en
Feedback
ቅድስት ፌብሮኒያ

ቅድስት ፌብሮኒያ

Open in Telegram

ይህ ቻናል ስለ ሕይወታችን የምንወያይበት ሁላችንም ሀሳብና አስተያየት የምናካፍልበት ነው ፤ እንዲሁም የተለያዩ መንፈሳዊ ነገሮች ይለቀቁበታል።

Show more
1 415
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-130 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
August '25
August '25
+7
in 0 channels
July '25
+17
in 0 channels
Get PRO
June '25
+14
in 0 channels
Get PRO
May '25
+25
in 0 channels
Get PRO
April '25
+28
in 1 channels
Get PRO
March '25
+29
in 0 channels
Get PRO
February '25
+26
in 0 channels
Get PRO
January '25
+44
in 1 channels
Get PRO
December '24
+36
in 0 channels
Get PRO
November '24
+24
in 0 channels
Get PRO
October '24
+63
in 0 channels
Get PRO
September '24
+81
in 0 channels
Get PRO
August '24
+78
in 1 channels
Get PRO
July '24
+26
in 0 channels
Get PRO
June '24
+14
in 0 channels
Get PRO
May '24
+25
in 12 channels
Get PRO
April '24
+25
in 0 channels
Get PRO
March '24
+22
in 13 channels
Get PRO
February '24
+17
in 0 channels
Get PRO
January '24
+45
in 15 channels
Get PRO
December '23
+132
in 18 channels
Get PRO
November '23
+21
in 18 channels
Get PRO
October '23
+14
in 19 channels
Get PRO
September '23
+27
in 0 channels
Get PRO
August '23
+42
in 0 channels
Get PRO
July '23
+97
in 0 channels
Get PRO
June '23
+45
in 0 channels
Get PRO
May '23
+18
in 0 channels
Get PRO
April '23
+21
in 0 channels
Get PRO
March '23
+29
in 0 channels
Get PRO
February '23
+24
in 0 channels
Get PRO
January '23
+33
in 0 channels
Get PRO
December '22
+44
in 0 channels
Get PRO
November '22
+17
in 0 channels
Get PRO
October '22
+34
in 0 channels
Get PRO
September '22
+39
in 0 channels
Get PRO
August '22
+40
in 0 channels
Get PRO
July '22
+35
in 0 channels
Get PRO
June '22
+97
in 0 channels
Get PRO
May '22
+47
in 0 channels
Get PRO
April '22
+30
in 0 channels
Get PRO
March '22
+28
in 0 channels
Get PRO
February '22
+46
in 0 channels
Get PRO
January '22
+173
in 0 channels
Get PRO
December '21
+225
in 0 channels
Get PRO
November '21
+44
in 0 channels
Get PRO
October '21
+58
in 0 channels
Get PRO
September '21
+79
in 0 channels
Get PRO
August '21
+89
in 0 channels
Get PRO
July '21
+145
in 0 channels
Get PRO
June '21
+414
in 0 channels
Get PRO
May '21
+394
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
13 August0
12 August+1
11 August0
10 August0
09 August+1
08 August0
07 August0
06 August0
05 August+1
04 August0
03 August0
02 August+1
Channel Posts
ተጋዳዩ ሐዋርያና ዘመናችን፤ የተወለደው ክርስቲያናዊ ካልሆኑ ቤተሰቦች ነው። ከአካባቢው ልጆች ጋር በነበረው ቀረቤታ ወደ ክርስትና ተሳበ። ተማረ፤ ተጠመቆም የእግዚአብሔር ልጅነትን አገኘ። በትጋትና በ
ተጋዳዩ ሐዋርያና ዘመናችን፤
የተወለደው ክርስቲያናዊ ካልሆኑ ቤተሰቦች ነው። ከአካባቢው ልጆች ጋር በነበረው ቀረቤታ ወደ ክርስትና ተሳበ። ተማረ፤ ተጠመቆም የእግዚአብሔር ልጅነትን አገኘ። በትጋትና በቅልጥፍና አገለገለ። ከዲቁና እስከ ጵጵስናም ደረሰ። በዘመኑ ነገረ ተዋሕዶውን አጣሞ ስሁት ትምህርት ሲያስተምር የነበረውን አርዮስን ከ317 ሌሎች ጳጳሳትና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የጉባዔው ጸሐፊ ሆኖ አወገዘ። ቀጥሎም 20ኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ኾኖ በትጋት ማገልገል ጀመረ። አርዮሳዊ ንጉሥ ሲነግሥ ግን እርሱን አባሮ አርዮሳዊ ሊቀ ጳጳሳት በመንበሩ አስቀመጠ። ለአስራ አምስት ዓመታት በእስር፣ በስደት፣ በእንግልት አሳለፈ። ጥፍሩንና የሰውነት ክፍሉን ቢቆራርጡት፥ የቆራረጡትን የአካል ክፍል አሽጎ “እነሆ የሃይማኖት ፍሬ” ብሎ በእምነታቸው ጸንተው እንዲጠብቁ ላከላቸው። በዚህ ሁኔታ የቤተክርስቲያንን እውነተኛ አስተምህሮ ጠብቆ፣ አስጠብቆ ለኛ ትውልድ አሸጋገረልን። ሐዋርያ የተባለው ቅዱስ አትናቴዎስ በዚህች ዕለት (ግንቦት 7) አረፈ። ዛሬም ቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ በባለሥልጣናት ተጽእኖ ተሾመው እንደ አርዮስ ሁሉ የክህደት ትምህርትን ያለመሸማቀቅ የሚያስተምሩበት ዘመን ላይ ነን። ያው ከትናንቱ የተለየ ነገር የለም። ያኔ እነ ቅዱስ አትናቴዎስ ታስረው፣ ተጋድለው እዚህ ያደረሷት ቤተክርስቲያን ዛሬም የሚጋደሉላትን ትጋብዛለች። የሚጋደሉ ይጋደሉላታል፤ የሚክዱም ይክዷታል። ነገንም ትቀጥላለች። እንደ አርዮስ አይነት ከሃዲ፣ ከእንደ ሁለተኛው አርዮሳዊው ቆስጠንጢኖስ ጋር እያሴረ፥ እንደ አትናቴዎስ አይነት ሃይማኖተኛ እየፈጠረ ዑደቱ ይቀጥላል። የቅዱስ አትናቴዎስ የተጋድሎውና የጸሎቱ በረከት ከሁላችን ጋር ይኑር! ይቀላቀሉ! 👇👇👇 https://t.me/burukie2014

2
ነብዩ ኤርምያስና የባቢሎን ምርኮ ነብየ እግዚአብሔር ኤርምያስ በአይሁድ እጅ ተወግሮ በዚህች ዕለት (ሚያዝያ 5) ሰማዕት ኾነ። የእግዚአብሔርን ቃል በማስተማሩ፣ ከኃጢአታቸው እንዲመለሱ፥ ንስሐም እንዲ
ነብዩ ኤርምያስና የባቢሎን ምርኮ ነብየ እግዚአብሔር ኤርምያስ በአይሁድ እጅ ተወግሮ በዚህች ዕለት (ሚያዝያ 5) ሰማዕት ኾነ። የእግዚአብሔርን ቃል በማስተማሩ፣ ከኃጢአታቸው እንዲመለሱ፥ ንስሐም እንዲገቡ በመንገሩ ወገሩት። እግዚአብሔር፥ በነብዩ በኩል ነግሯቸው አልሰማ ያለውን ሕዝብ ለባቢሎኑ ንጉሥ አሳልፎ ሰጣቸው። ሰባ ዓመትም በባርነትም ገዛቸው። በርኩሰቷ እግዚአብሔርን ያሳዘነችው “ታላቂቱ ከተማ” (ባቢሎን) ቅዱስ ቃሉን አልሰማ ያለን ሁሉ ትማርከዋለች። ባቢሎን እንዲህ ተብሎላታል፤ “የአጋንንት ማደሪያ ኾነች፤ የርኩሳንም መናፍስት ሁሉ መጠጊያ ሆነች፤ አሕዛብ ሁሉ ከዝሙቷ ቁጣ ወይን ጠጅ የተነሣ ወድቀዋልና፤ የምድርም ነገሥታት ከእርሷ ጋር ሴሰኑ፤ የምድርም ነጋዴዎች ከቅምጥልነቷ ኃይል የተነሣ ባለጠጋዎች ሆኑ፤” (ራእይ 18፥ 2-3)። ሕዝብ ወደ ባቢሎን በመማረኩ ቅዱሳን ያዝናሉ። ደስታቸውም በባቢሎን ላይ እግዚአብሔር የሚሰጠው ፍርድ ነው። “ሰማይ ሆይ! ቅዱሳን ሐዋርያት፥ ነቢያትም ሆይ! በእርሷ ላይ ደስ ይበላችሁ፤ እግዚአብሔር ፈርዶላችኋልና” (የዮሐንስ ራእየ 18)። አምላካችን እግዚአብሔር ከቤቱ የራቅነውን፣ የቅዱሳንን ቃል ሁሉ ያቃለልነውን በነብዩ ኤርምያስ ጸሎት ከባቢሎን ምርኮ መልሶ በቤቱ አጽንቶ ያኑረን! ይቀላቀሉ! ቴሌግራም፤ https://t.me/burukie2014 ዩቲዩብ፤ www.youtube.com/@ቤተኦርያ-BeteOria
0
3
መልካሟ ደጅ፥ ኦርያ ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ልምሾ ኾኖ የተወለደ ሰው ነበር። እግሩ አይቆምለትም፣ ወገቡ አይጸናለትም። ከቦታ ወደ ቦታ የሚያንቀሳቅሰው ሌላ ሰው ነው። ይህ ሰው አንድ ሥራ ብቻ ነበረው። ልመና። ሲነጋ ወስደው ከቤተክርስቲያን ደጅ ላይ ያስቀምጡታል። ከሚገባውና ከሚወጣው ሲለምን ይውላል። ማታ መጥተው፥ ያገኘውን ገንዘብ ተቀብለው፥ ወደ ቤቱ ይወስዱታል። ወደዚህ ቤተክርስቲያን ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ሁለት ሰዎች ለጸሎት እየገቡ ነው። ሁሉንም እንደሚለምነው ለመናቸው። በትኩረትም ተመለከቱት። ዘልቀው የልቡን ሁሉ ገመና አዩ። ያሰረውን ኃይል፣ የያዘውን ጠላት አስተዋሉ። ቀጥሎም አንደኛው እንዲህ አለው፤ “ወደ እኛ ተመልከት”። የሚሰጡትን ገንዘብ ከእጃቸው ሲፈልግ አየውና “ወርቅና ብር የለኝም፤ ያለኝን ግን እሰጥሃለሁ፤ እነሆ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሥተህ ሂድ” አለው። በቀኝ እጁም ይዞ አስነሣው። ቆመ፣ ዘለለ፣ ሮጠም። እግዚአብሔርንም እያመሰገነ ከእነርሱ ጋር ወደቤተ መቅደስ ገባ። ይህ ታሪክ በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ሦስት የተመዘገበ ነው። “ወደ እኛ ተመልከት” ያለው ቅዱስ ጴጥሮስ ነበር። አብሮትም የነበረው ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ነው። “ወደ እኛ ሃይማኖት ግባ” እያሉ፣ ጥሪ እያቀረቡለት ነበር። እርሱም ፊቱን ወደ እምነቱ መልሷል። በዚህም ተፈውሷል። ይህንን ያዩ የአካባቢው ሰዎች ተደንቀዋል፤ ይህ የተሠራው በሰቀሉት በጌታችን ስም በመኾኑ ተጸጽተዋል፤ ሐዋርያቱ ስለ ስሙ ኃይልና ሥልጣን አስተምረዋቸዋል። በዚህም አምነው፣ ንስሐ ገብተው፣ ተጠምቀዋል። ያ የተፈወሰ ሰው የተቀመጠባት ቦታ ኦርያ ትባላለች። ትርጉሟም መልካም ደጅ ማለት ነው። ፈውስ የሚገኝባት፥ ምህረት የሚደረግባት፥ እግዚአብሔር የሚመሰገንባት፥ ወደ እነ ጴጥሮስ ሃይማኖት የመግባት ጥሪ የሚደረግባት ሰናይ ደጅ። ወደድንም ጠላንም በዚህ ዘመን ከሚዲያ አሠራር ተጽእኖ ነጻ መኾን የማይቻልበት ሁኔታ ተፈጥሯል። የቅድስት ቤተክርስቲያን አስተዳደር ይህንን ሁኔታ ተረድቶ እንቅስቃሴ ከጀመረ ገና ጥቂት ጊዜው ነው። የተቀናጀ አሠራርን ከማስፈንና ሚዲያን በአግባቡ ከመጠቀም አንጻር በጣም ብዙ ወደ ኋላ የቀረንበት ነው። በእርግጥ ሚዲያን መልካም ደጅ የማድረግ ሥራ የሁሉም የቤተክርስቲያን ልጆች ኃላፊነት ነው ብለን እናምናለን። ቤተ ኦርያም እንደ አንድ የሚዲያ አማራጭ ቅድስት ቤተክርስቲያን የምትዘክራቸውን ቅዱሳን ትምህርታቸውን፣ ተጋድሏቸውንና ሕይወታቸውን ካለንበት ነባራዊ ሁኔታ አንጻር እየቃኘች ታቀርባለች። የሚዲያ አማራጮቻችንን ይቀላቀሉ! ቴሌግራም፤ https://t.me/burukie2014 ዩቲዩብ፤ www.youtube.com/@ቤተኦርያ-BeteOria ፌስቡክ፤ https://www.facebook.com/profile.php?id=61574859306729
0
4
ቅዱስ አባታችን አባ ሕርያቆስ የእመቤታችንን ቅዳሴ ያደረሰው የልደቷ ዕለት ነበር። ይህም የታወቀው አንድ ጻድቅ ባሕታዊ እመ አምላክን በጠየቃት አንድ ጥያቄ ነው። እንዲህ ሲል፤ “ከ33ቱ በዓላት ማንን
ቅዱስ አባታችን አባ ሕርያቆስ የእመቤታችንን ቅዳሴ ያደረሰው የልደቷ ዕለት ነበር። ይህም የታወቀው አንድ ጻድቅ ባሕታዊ እመ አምላክን በጠየቃት አንድ ጥያቄ ነው። እንዲህ ሲል፤ “ከ33ቱ በዓላት ማንን ትወጃለሽ?” ክብርት እመ አምላክም፤ ‹‹ኪዳነ ምሕረትን፣ ልደታን፣ አስተርእዮን፣ ፍልሰታን›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹ከእነዚህ ከአራቱስ ማንን ትወጃለሽ?›› አላት። እመ ብርሃንም፤ ‹‹ከጠባብ ወደ ሰፊ፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን የወጣሁበት ነውና ልደቴን እወዳለው፤ ቀድሞ እኔ ሳልወለድ እናትና አባቴን መባችሁን አንቀበልም ብለዋቸው አዝነው ተክዘው ነበር፡፡ የእነርሱ ሃዘን ሃዘኔ ነውና እኔን ከወለዱ በኋላ መባቸውን ተቀብለዋቸው ደስ ብሎዋቸዋል፡፡ የእነርሱ ደስታ ደስታዬ ነውና›› አለችው፡፡ እንኳን ለዚህች እመ አምላክ ከበዓሎቿ ሁሉ አብልጣ ለምትወዳት የልደቷ በዓል፣ አባ ሕርያቆስም ቅዳሴዋን ላደረሰባት ዕለት አደረሰን! ይቀላቀሉ👇👇👇 https://t.me/burukie2014
0
5
ሰማዕቱ ሐዋርያ ቅዱስ ማርቆስ፤ የአንድ ጫማ ሰፊን ሕይወት ከመለወጥ ጀምሮ በርዕሰ መንበርነት የቤተክርስቲያን አስተዳደርን በእስክንድርያ መሥርቶ የመራው ቅዱስ ማርቆስ በዚህች ዕለት ሰማዕት ኾነ። እና
ሰማዕቱ ሐዋርያ ቅዱስ ማርቆስ፤ የአንድ ጫማ ሰፊን ሕይወት ከመለወጥ ጀምሮ በርዕሰ መንበርነት የቤተክርስቲያን አስተዳደርን በእስክንድርያ መሥርቶ የመራው ቅዱስ ማርቆስ በዚህች ዕለት ሰማዕት ኾነ። እናቱ ቤቷን ለሐዋርያት የጸሎት ቤት አድርጋ የሰጠች ናት። አጎቱ በርናባስ ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር ሰባኪ ነበር። እኒህን የወንጌል አርበኞችም ተከትሎ ጵንፍልያ ወደምትባል ሀገር ሄዶ ነበር። በሐዋርያቱ የሚደርሰውን መከራ ባየ ጊዜ ግን ሸሽቶ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ። ክርስትና በሂደት የሚታደግበት መንገድ ነውና ሐዋርያቱ በእግዚአብሔር ተአምር በሰላም ተመልሰው፥ በመከራው መካከል ተረማምደው ያስመዘገቡትን ድል፣ የለወጡትን ሕይወት በነገሩት ጊዜ አዘነ። እንደገናም አብሮ መሄድ ፈለገ። ቅዱስ በርናባስም አስከትሎት አብሮ ሲሰብክ፣ ሲያስተምርም ቆይቷል። በኋላም በርናባስ ሲሞት ወደ ቅዱስ ጴጥሮስ ሀገረ ስብከት (ሮሜ) ሄዶ አብሮት አገልግሏል። እዚያም ሳለ ቅዱስ ጴጥሮስ እየተረጎመለት ዛሬ የምናነበውን የማርቆስ ወንጌልን ጽፏል። በእግዚአብሔርም ትእዛዝ ወደ እስክንድርያ ሄዶ ከአንድ ቤተሰብ ጀምሮ ብዙዎችን ወደ እውነተኛዋ ሕይወት መልሷል። የኛና የግብጻውያንንም መንበር በእስክንድርያ መሥርቷል። ብዙዎችን አስተምሮ፣ በክርስትና አጽንቶ ሥራውን ሁሉ ከፈጸመ በኋላ፥ እግዚአብሔር ወደ ዘለዓለማዊ መንግሥቱ ሊያሸጋግረው በወደደ ጊዜ በዕለተ ትንሣኤ በከሃድያን እጅ ጣለው። በገመድ አስረውም ብዙ አንገላትተው በዚህች ዕለት (ሚያዝያ 30) ገድለውታል። ሥጋውን ሊያቃጥሉም በሞከሩ ጊዜ እግዚአብሔር በነጎድጓድ፣ በውሽንፍርም በትኗቸዋል። ምእመናንም ክቡር ሥጋውን አንሥተው በክብር አሳርፈውታል። የሰማዕቱ የቅዱስ ማርቆስ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን! የቴሌግራም ቤታችንን ይቀላቀሉ።👇👇👇 https://t.me/burukie2014
0
6
የምስክርነት ዋጋና ሽልማት፤ ሰማዕትነት ላመኑት ምስክር መኾን ማለት ነው። ምስክርነት በአንድ በኩል ዋጋ ያስከፍላል። በሌላ ደግሞ ሽልማት አለው። ሰማያዊ፣ ዘለዓለማዊ ሽልማት። ዋጋውን ከፍሎ ሽልማቱን
የምስክርነት ዋጋና ሽልማት፤ ሰማዕትነት ላመኑት ምስክር መኾን ማለት ነው። ምስክርነት በአንድ በኩል ዋጋ ያስከፍላል። በሌላ ደግሞ ሽልማት አለው። ሰማያዊ፣ ዘለዓለማዊ ሽልማት። ዋጋውን ከፍሎ ሽልማቱን ለማግኘት ደገሞ ያመኑት ነገር ትክክል መኾን አለበት። ሚያዝያ 28 በዚህች ዕለት ሁለት ቅዱሳን ያመኑበትን ትክክለኛውን ክርስቲያናዊ ሃይማኖታቸውን ትተው በሌላ እንዲያምኑ ተገደው ነበር። የመጀመሪያው አባ ሜልዮስ ይባላል። ኮራሳን ከሚባል ተራራ ላይ ወጥቶ በተጋድሎ ከሚኖርበት የሀገሩ ንጉሥ ሁለት ልጆች ሄደው ለፀሐይና ለእሳት እንዲሰግድ አስገድደውት ነበር። ባልሰማቸውም ጊዜ ከፊትና ከኋላው በወታደሮች ፍላጻዎች ተወግቶ እንዲሞት ኾኖ ሰማዕትነትን ተቀብሏል። ይህ አባት ከመሞቱ በፊት ለገዳዮቹ አንድ ትንቢት ነግሯቸው ነበር። “እኔን በፍላጻ እንዳሰቃያችሁኝ እናንተም እንዲሁ በፍላጻችሁ ትሞታላችሁ” ብሎ። ይህ ቃል ከአንድ ቀን በኋላ ተፈጽሞባቸዋል። ሁለተኛው ደግሞ አባ ብስጣውሮስ ይባላል። ክርስቲያናዊ ሕይወቱ ያስቀናው ጎረቤቱ “ሃይማኖታችንንና ባሕላችንን አይቀበልም” በማለት ለእስላም መኳንንት ከሶታል። እምነቱን እንዲቀይር ብዙ ስጦታዎችን፣ ማታለያዎችን ቢሰጡትም አልተቀበላቸውም። የሚያምነውን ያውቃልና። በሰይፍ አንገቱን ተቆርጦ ሰማዕትነትን ተቀብሏል። ዓለም በእምነትህ ከቆምህ ሰይፏን ይዛ ትመጣብሃለች። የምታምነው እውነት መሆኑ ከገባህ አንገትህን ትሰጣታለህ። ካልገባህ ደግሞ እየሳቅህ የክህደት ትምህርቷን ትጋታለህ። አምላከ ቅዱሳን ከስህተት ጠብቆ፣ በእውነተኛዋ ሃይማኖት ያጽናን! ይቀላቀሉ👇👇 https://t.me/burukie2014
0
7
ሥልጣንን ለድኆችና ለተቸገሩት፣ ሥልጣንን ለገንዘብ፣ ለግል ጥቅማጥቅም ማካበቻ፣ ከፋ ሲልም ሌላውን ለመጉጃ መሣርያ አድርጎ መጠቀም ለዓለሙ ሰው የተለመደ ነው። ይህንን ዕድል ደግሞ ለበጎ የተጠቀሙ ቅዱ
ሥልጣንን ለድኆችና ለተቸገሩት፣ ሥልጣንን ለገንዘብ፣ ለግል ጥቅማጥቅም ማካበቻ፣ ከፋ ሲልም ሌላውን ለመጉጃ መሣርያ አድርጎ መጠቀም ለዓለሙ ሰው የተለመደ ነው። ይህንን ዕድል ደግሞ ለበጎ የተጠቀሙ ቅዱሳን አሉ። ቅዱስ ፊቅጦር ከነዚህ ይመደባል። አባቱ የጨካኙ ንጉሥ ዲዮቅልጢያኖስ አማካሪዎች አለቃ ነበር። እናቱ ደግሞ ደግ ክርስቲያን ነበረች። ልጇን ክርስቲያናዊ ሕይወትን አስተምራ አሳድጋለች። ሃያ ዓመት በኾነው ጊዜ አባት ከንጉሡ ዘንድ ልጁ ፊቅጦርን ወስዶ አሹሞታል። በማዕረግ ከንጉሡ ሦስተኛውን ደረጃ ተሰጥቶታል። በተሾመም ጊዜ ሥልጣኑን ድኆችን፣ ሕሙማንን፣ እስረኞችን፣ ረዳት የሌላቸውን የሚያግዛቸው ኾነ። በዘመኑ የተገደሉ ክርስቲያኖችን እንኳን አንሥቶ መቅበር የማይቻልበት ሁኔታ ነበር። ይህ ቅዱስ ግን ክርስቲያኖችን አክብሮ ይቀብር ነበር። በክርስቲያናዊ ምግባሩም ጣዖት አምላኪ አባቱ ለንጉሥ ከሶ ባሳሰረው ጊዜ እናቱን ያሳሰባት ነገር እርሱ ይረዳቸው የነበሩ ጠያቂ የሌላቸውን ችግረኞች ሁል ጊዜ እንድትጎበናቸው ነበር። ይህ ቅዱስ በዚህች ዕለት (ሚያዝያ 27) ሰማዕትነትን ተቀብሏል። አምላካችን እግዚአብሔር ሁላችንንም በሰማዕቱ ጸሎት ይማረን! ዩቲዩብ ገጽ፤ www.youtube.com/@ቤተኦርያ-BeteOria ፌስቡክ፤ https://www.facebook.com/profile.php?... ቴሌግራም፤ t.me/burukie2014
0
8
ስለ ጥምቀት የተከፈለ ዋጋ ሁለት ልጆችን አፍርተው በትዳር ይኖሩ የነበሩ ክርስቲያን ባልና ሚስት ነበሩ።ሀገሩ ሶርያ ነው። ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት።ንጉሥ ባልን አማካሪው አደረገው።ባልም፥ ስለሥልጣን ለን
ስለ ጥምቀት የተከፈለ ዋጋ ሁለት ልጆችን አፍርተው በትዳር ይኖሩ የነበሩ ክርስቲያን ባልና ሚስት ነበሩ።ሀገሩ ሶርያ ነው። ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት።ንጉሥ ባልን አማካሪው አደረገው።ባልም፥ ስለሥልጣን ለንጉሡ ጣዖት ሰገደ።ሚስት ግን በእምነቷ ጸናች። በዘመኑ በአንጾኪያ አብያተ ክስቲያናት አገልግሎት እንዳይሰጡ ተደርጎ ነበርና እናት ልጆቿን በመርከብ ይዛ ወደ እስክንድርያ ሄደች። በመካከሉም ከባድ ማዕበል ተነሥቶ ሊገለብጣቸው ደረሰ። ልጆቿ የናፈቀችላቸውን የክርስትናን ጥምቀት ሳይጠመቁ መሞታቸው እናትን አሳዘናት።በእምነት ኾና በደሟ ልጆቿን ለማጥመቅ ወሰነች።የቀኝ ጡቷን በምላጭ በጣች።ደምም ወጣ።በጣቷም እየነካች ልጆቿን በመስቀል ምልክት ቀባቻቸው።ከዚያም ማዕበሉ ቆመና እስክንድርያ ደረሰች።ልጆቿንም ይዛ ወደ ማጥመቂያው ሄደች።ካህኑም ልጆቿን ሊያተምቅ ሲሞክር ውኃው ከፈሳሽነት ተቀይሮ ጠጣር ኾነ።ሌሎችን ሲያጠምቅ ውኃ ይኾናል።እነርሱን ሊያጠምቅ ሲል ግን ይገግራል።ሦስት ጊዜ ከሞከረ በኋላ እናትን የኾነውን ጠየቃት።እርሷም ስለድፍረቷም ይቅር ይላት ዘንድ ለመነችው።ይህም አባት የእምነቷን ታላቅነት አድንቆ፣እኒህን ልጆች በእምነት ኾና ደሟን በቀባቻቸው ጊዜ በመለኮታዊ እጁ፣በተአምር ጌታችን እንዳጠመቃቸው ነገራት እርሷ ስለ እምነቷ ይህንን ያህል መንገድ ስትመጣ፥የፍቅር አምላክ ደግሞ ከእርሷ ብዙ እጥፍ ቅርቧ ኾኖላታል። ይህቺ ቅድስት እናት ሥራዋን ፈጽማ ወደ ሀገሯ ስትመለስ ባሏ ተቆጣ ።ለንጉሥም ሄዶ ከሰሳት። በዚህም በእምነት መካድ የተጀመረ የባል ኃጢአት የገዛ ሚስቱንና ልጆቹን ወደማስገደል ተሸጋገረ። ንጉሡም እርሷንና ልጆቿን በእሳት አስጥሎ ሰማዕትነትን እንዲቀበሉ አድርጓቸዋል። የሰማዕቷ ቅድስት ሣራ በረከት ከሁላችንም ጋር ይሁን! ይቀላቀሉ👇👇 https://t.me/burukie2014 @TnshuaBetechrstian
0
9
በዚህ ቪዲዮ ከሚያዝያ 19 እስከ 25 ባሉት ተከታታይ ቀናት በቅድስት ቤተክርስቲያን የሚታሰቡ ቅዱሳን ተጋድሏቸው ከምናገኘው ትምህርት ጋር ተሰናስሎ ቀርቦበታል። ቅዱሳንን በሚወዷቸው ዘንድ ሁሉ ይዳረስ ዘንድ ሊንኩን በማጋራት እንድትተባበሩ እጠይቃችኋለሁ! https://www.youtube.com/watch?v=nGhyG-5w3NE ዩቲዩብ ገጽ፤ www.youtube.com/@ቤተኦርያ-BeteOria ፌስቡክ፤ https://www.facebook.com/profile.php?id=61574859306729 ቴሌግራም፤ t.me/burukie2014
0
10
እናትን ከልጅ መለየት መልካም ነውን? ዕለቱ የእመቤታችን መታሰቢያ ቀን ነው። ለማኙ፥ ለቤተክርስቲያን አቅራቢያ ከሆኑ ጎዳናዎች በአንዱ ዳር ተቀምጠዋል። ከወጭ ወራጁ ገንዘብ፣ ወይም የሚበላ የሚሰጥ ካ
እናትን ከልጅ መለየት መልካም ነውን? ዕለቱ የእመቤታችን መታሰቢያ ቀን ነው። ለማኙ፥ ለቤተክርስቲያን አቅራቢያ ከሆኑ ጎዳናዎች በአንዱ ዳር ተቀምጠዋል። ከወጭ ወራጁ ገንዘብ፣ ወይም የሚበላ የሚሰጥ ካለ እየጠበቁ ይመስላል። ልብሳቸው የነተበ ነው። የፀሐዩ ሙቀትና የምድሩ ግለት መልካቸውን አወይቦታል። ... አባ፥ የማለዳ ጸሎታቸውን በፍጥነት አከናውነው ወደ ሥራቸው እየተጣደፉ በለማኙ በኩል ባለው መንገድ እያለፉ ነው። በቤታቸው ሁልጊዜ በዕለቷ ያስለመዷትን የእመ አምላክን መልክእ ከልጇ ከጌታችን መልክእ ጋር አብሮ ለመጸለይ እንኳን አላደረሳቸውም። የእርሷን ብቻ አድርሰዋል። በለማኙ ትይዩ ደረሱ። ለማኙም ተነሡና ተጣሩ፥ “አንተ? አንተን ነው? ስማ?!” አሏቸው። ተላላፊው ብዙ ነበርና ዞር ዞር ብለው ዐዩ። የለማኙ ዐይን ግን አባ ላይ ነው። ዝም ብለው ዐይዋቸው“እናትን ከልጅ መለየት መልካም ነውን?በል ከእርሱ ቤተክርስቲያን ጠጋ በልና መልክአ ኢየሱስንም አድርስ፣ አታስታጉል!” አሏቸውና ወደ ልመና ሥፍራቸው ተቀመጡ። ደግነቱ አባ የጸሎት መጽሐፍ ይዘው ነበርና በመገረም ከቤተክርስቲያኑ ተጠግተው የተባሉትን ፈጸሙ።ለዚህ የለማኙ ንግግር አንክሮ ይገባል! ለመኾኑ ቅዱስ፣ብፁዕ(ለማኙ) አባቴ፣እንዴት አድርገው ዐዩት? ለመኾኑ ቤት የለዎትም፣ እረፍት ግን አለዎት አይደል? ፣ ፍጹም ሰላም ግን አለዎት አይደል? ከደብዳቢ፣ ከሌባ የሚያስጥል ጉልበት ላይኖርዎት ይችላል፣ እመ አምላክ ግን አለችዎት አይደል? የታደሉ! በየጎዳናው፣ በየመቃብር ቤቱ፣ በየጎጆው፣ በየቤቱ ባላችሁት፣ የእመ አምላክ ፍቅሯ በበዛላችሁ በእናንተ በእናቶቻችንና አባቶቻችን ሐሴት እናደርጋለን። ደግሞም እንመካለን! የአባቶቻችንና እናቶቻችን አምላክ እግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን! www.youtube.com/@ቤተኦርያ-BeteOria✨ @Slehiwetwe
0
11
መልካም የምትመክር ሚስት ብዙ ጊዜ ሚስቶች መልካም መካሪ ናቸው። ቤትህ አምሽተህ አትግባ፣ አትጠጣ፣ በሱስ አትጠመድ፣ ሥራህን በአግባቡ ሥራ'የመሳሰሉትን። ይህ ለአንዳንድ ሰነፍና ትዕቢተኛ ወንዶች ላይ
መልካም የምትመክር ሚስት ብዙ ጊዜ ሚስቶች መልካም መካሪ ናቸው። ቤትህ አምሽተህ አትግባ፣ አትጠጣ፣ በሱስ አትጠመድ፣ ሥራህን በአግባቡ ሥራ'የመሳሰሉትን። ይህ ለአንዳንድ ሰነፍና ትዕቢተኛ ወንዶች ላይዋጥልን ይችላል። ነገር ግን ማንም ጓደኛ የማያይልህ የቅርብ የሚቆረቆርና መሻሻልህን የሚናፍቅ ሰው ብቻ አይቶ የሚሰጠህ ምክር ነው። በጌታችን ሕማምም ቀን መልካም በመምከር የምትታወቅ አንዲት ቅድስት ሴት አለች። የሮማዊው ጲላጦስ ሚስት፣ አብሮቅላ።ባሏ በንጹሑ ደም በጌታችን ላይ አንዳችም ክፉ ነገር እንዳያደርግበት በህልሟ ያየችውን ገልጣ በመልዕክተኛ መክራዋለች። ባሏ ግን ጌታችንን ጎሕ ሲቀድ ጀምሮ እስከ ሦስት ሰዓት መርምሮት ምንም ሳያገኝበት ንጽሕናውን እያወቀ በአይሁድ ጩኸት ተሸንፎ ገርፎ ይሰቅሉት ዘንድ ለፈቃዳቸው አሳልፎ ሰጥቶታል። ሚስቱ የመከረችውን ሰምቶ ሙሉ በሙሉ ፈጽሞ ቢሆን በመጽሐፍ ቅዱስ የምናውቀው የጲላጦስ ታሪክ ሌላ ይሆን ነበር። እርግጥ ነው ጲላጦስ ጌታችንን ለማዳን ብዙ ሞክሯል። ይህንንም አይቶለት ትንሣኤውን በራዕይ ገልጦለት ክርስቲያን ሆኗል። በዚህም የሮሙ ቄሳር ጠርቶ እምነቱን እንዲለውጥ ቢጠይቀውም ስላልተቀበለ በሮም አደባባይ በሰይፍ አንገቱን ተሰይፎ ሰማዕት ሁኗል። ሚስቱም ቁጥሯ ከሠላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አንስት ነው። ውለታ የማታጠፋው ቅድስት ቤተክርስቲያን እኒህን ባልና ሚስቶች በሰኔ ሃያ አምስት ታስባቸዋለች። ከኒህ ባልና ሚስቶች የምንማረው የሚስቶቻችንን መልካም ምክር መስማት ከእውነት ጋር እንድንቆም፣ ከእግዚአብሔር እንዳንርቅ ነውና መልካም የምትመክርን ሚስት ጠበቅ፣ እውነት ትጠፋ ዘንድ፣ ፍትሕ ይዛባ ዘንድ፣ ሥጋህ በመንፈሥህ ይበረታታ ዘንድ አብረኸኝ ተባበር የሚለውን የዓለሙን ሰው ደግሞ ለቀቅ እንድናደርግ ነው! @ቤተኦርያ-BeteOria @TnshuaBetechrstian✨
0
12
“አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል።” 1ኛ ቆሮ 15፥20 ይህ ለእኛ ታላቅ የምስራች ነው። ኢየሱስ ከሙታን ተለይቶ ተነስቷል። እርሱ ሕይወት ነው እና ሞት ይዞ ሊያስቀረው አይችልም። የሞትን ኃይል የሰበረው ኢየሱስ ከሙታን ተለይቶ ተነስቷል። የእርሱ መቃብር ባዶ ነው። ሕያው ነውና ከሙታን መካከል አንፈልገውም። በሞት ውስጥ ላሉት ሁሉ የምንነግራቸው ዜና ይህ ነው ኢየሱስ ከሙታን ተለይቶ ተነስቷል። እንኳን አደረሳችሁ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @Slehiwetwe
0
13
`ውበት ሐሰት ነው፥ ደም ግባትም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች።ምሳሌ 31:30፤'' @Slehiwetwe ይቀላቀሉን::
`ውበት ሐሰት ነው፥ ደም ግባትም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች።ምሳሌ 31:30፤'' @Slehiwetwe ይቀላቀሉን::
0
14
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! እንኳን አደረሳችሁ ‹‹ሰላም ለፀአተ ነፍስኪ እንበለ ፃዕር ወፃማ›› እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር ስድሳ አራት ዓመት ኖራለች፡፡ ይኸውም ሦስት ዓመት በእናት አባቷ ቤት፣ አሥራ ሁለት ዓመት በቤተመቅደስ፣ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ጌታን ፀንሳ፣ ሠላሳ ሶስት ዓመት ከሦስት ወር ከጌታችን ጋር፤ አሥራ አምስት ዓመት በቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ቤት ነው፤ ከዚህ በኋላ ጥር 21 ቀን በ49 ዓ.ም ዐርፋለች፡፡ በእረፍቷ ጊዜ ጌታችን ልታርፍ መሆኗን ሲገልጽት የአንተ እናት ሆኜ እንዴት እሞታለው ብላ ጠይቃ ነበር ጌታችንም መጀመሪያ በገነት ያሉትን ነፍሳት አሳያት በመቀጠልም በሲኦል ያሉ ነፍሳትን አሳያት ርህርህት እናት በሶኦል ያሉትን ማርልኝ አለችው እነዚህ እንዲማሩ( ከሲኦል እንዲወጡ) አንቺ ማረፍ አለብሽ ከዚያም ታወጫቸዋለሽ በማለት ነገራት እመቤታችንም ‹‹ እንዲህ ከሆነማ አንድ ጊዜ ብቻ አይደለም ሰባት ጊዜ ልሙት ›› አለች  በእረፍቷ ሰዓት ልጇ ወዳጇ ቅዱሳን መላእክትን አስከትሎ መጣ ፤ቅዱሳን ሐዋርያት ከያሉበት እንዲሰበሰቡ አደረግ መላእክት እያመሰገኗት ጥር 21 ቀን በ49 ዓ.ም አረፈች ፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡር ሥጋዋን ከመቃብር ለማሳረፍ ወደ ጌቴ ሴማኒ ሲሄዱ አይሁድ በቅናት መንፈስ ተነሣስተው “ቀድሞ ልጇን በ3ኛው ቀን ከሙታን ተነሣ፤ በአርባኛው ቀን ወደ ሰማይ ዐረገ፤ እንደገናም ተመልሶ ይህን ዓለም ለማሳለፍ ይመጣል፤ እያሉ በማስተማር ሕዝቡን ፈጽመው ወስደውታል፡፡ አሁን ደግሞ ዝም ብለን ብንተዋት እርሷንም እንደ ልጇ ተነሣች እያሉ በማስተማር ሲያውኩን ሊኖሩ አይደለምን ኑ ! ተሰብሰቡና በእሳት እናቃጥላት” ብለው ተማክረው ከመካከላቸው ብርቱዎችን መርጠው ላኩ፤ ታውፋንያ የተባለ ጎበዝ የከበረ ሥጋዋን ከሐዋርያት ነጥቆ ሊያስቀር የአልጋውን ሽንኮር ሲይዝ በመልአከ እግዚአብሔር እጁ ተቆርጦ ከአልጋው ላይ ተንጠልጥሎ ቀረ፡፡  ምሕረት በመለመኑ የተነሣ እመቤታችን እንደነበረ መልሳለታለች፡፡     ሰላም ለፀአተ ነፍስኪ እንበለ ፃዕር ወፃማ፡ ለነቢር ዘልፈ በየማነ ወልድኪ ፌማ፡ ማርያም ድንግል ክልልተ  ሞገሰ ወግርማ፡ አጽንዒ በረድኤትኪ ለሕይወትየ ድካማ፡ እምሕይወተ ኄራን አበው ኢታሕጽጺ ዐቅማ።     ‹‹ ያለ ጭንቅና ያለ ጻዕር ከሥጋዋ ለተለየች ነፍስሽ ሰላምታ ይገባል አነዋወሯ በልጀሽ ቀኝ ጎን በክብር ነው፡፡  ድንግል ሆይ ከፈጣሪ ዘንድ የባለሟልነትን ግርማን የተጎናጸፍሽ ነሽ በረድኤትሽ ሰውነቴን ከድካሟ አሳርፊያት ክበሯም ኃይሏም ከደጋግ አባቶች ክብር( ኃይል) ያነሰ አይሁን ፡፡
0
15
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! እንኳን አደረሳችሁ ‹‹ሰላም ለፀአተ ነፍስኪ እንበለ ፃዕር ወፃማ›› እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር ስድሳ አራት ዓመት ኖራለች፡፡ ይኸውም ሦስት ዓመት በእናት አባቷ ቤት፣ አሥራ ሁለት ዓመት በቤተመቅደስ፣ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ጌታን ፀንሳ፣ ሠላሳ ሶስት ዓመት ከሦስት ወር ከጌታችን ጋር፤ አሥራ አምስት ዓመት በቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ቤት ነው፤ ከዚህ በኋላ ጥር 21 ቀን በ49 ዓ.ም ዐርፋለች፡፡ በእረፍቷ ጊዜ ጌታችን ልታርፍ መሆኗን ሲገልጽት የአንተ እናት ሆኜ እንዴት እሞታለው ብላ ጠይቃ ነበር ጌታችንም መጀመሪያ በገነት ያሉትን ነፍሳት አሳያት በመቀጠልም በሲኦል ያሉ ነፍሳትን አሳያት ርህርህት እናት በሶኦል ያሉትን ማርልኝ አለችው እነዚህ እንዲማሩ( ከሲኦል እንዲወጡ) አንቺ ማረፍ አለብሽ ከዚያም ታወጫቸዋለሽ በማለት ነገራት እመቤታችንም ‹‹ እንዲህ ከሆነማ አንድ ጊዜ ብቻ አይደለም ሰባት ጊዜ ልሙት ›› አለች  በእረፍቷ ሰዓት ልጇ ወዳጇ ቅዱሳን መላእክትን አስከትሎ መጣ ፤ቅዱሳን ሐዋርያት ከያሉበት እንዲሰበሰቡ አደረግ መላእክት እያመሰገኗት ጥር 21 ቀን በ49 ዓ.ም አረፈች ፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡር ሥጋዋን ከመቃብር ለማሳረፍ ወደ ጌቴ ሴማኒ ሲሄዱ አይሁድ በቅናት መንፈስ ተነሣስተው “ቀድሞ ልጇን በ3ኛው ቀን ከሙታን ተነሣ፤ በአርባኛው ቀን ወደ ሰማይ ዐረገ፤ እንደገናም ተመልሶ ይህን ዓለም ለማሳለፍ ይመጣል፤ እያሉ በማስተማር ሕዝቡን ፈጽመው ወስደውታል፡፡ አሁን ደግሞ ዝም ብለን ብንተዋት እርሷንም እንደ ልጇ ተነሣች እያሉ በማስተማር ሲያውኩን ሊኖሩ አይደለምን ኑ ! ተሰብሰቡና በእሳት እናቃጥላት” ብለው ተማክረው ከመካከላቸው ብርቱዎችን መርጠው ላኩ፤ ታውፋንያ የተባለ ጎበዝ የከበረ ሥጋዋን ከሐዋርያት ነጥቆ ሊያስቀር የአልጋውን ሽንኮር ሲይዝ በመልአከ እግዚአብሔር እጁ ተቆርጦ ከአልጋው ላይ ተንጠልጥሎ ቀረ፡፡  ምሕረት በመለመኑ የተነሣ እመቤታችን እንደነበረ መልሳለታለች፡፡     ሰላም ለፀአተ ነፍስኪ እንበለ ፃዕር ወፃማ፡ ለነቢር ዘልፈ በየማነ ወልድኪ ፌማ፡ ማርያም ድንግል ክልልተ  ሞገሰ ወግርማ፡ አጽንዒ በረድኤትኪ ለሕይወትየ ድካማ፡ እምሕይወተ ኄራን አበው ኢታሕጽጺ ዐቅማ።     ‹‹ ያለ ጭንቅና ያለ ጻዕር ከሥጋዋ ለተለየች ነፍስሽ ሰላምታ ይገባል አነዋወሯ በልጀሽ ቀኝ ጎን በክብር ነው፡፡  ድንግል ሆይ ከፈጣሪ ዘንድ የባለሟልነትን ግርማን የተጎናጸፍሽ ነሽ በረድኤትሽ ሰውነቴን ከድካሟ አሳርፊያት ክበሯም ኃይሏም ከደጋግ አባቶች ክብር( ኃይል) ያነሰ አይሁን ፡፡
0
16
" ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።" (ትንቢተ ኢሳይያስ 9:6)
" ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።" (ትንቢተ ኢሳይያስ 9:6) እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ  በዓሉ የደስታ፣የድህነት ፣የተስፋ ፣የእምነት፣ የፍቅር ፣ የስኬት፣ ያሰብነው የሚፈፀምበት ይሁንልን !!! @Slehiwetwe ይቀላቀሉን።
0
17
ተወዳጆች። ብፁዕ አባታችን አቡነ ኤርምያስ (ዶ/ር) #በኢንቴክስ-ፉድ-ኤይድ-ፕላስ በሰላም ዘርፍ ዕጩ ሁነዋል። ሁላችንም በመምረጥ እኛኑ ለምነው ተጨንቀው ለጉባኤ ቤት ከሚደክሙት ባሻገር በዚህም ተሳትፈን ለዓላማቸው መሳካት መንፈሳዊ ድርሻችንን መወጣት አለብን። ካሸነፉ #10 ሚሊዮን ብር ያገኛሉ። 9355 ላይ BIW08 ን በመላክ መምረጥ ይቻላል። 🗓 ድምጽ መስጠቱ  እስከ ሐሙስ ታህሳስ 17 ቀን 6፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ይካሄዳል! @Slehiwetwe
0
18
#ሼር #የካህኑን_ልጅ_እንድረስላት በዓለም ዙርያ የምትኖሩ ልጅ የምትወዱ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ወገኖቼ በምስሉ የምናያት ህጻን ስርጉት ጥዑመ ልሳን ትባላለች። ገና የአንድ አመት ከስምንት ወ+2
#ሼር #የካህኑን_ልጅ_እንድረስላት በዓለም ዙርያ የምትኖሩ ልጅ የምትወዱ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ወገኖቼ በምስሉ የምናያት ህጻን ስርጉት ጥዑመ ልሳን ትባላለች። ገና የአንድ አመት ከስምንት ወር ህጻን ስትሆን ዕድሏ ሆኖ መናገርም መንቀሳቀስም በሰላም መተንፈስም መቦረቅም አልቻለችም ከተወለደች ጊዜ ጀምሮ በህመም ላይ ነችና። ወላጆቿ ምንም ገቢ ስለሌላቸው የተሻለ ህክምና ማግኘት አልቻለችም። ዛሬ ላይ #ወገን_ቢያግዘን_የተሻለ_ህክምና ብንሞክርላት ብለው ፊታችን ቆመዋልና ደጋግ ወገኖቻችን ከቻላችሁ በገንዘብ ካልቻላችሁ በሀሳብ፣ በጸሎትና ለሌሎች ረጂዎች እንዲደርስ ሼር በማድረግ እንድታግዟቸው እንማጸናችኋለን። ቄስ ጥዑመ ልሳን ገደፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000561662014 ለበለጠ መረጃ ቄስ ጥዑመ ልሳን ➛ +251967438386
0
19
#ስለ #ትንሿ #ቤተክርስቲያን 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TnshuaBetechrstian
#ስለ #ትንሿ #ቤተክርስቲያን 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TnshuaBetechrstian
0
20
ወርኃ ጽጌ - (ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 6) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስርአት መሰረት ከመስከረም 26 ቀን እስከ ሕዳር 6 ቀን ያለው 40 ቀን የእመቤታችን ና የልጇን ስደት በማሰብ ወርኃ ጽጌን (ዘመነ ጽጌን) ታከብራለች፡፡ ይህ 40 ቀን የእመቤታችንና የጌታ ስደት የሚታሰብበት ዘመን ነው፡፡ ወቅቱ የአበባና የፍሬ ወቅት በመሆኑ እመቤታችን በአበባ ጌታን በፍሬ እየተመሰሉ ጌታችን በአምልላክነት እመቤታችን በፈጣሪ እናትነቷ በተለየ ምስጋና ይመሰገናሉ፡፡ በዚህ በወርኃ ጽጌ (በዘመነ ጽጌ) የሚጾሙ ክርስቲያኖች ሲኖሩ ጾሙን መንፈሳውያን ሰዎች ሳይታዘዙ በራሳቸው ፈቃድ የሚጾሙት ጾም በመሆኑ (የፈቃድ) የትሩፋት ጾም ይባላል፡፡ በቀኖና ቤተክርስቲያን ከታዘዙት ከ7ቱ አጽዋማት ውጪ የሆነ ትርፍ ጾም ማለት ነው፡፡ ከታዘዘው አትርፎ የጾመ ሰው የመጾሙን ዋጋ ያገኛል፡፡ ብዙ መንፈሳዊ ሥራ የሰራ ሰው ብዙ ክብር እንደሚያገኝ መጽሐፍ ይናገራልና፡፡ ‘’እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ሐጢአትዋ ተሰርዮላታል፡፡ ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል’’ (ሉቃ. 7፡47) እንዲል፡፡ የጽጌን ጾም የሚጾሙ ሰዎች በክብርም ከእመቤታችን ጋር ይተባበራሉ፡፡ ነገር ግን የጽጌን ጾም የሚጾሙ ሰዎች ለመመጻደቅ መጾም የለባቸውም፡፡ የማይጾሙ ሰዎችንም መንቀፍና መክሰስ የለባቸውም፡፡ የጽጌ ጾም እንዲጾም በቀኖና ቤተክርስቲያን ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ ተደርጎ ስላልተወሰነ የማይጾሙ ሰዎች ሕገ ጾምን እንዳፈረሱ አድርጎ መውሰድ ስሕተት ነው፡፡ ይልቁንም የሚጾሙ ሰዎች ቢችሉ መጾማቸው እንዳይታወቅባቸው ቢያደርጉ የተሻለ ነው፡፡ "ስትጾሙ እንደግብዞች አትጠውልጉ" (ማቴ. 6፥16) የተባለው ለዚህ ዓይነቱ ጾም ነው፡፡
0