en
Feedback
University of Gondar(UoG)Atse Tewodros Compus Student Union 2015 E.C

University of Gondar(UoG)Atse Tewodros Compus Student Union 2015 E.C

Open in Telegram

ውድ የግቢያችን ተማሪዎች ሰላምና ፍቅር ከእናንተ ጋር ይሁን እያልን ማንኛውንም ወቅታዊ መረጃዎች በዚህ ቻናል የምታገኙ መሆኑን እናሳውቃለን::ለሌሎችም እንዲደርሳቸው ሼር አድርጉላቸው!!!! ማንኛውንም ጥያቄና መረጃ በዚህ አድርሱን 👉👉 https://t.me/+5NelehOUNtthNDA0 (0918759849)

Show more
833
Subscribers
+324 hours
+107 days
+5830 days
Posts Archive
ለሪሜዲያል ተማሪዎች በሙሉ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ በ2015 ዓ፣ም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሪሜዲያል ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የነበራችሁ ተማሪዎች፦ 1. የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ 200 እና በላይ 2. ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ 150 እና በላይ 3. የዓይነ ስዉራን ተማሪዎች ማለፊያ ነጥብ 100 እና በላይ መሆኑን እየገለዕን ዉጤታችሁን ከታች በተቀመጠዉ ሊንክ እየገባችሁ ማወቅ የምትችሉ መሆኑን እናሳስባለን፣፣ ከግቢ ዉጪ http፡//213.55.79.200 ከግቢ ዉስጥ http፡//10.139.8.79 ለልህቀት እንተጋለን! ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ህዝብና ዓለም ዓቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ሐምሌ 22/2015 ዓ.ም

Notice for Remedial students you can see your grade via this portal http://213.55.79.200

" ተፈታኞች በአካልም ይሁን በስነልቦና እራሳችሁን ዝግጁ አድርጉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መ
" ተፈታኞች በአካልም ይሁን በስነልቦና እራሳችሁን ዝግጁ አድርጉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መርሃ ግብርን ይፋ አድርጓል። በዚህም ፥ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ሐምሌ 16 እና 17/2015 ዓ.ም ወደተመደቡበት ተቋም ይገባሉ። ሐምሌ 18/2015 ዓ.ም ገልጻ ይሰጣቸዋል። ከሐምሌ 19 እስከ 21/2015 ዓ.ም ፈተናቸውን ይወስዳሉ። ከሚቀጥለው ቀን ጀምሮ ተማሪዎች ወደመጡበት ይመለሳሉ። የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች  ደግሞ ሐምሌ 22 እና 23/2015 ዓ.ም ወደተመደቡበት ተቋም ይገባሉ። ሐምሌ 24/2015 ዓ.ም ገለጻ ይሰጣቸዋል። ከሐምሌ 25 እስከ 28/2015 ዓ.ም ፈተናቸውን ይወስዳሉ።  ከሚቀጥለው ቀን ጀምሮ ተማሪዎች ወደመጡበት ይመለሳሉ። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናውን በሚውስዱበት ጊዜ የፈተናውን ህግና ስርዓት እንዲያከብሩ በጥብቅ አሳስቧል። ተፈታኝ ተማሪዎች ለፈተናው ግልጋሎት ከሚሰጡ የፅህፈት መሳሪያዎች እርሳስ፣ ላጲስ፣ መቅረጫ እና ስክቢቶ ውጭ ወደ ፈተና ክፍል ይዞ መግባት ፈፅሞ የተከለከለ መሆኑን እንዲያውቁት ብሏል። ተማሪዎቹ ከቤታቸው ሲወጡ፦ - መታወቂያ ፣ - አድሚሽን ካርድ - የት/ቤት ዩኒፎርም መያዛቸውን እንዳይረሱ ፤ ወላጆችም ይህንን እንዲያስታውሷቸው ጥሪ ቀርቧል። ወደ መፈተኛ ተቋማት ቆሎ፣ ጭኮ፣ በሶ የመሳሰሉ ደረቅ ምግቦችን ይዞ መግባት የሚፈቀድ ሲሆን የቴክኖሎጂ ውጤቶች፣ አይፓድ፣ ላፕቶፕ የመሳሰሉ እንዲሁም ማንኛውም ጌጣጌጥ ይዞ መግባት ፈፅሞ የተከለከለ ነው። ለኢንትራንስ ተፈታኞች👇 https://t.me/ATC_UEE ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሐምሌ 19 ጀምሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ይሰጣል። የተፈታኝ ተማሪዎች መብቶች፦ ➭ ከፈተና ጥያቄ ውጪ ማንኛውንም ያልተረዳውን ነገር ጠይቆ የመረዳት መብት አላቸው። ➭ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ የምግብ፣ የህክምና አገልግሎት፣ የማደሪያ ክፍል፣ ፍራሽ እና ትራስ የማግኘት መብት አላቸው። ➭ ማንኛውም ተፈታኝ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ያለውን የቤተ መፅሐፍት፣ የመጸዳጃ ቤቶች፣ የሻወር፣ የካፍቴሪያዎች፣ የሚኒ ሱፐር ማርኬቶች፣ የተለያዩ ሱቆች እንዲሁም የመናፈሻና መዝናኛ አገልግሎቶችን የመጠቀም መብት አላቸው። ➭ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ የጋራ የደህንነት ጥበቃ የማግኘት መብት አላቸው። ➭ በፈተና ሰዓት መፈተኛ ክፍል ገብቶ ብርሃናማ የመፈተኛ ቦታ፣ ወንበርና መፃፊያ ጠረጴዛ የማግኘት መብት አላቸው። ➭ ፈተና ከመጀመሩ አንድ ቀን ቀድሞ ስለፈተናው ገለጻ (ኦሬንቴሽን) የማግኘት መብት አላቸው። የተፈታኝ ተማሪዎች ግዴታዎች፡- ➤ ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕከልና መፈተኛ ክፍል አድሚሽን ካርድ ይዞ የመገኘት ግዴታ አለበት። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ የትምህርት ቤት ወይም የነዋሪነት መታወቂያ ይዞ መገኘት አለበት። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ግቢ ከመግባቱ በፊትና ወደ መፈተኛ ክፍል ከመግባቱ በፊት ሙሉ አካላዊ ፍተሻ የመፈተሽ ግዴታ አለበት። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ በዩኒቨርሲቲ ግቢና በመፈተኛ ክፍል የተከለከሉ ዕቃዎችን መያዝ የለበትም። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ እርሳስ፣ ላጲስና የእርሳስ መቅረጫ ይዞ መገኘት አለበት። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብን የማክበር ግዴታ አለበት። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕከል/በመፈተኛ ክፍል ውስጥ የፈተና አስፈጻሚዎች የፈተና አስተዳደር ሥራን ውጤታማ ለማድረግና ሁኔታዎችን ለማመቻቸት የሚያደርጉትን ጥረት የመተባበር ግዴታ አለበት። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ ፈተና ከመጀመሩ በፊት መፈተኛ ክፍል የመገኘት ግዴታ አለበት። ➤ ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ከፈተና ክፍል የሚወጣ ከሆነ የፈተና ጥያቄ የያዘውን ቡኩሌት ለፈታኙ የማሰረከብ ግዴታ አለበት። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደተመደበበት ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና የትራስ ጨርቅ ይዞ የመምጣት ግዴታ አለበት። ለተፈታኝ ተማሪዎች የተፈቀዱ ነገሮች፦ ➣ አዲስ ወይም ቀድሞ ለመማር እና ለማጥናት ሲጠቀሙበት የነበሩ ማስተወሻ ደብተር፣ የትምህርት መፅሐፍ፣ መንፈሳዊ/ኃይማኖታዊ መፅሐፍት፣ ባዶ ወረቀት ➣ ደረቅ ምግቦች (ጩኮ፣ በሶ፣ ዳቦ ቆሎ፣ ቆሎ….) ➣ ገንዘብ (ብር) ➣ የልብስ ወይም የእጅ ቦርሳ፣ የግል ልብስ፣ ጫማ ➣ የግል ንጽህና መጠበቂያዎች (ሳሙና፣ ሞዴስ፣ የጥርስ ብሩሽ፣ የጥርስ ሳሙና፣ ፎጣ፣ ሶፍት፣ ሻምፖ፣ ኮንዲሽነር፣ ሎሽን፣ ቻፕስቲክ፣ የጸጉር ቅባት፣ የፊት ቅባት) ለተፈታኝ ተማሪዎች የተከለከሉ ነገሮች፦ ➣ ማንኛውንም ዓይነት የጦር መሣሪያ ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው፡፡ ➣ ማንኛውንም ዓይነት ስለት እና ሹልነት ያላቸውን ብረታ ብረቶችና ጠንካራ ፕላስትኮች ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው። ➣ ማንኛውም ድምጽ የሚቀዳ፣ ፎቶ የሚያነሳ፣ ቪዲዮ የሚቀርጽ፣ ከቴሌ መስመርም ሆነ ከቴሌ መስመር ውጭ መልዕክት በዲጂታል መንገድ የሚሰጥ ወይም የሚቀበል የግል ዕቃ/መሳሪያ/የቴክኖሎጂ ውጤት፣ ስልክ፣ አይ-ፓድ፣ ታብሌት፣ ኮምፕዩተር፣ ላፕቶፕ፣ ስማርት ሰዓት፣ ማጂክ ብዕር/እስክሪብቶ፣ ማጂክ ኮት/ጃኬት እና ሌሎች ማንኛቸውም ፎቶ፣ ምስል እና ድምጽ የሚቀርጹ የኤሌክትሮኖክስ መሣሪያዎችን በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥም ሆነ ግቢ ዙሪያ ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡ ➣ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ማንኛውንም ዓይነት የግል ፍላሽ ዲስክ፣ ሃርድ ዲስክ፣ ሲዲ፣ ሚሞሪ፣ ሚሞሪ ሪደር፣ ኦ-ቲጂ ኮንቨርተርና መሰል ዕቃዎችን ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡ ➣ ማንኛውም አደንዛዥ እጾች (ጫት፣ ሲጋራ፣ በሐኪም ማዘዣ የሌለው መድኃኒት)፣ ህክምና መስጫ መርፌ መያዝ ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡ ➣ ማንኛውም ዓይነት የአልኮል መጠጥ ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡ ➣ ማንኛውም ዓይነት የአንገት ሐብል፣ የጸጉር ጌጥ፣ የጆሮ ጌጥ፣ የጣት ቀለበት፣ የእጅ አንባር፣ አድርጎ ወይም ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው፡፡ (ከልሙጥ የጋብቻ ቀለበት በስተቀር) ➣ ፈተና ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በኋላ ወደ ፈተና ክፍል መግባት እና ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ከፈተና ክፍል መውጣት የተከለከለ ነው፡፡ ➣ ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ከፈተና ክፍል የሚወጣ ከሆነ የፈተና ጥያቄ የያዘውን ቡኩሌት ይዞ መውጣት ተከለከለ ነው፡፡ ➣ በፈተና ሰዓት በመፈተኛ ክፍል ውስጥ ማስቲካ መያዝም ሆነ መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡ ➣ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ በግልም ሆነ በቡድን መጮህ ወይም በጣም ከፍተኛ ድምጽ ማሰማት የተከለከለ ነው። ለኢንትራንስ ተፈታኞች👇 https://t.me/ATC_UEE ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

በተማሪዎቻችን ውጤት ደስ ብሎናል እንኳን ደስ አላችሁ! ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ በዚህ ዓመት በተተገበረው አገር ዓቀፍ የመውጫ ፈተና ተማሪዎቻችን ከፍተኛ ውጤት አስመዝግበዋል። ይህም በሀገራችን ከሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ዩኒቨርሲቲያችን ቀዳሚ አድርጎታል። በገለልተኛ አካል አስፈትኖ ይህን ውጤት ማግኘት የበለጠ የሚያበረታታና ለነገ ተስፋ የሚሰጥ ጅማሮ ነው። ይህ ውጤት የተማሪዎቻችን፣ የመምህራንና መላ የዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ ፣ የወላጆች፣ አቅፎና ደግፎ እዚህ ያደረሳቸው የጎንደር ሕዝብ እና የቅርብ አጋሮቻችን የረጅም ጊዜ ድካምና ልፋት ውጤት ነው። ከምንም በላይ የሁሉም የዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ ሥራን በሙያዊነት፣ በተቆርቋሪነት እና በጋራ የመሥራት መንፈስ ውጤት ነው። አገር የሚፈርሰውም የሚሠራውም በትምህርት ነውና ለጥራት ከምንጊዜውም በላይ ተግተን እንሠራለን። "ሰው የዘራውን ያጭዳል" ነውና ሁላችንም የድካማችን ፍሬ ማየት በመብቃታችን እንኳን ደስ አለን። ሙያዊ ሆኖ መስራት ምላሹ ብዙ ነው! ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ዶክተር አሥራት ዓጸደወይን የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሐምሌ 09/2015 ዓ.ም

በአገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ዩኒቨርሲቲያችን በግምባር ቀደምትነት ተማሪዎችን በማሳለፉ እንኳን ደስ አለን፤ እንኳን ደስ አላችሁ። ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ በአገር ዓቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በተተገበረው እና በዩኒቨርሲቲያችን ባሉ 8 ኮሌጆች፣ 2 ኢንስቲትዩቶችና 1 ትምህርት ቤት ስር በሚገኙ 73 ትምህርት ክፍሎች ሲሰጥ የቆየው የመውጫ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል። በአጠቃላይ ካስፈተናቸው 3,089 ተማሪዎች ውስጥ 2,760(89.35%) ተፈታኞች በብቃት አልፈዋል። ፈተናውን ከወሰዱ 73 ትምህርት ክፍሎች መካከል 34 ትምህርት ክፍሎች ሙሉ በሙሉ (100%) አሳልፈዋል። ከአጠቃላይ ተፈታኞች መካከል በመደበኛ መርሐግብር ካስፈተናቸው 2,919 ተማሪዎች 2,703 (92.6%) ያለፉ ሲሆን ቀሪዎቹ 170 ተማሪዎች በተከታታይ መርሐግብር ተፈተነው 57(33.53%) ፈተናውን በብቃት አልፈዋል። ይህም ውጤት በአገሪቱ ካሉ አቻ ተቋማት ቀዳሚ ያደርገዋል። በዚህም መላው የዩኒቨርስቲያችን ማህበረሰብና አጋሮቻችን ከፍተኛ ኩራትና ደስታ ተሰምቷቸዋል። የተገኘው ስኬት አበረታችና ለቀጣይ ትልቅ ኃላፊነትን የሰጠን ነው። ስለሆነም ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆች፣ የቴክኒክ ረዳቶች፣ የአስተዳደር ሠራተኞች፣ ትምህርት ሚኒስቴርና ሌሎች አጋር አካላት እንዲሁም መላ የትምህርት ቤተሰቡ በትብብር ያስመዘገባችሁት ውጤት በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እንወዳለን። ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ለልህቀት እንተጋለን! ህዝብና ዓለም ዓቀፍ ግኝኙነት ዳይሬክቶሬት ሐምሌ 09/2015 ዓ.ም

#UniversityofGonder 🎉 በአገር ዓቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በተተገበረው የመውጫ ፈተና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአገሪቱ ካሉ አቻ ተቋማት ቀዳሚ ሆኗል። የጎንደር ዩንቨርሲቲ በአጠቃላይ ካስፈ
#UniversityofGonder 🎉 በአገር ዓቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በተተገበረው የመውጫ ፈተና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአገሪቱ ካሉ አቻ ተቋማት ቀዳሚ ሆኗል። የጎንደር ዩንቨርሲቲ በአጠቃላይ ካስፈተናቸው 3,089 ተማሪዎች ውስጥ 2,760(89.35%) ተፈታኞች በብቃት ማሳለፍ የቻለ ሲሆን ፈተናውን ከወሰዱ 73 ትምህርት ክፍሎች መካከል 34 ትምህርት ክፍሎች ሙሉ በሙሉ (100%) አልፈዋል። ይህንን ስኬት አስመልክቶ ዩኒቨርሲቲው ለተማሪዎቹ፣ ለመምህራን፣ ለወላጆች፣ ለቴክኒክ ረዳቶች፣ ለአስተዳደር ሠራተኞች፣ ለትምህርት ሚኒስቴርና ለሌሎች አጋር አካላት እንዲሁም ለመላ የትምህርት ቤተሰቡ ምስጋና አቅርቧል። ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

ውጤት አሁን ይፍ ሁኗል እየገባችሁ ማየት ትችላላሁ መልካም ውጤት

Repost from ATC NEWS
#UniversityofGonder የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለመውጫ ፈተና ካስፈተናቸው 3112 ተማሪዎች ውስጥ 2776 ያህሉ ማለትም 89.2% በጥሩ ውጤት አልፈዋል። ተመራቂ ተማሪዎች የመዉጫ ፈተና ውጤታችሁ
+1
#UniversityofGonder የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለመውጫ ፈተና ካስፈተናቸው 3112 ተማሪዎች ውስጥ 2776 ያህሉ ማለትም 89.2% በጥሩ ውጤት አልፈዋል። ተመራቂ ተማሪዎች የመዉጫ ፈተና ውጤታችሁን በዚህ ሊንክ ➡️ https://result.ethernet.edu.et በመግባት ማወቅ ትችላላችሁ። ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

እንኳን ደስ ያላቹሁ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ዩኒቨርሲቲያችን "የጎንደር ዩኒቨርሲቲ" ለመውጫ ፈተና ካስፈተናቸው ተማሪዎች ውስጥ 89.2% በጥሩ ውጤት አልፈዋል። ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ለልህቀት እንተጋለን

#ExitExam #ቁጥራዊ_መረጃ በመንግስት ዩንቨርሲቲዎች 77,981 ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ወስደው 👉48,632 ያህሉ ማለትም 62.37% አልፈዋል። በግል ተቋማት 72,203 ተማሪዎች የመውጫ ፈተና
#ExitExam #ቁጥራዊ_መረጃ በመንግስት ዩንቨርሲቲዎች 77,981 ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ወስደው 👉48,632 ያህሉ ማለትም 62.37% አልፈዋል። በግል ተቋማት 72,203 ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ወስደው 👉12,422 ያህሉ ማለትም 17.2% ተማሪዎች ብቻ አልፈዋል። ♨️በድምሩ 150,184 ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ወስደው 61,054 ማለትም 40.65% ተማሪዎች አልፈዋል። ተማሪዎች ከነገ ጀምሮ ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ። 👉 Read More ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" የ2015 የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን ከእሁድ ማታ ጀምሮ ለፈተናው የተሰጣቸውን User Name በመጠቀም በዚህ ሊንክ https://result.ethernet.edu.et/ ገብተው ማወቅ
+3
" የ2015 የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን ከእሁድ ማታ ጀምሮ ለፈተናው የተሰጣቸውን User Name በመጠቀም በዚህ ሊንክ https://result.ethernet.edu.et/ ገብተው ማወቅ ይችላሉ " - ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተና መጠናቀቅን አስመልክቶ መግለጫ ልኮልናል። ለመውጫ ፈተና ሊቀመጡ ይችላሉ ተብሎ ተገምቶ የነበረው 240 ሺህ ተማሪዎች ሲሆኑ የመውጫ ፈተናን ለመውሰድ ብቁ ሆነው የተመዘገቡት ከ48 መንግስት ተቋማት 84,627 እና ከ171 የግል ተቋማት 109,612 በድምሩ 194,239 ተማሪዎች ናቸው፡፡ የመውጫ ፈተናን ለመውስድ ከተመዘገቡት ውስጥ ከመንግስት ተቋማት 77,981 ተማሪዎች ከተመዘገቡት 92.15 ከመቶ እንደዚሁም ከግል ተቋማት 72, 203 ተማሪዎች 65.87 ከመቶ በድምሩ 150,184 ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን ወስደዋል፡፡ በመንግስት ተቋማት ለፈተና ከተቀመጠት ውስጥ 48,632 ተማሪዎች 62.37 በመቶ የማለፊያውን 50 እና ከዚያ በላይ አስመዝግበዋል፡፡ በተመሳሳይ ከግል ተቋማት ለፈተና ከተቀመጡት ውስጥ 12,422 ተማሪዎች 17.2 በመቶ የማለፊያውን 50 እና ከዚያ በላይ አስመዝግበዋል፡፡ በድምሩ ለፈተና ከተቀመጡት ውስጥ 61,054 ተማሪዎች 40.65 በመቶ የማለፊያውን ነጥብ አስመዝገበዋል፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር በላከልን መግለጫ የ2015 የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን #ከእሁድ ማታ ጀምሮ ለፈተናው የተሰጣቸውን User Name በመጠቀም በዚህ ሊንክ https://result.ethernet.edu.et/ ገብተው ማወቅ ይችላሉ ብሏል። (ትምህርት ሚኒስቴር የላከልን ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል) @tikvahethiopia

ለዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከተቀመጡት ተማሪዎች ውስጥ 40.65 በመቶዎቹ የማለፊያ ነጥብ አስመዘገቡ! ለዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከተቀመጡት ተማሪዎች ውስጥ 40 ነጥብ 65 በመቶዎቹ የማለፊያ ነጥብ ማስመ
ለዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከተቀመጡት ተማሪዎች ውስጥ 40.65 በመቶዎቹ የማለፊያ ነጥብ አስመዘገቡ! ለዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከተቀመጡት ተማሪዎች ውስጥ 40 ነጥብ 65 በመቶዎቹ የማለፊያ ነጥብ ማስመዝገባቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ ከሰኔ 30 ቀን ጀምሮ ለስድስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው የዩኒቨርሲቲ ትምህርት መውጫ ፈተና በስኬት መጠናቀቁን ገልፀዋል። ለመውጫ ፈተና ሊቀመጡ ይችላሉ ተብሎ ተገምቶ ከነበረው 240 ሺህ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን 194 ሺህ 239 ተማሪዎች ብቁ ሆነው ለፈተና መመዝገባቸውንም ነው የተናገሩት። ከዚህ ውስጥ ከ48 የመንግስት ተቋማት 84 ሺህ 627 ተማሪዎች እና ከ171 የግል ተቋማት 109 ሺህ 612 ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን ለመውሰድ መመዝገባቸውም ነው የገለጹት። የመውጫ ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት ውስጥ ከመንግስት ተቋማት 77 ሺህ 981 ተማሪዎች እንዲሁም ከግል ተቋማት 72 ሺህ 203 ተማሪዎች በድምሩ 150 ሺህ 184 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል ብለዋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 61 ሺህ 54 ተማሪዎች ወይም 40 ነጥብ 65 በመቶ የማለፊያውን ነጥብ አስመዝገበዋል ነው የተባለው፡፡ ለተቋማትም የተማሪዎቻቸውን ውጤት የመላክ ሥራ መጀመሩንም ጠቁመዋል። #ኢፕድ

+3
Share UOG Mgt Session 1 Hamle 6.xlsx

#update university of Gondar Exit Exam Schedule Hamle 3-5,2015 E.C (1).pdf

ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት የተሰጠ መግለጫ! በቅድሚያ በዩኒቨርሲቲ ቆይታችሁ ማሟላት የሚጠበቅባችሁን አሟልታችሁ ለዚህ ለበቃችሁ ውድ እጩ ምሩቃን እና ክቡራን የምሩቃን ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ እያልን በዚህ አመት በሁሉም የትምህርት ክፍሎች የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና፤ ተመራቂ ተማሪዎች ያላቸውን ብቃት ለመለካት የተዘጋጀ እና ለት/ት ጥራት የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ቢሆንም የነበሩ ክፍተቶችን እና በቅድሚያ መሟላት የነበረባቸው ሁኔታዎችን በዝርዝር በማስቀመጥ ቢያንስ ቁጥራቸው በዛ ያሉ ተመራቂዎች በሚገኙባቸው የት/ት ፕሮግራሞች በዚህ አመት እንዲጀመር አልያም በሙከራ ደረጃ እንዲሰጥ ያላሳለሰ ጥረት አድርገናል። ሆኖም የት/ት ጥራትን ለማምጣት በሁሉም የት/ት ክፍሎች እንዲጀመር በመወሰኑ፤ ያሉ ነባራዊ ሁኔታዎችን ከግምት በማስገባት በትግበራው ተማሪው ተጎጂ እንዳይሆን እያደረግን ቆይተናል። በቅርቡ በተሰጡት የመለማመጃ እና የሙከራ ፈተናዎች ወቅት የነበሩ ክፍተቶችን ከየዩኒቨርሲቲው የተማሪ ህብረቶች በመሰብሰብ እና በዋናው ፈተና ወቅት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን በመለየት እንዲስተካከሉ ለት/ት ሚኒስቴር ከወዲሁ አሳውቀናል። በተጨማሪም ምርቃት እና የመውጫ ፈተናን በተመለከተ ከት/ት ሚኒስቴር ጋር በነበረን ቅድመ ውይይት የምረቃ  መርሀ-ግብር ላይ የሚሳተፉ ተማሪዎችን በተመለከት ዩኒቨርሲቲዎች የቀደመ አሰራራቸውን መከተል እንደሚችሉ ስምምነት ላይ ደርሰን የነበረ ቢሆንም፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ “የመውጫ ፈተናን ያላለፉ ተማሪዎች የምርቃት ፕሮግራም ላይ አይሳተፉም” በማለት በድንገት አሳውቆ የነበረ መሆኑ ይታወቃል። ውሳኔው ከተገለፀበት እለት ጀምሮ እንደ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ጉዳዩ አግባብነት የሌለው፣ በህግ ለተቋማት ሴኔት በተሰጠ ስልጣን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ያለ አግባብ ጣልቃ መግባቱን እንዲሁም ውሳኔው ከ4-7 አመታት የተማረው ተማሪን ብቻ ሳይሆን የሀገር መሰረት የሆነውን ቤተሰብንም ጭምር የሚጎዳ፤ ለት/ት ጥራቱም ምንም ፋይዳ የሌለው መሆኑን በመግለፅ በተደጋጋሚ ውይይት ያደረግን ሲሆን በዚህም መሰረት ት/ት ሚኒስቴር በግብታዊነት ያስተላለፈውን ውሳኔ በማሻሻል ወደቀድሞ ሀሳብ ተመልሷል። ለዚህም በተመራቂ ተማሪዎች ስም ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ምስጋናችንን እናቀርባለን። በዚህም መሰረት በሀገራችን የሚገኙ ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አንድ/ሁለት ያልተሟላ ውጤት ኖሯቸው ከግማሽ በላይ ጠቅላላ ድምር ውጤት(CGPA>=2.00) ያላቸውን ተማሪዎች የምርቃት መርሀ-ግብር እንዲሳተፉ አድርገው ሲያሟሉ ዲግሪ የሚሰጡ ሲሆን አሁንም በተመሳሳይ የመውጫ ፈተናውን የማያልፍ ተማሪ ካለ የምርቃት መርሀ-ግብር ላይ በመሳተፍ ለምዘናው ብቁ በሆነ ጊዜ በየሶስት ወሩ በሚሰጠው ፈተና ያለገደብ መመዘን ብሎም ድጋሚ የመፈተን ፍላጎት የሌለው እጩ ምሩቅ በደረጃ ዝቅ ያለ የት/ት ማስረጃ መውሰድ እንደሚችል በመመሪያ ተቀምጧል። በመሆኑም ውድ እጩ ምሩቃን በምርቃት መርሀ-ግብር ዙሪያ ሲነሱ የነበሩ ነገሮችን ታግሳችሁ ከሚመለከታቸው አካላት መልስ እስኪሰጥ በትግስት ስለጠበቃችሁ ምስጋናችንን እያቀረብን፤ ጥያቄያችን መልስ አግኝቶ ሁሉም ተመራቂ ተማሪ የምርቃት መርሀ-ግብር ላይ የሚሳተፍ በመሆኑን እንገልፃለን። በተያያዘም የመውጫ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች በትምህርት ማስረጃቸው ላይ ከ100 ያመጡት ውጤት የሚገለፀው በጊዜያዊው ማስረጃቸው(Tempo) ላይ ሳይሆን በትራንስክሪፕት ማለትም የወጪ መጋራታቸውን ከፍለው ሲያጠናቅቁ በሚሰጣቸው፤ የወሰዱትን የት/ት አይነቶች ከነውጤታቸው በሚያሳየው ማስረጃ ላይ መሆኑን እየገለፅን መንግስት አዲስ ቅጥር ማቆሙን ካሳወቀ 2 አመታት ያለፉ ቢሆንም በግሉ ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በመንግስት መስሪያ ቤቶችም የተለያዩ አዲስ ቅጥሮች ሲፈፀሙ የቆዩ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን። በመጨረሻም ክቡራን እጩ ምሩቃን፦    1) የምትፈተኑበት ኮምፒውተር ፈተና ከመጀመሩ በፊት ሙሉ አገልግሎት እንደሚሰጥ ፈትሻችሁ እንድትቀመጡ፤ 2) ፈተናውን በምትሰሩበት ወቅት የኮምፒውተር ገመዶች በሰውነታችሁም ሆነ በሌላ ነገሮች እንዳይነኩ እና እንዳይቋረጡ ጥንቃቄ እንድታደርጉ፤ 3) ወደ መፈተኛ ክፍሎች ስትገቡ እና ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ መመሪያዎችን እንድታከብሩ፤ 4) ምዘናው በበይነመረብ የሚሰጥ እንደመሆኑ በፈተናው ወቅት ችግሮች ካጋጠሙም ወድያው መፍታት ስለሚቻል እንከን ሲያጋጥማችሁ በየመፈተኛ አዳራሹ ለተመደቡ የአይሲቲ ባለሙያዎች በፍጥነት እንድታሳውቁ እንዲሁም የሚያጋጥሟችሁን የትኛውም ተግዳሮቶች በግቢያቹ ላለው ህብረታችሁ በማመልከት ከግቢው ከአቅም በላይ ከሆነ በእኛ በኩል በሚመለከተው አካል እንዲፈታ የምናደርግ መሆኑን እየገለፅን በቅርቡ በተሰጠው የሙከራ ፈተና ልክ በመዘጋጀት ያለምንም ፍርሀት እና ጭንቀት የፈተና ስነ-ምግባርን በጠበቀ መልኩ እንድትፈተኑ አደራ እያልን መልካም ፈተና እንዲሆንላችሁ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎች ስም አብዝተን እንመኛለን።              መልካም እድል! የጎ/ዩ/አ/ቴ ግቢ ተማሪዎች ህብረት         ቅድሚያ ለተማሪዎች ❗️     📌 የተማሪዎች ህብረት https://t.me/UoGATstudentunion

ወደ ደሴም ተሰባሰቡና 1 መኪና የምትቃረቡ ከሆነ እናዘጋጅላችኋለን

የሄ ለተመራቂወች እና በተለያዬ ምክንያት ግቢ ውስጥ ላላችሁ ነው