1 296
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 296
Repost from ሙሐመድ የንፅፅር ማህደር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ፥ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
መፅሐፍ ቅዱስ (ወንጌል) በየጊዜው ይሻሻላል፣ ይበረዛል፣ ይጨመራል፣ ይቀነሳል የምንለው ዝም ብለን አይደለም።
እግዚአብሔር ሚስት አግብቶ መውለዱ ለምን ከአዲሱ የመፅሀፍ ቅዱስ እትም ተወገደ?
ሚስጥር እውነትም ሚስጥር!
1 እግዚአብሔር አፍሮ ቃል ኪዳን አስሮ ቀመሰ...
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
«... እንደገናም በአጠገብሽ ሳልፍ #በፍቅር የምትነደፊበት ጊዜ እንደደረሰ አወኩ የተራቆተውንም #ሰውነትሽንም #በመጎናፀፊያዬ #ሸፍኜ #እንደምወዲሽ ቃሌን ገባሁልሽ ከአንቺም ጋር #የጋብቻ_ቃል_ኪዲን_ገብቼ የእኔ የግሌ አደረግኩሽ ይህን የተናገረ ልኡል እግዘአብሔር ነው፡፡»
(ትንቢተ ሕዝቅኤል 16 ፡ 3-8 ) ቀለል ባለ አማርኛ የተተረጎመ #የ1980 #እትም?
2 እግዚአብሔርሚስት አግብቶ በለተ።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
#አታፍሪምና #አትፈሪ #አትዋረጂምና #አትደንግጪ የህፃንነትሽንም #እፍረት ትረሺዋለሽ #የመበለትሽንም ስድብ ከእንግዲህ ወዲህ አታስቢም፡፡ #ፈጣሪሽ #ባልሽ ነው፡፡ #ስሙም_የሰራዊት_ጌታ #እግዘአብሔር_ነው፡፡ የእስራኤል ቅዱስ ታዳጊሽ ነው እርሱም የምድር ሁለ አምላክ ይባላል፡፡
( ኢሳይያስ 54 ፡ 4)
3 እግዚብሄር ሚስት አግብቶ ልጆች ወለደ ።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
«ጌታ እግዘአብሔር “ለእኔም #የወለድሻቸውን #ወንዶችና #ሴቶች #ልጆችሽን ወስደሽ መብሌ ይሆኑ ዘንዴ ሰዋሽላቸው”፡፡» ( ሕዝቄል 16 ፡ 20 )
ፈጣሪ አምላካችን ጢሙን በላው በምላጭም ተላጨ
«በዚያም ቀን እግዘአብሄር ከወንዝ ማዶ በተከራየው ምላጭ በአሶር ንጉሥ የራሱንና የእግሩ ጠጉር ይላጨዋሌ፤ ምላጩን ጢሙን ደግሞ ይበላዋሌ፡፡» ትንቢተ ኢሳይያስ (7፡20)
ሕዝቅኤል 16
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁷ በእርሻ ላይ እንዳለ ቡቃያ አበዛሁሽ፥ አንቺም አደግሽ ታላቅም ሆንሽ፥ በእጅጉም አጌጥሽ፤ ጡቶችሽም አጐጠጐጡ ጠጕርሽም አደገ፥ ነገር ግን ዕርቃንሽን ሆንሽ፥ ተራቍተሽም ነበርሽ።
⁸ በአንቺ ዘንድ ባለፍሁና ባየሁሽ ጊዜ፥ እነሆ፥ ጊዜሽ የፍቅር ጊዜ ነበረ፤ እኔም መጐናጸፊያዬን በላይሽ ዘረጋሁ ኀፍረተ ሥጋሽንም ከደንሁ፤ ማልሁልሽም ከአንቺም ጋር ቃል ኪዳን ገባሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፥ አንቺም ለእኔ ሆንሽ። (ሕዝቅኤል 16:7–8) የ 1980 ቀላል የአማርኛ ትርጉም ላይ አገባሁሽ ልጆችንም ወለድሽልኝ ይላል
በአዲሱ ትርጉም ላይ ግን ነቅለው አውጥተው በሌላ ተክተውታል፣ ለምን?
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
4 እግዝአብሔር አመንዝራ /ዝሙተኛ/ ከሆኑ ሁለት እህትማማቾች ወንድና ሴት ልጆችን እንደወለደም ይነግረናል።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
«የእግዘአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ “የሰው ልጅ ሆይ! #የአንድት #እናት ልጆች የሆኑ #ሁለት #ሴቶች ነበሩ፡፡ በግብፅም #አመነዘሩ በኮረዲነታቸውም ስላመነዘሩ በዚያ
#ጡቶቻቸው #ሟሸሹ ከዚያም #የድንግሌናቸውን #ጡቶች ዳበሱ፡፡ ስማቸው የታላቂቱ #ኦሆላ የእህቷም #ኦሆሊባ ነበረ #ለእኔም #ሆኑ ወንዶችንና ሴቶች ልጆችንም ወለዱልኝ፡፡..»
(ትንቢተ ሕዝቄል 23:1-4 ) የ1980 የመጽሃፍ ቅዱስ እትም ላይ ንዑስ ርዕሱን «በዝሙት ኃጢያት የተባበሩ እህትማማቾች» ብሎ ሰይሞታል፡፡
አዲሱ እትም ላይ ግን ሰርዘውታል፣ ደልዘውታል እኮ ለምን?
እግዚአብሔር ላይ ሚስቱ አመነዘረችበት
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
ሕዝቅኤል 16
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁹ በውኃም አጠብሁሽ ከደምሽም አጠራሁሽ በዘይትም ቀባሁሽ።
¹⁰ ወርቀ ዘቦም አለበስሁሽ በአቆስጣ ቁርበትም ጫማ አደረግሁ
#አንዳንደ አምላክ በግድ የሰወችን #አይን ይገልጣል ሰወቹ ዳግም ቢጨፍኑትም ።።
---------------------------------------------------------------------------------------------
https://t.me/muhammed6964
ወሠላሙ ዐለይኩም
1 296
የሚጸልይ ፍጡር አታምልኩ!
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
2፥186 ባሮቼም ከእኔ በጠየቁህ “እኔ ቅርብ ነኝ፥ የለማኝን ጸሎት በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ፡፡ وَإِذَا سَأَلَكَ عِبَادِي عَنِّي فَإِنِّي قَرِيبٌ ۖ أُجِيبُ دَعْوَةَ الدَّاعِ إِذَا دَعَانِ
ኢየሱስ በምድር ሲመላለስ በጸሎት ብርቱ ስለነበር ሌሊቱን ሙሉ ወደ አምላክ ሲጸልይ ያድር ነበር፦
ሉቃስ 6፥12 በነዚህም ወራት ይጸልይ ዘንድ ወደ ተራራ ወጣ፥ ሌሊቱንም ሁሉ "ወደ" አምላክ ሲጸልይ አደረ። Ἐγένετο δὲ ἐν ταῖς ἡμέραις ταύταις ἐξελθεῖν αὐτὸν εἰς τὸ ὄρος προσεύξασθαι, καὶ ἦν διανυκτερεύων ἐν τῇ προσευχῇ τοῦ Θεοῦ.
"ወደ" የሚለው መስተዋድድ ጸላዩን ኢየሱስ ከሚጸለይለት አምላክ ለይቶ ያስቀምጠዋል። ኢየሱስ እራሱ አንዱን አምላክ ጠይቆ መልስ የሚጠብቅ ለማኝ ነበር፦
ዮሐንስ 11፥22 አሁንም ከአምላክ የምትለምነውን ሁሉ አምላክ እንዲሰጥህ አውቃለሁ አለችው። καὶ νῦν οἶδα ὅτι ὅσα ἂν αἰτήσῃ τὸν Θεὸν δώσει σοι ὁ Θεός.
ኢየሱስ አንዱን አምላክ ለምኖ አሕዛብን ለርስቱ የምድርንም ዳርቻ ለግዛቱ እንዲሰጠው አምላክ ኢየሱስን "ለምነኝ" ብሎታል፦
መዝሙር 2፥8 "ለምነኝ"! አሕዛብን ለርስትህ የምድርንም ዳርቻ ለግዛትህ እሰጥሃለሁ።
ኢየሱስ በምድር ላይ እያለ አሕዛብን ለርስቱ የምድርንም ዳርቻ ለግዛቱ እንዲሰጠው አምላክን አለመነም፥ ቅሉ ግን አብ ኢየሱስን "ለምነኝ" ባለው መሠረት ይለምነዋል። ኢየሱስ አምላክን ለምኖ የሚሰጠው ከሆነ እርሱ ለማኝ ነቢይ እንጂ ተለማኝ አምላክ በፍጹም አይደለም። ኢየሱስ ካረገም በኃላ አብን በጸሎት ይለምናል፦
ዮሐንስ 14፥16 እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል።
ለዘላለምም ከሰዎች ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ እንዲሰጥ የጸለየበት ክፍል በምድር ላይ የለም። ነገር ግን ካረገ በኃላ የሚጸልየው ጸሎት ነው፥ ምክንያቱም ኢየሱስ በአምላክ ቀኝ ሆኖ እንደሚያማልድ በግልጽ ተቀምጧል፦
ሮሜ 8፥34 በአምላክ ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው። ὅς ἐστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ Θεοῦ, ὃς καὶ ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν.
"ኢንቱካኖ" ἐντυγχάνω ማለት "ጠራ" "ማለደ" "አማለደ" ሲሆን መሠረታዊ ትርጉሙ "ለመነ" ማለት ነው፥ ኢየሱስ ለማኝ መሆኑን አምላክ ተለማኝ መሆኑን ፍንትው አርጎ ያሳያል። በ 1879 እንደ ጽብሓውያን ኦርቶዶክስ አቆጣጠር የተዘጋጀው የአባ ሮሜ የቁም ጽሑፍ የሚባል የባይብል ዕትም ኢየሱስ አማላጅ እንደሆነ ይናገራል፦
1ኛ ዮሐንስ 2፥1 ከላንትም ማንም ኃጢአት ቢሰራ ከአብ ዘንድ "አማላጅ" አለን፥ የሱስ ክርስቶስ ጻድቅ። ሮሜ ፰፤፫፬ ዕብ ፯፤፪፭
"ምልጃ" ማለት ለሌላው ማንነት የምናቀርበው ልመና ነው። ኢየሱስ ካረገ በኃላ አብን እንደሚለምን ድርሳነ ማርያም ላይ ተቀምጧል፦
ድርሳነ ማርያም ገጽ 49 "እኔም እሄዳለው አባቴንም እለምነዋለው"
ድርሳነ ሰንበት ላይ ደግሞ አማኞች በሥራቸው ደካማ የሆኑትን ኢየሱስ እንደሚጸልይላቸው ይናገራል፦
ድርሳነ ሰንበት ገጽ ገጽ 49 ምዕራፍ 17 ቁጥር 1 "ጸሎት ይጸልይላቸው ዘንድ መላእክት ያቀርቧቸዋል"
ዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ፦ "ኢየሱስ አምላክ ከሆነ ወደ ማን ነው የሚለምነው? ስንት አምላክ ነው ያለው? ለማኝ እና ተለማኝ ካለ ሁለት ናቸው ማለት ነው" በማለት ተናግሯል።
ዲያቆን አባይነህ ካሴ ደግሞ፦ "ኢየሱስ እግዚአብሔር ከሆነ እዚህ ጋር እንዲህ ሆኖ ይማልዳል እዚህ ጋር እንዲህ ሆኖ ይጸልያል የሚባል ነገር አለ ወይ? የለም፥ ሊኖርም አይችልም። ማን ወደ ማን ይጸልያል? አብን እግዚአብሔር ካልን ወልድን እግዚአብሔር ካልን ማን ወደ ማን ይጸልያል?" በማለት ተናግሯል።
ሁለቱም አምላክ ተለማኝ እንጂ ለማኝ እንዳልሆነ ክፉኛ በመቆርቆር መናገራቸው አግባብ ነው፥ ለማኝ አምላክ እና ተለማኝ አምላክ ካለ ሁለት አምላክ ይሆናሉ።
እንግዲያውስ ሁላችሁም ቢመራችሁም ዋጡት! ኢየሱስ ለማኝ ፍጡር ብቻ እና ብቻ ነው። ክርስቲያኖች ሆይ! የሚጸልይ ፍጡርን አታምልኩ!
“ዱዓእ” دُعَآء የሚለው ቃል “ደዓ” دَعَا ማለትም “ለመነ” “ጠራ” “ጸለየ” “ተማጸነ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ልመና” “ጥሪ” “ጸሎት” “ተማጽንዖ” ማለት ነው። ዱዓእ የአንዱ አምላክ የአሏህ ሐቅና ገንዘብ ነው፦
2፥186 ባሮቼም ከእኔ በጠየቁህ “እኔ ቅርብ ነኝ፥ የለማኝን ጸሎት በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ፡፡ وَإِذَا سَأَلَكَ عِبَادِي عَنِّي فَإِنِّي قَرِيبٌ ۖ أُجِيبُ دَعْوَةَ الدَّاعِ إِذَا دَعَانِ
አንዱ አምላክ "የለማኝን ጸሎት በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ" በማለት እርሱ ተለማኝ እንደሆነ አበክሮ ይናገራል፥ "ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና" በማለት ፍጡራን ለማኝ መሆናቸውን ያስረዳል፦
40፥60 ጌታችሁም አለ «ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና፡፡ እነዚያ እኔን ከማምለክ የሚኮሩት ተዋራጆች ኾነው ገሀነምን በእርግጥ ይገባሉ”፡፡ وَقَالَ رَبُّكُمُ ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ ۚ إِنَّ الَّذِينَ يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِي سَيَدْخُلُونَ جَهَنَّمَ دَاخِرِينَ
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 34, ሐዲስ 2
አን-ኑዕማን ኢብኑ በሺር እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” አሉ፦ "ዱዓእ ዒባዳህ ነው፥ ከዚያም፦ “ጌታችሁም አለ «ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና” የሚለውን አንቀጽ ቀሩ”። عَنِ النُّعْمَانِ بْنِ بَشِيرٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ” إِنَّ الدُّعَاءَ هُوَ الْعِبَادَةُ ” . ثُمَّ قَرَأَ {وَقَالَ رَبُّكُمُ ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ}
"ዒባዳህ" عِبَادَة የሚለው ቃል "ዓበደ" عَبَدَ ማለትም "አመለከ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “አምልኮ” ማለት ነው።
አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
1 296
Repost from አነፃፃሪው-Comparator
እንባ...😭
የጠቆረው ፊትሽ በኑርሽ ይረሳል😔
የወደመው ቤትሽ በሀቅሽ ይነሳል😢
🇪🇬🇱🇾🇸🇩🇩🇿🇲🇦🇲🇷🇹🇳🇩🇯🇸🇴🇰🇲🇦🇴🇺🇬🇪🇹🇲🇺🇸🇹🇨🇫🇸🇿🇧🇯🇧🇼🇧🇫🇧🇮🇹🇿🇹🇩🇹🇬🇿🇦🇸🇨🇧🇮🇿🇲🇿🇼🇨🇮🇸🇳🇬🇼🇬🇳🇬🇶🇬🇼🇵🇬🇬🇦🇬🇲🇬🇭🇰🇪🇨🇲🇨🇩🇨🇬🇱🇷🇲🇿🇲🇱🇳🇪🇳🇬🇨🇩🇨🇬🇲🇼🇱🇸🇲🇬🇳🇦🇹🇷🇮🇷🇮🇩🇲🇾🇮🇷🇦🇿🇦🇱🇧🇦🇰🇼🇾🇪🇮🇶🇸🇦🇧🇭🇦🇪🇶🇦🇯🇴🇱🇧🇸🇾🇵🇰🇺🇿🇧🇩🇰🇿🇹🇯🇴🇲🇲🇻🇽🇰 🚨
#PalestineWillBeFree🤲
✊ያ ጀመአ ለአላህ ስንል ሼር እናርገው✊
t.me/islamcomparator
1 296
Repost from አነፃፃሪው-Comparator
🛑ኢንሻአላህ ከቅዳሜ ጀምሮ ይሰጣል ያልተመዘገባችሁ ደርሱ ሳይጀመር ፈጥነው ይመዝገቡ።
@Thecomparator
ወሰላሙ አለይኩም👋
1 296
Repost from አነፃፃሪው-Comparator
👇Rᴇǫᴜᴇsᴛ Tᴏ Jᴏɪɴ Cʜᴀɴɴᴇʟ👇
https://t.me/+lmQv_KJlXNZhNTY8
https://t.me/+lmQv_KJlXNZhNTY8
https://t.me/+lmQv_KJlXNZhNTY8
1 296
Repost from አነፃፃሪው-Comparator
@AhmedMuhammedMengistu
ያ ጀመአ ወዮ Application በተባለለትና በሙስሊም ወገኖች በተሰራው በUmma Life መጥቻለሁ፤እናንተም Follow እያደረጋችሁ ወዮ አሰኙኝ😁
