትዮጵያዊያን ጀግኖች ወራሪውን ኃይል በማይደፈር ክንዳቸው አርበድብደው ባንዳን አባረው ቅኝ ያልተገዛች ሀገር አውርሰውናል ያሉት አዛዡ  የዚህ ዘመን ትውልድ የሆነው እኛም የተረከብናትን ሀገር ነፃነቷን ሳናስደፍር ለትውልድ ከነሙሉ ክብሯ እናስረክባለን ሲሉ ተናግረዋል። በየጊዜው የሀገርን ልማትና ብልፅግና ለማደናቀፍ የሚሞክሩ ሳይመቻቸው ሲቀር ደሞ በዘርና በሃይማኖት የሃሰት ትርክት እየነዙ የገራችን ሰላም የሚነሱ ባንዳዎች ህልማቸው ቅዠት እንዲሆን ማድረግ ብቻም ሳይሆን  የኢትዮጵያ ስጋት እንዳይሆኑ አስፈላጊው እርምጃ እንደሚወሰድባቸውም አዛዡ አንስተዋል። በስልጠና የተገኘውን አቅም ማጎልበት፤ ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር የሆነውን እሴት በመላበስ የህዝባችን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የበለጠ ዝግጁ መሆን እንደሚገባም ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ አሳስበዋል። ዘጋቢ ሮቤል ስዩም ፎቶግራፍ እንዳልካቸው ሀጂ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official