cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Orthodox twahdo💒✝️✝️

Advertising posts
198
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ለኔስ እናቴ እመቤቴ ክብሬ ነሽ እና ግቢ ቤቴ ☺️🙏 #Share 💚 @orthodox_photo💚 💛 @orthodox_photo💛 ❤️ @orthodox_photo❤️
Show all...
"…በጽዮን መለከትን ንፉ፥ ጾምንም ቀድሱ፥ ጉባኤውንም አውጁ፥ ሕዝቡንም አከማቹ፥ ማኅበሩንም ቀድሱ፥ ሽማግሌዎቹንም ሰብስቡ፥ ሕፃናቱንና ጡት የሚጠቡትን አከማቹ ሙሽራው ከእልፍኙ፥ ሙሽራይቱም ከጫጉላዋ ይውጡ። …የእግዚአብሔርም አገልጋዮች ካህናት ከወለሉና ከመሠዊያው መካከል እያለቀሱ፦ አቤቱ፥ ለሕዝብህ ራራ፥ አሕዛብም እንዳይነቅፉአቸው ርስትህን ለማላገጫ አሳልፈህ አትስጥ፤ ከአሕዛብ መካከል፦ አምላካቸው ወዴት ነው? ስለ ምን ይላሉ? ይበሉ። ኢዮኤ 2፥ 15-17 "…እንደምን አደራችሁ? "…እንደምን አረፈዳችሁ? "…እንደምን ዋላችሁ? "…እንደምን አመሻችሁ? "… መልሱ እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼
Show all...
#ተፈቷል❗️ የማንቂያ ደወል ሚዲያ ባለቤት መምህር ምህረትአብ አሰፋ ዛሬ ከዕስር መፈታቱ ታውቋል። @ortodoxtewadochannal @ortodoxtewadochannal
Show all...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሦስቱ አባቶች መመለስ ታላቅ ደስታ ተሰምቷታል " - ቅዱስ ሲኖዶስ ከቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ውስጥ የተወሰደ ፦ " ... በዛሬው ዕለት የቤተ ክርስቲያን ጸሎቷ፣ ሐዘኗና ጩኸቷ ተሰምቶ ወደ ነበረችበት ልዕልናዋና አንድነቷ ተመልሳለች፡፡ ይህ አንድነቷና ልዕልናዋ እስከ ዓለም ፍጻሜ ተጠብቆ ይኖራል፡፡ በቅርቡ በቤተ ክርስቲያናችን ተከስቶ የነበረው ችግርም በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት ተፈትቷል፡፡ ... በችግሩ አፈታት ወቅት መንግሥት በተለይም ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ፖለቲካዊ ችግሩን በፖለቲካዊ መንገድ ከመፍታታቸውም ባሻገር የቤተ ክርስቲያን ችግር በቀኖናና በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን መሠረት እንዲፈታ ታላቁን አስተዋጽኦ አበርክተዋል፡፡ ክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ቀደም ሲል ሁለቱን ሲኖዶስ አንድ በማድረግ ያደረጉትን አስተዋጽኦ አሁንም የቤተ ክርስቲያን አንድነት ተጠብቆ እንዲኖር ላደረጉት መልካም ተግባር ቤተ ክርስቲያን ከልብ ታመሰግናለች፡፡ ... ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሦስቱ አባቶች መመለስ ታላቅ ደስታ ተሰምቷታል፡፡ ካህናት፣ ምእመናን በሀዘናችን ተካፋይ የነበራችሁ በሙሉ የዚህ ደስታ ተካፋዮች በመሆናችሁ እንኳን ደስ ያላችሁ በማለት ቅድስት ቤ ክርስቲያን ደስታዋን ትገልጻለች፡፡ " @tikvahethiopia
Show all...
#ከኢንሳ_የመጣ_አዲስ_መረጃ…! "…ዘመዴ እንደምንም ብለህ ይሄን መረጃ ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት እና ለሕዝቡ አድርስ። መንግሥት በቅዱስ ሲኖዶስ አባቶች እና በአንተ ላይ ዶክመንተሪ እንዲሠራ አዟል። በአባቶች ላይ የውሸት ድምጽ ማስመሰል ሊሠራ ያቀደ ሲሆን ሲሠራም 2 ዋና ዋና ነገሮችን አስቦ ነው። 1ኛ፥ ለማኅበረሰቡ በውሸት እነዚህ አባቶች የፖለቲካ ንክኪ አጀንዳ እንዳሏቸው ለማስረዳት፥ 2፥ የኦሮሞን ህዝብ እንደሰው እንደማይቆጥሩት የሚያሳይ ድምጽ ለማውጣት ነው። "…በዚህም የታሰበው በማኅበረሰቡ ብቻ ሳይሆን የሲኖዶሱ አባቶች እርስ በእርሳቸው መተማመን እንዲያጡ ለማድረግ የታሰበ ነው። እናም ስልክ ደግሞ 100% በኢትዮቴሌኮም የፎቶጋለሪ ሳይቀር መመልከት ይችላሉ። እንዲህ መጠቀም ከጀመሩ 1 አመት አልፏቸዋል። "…የInsa cyber security specialist ከሰለሞን ሶካ የ insa director encrypted መልዕክት ተልኳል። ይህም የቅዱስ ሲኖዶሱ አባላት አባቶች እንዲሁም የሃይማኖት ተቆርቋሪዎች accounts check እንዲያደረጉ፣ እንቅስቃሴያቸው እንዲጠና፣ እንዲሁም የማኅበረሰብ አንቂዎች ጭምር እንዲበረበር፣ ከዚያውስጥ ደግሞ ዘመዴ ላይ Documentary ለመሥራት Vulnerability እየፈለጉ ነው። በቅርቡም በአቡነ ማቲያስና በአቡነ አብርሃም ላይ የተሠራ voice over ለማኅበረሰቡ ለማውጣት በዝግጅት ላይ ናቸው። "…በቀደም ዕለት በእነ አካለወልድ የተሰጠው መግለጫ ተመልክቶ ከመግለጫው በፊት እነ ሽመልስ አብዲሳ የነገሯቸው ነገር "እኛ ውስጥ ውስጡን እንጨርሰዋለን እናንተ ግን ግፉበት። ወደ ኋላ የሚል በህይወቱ ላይ እንደፈረደ ይቁጠር። አንዴ ገብተንበታል ዳር ሳናደርስ አንመለስም። የብልፅግናን ፈጥረን ወደ አራት ኪሎ የመጣነው በዚሁ መንገድ ነው። አዲሲቱን ኦሮሚያ ለመፍጠር በሚደረገው ሂደት ላይ የእናንተ ድርሻ ቀላል አይደለም። በርቱ ነበር ያላቸው። ከኢትዮጵያ ጋር አብሮ መኖር ካልተቻለ ዐማራን ለትግሬና ለሱዳን ሰጥተን፣ ሱማሌ ወደ ፈለገበት እንዲሄድ አድርገን፣ ደቡብን ከእኛ ጋር ቀላቅለን በኃይ ግማሽ ደቡብ ወሎን እና አዲስ አበባን ጨምሮ ይዘን መገንጠል ነው።" ይሄ ሕገ መንግሥታዊ መብታችን ነው። ማንም አያስቆመንም። ምንም አትስጉ ነው ያላቸው። መነኩሴዎቹ አሁን ታግተው ነው ያሉት። "…ዘመዴ Voice over ን በተመለከተ እንደምንም ብለህ ለቅዱስ ሲኖዶሱም ለኅበረተሰቡም ቀድመህ ማድረስ አለብህ። መንግሥት ቅዱስ ሲኖዶሱን ከህዝቡ ለመነጠል እንደ ዋነኛ መንገድ ነው ሊጠቀመው ያሰበው። ይህም ስል የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት አባቶች በኩራት እንዳይቃወሙት አንገት ማስደፊያ ነው። መረጃው ቀድሞ ከወጣ የጨጓራ በሽተኞች ከመሆን በዘለለ ምንም አባታቸው አያመጡም። የሚገርምህ እኔ ሃይማኖቴ አይደለም። ነገር ግን ሰዎቹ ሊፈጥሩ ያሰቡት ምስቅልቅል ስላሳሰበኝ ነው። በአሁን ወቅት ደግሞ በጣም የምት ሰማው እና ታማኝ የመረጃ ምንጭ ስለሆንክ ብዬ ነው ወዳንተ መምጣቴ። "…በአጠቃላይ ስለዚህ ሥራ የሚያውቁ ሰዎች 3 የኮምፒዩተር ስፔሻሊስቶች፣ አንድ ስሙን ከሰሞኑ ስሙን የምነግርህ አርቲስት የድምጽ የአባቶችን ድምፅ የማስመሰሉን ሥራ እንዲሠራ ተመርጧል። አርቲስቱን በፎቶ እሰጥሃለሁ። አርቲስቱ ያስመሰለውን የአባቶች ድምጽ ወደ ኮምፒዩተራቸው አስገብተው ነው በስልክ እንደተነጋገሩ የሚያስመስሉት። ንግግሩ ኦሮሞን የሚያንቋሽሽ አድርገው እንዲሠራ ነው የታዘዘው። ድምፁ ከተሠራ በኋላ አርቲስቱ ይገደላል ወይ መርፌ ወግተው ያጀዝቡታልም ተብሏል። አዛዡ ሰለሞን ሶካ እና ከሱ በላይ ያሉ ሰዎች ናቸው። "…አንተን በተመለከተ ኢንተርኔት ላይ ባለህ እንቅስቃሴ የተውካቸውን ኮቴዎች ተከተለው አካውንት መጥለፍ ሲሆን፣ በዚያም ሳታውቅባቸው የሚችሉትን ያህል መረጃ መውሰድ ነው። ካልቻሉ ደግሞ ሶሻል enginering የሚባለውም ቴክኒክ በመጠቀም ነው ሊመጡብህ ያሰቡት። በዚህም ወዳጅ መስለዉ መረጃው መመዝበር ነው። ከዛ በራስህ መረጃ documentary ሠርተው ያንተ ተከታዮች ላይ conspiracy መፍጠር። ይሄን ካሳካን ቢያንስ እንደ ጉድ ከሚከተሉህ ሰዎች ከብዙ ሚልዮኖቹ ቢያንስ ግማሽ የሚሆነው ሰው ከአንተ መራቅ ነው የፈለጉት። "…ያንተከትሎ ከዚያ በኋላ በዋና ዋና መገናኛ ብዙሃን ሚዲያዎች የሠሩትን documentary አንተን ለኢትዮጵያ ሕዝብ እንደ አሸባሪ ማሳየት ነው የፈለጉት። በዚህም ዋና ዓላማው አንተን በወንጀለኛ፣ በዘር አጥፊነት ለመፈረጅ ነው። ጭቅጭቅ ነበረባቸው። ልጁ ለዚህ ፍረጃ አይመችም የሚል ነገር ተነሥቶም ነበር። ነገርግን አቶ ሰሎሞን ሶካ ይገባናል ነገርግን ሌላ የተሻለ ምርጫ የለንም ስለዚህ በዚሁ ግፉበት የሚል መመሪያ ሰጥቷቸዋል። "…ዛሬ voice over እንዲሰሩ ከታዙት መካከል ከinsa ፕሮጀክቶች በሙሉ ወደ እኛ ወደ ኦሮምያ ደኅንነት ቢሮ እንዲመጡ ተደርጓል። በኦሮሚያ ደህንነት ቢሮ እንዲሠራ የተፈለገው አቶ ተመስገን በሚሠራው የደኅንነት ቢሮ መተማመን በማጣታቸውና ዐማሮቹ እንደ ፓርቲም፣ እንደ ክልልም ለእኛ ለኦሮሚያ ብልጽግና የሚያሳዩት እንቅስቃሴ እጅግ መተማመን ስለጠፋበት ነው። አቶ ደመቀ ከእነ አቢይ ያፈነገጠ ይመስለኛል። አቶ ተመስገንም በጎጃሜዎቹ የተጠለፈ ነው ብለው አያምኑትም። በመከላከያውም ስንጥቃት አለ። የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ በአባቶች ጥበብ አለፈ እንጂ ከህዝቡ ይልቅ ጦሩ ነበር የሚፋጀው። "…በኦሮሚያ ደኅንነት ቢሮ የሚሠሩት ከቱርክ ተምረው የመጡ እንዲሁም የቀድሞ insa ላይ የነበሩ ሰዎች ናቸው። አንተ አሁን መረጃውን ለማኅበረሰቡ እና ለቅዱስ ሲኖዶሱ አሳውቅ። ዘመዴ ፍጠን ትናንት ምሳ ሰዓት ላይ ሙሉ ለሙሉ ፕሮጀክቶቹን በአጠቃላይ ወደ እኛ ኦሮሚያ ደህንነት ቢሮ መጥቷል። ሁሉም ያነቡሃል። ግትርነትህን፣ ሃቅህን ይወዱታል፣ እልህህ ደስስ ይላቸዋል። የሚጠሉት ሴራቸውን ስለምታፈራርሰው ነው። በፊት በፊት ጓደኛህ ስለሆነ ዳንኤል ክብረት ነው መረጃ የሚሰጠው ብለው ይሟገቱ ነበር። አሁን አሁን ግን በተለይ ዳንኤል ላይ ከጻፍክ በኋላ ስለ ዳንኤል እንደ አዲስ መረጃ ካንተ ስላገኙ በአንተ ላይ ክትትልና የመረጃ ምንጮችህን ለማወቅ እንቅልፍ አጥተዋል። ነገር ግን ምንም ዱካ ሊያገኙ አልቻሉም። የአንስ ልዩ ነው። በርታ ዘመዴ። ህዝቡ አስቀድሞ ተጠንቅቆ እንዲጠብቅ አንተ ይሄን ቀድመህ አውጣሁ። "…ስላለኝ አውጥቼዋለሁ። እኔን በተመለከተ ግን በ email የምጻጻፈው ከጀርመን መንግሥት ለሥራ ጉዳዮች ብቻ ነው። ለማንም በኢሜል መልስ ሰጥቼ አላውቅም። ሲበረብሩ ውለው ቢያድሩ የሚጣሉት ከጀርመን መንግሥት ጋር ነው። በተረፈ በስልኬ ላይ የሚቀመጥ ምንም የተለየ ነገር የለኝም። የማገኛቸውን መረጃዎች ሃገር የሚያፈርሱትን በመደበቅ ነው በስሱ እንዲደነግጡ፣ ንስሀም እንዲገቡ የምለቅላቸው። የብዙዎቹን ነውር ሁላ ደብቄያለሁ። እነሱ አሸባሪ ሲሉኝ እኔ ደግሞ እየቀፈፈኝ ገመድ ፈልገው ይታነቁ ዘንድ የሚያደርጋቸው መረጃዎችንም እለቃለሁ። "…ቆይቼ የአስተያየት መስጫ ሰንዱቁን እከፍትላችኋለሁ። #ShareThisPost በቴሌግራም 👇 t.me/DebteraMedia
Show all...
ሰበር ዜና በሕገ ወጡ ቡድን የጵጵስና ልብስ አልብሶ ሾሜዎታለሁ ካላቸው መነኮሳት መካከል ከኢየሩሳሌም የመጡት "አባ" ንዋየሥላሴ አክሊሉ ቅዱስ  ሲኖዶስ የሰጠውን ዕድል በመጠቀም በመንበረ ፓትርያርክ በመገኘት አስኬማቸውንና አርዌ በትሩን ለሕጋዊዋ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በማስረከብ ቤተክርስቲያንንና ምእመናንን ይቅርታ ጠይቀዋል። በይቅርታ ደብዳቤያቸውም ሰሞኑን በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ከቅዱስ ሲኖዶሱ እውቅና ውጪ አዲስ ኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ሲካኼድ ከኢየሩሳሌም መጥቼ ከተሾሙት አንዱ ነበርኩ። በዚህ ምእመናንን ባሳዘነ ቅዱስ ሲኖዶስ ቃለ ውግዘት ባስተላለፈበት ሕገ ወጥ ሢመት ውስጥ ባለማወቅና ነገሩን ሳላጣራ የገባሁበት በመሆኑ በእጅጉ የተጸጸትኩና በዚህም ተግባር ያዘንኩ መሆኔን በይቅርታ ልብ ለመግለጥ እወዳለሁ። በመሆኑም በዛሬው ዕለት ቅዱስ ሲኖዶስ በሠየመው አቀራራቢና በይቅርታ ኮሚቴ አማካኝነት በቅዱስ ሲኖዶሱ ውሳኔ መሠረት በተከፈተው የይቅርታና የምሕረት በር ወደ እናት ቤተክርስቲያኔ እና የመንፈስ ቅዱስ አባቶቼ እንዲሁም ምእመናን ለይቅርታ የቀረብኩ ስለሆነ ቋሚ ሲኖዶሱ በምልዓተ ጉባኤው ውሳኔ መሠረት ይቅርታዬን በአባትነት መንፈስ ይቀበለኝ ዘንድ በታላቅ ትህትና እጠይቃለሁ ብለዋል ። EOTC TV @ortodoxtewadochannal @ortodoxtewadochannal
Show all...
ሰበር ዜና ብፁዑ አቡነ ናትናኤል «መንግስት ቃሉን የማያከብር ከሆነ፣ በቤተክርስቲያን ድርድር ስለሌለ ምዕመናን ልጆቻችን በተጠንቀቅ በመቆም አይናቸውን ቤተክርስቲያን ላይ ጆሯቸውን ወደ ቅዱስ ሲኖዶስ አድርገው የአባቶችን ድምፅ ይጠብቁ» በማለት አሁን ቀጥታ እየተላለፈ ባለው መግለጫቸው አስጠነቀቁ!
Show all...
መምህር ምሕረተአብ አሰፋ እና የማንቂያ ደውል አገልጋዮች ዲ/ን አማኑኤል አያሌው እንዲሁም ዲ/ን ኪሩቤል አሰፋ በዛሬው ዕለት ታስረዋል ! #Share 💚 @orthodox_photo💚 💛 @orthodox_photo💛 ❤️ @orthodox_photo❤️
Show all...
መረጃ በሀገራችን የሀይማኖት አባቶች ከፍ ያለ ክብር አላቸው። ሼክ ይሁን ቄስ፣ ነብይ ይሁን መምህር ዝቅ ተብሎ ሰላም መስጠት ያደግንበት ነው፣ እንዲህ አይነት በጥፊ የሚማታ ጋጠወጥ ግን አይተንም አናውቅ። የምታውቁት ሰዎች ካላችሁ [ምናልባት ፍትህ ከተገኘ] ለፀጥታና ፍትህ አካላት አሳውቁ። ነውሩን መሸፋፈን ሳያስፈልግ ጠቁሙ። EliasMeseret አዎ ይታወቃል ብዙ በካሜራ ያልተቀረፁ ነውሮች ተፈፅመዋል ግን ቢያን መረጃ ያለንን እናጋልጥ። ይሄ ሰውዬ ለፍርድ እስኪቀርብ ሼር አድርጉት!! ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇                 •➢ ሼር // SHARE 💚  •✥• @abenet_tmhert •✥•💚    💛  •✥• @z_tewodros •✥•💛 💖✥ @abenet_tmhert •✥•   💖              ✧━━━━━━━━━━━━━━✧‌‌
Show all...
በወለቴ ያለችው ቤተክርስቲያን ትጣራለች! በሻሸመኔ የብዙ ንፁሀንን ደም ያፈሰሰው ሕገ ወጡ ቡድን በመንግስት በታጠቁ ኃይሎችን ወደ ቤተክርስቲያኗ እየተኮሰ ይገኛል ! በወለቴ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን በከባድ መሳሪያ የታገዘ ድብደባ እየተፈፀመ ይገኛል እስከ አሁን ሁለት ሰዎች እንደተመቱ መረጃዎች ቢያሳዩም ከፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ግን የታየ ምላሽ የለም!
Show all...