Ethiopia Andinet school🇪🇹
Open in Telegram
ይህ ቻናል በዓለም አቀፍ ደርጃ በተከስተው የኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ ተማሪዋች በወላጅ ድጋፍ ቤት ሆነው የተለያዩ ጥያቄዋችን እንዲሰሩ እና የት/ቤት መልዕክትን ለማስተላለፍ የተዘጋጅ የቴሌግራም ቻናል ነው
Show more402
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የመማሪያ መፃህፍት እስከ መስከረም 12 ድረስ ሙሉ ለሙሉ ለተማሪዎች እንደሚደርሱ ተገለፀ
በአዲሱ ስርአተ ትምህርት መሰረት የታተሙ የመማሪያ መፃህፍትን ለትምህርት ቤቶች የማሰራጨት ስራ በፍጥነት እየተሰራ እንደሚገኝ #የአዲስ_አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የትምህርት ማሻሻል እና ግብአት አቅርቦት ባለሙያ አቶ አለሙ ሃይሉ ለአሀዱ ገልጸዋል፡፡
አዲሱ የትምህርት ስርአት ካለፈው አመት ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገ ቢሆንም በህትመት መጓተት ምክንያት ብዙ ተማሪዎች ሳይደርሳቸው ቆይቷል፡፡
አሁን ላይ ግን ቀደም ብሎ የማሰራጨት ስራዎች መጀመራቸውን አንስተው እስከ መስከረም 12 ባለው ጊዜ ውስጥም ሙሉ ለሙሉ ለማዳረስ ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
የመማሪያ መጽሀፍት ስርጭቱ የግል ትምህርት ቤቶችንም ያካተተ ሲሆን መጽሀፎቹ በነፃ መሰራጨት እንዳለባቸው እና በአስገዳጅ ሁኔታ ክፍያ የሚያስከፍሉ ትምህርት ቤቶች ላይ አስፈላጊው ቁጥጥር እና እርምጃዎች እንደሚወሰዱም አሳስበዋል፡፡
#አሀዱ
በልጆቻችን ትምህርት ከደ/ር ሰለሞን በላይ ጋር ቀጣይ ቆይታ አድርገናል።
ምን ምን ሀሳቦች በውይይቱ ተነሱ፦
- ወላጆች ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን ትምህርት ቤት ሄደው ልጃቸው በምን አይነት ሁኔታ እየተማረ እንደሚገኝ መጠየቅ አለባቸው።
- የወላጆች ኮሚቴ ዋና ሥራው ቁጥጥር አይደለም። ዋነኛ ተሳትፎ መሆን ያለበት የተሻለ የሥርዓተ ትምህርት እንዲኖርና ልጆች ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ ማስቻል ነው።
- በወላጅና በትምህርት ቤት መካከል ያለው ግንኙነት የሻጭና የገዢ መሆን የለበትም።
- ትምህርት በመማማር ሂደት ውስጥ 4 ነገሮች ለተማሪዎች መተላለፍ አለባቸው
1. እውቀት (Knowledge)
2. ክህሎት (Skill)
3. አመለካከት (Altitude)
4. ከሰው ጋር ያለ መስተጋብር (Human Interaction)
- ለተማሪዎች ትምህርት ቤት ሲማሩት የቆዩትን ነገር መልሶ የቤት ሥራ እንዲሰሩ መደረግ የለበትም።
🎧 ሙሉ ውይይቱን ቢያደምጡ ያተርፉበታል።
✅️@TikvahethMagazine
02.1.2016
ለት/ቤቱ ተማሪ ወላጆች በሙሉ
የ2016 መማር ማስተማር በ7.1.2016 ይጀመራል በመሆኑም በትምህርት አጀማመሩና ቀጣይም የት/ቤቱ ዕቅድ ዙሪያ እሁድ መስከረም 6/2016 አጠቃላይ ስብሰባ ስለሚኖር 2:30 በት/ቤቱ እንድትገኙ በጥብቅ እናሳስባለን::
ቴሌ ገራም ቻናል ለማይከታተሉ ወላጆች ተደራሽ በማድረግ ሃላፊነታችንን እንወጣ።
ጉዳዩ፡- የ7ኛ ክፍል ተማረዎችን ይመለከታል፡፡
✍️ከላይ በርዕሱ ለመጥቅስ እንደተሞከረው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2015ዓ.ም የ6ኛ ክፍል የከተማ አቀፍ ፈተና መፈተናችን ይታወቃል፡:
✍️ሆኖም በተለያዩ ምክንያት በመሸኛ ከክልል እና ከተለያዩ ሀገራት ወደ አዲስ አበባ ለመማር የሚመጡ ተማሪዎች የፈተና የሚፈተኑ መሆኑን ያሳወቅን ሲሆን በሁሉም ትምህርት ቤት የተመዘገቡ የ7ኛ ክፍል ተማሪዎች መረጃ በክፍለ ከተማ እና በትምህርት ቤት በመለየት እስከ ቅዳሜ 5/01/2016ዓ.ም ስም ዝርዘራቸው እንድታሳውቁን እየጠየቅን የፈተናው ውጤት በክፍለ ከተማ በኩል በ09/01/2016ዓ.ም የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን ፡፡
✍️የፈተና ቀን ማክሰኞ 08/1/2016 ዓ.ም ዳግማዊ ሚኒሊክ 2ኛ ደ/ት/ቤት
በመሆኑም በወረዳቹህ /በትቤታቹህ እነዚህ ተማሪዎች ካሉ ለክፍለ ከተማ እንድትልኩልን!!
Repost from Addis Ababa Education Bureau
#መረጃ
አዲስ አበባ ነሀሴ 20 /2015 ዓ.ም የአዲስ አበበ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ በነገው እለት 'እሁድ ነሃሴ 21, 2015 ዓ.ም' አገልግሎት እንደሚሰጥ አስታውቋል።
ኤጀንሲው ከአዲእስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ጋር በጋር በመተባበሮ የተማሪዎች የልደት ምዝገባ ስራን እያከናወነ ይገኛል።
በመሆኑም የወላጆችን የአገልግሎት ፍላጎት ለማርካት ከቅዳሜ አገልግሎት በተጨማሪ እሁድ ነሃሴ 21 እስከ ቀኑ 9:00 ድረስ የልደት ምዘገባ አገልግሎት በሁሉም የከተማዋ ወረዳዎቻች አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል።
ለበለጠ መረጃ እንዲሁም ለማንኛውም ጥቆማ እና ማብራርያ በኤጀንሲው ነፃ የተገልጋይ የስልክ መስመር 7533 ደውለው ያግኙን ሲልም መልዕክቱን አስተላልፏል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
Repost from Addis Ababa Education Bureau
ሰበር ዜና!
በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተሰጠው የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ነገ ይፋ ይሆናል፡፡
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24፣ 2015 (ትምህርት ቢሮ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጀነራል ካውንስል በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት ለመጀመሪያ ጊዜ በተሰጠው በ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ማለፊያ ነጥብ ላይ ውይይት በማድረግ የማለፊያ ነጥቡን በሙሉ ድምጽ ወስናል፡፡
ውጤቱንም በማስመልከት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ለሚዲያ አካላት ነገ 4 ሰሃት ላይ ማብራሪያ ከሰጡ በኋላ ይፋ ይሆናል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2015 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰኔ 28-30/10/2015 ዓ.ም ድረስ በ182 የፈተና ጣቢያዎች ለ75,090 ተማሪዎች ፣ 1,900 ፈታኞችን፣ 700 ሱፐር ቫይዘሮችንና 182 የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎችን በማሳተፍ መሰጠቱ ይታወሳል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
እራሱን ከሚገባው በታች ዝቅ አድረጎ የአምላኩን ምህረት የመሰከረ የምድሪቱ የሁል ግዜም ታላቅ ሰው ክቡር ዶ/ር ቢኒያም
