en
Feedback
University of Gondar(UoG)Atse Tewodros Compus Student Union 2015 E.C

University of Gondar(UoG)Atse Tewodros Compus Student Union 2015 E.C

Open in Telegram

ውድ ዚግቢያቜን ተማሪዎቜ ሰላምና ፍቅር ኚእናንተ ጋር ይሁን እያልን ማንኛውንም ወቅታዊ መሚጃዎቜ በዚህ ቻናል ዚምታገኙ መሆኑን እናሳውቃለን::ለሌሎቜም እንዲደርሳ቞ው ሌር አድርጉላ቞ው!!!! ማንኛውንም ጥያቄና መሹጃ በዚህ አድርሱን 👉👉 https://t.me/+5NelehOUNtthNDA0 (0918759849)

Show more
833
Subscribers
+324 hours
+107 days
+5830 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
December '24
December '24
+38
in 0 channels
November '24
+42
in 0 channels
Get PRO
October '24
+48
in 0 channels
Get PRO
September '24
+63
in 0 channels
Get PRO
August '24
+61
in 0 channels
Get PRO
July '240
in 0 channels
Get PRO
June '240
in 0 channels
Get PRO
May '240
in 0 channels
Get PRO
April '240
in 0 channels
Get PRO
March '240
in 0 channels
Get PRO
February '24
+146
in 0 channels
Get PRO
January '24
+29
in 0 channels
Get PRO
December '230
in 0 channels
Get PRO
November '230
in 0 channels
Get PRO
October '230
in 0 channels
Get PRO
September '23
+4
in 0 channels
Get PRO
August '23
+6
in 0 channels
Get PRO
July '23
+63
in 0 channels
Get PRO
June '23
+802
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
21 December+2
20 December+7
19 December0
18 December+4
17 December+1
16 December+3
15 December0
14 December0
13 December0
12 December+2
11 December+2
10 December+6
09 December0
08 December0
07 December+2
06 December0
05 December0
04 December+1
03 December0
02 December0
01 December+8
Channel Posts
ለሪሜዲያል ተማሪዎቜ በሙሉ ፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚ በ2015 ዓ፣ም በጎንደር ዩኒቚርሲቲ ዚሪሜዲያል ትምህርታቜሁን ስትኚታተሉ ዚነበራቜሁ ተማሪዎቜፊ 1. ዚተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎቜ ዚማለፊያ ነጥብ 200 እና በላይ 2. ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎቜ ዚማለፊያ ነጥብ 150 እና በላይ 3. ዹዓይነ ስዉራን ተማሪዎቜ ማለፊያ ነጥብ 100 እና በላይ መሆኑን እዚገለዕን ዉጀታቜሁን ኚታቜ በተቀመጠዉ ሊንክ እዚገባቜሁ ማወቅ ዚምትቜሉ መሆኑን እናሳስባለን፣፣ ኚግቢ ዉጪ http፡//213.55.79.200 ኚግቢ ዉስጥ http፡//10.139.8.79 ለልህቀት እንተጋለን! ፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚ ህዝብና ዓለም ዓቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ሐምሌ 22/2015 ዓ.ም

2
Notice for Remedial students you can see your grade via this portal http://213.55.79.200
543
3
No text...
732
4
" ተፈታኞቜ በአካልም ይሁን በስነልቊና እራሳቜሁን ዝግጁ አድርጉ " - ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ዹ2015 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መ
" ተፈታኞቜ በአካልም ይሁን በስነልቊና እራሳቜሁን ዝግጁ አድርጉ " - ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ዹ2015 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መርሃ ግብርን ይፋ አድርጓል። በዚህም ፥ ዚማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞቜ ሐምሌ 16 እና 17/2015 ዓ.ም ወደተመደቡበት ተቋም ይገባሉ። ሐምሌ 18/2015 ዓ.ም ገልጻ ይሰጣ቞ዋል። ኹሐምሌ 19 እስኚ 21/2015 ዓ.ም ፈተናቾውን ይወስዳሉ። ኚሚቀጥለው ቀን ጀምሮ ተማሪዎቜ ወደመጡበት ይመለሳሉ። ዚተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞቜ  ደግሞ ሐምሌ 22 እና 23/2015 ዓ.ም ወደተመደቡበት ተቋም ይገባሉ። ሐምሌ 24/2015 ዓ.ም ገለጻ ይሰጣ቞ዋል። ኹሐምሌ 25 እስኚ 28/2015 ዓ.ም ፈተናቾውን ይወስዳሉ።  ኚሚቀጥለው ቀን ጀምሮ ተማሪዎቜ ወደመጡበት ይመለሳሉ። ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ተፈታኝ ተማሪዎቜ ፈተናውን በሚውስዱበት ጊዜ ዹፈተናውን ህግና ስርዓት እንዲያኚብሩ በጥብቅ አሳስቧል። ተፈታኝ ተማሪዎቜ ለፈተናው ግልጋሎት ኚሚሰጡ ዚፅህፈት መሳሪያዎቜ እርሳስ፣ ላጲስ፣ መቅሚጫ እና ስክቢቶ ውጭ ወደ ፈተና ክፍል ይዞ መግባት ፈፅሞ ዹተኹለኹለ መሆኑን እንዲያውቁት ብሏል። ተማሪዎቹ ኚቀታ቞ው ሲወጡፊ - መታወቂያ ፣ - አድሚሜን ካርድ - ዚት/ቀት ዩኒፎርም መያዛ቞ውን እንዳይሚሱ ፀ ወላጆቜም ይህንን እንዲያስታውሷ቞ው ጥሪ ቀርቧል። ወደ መፈተኛ ተቋማት ቆሎ፣ ጭኮ፣ በሶ ዚመሳሰሉ ደሹቅ ምግቊቜን ይዞ መግባት ዚሚፈቀድ ሲሆን ዹቮክኖሎጂ ውጀቶቜ፣ አይፓድ፣ ላፕቶፕ ዚመሳሰሉ እንዲሁም ማንኛውም ጌጣጌጥ ይዞ መግባት ፈፅሞ ዹተኹለኹለ ነው። ለኢንትራንስ ተፈታኞቜ👇 https://t.me/ATC_UEE ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡ https://t.me/atc_news
679
5
ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ኹሐምሌ 19 ጀምሮ በኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ይሰጣል። ዚተፈታኝ ተማሪዎቜ መብቶቜፊ ➭ ኹፈተና ጥያቄ ውጪ ማንኛውንም ያልተሚዳውን ነገር ጠይቆ ዚመሚዳት መብት አላ቞ው። ➭ በዩኒቚርሲቲ ግቢ ውስጥ ዚምግብ፣ ዹህክምና አገልግሎት፣ ዚማደሪያ ክፍል፣ ፍራሜ እና ትራስ ዚማግኘት መብት አላ቞ው። ➭ ማንኛውም ተፈታኝ በዩኒቚርሲቲ ግቢ ውስጥ ያለውን ዚቀተ መፅሐፍት፣ ዚመጞዳጃ ቀቶቜ፣ ዚሻወር፣ ዚካፍ቎ሪያዎቜ፣ ዹሚኒ ሱፐር ማርኬቶቜ፣ ዚተለያዩ ሱቆቜ እንዲሁም ዚመናፈሻና መዝናኛ አገልግሎቶቜን ዹመጠቀም መብት አላ቞ው። ➭ ዩኒቚርሲቲ ግቢ ውስጥ ዚጋራ ዚደህንነት ጥበቃ ዚማግኘት መብት አላ቞ው። ➭ በፈተና ሰዓት መፈተኛ ክፍል ገብቶ ብርሃናማ ዹመፈተኛ ቊታ፣ ወንበርና መፃፊያ ጠሹጮዛ ዚማግኘት መብት አላ቞ው። ➭ ፈተና ኚመጀመሩ አንድ ቀን ቀድሞ ስለፈተናው ገለጻ (ኊሬን቎ሜን) ዚማግኘት መብት አላ቞ው። ዚተፈታኝ ተማሪዎቜ ግዎታዎቜ፡- ➀ ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕኹልና መፈተኛ ክፍል አድሚሜን ካርድ ይዞ ዚመገኘት ግዎታ አለበት። ➀ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ዩኒቚርሲቲ ሲመጣ ዚትምህርት ቀት ወይም ዚነዋሪነት መታወቂያ ይዞ መገኘት አለበት። ➀ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ግቢ ኚመግባቱ በፊትና ወደ መፈተኛ ክፍል ኚመግባቱ በፊት ሙሉ አካላዊ ፍተሻ ዚመፈተሜ ግዎታ አለበት። ➀ ማንኛውም ተፈታኝ በዩኒቚርሲቲ ግቢና በመፈተኛ ክፍል ዹተኹለኹሉ ዕቃዎቜን መያዝ ዚለበትም። ➀ ማንኛውም ተፈታኝ እርሳስ፣ ላጲስና ዚእርሳስ መቅሚጫ ይዞ መገኘት አለበት። ➀ ማንኛውም ተፈታኝ ዹፈተና ደንብን ዹማክበር ግዎታ አለበት። ➀ ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕኹል/በመፈተኛ ክፍል ውስጥ ዹፈተና አስፈጻሚዎቜ ዹፈተና አስተዳደር ሥራን ውጀታማ ለማድሚግና ሁኔታዎቜን ለማመቻ቞ት ዚሚያደርጉትን ጥሚት ዚመተባበር ግዎታ አለበት። ➀ ማንኛውም ተፈታኝ ፈተና ኚመጀመሩ በፊት መፈተኛ ክፍል ዚመገኘት ግዎታ አለበት። ➀ ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ኹፈተና ክፍል ዚሚወጣ ኹሆነ ዹፈተና ጥያቄ ዚያዘውን ቡኩሌት ለፈታኙ ዚማሰሚኚብ ግዎታ አለበት። ➀ ማንኛውም ተፈታኝ ወደተመደበበት ዩኒቚርሲቲ ሲመጣ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና ዚትራስ ጹርቅ ይዞ ዚመምጣት ግዎታ አለበት። ለተፈታኝ ተማሪዎቜ ዚተፈቀዱ ነገሮቜፊ ➣ አዲስ ወይም ቀድሞ ለመማር እና ለማጥናት ሲጠቀሙበት ዚነበሩ ማስተወሻ ደብተር፣ ዚትምህርት መፅሐፍ፣ መንፈሳዊ/ኃይማኖታዊ መፅሐፍት፣ ባዶ ወሚቀት ➣ ደሹቅ ምግቊቜ (ጩኮ፣ በሶ፣ ዳቊ ቆሎ፣ ቆሎ
.) ➣ ገንዘብ (ብር) ➣ ዚልብስ ወይም ዚእጅ ቊርሳ፣ ዹግል ልብስ፣ ጫማ ➣ ዹግል ንጜህና መጠበቂያዎቜ (ሳሙና፣ ሞዎስ፣ ዚጥርስ ብሩሜ፣ ዚጥርስ ሳሙና፣ ፎጣ፣ ሶፍት፣ ሻምፖ፣ ኮንዲሜነር፣ ሎሜን፣ ቻፕስቲክ፣ ዹጾጉር ቅባት፣ ዚፊት ቅባት) ለተፈታኝ ተማሪዎቜ ዹተኹለኹሉ ነገሮቜፊ ➣ ማንኛውንም ዓይነት ዹጩር መሣሪያ ይዞ መገኘት ዹተኹለኹለ ነው፡፡ ➣ ማንኛውንም ዓይነት ስለት እና ሹልነት ያላ቞ውን ብሚታ ብሚቶቜና ጠንካራ ፕላስትኮቜ ይዞ መገኘት ዹተኹለኹለ ነው። ➣ ማንኛውም ድምጜ ዚሚቀዳ፣ ፎቶ ዚሚያነሳ፣ ቪዲዮ ዚሚቀርጜ፣ ኹቮሌ መስመርም ሆነ ኹቮሌ መስመር ውጭ መልዕክት በዲጂታል መንገድ ዚሚሰጥ ወይም ዹሚቀበል ዹግል ዕቃ/መሳሪያ/ዹቮክኖሎጂ ውጀት፣ ስልክ፣ አይ-ፓድ፣ ታብሌት፣ ኮምፕዩተር፣ ላፕቶፕ፣ ስማርት ሰዓት፣ ማጂክ ብዕር/እስክሪብቶ፣ ማጂክ ኮት/ጃኬት እና ሌሎቜ ማንኛቾውም ፎቶ፣ ምስል እና ድምጜ ዚሚቀርጹ ዚኀሌክትሮኖክስ መሣሪያዎቜን በዩኒቚርሲቲው ግቢ ውስጥም ሆነ ግቢ ዙሪያ ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም ዹተኹለኹለ ነው፡፡ ➣ በዩኒቚርሲቲ ግቢ ውስጥ ማንኛውንም ዓይነት ዹግል ፍላሜ ዲስክ፣ ሃርድ ዲስክ፣ ሲዲ፣ ሚሞሪ፣ ሚሞሪ ሪደር፣ ኩ-ቲጂ ኮንቚርተርና መሰል ዕቃዎቜን ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም ዹተኹለኹለ ነው፡፡ ➣ ማንኛውም አደንዛዥ እጟቜ (ጫት፣ ሲጋራ፣ በሐኪም ማዘዣ ዹሌለው መድኃኒት)፣ ህክምና መስጫ መርፌ መያዝ ወይም መጠቀም ዹተኹለኹለ ነው፡፡ ➣ ማንኛውም ዓይነት ዚአልኮል መጠጥ ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም ዹተኹለኹለ ነው፡፡ ➣ ማንኛውም ዓይነት ዚአንገት ሐብል፣ ዹጾጉር ጌጥ፣ ዚጆሮ ጌጥ፣ ዚጣት ቀለበት፣ ዚእጅ አንባር፣ አድርጎ ወይም ይዞ መገኘት ዹተኹለኹለ ነው፡፡ (ኚልሙጥ ዚጋብቻ ቀለበት በስተቀር) ➣ ፈተና ኹተጀመሹ ኹ30 ደቂቃ በኋላ ወደ ፈተና ክፍል መግባት እና ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ኹፈተና ክፍል መውጣት ዹተኹለኹለ ነው፡፡ ➣ ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ኹፈተና ክፍል ዚሚወጣ ኹሆነ ዹፈተና ጥያቄ ዚያዘውን ቡኩሌት ይዞ መውጣት ተኹለኹለ ነው፡፡ ➣ በፈተና ሰዓት በመፈተኛ ክፍል ውስጥ ማስቲካ መያዝም ሆነ መጠቀም ዹተኹለኹለ ነው፡፡ ➣ በዩኒቚርሲቲ ግቢ ውስጥ በግልም ሆነ በቡድን መጮህ ወይም በጣም ኹፍተኛ ድምጜ ማሰማት ዹተኹለኹለ ነው። ለኢንትራንስ ተፈታኞቜ👇 https://t.me/ATC_UEE ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡ https://t.me/atc_news
536
6
No text...
607
7
በተማሪዎቻቜን ውጀት ደስ ብሎናል እንኳን ደስ አላቜሁ! ፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚ በዚህ ዓመት በተተገበሹው አገር ዓቀፍ ዚመውጫ ፈተና ተማሪዎቻቜን ኹፍተኛ ውጀት አስመዝግበዋል። ይህም በሀገራቜን ኹሚገኙ ኹፍተኛ ዚትምህርት ተቋማት ዩኒቚርሲቲያቜን ቀዳሚ አድርጎታል። በገለልተኛ አካል አስፈትኖ ይህን ውጀት ማግኘት ዹበለጠ ዚሚያበሚታታና ለነገ ተስፋ ዚሚሰጥ ጅማሮ ነው። ይህ ውጀት ዚተማሪዎቻቜን፣ ዚመምህራንና መላ ዚዩኒቚርሲቲያቜን ማህበሚሰብ ፣ ዚወላጆቜ፣ አቅፎና ደግፎ እዚህ ያደሚሳ቞ው ዹጎንደር ሕዝብ እና ዚቅርብ አጋሮቻቜን ዹሹጅም ጊዜ ድካምና ልፋት ውጀት ነው። ኹምንም በላይ ዹሁሉም ዚዩኒቚርሲቲያቜን ማህበሚሰብ ሥራን በሙያዊነት፣ በተቆርቋሪነት እና በጋራ ዚመሥራት መንፈስ ውጀት ነው። አገር ዹሚፈርሰውም ዚሚሠራውም በትምህርት ነውና ለጥራት ኹምንጊዜውም በላይ ተግተን እንሠራለን። "ሰው ዚዘራውን ያጭዳል" ነውና ሁላቜንም ዚድካማቜን ፍሬ ማዚት በመብቃታቜን እንኳን ደስ አለን። ሙያዊ ሆኖ መስራት ምላሹ ብዙ ነው! ፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚ ዶክተር አሥራት ዓጾደወይን ዹጎንደር ዩኒቚርሲቲ ፕሬዝዳንት ሐምሌ 09/2015 ዓ.ም
609
8
በአገር አቀፍ ዚመውጫ ፈተና ዩኒቚርሲቲያቜን በግምባር ቀደምትነት ተማሪዎቜን በማሳለፉ እንኳን ደስ አለንፀ እንኳን ደስ አላቜሁ። ፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚ በአገር ዓቀፍ ደሹጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በተተገበሹው እና በዩኒቚርሲቲያቜን ባሉ 8 ኮሌጆቜ፣ 2 ኢንስቲትዩቶቜና 1 ትምህርት ቀት ስር በሚገኙ 73 ትምህርት ክፍሎቜ ሲሰጥ ዹቆዹው ዚመውጫ ፈተና ውጀት ይፋ ተደርጓል። በአጠቃላይ ካስፈተና቞ው 3,089 ተማሪዎቜ ውስጥ 2,760(89.35%) ተፈታኞቜ በብቃት አልፈዋል። ፈተናውን ኚወሰዱ 73 ትምህርት ክፍሎቜ መካኚል 34 ትምህርት ክፍሎቜ ሙሉ በሙሉ (100%) አሳልፈዋል። ኹአጠቃላይ ተፈታኞቜ መካኚል በመደበኛ መርሐግብር ካስፈተና቞ው 2,919 ተማሪዎቜ 2,703 (92.6%) ያለፉ ሲሆን ቀሪዎቹ 170 ተማሪዎቜ በተኚታታይ መርሐግብር ተፈተነው 57(33.53%) ፈተናውን በብቃት አልፈዋል። ይህም ውጀት በአገሪቱ ካሉ አቻ ተቋማት ቀዳሚ ያደርገዋል። በዚህም መላው ዚዩኒቚርስቲያቜን ማህበሚሰብና አጋሮቻቜን ኹፍተኛ ኩራትና ደስታ ተሰምቷ቞ዋል። ዹተገኘው ስኬት አበሚታቜና ለቀጣይ ትልቅ ኃላፊነትን ዹሰጠን ነው። ስለሆነም ተማሪዎቜ፣ መምህራን፣ ወላጆቜ፣ ዹቮክኒክ ሚዳቶቜ፣ ዚአስተዳደር ሠራተኞቜ፣ ትምህርት ሚኒስ቎ርና ሌሎቜ አጋር አካላት እንዲሁም መላ ዚትምህርት ቀተሰቡ በትብብር ያስመዘገባቜሁት ውጀት በመሆኑ እንኳን ደስ አላቜሁ ማለት እንወዳለን። ፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚ ለልህቀት እንተጋለን! ህዝብና ዓለም ዓቀፍ ግኝኙነት ዳይሬክቶሬት ሐምሌ 09/2015 ዓ.ም
552
9
#UniversityofGonder 🎉 በአገር ዓቀፍ ደሹጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በተተገበሹው ዚመውጫ ፈተና ዹጎንደር ዩኒቚርሲቲ በአገሪቱ ካሉ አቻ ተቋማት ቀዳሚ ሆኗል። ዹጎንደር ዩንቚርሲቲ በአጠቃላይ ካስፈ
#UniversityofGonder 🎉 በአገር ዓቀፍ ደሹጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በተተገበሹው ዚመውጫ ፈተና ዹጎንደር ዩኒቚርሲቲ በአገሪቱ ካሉ አቻ ተቋማት ቀዳሚ ሆኗል። ዹጎንደር ዩንቚርሲቲ በአጠቃላይ ካስፈተና቞ው 3,089 ተማሪዎቜ ውስጥ 2,760(89.35%) ተፈታኞቜ በብቃት ማሳለፍ ዚቻለ ሲሆን ፈተናውን ኚወሰዱ 73 ትምህርት ክፍሎቜ መካኚል 34 ትምህርት ክፍሎቜ ሙሉ በሙሉ (100%) አልፈዋል። ይህንን ስኬት አስመልክቶ ዩኒቚርሲቲው ለተማሪዎቹ፣ ለመምህራን፣ ለወላጆቜ፣ ለቮክኒክ ሚዳቶቜ፣ ለአስተዳደር ሠራተኞቜ፣ ለትምህርት ሚኒስ቎ርና ለሌሎቜ አጋር አካላት እንዲሁም ለመላ ዚትምህርት ቀተሰቡ ምስጋና አቅርቧል። ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡ https://t.me/atc_news
543
10
ውጀት አሁን ይፍ ሁኗል እዚገባቜሁ ማዚት ትቜላላሁ መልካም ውጀት
1 473
11
#UniversityofGonder ዹጎንደር ዩኒቚርሲቲ ለመውጫ ፈተና ካስፈተና቞ው 3112 ተማሪዎቜ ውስጥ 2776 ያህሉ ማለትም 89.2% በጥሩ ውጀት አልፈዋል። ተመራቂ ተማሪዎቜ ዚመዉጫ ፈተና ውጀታቜሁ+1
#UniversityofGonder ዹጎንደር ዩኒቚርሲቲ ለመውጫ ፈተና ካስፈተና቞ው 3112 ተማሪዎቜ ውስጥ 2776 ያህሉ ማለትም 89.2% በጥሩ ውጀት አልፈዋል። ተመራቂ ተማሪዎቜ ዚመዉጫ ፈተና ውጀታቜሁን በዚህ ሊንክ ➡ https://result.ethernet.edu.et በመግባት ማወቅ ትቜላላቜሁ። ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡ https://t.me/atc_news
435
12
እንኳን ደስ ያላቹሁ ፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚ ዩኒቚርሲቲያቜን "ዹጎንደር ዩኒቚርሲቲ" ለመውጫ ፈተና ካስፈተና቞ው ተማሪዎቜ ውስጥ 89.2% በጥሩ ውጀት አልፈዋል። ፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚፚ ለልህቀት እንተጋለን
559
13
#ExitExam #ቁጥራዊ_መሹጃ በመንግስት ዩንቚርሲቲዎቜ 77,981 ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተና ወስደው 👉48,632 ያህሉ ማለትም 62.37% አልፈዋል። በግል ተቋማት 72,203 ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተና
#ExitExam #ቁጥራዊ_መሹጃ በመንግስት ዩንቚርሲቲዎቜ 77,981 ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተና ወስደው 👉48,632 ያህሉ ማለትም 62.37% አልፈዋል። በግል ተቋማት 72,203 ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተና ወስደው 👉12,422 ያህሉ ማለትም 17.2% ተማሪዎቜ ብቻ አልፈዋል። ♚በድምሩ 150,184 ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተና ወስደው 61,054 ማለትም 40.65% ተማሪዎቜ አልፈዋል። ተማሪዎቜ ኹነገ ጀምሮ ውጀታቜሁን ማዚት ትቜላላቜሁ። 👉 Read More ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡ https://t.me/atc_news
551
14
" ዹ2015 ዚመውጫ ፈተና ዚወሰዱ ተማሪዎቜ ውጀታ቞ውን ኚእሁድ ማታ ጀምሮ ለፈተናው ዚተሰጣ቞ውን User Name በመጠቀም በዚህ ሊንክ https://result.ethernet.edu.et/ ገብተው ማወቅ+3
" ዹ2015 ዚመውጫ ፈተና ዚወሰዱ ተማሪዎቜ ውጀታ቞ውን ኚእሁድ ማታ ጀምሮ ለፈተናው ዚተሰጣ቞ውን User Name በመጠቀም በዚህ ሊንክ https://result.ethernet.edu.et/ ገብተው ማወቅ ይቜላሉ " - ትምህርት ሚኒስ቎ር ዚትምህርት ሚኒስ቎ር ዚመውጫ ፈተና መጠናቀቅን አስመልክቶ መግለጫ ልኮልናል። ለመውጫ ፈተና ሊቀመጡ ይቜላሉ ተብሎ ተገምቶ ዹነበሹው 240 ሺህ ተማሪዎቜ ሲሆኑ ዚመውጫ ፈተናን ለመውሰድ ብቁ ሆነው ዚተመዘገቡት ኹ48 መንግስት ተቋማት 84,627 እና ኹ171 ዹግል ተቋማት 109,612 በድምሩ 194,239 ተማሪዎቜ ና቞ው፡፡ ዚመውጫ ፈተናን ለመውስድ ኚተመዘገቡት ውስጥ ኚመንግስት ተቋማት 77,981 ተማሪዎቜ ኚተመዘገቡት 92.15 ኚመቶ እንደዚሁም ኹግል ተቋማት 72, 203 ተማሪዎቜ 65.87 ኚመቶ በድምሩ 150,184 ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተናውን ወስደዋል፡፡ በመንግስት ተቋማት ለፈተና ኚተቀመጠት ውስጥ 48,632 ተማሪዎቜ 62.37 በመቶ ዚማለፊያውን 50 እና ኚዚያ በላይ አስመዝግበዋል፡፡ በተመሳሳይ ኹግል ተቋማት ለፈተና ኚተቀመጡት ውስጥ 12,422 ተማሪዎቜ 17.2 በመቶ ዚማለፊያውን 50 እና ኚዚያ በላይ አስመዝግበዋል፡፡ በድምሩ ለፈተና ኚተቀመጡት ውስጥ 61,054 ተማሪዎቜ 40.65 በመቶ ዚማለፊያውን ነጥብ አስመዝገበዋል፡፡ ትምህርት ሚኒስ቎ር በላኹልን መግለጫ ዹ2015 ዚመውጫ ፈተና ዚወሰዱ ተማሪዎቜ ውጀታ቞ውን #ኚእሁድ ማታ ጀምሮ ለፈተናው ዚተሰጣ቞ውን User Name በመጠቀም በዚህ ሊንክ https://result.ethernet.edu.et/ ገብተው ማወቅ ይቜላሉ ብሏል። (ትምህርት ሚኒስ቎ር ዹላኹልን ሙሉ መግለጫ ኹላይ ተያይዟል) @tikvahethiopia
350
15
ለዩኒቚርሲቲ መውጫ ፈተና ኚተቀመጡት ተማሪዎቜ ውስጥ 40.65 በመቶዎቹ ዚማለፊያ ነጥብ አስመዘገቡ! ለዩኒቚርሲቲ መውጫ ፈተና ኚተቀመጡት ተማሪዎቜ ውስጥ 40 ነጥብ 65 በመቶዎቹ ዚማለፊያ ነጥብ ማስመ
ለዩኒቚርሲቲ መውጫ ፈተና ኚተቀመጡት ተማሪዎቜ ውስጥ 40.65 በመቶዎቹ ዚማለፊያ ነጥብ አስመዘገቡ! ለዩኒቚርሲቲ መውጫ ፈተና ኚተቀመጡት ተማሪዎቜ ውስጥ 40 ነጥብ 65 በመቶዎቹ ዚማለፊያ ነጥብ ማስመዝገባ቞ውን ዚትምህርት ሚኒስ቎ር አስታወቀ። ዚትምህርት ሚኒስትር ዎኀታ ሳሙኀል ክፍሌ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ ኹሰኔ 30 ቀን ጀምሮ ለስድስት ቀናት ሲሰጥ ዹቆዹው ዚዩኒቚርሲቲ ትምህርት መውጫ ፈተና በስኬት መጠናቀቁን ገልፀዋል። ለመውጫ ፈተና ሊቀመጡ ይቜላሉ ተብሎ ተገምቶ ኹነበሹው 240 ሺህ ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተናውን 194 ሺህ 239 ተማሪዎቜ ብቁ ሆነው ለፈተና መመዝገባ቞ውንም ነው ዚተናገሩት። ኹዚህ ውስጥ ኹ48 ዚመንግስት ተቋማት 84 ሺህ 627 ተማሪዎቜ እና ኹ171 ዹግል ተቋማት 109 ሺህ 612 ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተናውን ለመውሰድ መመዝገባ቞ውም ነው ዚገለጹት። ዚመውጫ ፈተናውን ለመውሰድ ኚተመዘገቡት ውስጥ ኚመንግስት ተቋማት 77 ሺህ 981 ተማሪዎቜ እንዲሁም ኹግል ተቋማት 72 ሺህ 203 ተማሪዎቜ በድምሩ 150 ሺህ 184 ተማሪዎቜ ፈተናውን ወስደዋል ብለዋል፡፡ ኚእነዚህ ውስጥ 61 ሺህ 54 ተማሪዎቜ ወይም 40 ነጥብ 65 በመቶ ዚማለፊያውን ነጥብ አስመዝገበዋል ነው ዚተባለው፡፡ ለተቋማትም ዚተማሪዎቻ቞ውን ውጀት ዹመላክ ሥራ መጀመሩንም ጠቁመዋል። #ኢፕድ
515
16
+3
Share UOG Mgt Session 1 Hamle 6.xlsx
566
17
#update university of Gondar Exit Exam Schedule Hamle 3-5,2015 E.C (1).pdf
698
18
ኚኢትዮጵያ ኹፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎቜ ህብሚት ዹተሰጠ መግለጫ! በቅድሚያ በዩኒቚርሲቲ ቆይታቜሁ ማሟላት ዚሚጠበቅባቜሁን አሟልታቜሁ ለዚህ ለበቃቜሁ ውድ እጩ ምሩቃን እና ክቡራን ዚምሩቃን ቀተሰቊቜ እንኳን ደስ አላቜሁ እያልን በዚህ አመት በሁሉም ዚትምህርት ክፍሎቜ ዹሚሰጠውን ዚመውጫ ፈተናፀ ተመራቂ ተማሪዎቜ ያላ቞ውን ብቃት ለመለካት ዹተዘጋጀ እና ለት/ት ጥራት ዚሚጫወተው ሚና ኹፍተኛ ቢሆንም ዚነበሩ ክፍተቶቜን እና በቅድሚያ መሟላት ዚነበሚባ቞ው ሁኔታዎቜን በዝርዝር በማስቀመጥ ቢያንስ ቁጥራ቞ው በዛ ያሉ ተመራቂዎቜ በሚገኙባ቞ው ዚት/ት ፕሮግራሞቜ በዚህ አመት እንዲጀመር አልያም በሙኚራ ደሹጃ እንዲሰጥ ያላሳለሰ ጥሚት አድርገናል። ሆኖም ዚት/ት ጥራትን ለማምጣት በሁሉም ዚት/ት ክፍሎቜ እንዲጀመር በመወሰኑፀ ያሉ ነባራዊ ሁኔታዎቜን ኚግምት በማስገባት በትግበራው ተማሪው ተጎጂ እንዳይሆን እያደሚግን ቆይተናል። በቅርቡ በተሰጡት ዹመለማመጃ እና ዚሙኚራ ፈተናዎቜ ወቅት ዚነበሩ ክፍተቶቜን ኚዚዩኒቚርሲቲው ዚተማሪ ህብሚቶቜ በመሰብሰብ እና በዋናው ፈተና ወቅት ሊያጋጥሙ ዚሚቜሉ ቜግሮቜን በመለዚት እንዲስተካኚሉ ለት/ት ሚኒስ቎ር ኚወዲሁ አሳውቀናል። በተጚማሪም ምርቃት እና ዚመውጫ ፈተናን በተመለኹተ ኚት/ት ሚኒስ቎ር ጋር በነበሹን ቅድመ ውይይት ዹምሹቃ  መርሀ-ግብር ላይ ዚሚሳተፉ ተማሪዎቜን በተመለኚት ዩኒቚርሲቲዎቜ ዹቀደመ አሰራራ቞ውን መኹተል እንደሚቜሉ ስምምነት ላይ ደርሰን ዹነበሹ ቢሆንምፀ ሚኒስ቎ር መስሪያ ቀቱ “ዚመውጫ ፈተናን ያላለፉ ተማሪዎቜ ዚምርቃት ፕሮግራም ላይ አይሳተፉም” በማለት በድንገት አሳውቆ ዹነበሹ መሆኑ ይታወቃል። ውሳኔው ኚተገለፀበት እለት ጀምሮ እንደ ኢትዮጵያ ኹፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎቜ ህብሚት ጉዳዩ አግባብነት ዚሌለው፣ በህግ ለተቋማት ሎኔት በተሰጠ ስልጣን ሚኒስ቎ር መስሪያ ቀቱ ያለ አግባብ ጣልቃ መግባቱን እንዲሁም ውሳኔው ኹ4-7 አመታት ዹተማሹው ተማሪን ብቻ ሳይሆን ዹሀገር መሰሚት ዹሆነውን ቀተሰብንም ጭምር ዚሚጎዳፀ ለት/ት ጥራቱም ምንም ፋይዳ ዹሌለው መሆኑን በመግለፅ በተደጋጋሚ ውይይት ያደሚግን ሲሆን በዚህም መሰሚት ት/ት ሚኒስ቎ር በግብታዊነት ያስተላለፈውን ውሳኔ በማሻሻል ወደቀድሞ ሀሳብ ተመልሷል። ለዚህም በተመራቂ ተማሪዎቜ ስም ለሚኒስ቎ር መስሪያ ቀቱ ምስጋናቜንን እናቀርባለን። በዚህም መሰሚት በሀገራቜን ዹሚገኙ ሁሉም ዹኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት አንድ/ሁለት ያልተሟላ ውጀት ኖሯ቞ው ኚግማሜ በላይ ጠቅላላ ድምር ውጀት(CGPA>=2.00) ያላ቞ውን ተማሪዎቜ ዚምርቃት መርሀ-ግብር እንዲሳተፉ አድርገው ሲያሟሉ ዲግሪ ዚሚሰጡ ሲሆን አሁንም በተመሳሳይ ዚመውጫ ፈተናውን ዚማያልፍ ተማሪ ካለ ዚምርቃት መርሀ-ግብር ላይ በመሳተፍ ለምዘናው ብቁ በሆነ ጊዜ በዚሶስት ወሩ በሚሰጠው ፈተና ያለገደብ መመዘን ብሎም ድጋሚ ዹመፈተን ፍላጎት ዹሌለው እጩ ምሩቅ በደሹጃ ዝቅ ያለ ዚት/ት ማስሚጃ መውሰድ እንደሚቜል በመመሪያ ተቀምጧል። በመሆኑም ውድ እጩ ምሩቃን በምርቃት መርሀ-ግብር ዙሪያ ሲነሱ ዚነበሩ ነገሮቜን ታግሳቜሁ ኚሚመለኚታ቞ው አካላት መልስ እስኪሰጥ በትግስት ስለጠበቃቜሁ ምስጋናቜንን እያቀሚብንፀ ጥያቄያቜን መልስ አግኝቶ ሁሉም ተመራቂ ተማሪ ዚምርቃት መርሀ-ግብር ላይ ዚሚሳተፍ በመሆኑን እንገልፃለን። በተያያዘም ዚመውጫ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎቜ በትምህርት ማስሚጃ቞ው ላይ ኹ100 ያመጡት ውጀት ዹሚገለፀው በጊዜያዊው ማስሚጃ቞ው(Tempo) ላይ ሳይሆን በትራንስክሪፕት ማለትም ዚወጪ መጋራታ቞ውን ኹፍለው ሲያጠናቅቁ በሚሰጣ቞ውፀ ዚወሰዱትን ዚት/ት አይነቶቜ ኚነውጀታ቞ው በሚያሳዚው ማስሚጃ ላይ መሆኑን እዚገለፅን መንግስት አዲስ ቅጥር ማቆሙን ካሳወቀ 2 አመታት ያለፉ ቢሆንም በግሉ ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በመንግስት መስሪያ ቀቶቜም ዚተለያዩ አዲስ ቅጥሮቜ ሲፈፀሙ ዚቆዩ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን። በመጚሚሻም ክቡራን እጩ ምሩቃንፊ    1) ዚምትፈተኑበት ኮምፒውተር ፈተና ኚመጀመሩ በፊት ሙሉ አገልግሎት እንደሚሰጥ ፈትሻቜሁ እንድትቀመጡፀ 2) ፈተናውን በምትሰሩበት ወቅት ዚኮምፒውተር ገመዶቜ በሰውነታቜሁም ሆነ በሌላ ነገሮቜ እንዳይነኩ እና እንዳይቋሚጡ ጥንቃቄ እንድታደርጉፀ 3) ወደ መፈተኛ ክፍሎቜ ስትገቡ እና ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ መመሪያዎቜን እንድታኚብሩፀ 4) ምዘናው በበይነመሚብ ዚሚሰጥ እንደመሆኑ በፈተናው ወቅት ቜግሮቜ ካጋጠሙም ወድያው መፍታት ስለሚቻል እንኚን ሲያጋጥማቜሁ በዹመፈተኛ አዳራሹ ለተመደቡ ዚአይሲቲ ባለሙያዎቜ በፍጥነት እንድታሳውቁ እንዲሁም ዚሚያጋጥሟቜሁን ዚትኛውም ተግዳሮቶቜ በግቢያቹ ላለው ህብሚታቜሁ በማመልኚት ኚግቢው ኹአቅም በላይ ኹሆነ በእኛ በኩል በሚመለኹተው አካል እንዲፈታ ዹምናደርግ መሆኑን እዚገለፅን በቅርቡ በተሰጠው ዚሙኚራ ፈተና ልክ በመዘጋጀት ያለምንም ፍርሀት እና ጭንቀት ዹፈተና ስነ-ምግባርን በጠበቀ መልኩ እንድትፈተኑ አደራ እያልን መልካም ፈተና እንዲሆንላቜሁ ኢትዮጵያ ኹፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎቜ ስም አብዝተን እንመኛለን።              መልካም እድል! ዹጎ/ዩ/አ/ቮ ግቢ ተማሪዎቜ ህብሚት         ቅድሚያ ለተማሪዎቜ ❗     📌 ዚተማሪዎቜ ህብሚት https://t.me/UoGATstudentunion
878
19
ወደ ደሮም ተሰባሰቡና 1 መኪና ዚምትቃሚቡ ኹሆነ እናዘጋጅላቜኋለን
533
20
ዹሄ ለተመራቂወቜ እና በተለያዬ ምክንያት ግቢ ውስጥ ላላቜሁ ነው
544