የኢስላም መልእክት
Open in Telegram
«የፈጠርናችሁ ለከንቱ መኾኑን እናንተም ወደኛ የማትመለሱ መኾናችሁን ጠረጠራችሁን» (ለከንቱ የፈጠርናችሁ መሰላችሁን። ((23፥115))
Show more3 754
Subscribers
-724 hours
-227 days
-9530 days
Posts Archive
3 755
📘 አዲስ የፒዲኤፍ (PDF) መጽሐፍ ተለቀቀ!
"ኢስላማዊ አጣብቂኝ" በሚል የክርስቲያን ወገኖች ለሚነሳው ጥያቄ የተሰጠ ምላሽ
ባለፉት ዓመታት በተለያዩ ወገኖች ሲነሱ ለነበሩና በቅርቡ ደግሞ "Islamic Dilemma" በሚል ስም ዳግም ለተቀሰቀሱ ጥያቄዎች ተከታታይነት ያለው ምላሽ በአንድ ሰነድ ተጠቃሎ ቀርቧል። በዚህ መጽሐፍ ውስጥ፦
— "ቁርአን መጽሐፍ ቅዱስን እውነተኛ ይለዋልን?" ለሚለው ጥያቄ ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
— በዴቪድ ውድ እና መሰል ወገኖች ለሚነሱ "አጣብቂኝ" የሚመስሉ ነጥቦች አሳማኝ ምላሾች ተካተዋል።
— ለዳዒዎችና ለንጽጽር ጥናት ፈላጊዎች እንደ ግብዓት የሚያገለግሉ ነጥቦች ተዳስሰዋል።
የእውቀት አድማሳችንን ለማስፋትና ለሚነሱ ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ይረዳ ዘንድ ሰነዱን አውርዳችሁ አንብቡት፤ ለሌሎችም አጋሩት።
https://t.me/Yahyanuhe/4190
3 755
እፎይ የሚባለው የኦርቶዶክስ ተሳዳቢ ሙስሊሞች ይከራከሩኝ ብሎ አመት ሙሉ ፈሩኝ እያለ ሲያስወራ ኖሮ፤ እሺ በሰላም እንወያይ ብለውት ሙስሊም ክርስቲያኑ ጥሪውን እያስተጋባ ሳለ፤ ይሄው የእውነት የማይሆን መስሎት ነበር መሰል በዛው ቀርቷል።
ምናልባት ሰልሞ ውዱእ አድርጎ እየሰገደ እንደሆነ ቸክ አድርጉት።
ከዚህ ላይቭ ላይ እየጠበቃችሁ ካላችሁት 81,000+ ህዝቦች መካከል ግማሽ ያክሉ ክርስቲያኖች ከሆናችሁ፤ ስለሙ‼
ልጁ አዋርዷችኋል፣ ለጥቅሙ እናንተን ቢሰክሳችሁም እውነታውን ስለሚያውቅ ፊት ለፊት ተጋፍጦ መዋረድ አልፈለገም።
እስከዛሬም ጥሪ ሲያቀርብ የነበረው፤ እሱ ተሳዳቢ ስለሆነ ከርሱ ጋር ውይይት አያስፈልግም ይላሉ ብሎ ነው።
እስልምና ሁሌም ያኮራል።
በነገራችን ላይ ምንም እንኳ አዋቂ መስለው ለሚሸውዷቸው መንጋዎቻቸው በዚህ መልኩ ጭምብላቸውን መግለጥ ተገቢ ቢሆንም፤ ከእንዲህ አይነቱ አላህን እና መልዕክተኛውን ⏩️ ከሚሳደብ ከግብረ ገብነት ከወጣ ባለጌ ጋር መወያየት ተገቢ ነው ብዬ አላምንም።
ለስድቡ ሰበብ ላለመሆን!
ቀድሞ አቅሙን አውቆ ፈርቶ ቀረ እንጂ ቢመጣ ራሱ ከስድብና አቃቂር ውጭ ምንም አያመጣም ነበር።
||
t.me/MuradTadesse
3 755
🌱 ደማቅ የዳዕዋ መድረክ !
•በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር
•በኡስታዝ ሰዓድ ጅላሉ
🗓 እሁድ ግንቦት 2/2018 🕒 ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ
🕌 ሙስዓብ መስጂድ
📍 አድራሻ - አለም ባንክ
• ለሴቶች በቂ ቦታ አለ !
Map location - https://maps.app.goo.gl/QBQTbrq6figoZ38w5?g_st=atg
3 755
+2
አሠላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱሁ ለመጀመሪያ እና ለሁለተኛ ዙር ተማሪዎች አንኳን ደስ አላችሁ። ለአዲስ ተማሪዎች ደሞ በ «አል-ኢዝሃር ኢስላማዊ ጥናት እና ምርምር ተቋም» በአይነቱ ለየት ያለ የሦስተኛ ዙር የ አረብኛ ቋንቋ "Arabic grammar" ትምህርት ለ ተከታታይ ሥስት(3) ወራት ለመስጣት እናንታን በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።ለመመዝገብ ተቋሙ ባስቀመጠው ሊንክ ወደ መመልመያ ግሩፕ ይቀላቀሉ። ሙሉ መረጃ አዛው ይጠብቁ። https://t.me/+fGtleQNfLc83Nzdk
ማስታወቂያው የሚቆይበት ግዜ ለተከታታይ አምስት ቀናት 30/8/2018 እስከ 05/09/2018 ድረስ ነው።
3 755
ከሚከተሉት መካከል በአረበኛ ሚዲያ የዩቱዩብ ቻናል የትኛውን ጠቃሚ ትምህርት መማር ይፈልጋሉ✍የአረበኛ የእጅ ፅሁፍ ትምህርት ✍የአረበኛ ፊደላቶች አነባበብ ትምህርት ✍ሶርፍ/متن البناء في علم التصريف / ✍ነህው/متن الآجرومية/ ✍አረበኛ ቋንቋ/دروس اللغة العربية / ✍ተጅዊድ/تيسير أحكام التجويد / ✍ቁረአን / القرآن الكريم / ✍ሁሉንም በደረጃ ለመማር ወደ ቴሌግራም ቻናል ለመቀላቀል https://t.me/arabicmedia1
3 755
3 755
Repost from AAU - Muslim Students Union
ሴኩላር ነኝ ብሎ ኒቃብን በመመሪያ የከለከለው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ተመልከቱት። ስለ ስቅለት የደስታ መልዕክት ሲያስተላልፍ "እንኳን ለጌታችን መድሃኒታችን ...." በማለት እንደ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ተቋም ሳይሆን እንደ ሐይማኖት ተቋም ነው ያደረገው። ይህ ተቋማዊነትን የሚጥስ፤ ሴኩላሪዝምን የሚንድ ፍፁም ስህተት የሆነ አካሄድ ነው። ለየትኛውም በዓላት መልዕክት ሲተላለፍ የእምነት ተከታዩን ጠቅሶ ገለልተኛ መልዕክት ይተላለፋል እንጂ በዓሉን የሁሉም የተቋሙ አድርጎ አይተላለፍም። ሊስተካከል ይገባል ! ! ! ደግሞ ኮሜንት እንኳ እንዳይሰጣቸው አስተያየት መስጫውን ቆልፈውታል።
©️ MohammadamminKassaw
@aaumsu
3 755
ስቅለተ ዐርብ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥157 ጥርጣሬን ከመከተል በስተቀር በእርሱ ነገር ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ በእርግጥም አልገደሉትም፡፡ مَا لَهُم بِهِ مِنْ عِلْمٍ إِلَّا اتِّبَاعَ الظَّنِّ ۚ وَمَا قَتَلُوهُ يَقِينًا
ክርቲያኖች እራሳቸውን የሚያስጠጉበት ጳውሎስ ኢየሱስ በተቀበረ "በሦስተኛው ቀን ተነሣ" ይለናል፦
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥3 መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ፥ that he was buried and that he was raised on the third day according to the Scriptures.
ሦስቱ ቀን የሚጀምረው ከተቀበረበት ከሆነ በምድር ልብ ማለትም በመቃብር ውስጥ ሦስት ቀን እና ሦስት ሌሊት እንደሚሆን ይናገራል፦
ማቴዎስ ወንጌል 12፥40 ዮናስ በዓሣ አንባሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ፥ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል።
ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት በመቃብር ያለውን ጊዜ የሚሸፍን መሆኑን ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ያ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ወደ መቃብር የገባው ደግሞ በምሽት ነው፦
ማርቆስ 15፥42-46 አሁንም "በመሸ ጊዜ" የሰንበት ዋዜማ የሆነ የማዘጋጀት ቀን ስለ ነበረ።
"በመሸ ጊዜ" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! አይሁድ የሚያከብሩት በዓል ከ 12 ሰዓት በኃላ የነገው ነው፥ ያ በዓል የሚጀመረውም ሌሊቱ ከምሽቱ 12 ነው። ምሽት የሌሊት መጀመሪያ ነው፦
ዘጸአት 12፥18 በመጀመሪያውም ወር በአሥራ አራተኛው ቀን "በመሸ ጊዜ" ከወሩም እስከ ሀያ አንድ ቀን በመሸ ጊዜ የቂጣ እንጀራ ትበላላችሁ።
ማቴዎስ 26፥20 "በመሸም ጊዜ" ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ጋር በማዕድ ተቀመጠ።
ማርቆስ 1፥32 "ፀሐይም ገብቶ በመሸ ጊዜ"፥ የታመሙትንና አጋንንት ያደረባቸውን ሁሉ ወደ እርሱ አመጡ፤
"ፀሐይም ገብቶ በመሸ ጊዜ" የሚለው ይሰመርበት! ምሽት ማለት የፀሐይ መግባት ነው። እንግዲህ ከዚህ ከሰንበት ማለት ከቅዳሜ ዋዜማ ምሽቱ የቅዳሜ ከሆነ ከዚያ ጀምራችሁ ቁጠሩት! ሰኞ ማታ ለማክሰኞ ዋዜማ ላይ ይመጣል፥ ያ ማለት ሥስት ቀን እና ሦስት ሌሊት አይሞላም። አንድ የቅዳሜ ሌሊት እና አንድ የእሑድ ሌሊት ሲሆን ሁለት ሌሊት ይሆናል፥ አንድ የቅዳሜ መዓልት(ቀን) ብቻ ይተርፋል። በጥቅሉ ሁለት ሌሊት እና አንድ መዓልት እንጂ ሦስት ሌሊት እና ሦስት መዓልት አይሞላም፦
ዮሐንስ 20፥1 ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን መግደላዊት ማርያም ገና ጨለማ ሳለ ማለዳ ወደ መቃብር መጣች ድንጋዩም ከመቃብሩ ተፈንቅሎ አየች።
በአይሁድ የሳምንቱም ፊተኛው ቀን እሑድ ሲሆን እሑድ እጅግ በማለዳ ፀሐይ ሳትወጣ ጨለማ ሳለ ከመቃብር ተነሳ ካለ ሦስት ሌሊት እና ሦስት መዓልት አይሞላም። ይህ የገባው የፕሮቴስታንት መምህር ሀብታሙ ታደሰ "ኢየሱስ የሞተው ረቡዕ ነው" በማለት ከእሑድ ወደ ኃላ በመቁጠር ሦስት ሌሊት እና ሦስት መዓልት የሚለውን ለማስታረቅ ሞክሯል። ቅሉ እና ጥቅሉ ግን ቤተክርስቲያን ሆነች የቤተክርስቲያን አበው "ረቡዕ" የሚለውን ሳይሆን "ዓርብ" የሚለውን ስላስቀመጡ ስቅለት የሚባል በዓል በዓመት አንድ ጊዜ ዓርብ ቀን ያከብራሉ፦
ዲድስቅልያ 30፥25 ዓርብ ቀን ሰቀሉት፥ ተሰቅሎ በሞተ በሦስተኛው ቀን ተነሣ።
ዲድስቅልያ"didache" የጥንት ጽሑፍ ነው። እሩቅ ሳንሄድ የ 1980 አዲስ ትርጉም ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ እና ፕሮቴስታንት የተሳተፉበት የትርጉም ሥራ ሲሆን የሸንጎ አማካሪ የሆነ ዮሴፍ በዓለት በተዋቀረ መቃብር የቀበረው ዓርብ ማታ እንደሆነ ተጽፏል፦
ሉቃስ 23፥54 ይህንንም ያደረገው "ዓርብ" ማታ ለሰንበት ዝግጅት በሚደረግበት ጊዜ ነው።
የ 1993 አዲሱ መደበኛ ትርጉም ሉቃስ 23፥54 ጥቅስን በሚያብራራበት የግርጌ ማብራሪያ ላይ "የመዘጋጀት ቀን ለሰንበት ቀን የሚያስፈልግ ማንኛውም ነገር የሚሰናዳበት ቀን ሲሆን ቀኑም ዓርብ ነው" በማለት እንቅጩን አስቀምጧል። ከመነሻው ሰንበት ቅዳሜ ከሆነ የሰንበት ዋዜማ ዐርብ ነው፦
ማርቆስ 15፥42 አሁንም በመሸ ጊዜ የሰንበት ዋዜማ የሆነ የማዘጋጀት ቀን ስለ ነበረ፥ የከበረ አማካሪ የሆነ የአርማትያስ ዮሴፍ መጣ።
"የሰንበት ዋዜማ" የሚለው ይሰመርበት! የማርቆስ 15፥42 የትርጓሜ መጽሐፍ አንድምታው፦ "ዓርብ ሲመሽ ያን ጊዜም የሰንበት መግቢያ ነበር" በማለት ፍርጥ አርጎ አስቀምጦታል። ገና ለገና ከሙሥሊም ሙግት ለማምለጥ ታሪክን እና ትውፊትን ጥሶ እና በርጥሶ "የተሰቀለው ረቡዕ ነው" ብሎ መጨነቅ እና መጨናነቅ ለምን አስፈለገ? ጥርጣሬን ከመከተል በስተቀር በኢየሱስ ነገር ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ በእርግጥም አልገደሉትም፦
4፥157 ጥርጣሬን ከመከተል በስተቀር በእርሱ ነገር ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ በእርግጥም አልገደሉትም፡፡ مَا لَهُم بِهِ مِنْ عِلْمٍ إِلَّا اتِّبَاعَ الظَّنِّ ۚ وَمَا قَتَلُوهُ يَقِينًا
አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
3 755
[ እኛ ግን የማይሞተውን አምላክ እናመልካለን ]
وَتَوَكَّلۡ عَلَى ٱلۡحَيِّ ٱلَّذِي لَا يَمُوتُوَتَوَكَّلۡ عَلَى ٱلۡحَيِّ ٱلَّذِي لَا يَمُوتُ وَسَبِّحۡ بِحَمۡدِهِۦۚ وَكَفَىٰ بِهِۦ بِذُنُوبِ عِبَادِهِۦ خَبِيرًا
— سورة الفرقان (25:58)
በዚያም #በማይሞተው_ሕያው #አምላክ ላይ ተመካ፡፡ #ከማመስገንም ጋር #አጥራው፡፡ በባሮቹ ኀጢኣቶችም ውስጠ ዐዋቂ በእርሱ በቃ፡፡
— አል ፉርቃን (25:58)
3 755
3 755
Repost from የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe
ከአመታት በፊት በአሜሪካ ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ የሚማር አንድ ወንድማችን ለሒዳያ እስላማዊ ማዕከል አንድ አፕሊኬሽን በነፃ ሰርቶ አስረከበን። ስራው እጅግ የሚያምር ስለነበር ከልብ አመሰገንኩት። እሱ ግን በሰራው ስራ ብቻ ሳይረካ "ኡማውን የሚጠቅም ሌላ ምን ልስራ? ጠቁመኝ" አለኝ።
በወቅቱ አንድ ሁሌም የሚረብሸኝ ጉዳይ ነበር። የቁርኣን አፕሊኬሽኖች ለአጠቃቀም ምቹ አለመሆናቸውና በተለይ ገፅታቸው (Interface) ከሌሎች ተመሳሳይ የሌላ እምነት አፖች አንፃር ሲታይ ማራኪ አለመሆኑ ያበሳጨኝ ነበር። "ለምን ለአጠቃቀም ቀላልና እጅግ ማራኪ የሆነ የቁርኣን አፕሊኬሽን አትሰራም? አኼራህ ላይ ትልቅ ሰደቀተል ጃሪያ ይሆንልሃል" አልኩት፤ ሌሎች ጥቂት ሀሳቦችንም ተወያየን።
ከዚህች አጭር ውይይት በኋላ ዓመታት አለፉ። ስለ ጉዳዩም ምንም መረጃ አልነበረኝም። ነገር ግን ሰሞኑን፣ በእነዚህ በተባረኩ የረመዳን የመጨረሻ ቀናት ውስጥ... ፈጽሞ ያልጠበቅኩትን እጅግ አስደሳች ብስራት አበሰረኝ! ያኔ ያሰብነው ህልም እውን ሆኖ፣ በአማርኛ፣ በኦሮምኛ፣ በአፋርኛ እና በሌሎችም የሀገራችን ቋንቋዎች የተዘጋጀ፣ እጅግ ውብና ለመጠቀም ቀላል የሆነ የቁርኣን አፕሊኬሽን ሰርቶ መጨረሱን አበሰረኝ!
አፕሊኬሽኑ ለአንድሮይድም ሆነ ለአይፎን ተጠቃሚዎች ዝግጁ የተደረገ ሲሆን ወንድማችን ይህንን ትልቅ ስራ የሰራው ያለውን ውድ ሰዓት እያጣበበ በትርፍ ጊዜው ነው። አላህ (ሱ.ወ) መልካም ምንዳውን ይክፈለው!
ሁላችሁም ይህንን አፕሊኬሽን ከታች ባለው ሊንክ ዳውንሎድ አድርጋችሁ እንድትጠቀሙበት በደስታ እጋብዛችኋለሁ። ከተጠቀማችሁት በኋላ እንዲስተካከል ወይም እንዲጨመር የምትፈልጉትን ሀሳብ ኮመንት ላይ ብታካፍሉን ደግሞ ይበልጥ እናዳብረዋለን። ለዚህ ቀና ወንድማችን ከልብ የሆነ ዱዓ እናድርግለት! ፖስቱን ሼር በማድረግ በተጠቃሚው ልክ እርስዎም የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ።
🔗ለአንድሮይድ፦
https://play.google.com/store/apps/details?id=dev.ridwan.quran
📎 ለአይፎን፦
https://apps.apple.com/us/app/nur-quran-app/id6759636756
ሁላችንም ሼር በማድረግ ተደራሽ እናድርገው።
3 755
Qur’an Reference: Sūrat al‑Mu’minūn (23:12‑14)
Embryology Reference: Moore, K. L., Persaud, T. V. N., & Torchia, M. G. (2020). The Developing Human: Clinically Oriented Embryology (11th ed.). Elsevier.
3 755
Repost from قناة رياض الجنة 🌱 {የጀነት ጨፌ}
⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️
🌱 ሰበር ዜና
🇸🇦 ...*عاجل ... عاجل*... 🇸🇦
💡*تم رصد هلال شوال في تمير*💡
*بعد غداً الجمعة أول أيام شهر شوال *
*{ عِـــــــــيْــــــــدٌكـــم مُــــــبَــــارك }*
🇸🇦 ሳዑዲ ላይ ጨረቃ ስላልታየች አላህ
ካለ ከነገ ወዲያ ጁሙዓህ ኢድ ይሆናል።
• ዛሬ ተራዊሒ እንሰግዳለን
👈 قناة رياض الجنة.
👉〖የጀነት ጨፌ〗
╭┈──── ••↯↯↯
╰┈➢🌐@tewhedandsuna ✰••👈
3 755
Repost from قناة رياض الجنة 🌱 {የጀነት ጨፌ}
⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️
• የዘንድሮ ዒድ ሰላት በመስጂደል ሐራም የሚያሰግዱት ፦
ኸጢብ (ኢማም)፦ ሼህ ኡሳማ ኸያጥ (Sheikh Usaamah Khayat)
👈 قناة رياض الجنة.
👉〖የጀነት ጨፌ〗
╭┈──── ••↯↯↯
╰┈➢🌐@tewhedandsuna ✰••👈
3 755
Repost from قناة رياض الجنة 🌱 {የጀነት ጨፌ}
🌱 ኢድ መቼ ነው ❔
• ዛሬ አመሻሽ ላይ የሸዋል ጨረቃ ከታየች ነገ ሐሙስ ኢድ ይሆናል
• ካልታየች ደግሞ ነገ ፁመን ጁሙዓህ ኢድ እናከብራለን ።
• ኢድ መች
እደሆነ ለማወቅ ከናንተ የሚጠበቁው " የጀነት ጨፌ " ቻናልን ተቀላቅሎ መከታተል ብቻ ነው ።
👈 قناة رياض الجنة.
👉〖የጀነት ጨፌ〗
╭┈──── ••↯↯↯
╰┈➢🌐@tewhedandsuna ✰••👈