cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ራዕየ ማርያም ✝

በኖኅ ዘመን የነበሩ ሰዎች የተሰጣቸውን ትምህርት ችላ በማለት ሲጨፍሩና ሲደንሱ የጥፋት ውሃ ድንገት ጠራርጎ እንደወሰዳቸው የዓለም ኅልፈት የክርስቶስ መምጣት እንዲሁ ባልታሰበበት ሰዓት ነውና ተዘጋጅታችሁ ጠብቁ። ሠማይ እና ምድር ያልፋሉ፤ ቃሌ ግን ፈፅሞ አያልፍም። ማቴ 24:35

Show more
Advertising posts
1 478Subscribers
No data24 hours
+57 days
+3230 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ቀራኒዮ ቀራኒዮ ስታዩ የእግዚአብሔር ፍቅር ያሟላል ። አንዱን የክርስቶስ ሞት ስታዩ ፍቅርን ይገልጣል፤አንዱን የክርስቶስ ሞት ስታዩ ፍርዱን ያሟላል ስለዚህ ፍርዱን ለራሱ ምህረት ደሞ ለኛ አድርጎ ነው ያዳነን፣ ግርፋቱን ለራሱ ፈውስን ደሞ ለኛ አድርጎ ነው ያዳነን፣የእሾ አክሊሉን ለራሱ ለኛ ደሞ የህይወትን አክሊል አድርጎ ነው ያዳነን። ይህ የክርስቶስ መከራ ሁልጊዜ መታሰብ አለበት! ለምን ይመስላችኋል በቀራንዮ ላይ ጌታ የተሰቀለው ? ቀራኒዮ ማለት "የራስ-ቅል" ማለት ነው ስለዚህ በራስ-ቅል ስፍራ ላይ ጌታችን ተሰቅሎ የሞተው" ሁልጊዜ መከራ ሞቱን ሁልጊዜ መሰቀሉን በአእምሯችን እድናስበው እድናብላላው ነው" (ሳሙኤል አስረስ ) https://t.me/raiye_mariyam
Show all...
2
በይስሐቅ ፈንታ የበገና መዝሙር በይስሐቅ ፈንታ ኢየሱስ ታረደ/2/ ደሙን ከፈለና አዳምን ታደገ/2/ ተጨነቀ ጌታ ተሰቃየ ጌታ የኔ መድኃኔዓለም የአዳም ልጅ አለኝታ እንደሚታረድ በግ ተነዳ ወደ ሞት ንፁህ ኢየሱስ በደል የሌለበት በማመን ሲሸከም የአዳምን መከራ ስቃይ ተቀበለ ደሙ እየተዘራ ለሚገርፋት ሁሉ ምህረትን ሲቸር እርሱ ግን ሲገረፍ ብዙ ተቸገረ የሰማነውን ድምፅ ማን ሰው እኮ አምኗል የእግዚአብሔርስ ክንድ ለነማን ተገልጿል ባየነው ጊዜ ህመም ተሸክሞ ስለበደላችን ተገርፎና ታሞ እጁ የታሰረው ይስሀቅ ተፈቶ ኢየሱስ ቀረበ በሰው ልጆች ፈንታ ንፁህ በግ ቀረበ በደል የሌለበት በደለኛ ሆኖ ሊሰቀል ሊገደል መስቀሉን ተጭኖ በእውነት ደዌያችንን እርሱ ተሰቀለ በሰው ልጆች ፈንታ በእንጨት ተሰቀለ እኛ ግን ከሰስነው እንደ ወንጀለኛ ስለ እኛ ቢሰቀል ሰማያዊው ዳኛ ለሰው ልጆች ህይወት የታሰበውን ሰይፍ አይተናል ሰምተናል በኢየሱስ አንገት ሲያልፍ የመስቀሉ ስዕል ኧረ እንዴት ይገርማል እዩት ንፁህ በግ በአርምሞይነ 🌺🌺 🤲🤲🤲 😥😥
Show all...
😭 2
🙏 5
Repost from Real airdrops
Everyone from now on i'll post real airdrops that have strong community and also are strong projects and also that are real so stay tuned. And i want you to share the link for your contacts and friends tnx y'all. Airdrop|ኤርድሮፕ| በነፃ ያለምንም ገንዘብ በ 24ሰአት አንዴ እየገባችሁ በመቀበል ገንዘብ የምትሰሩበት የ Crypto ዘርፍ ነው 👉🏿በነፃ ያለምንም ገንዘብ የሚሰራ ስራ ነው 👉🏿ብዙ ጊዜ አይፈልግም ለመስራት 👉🏿ማንኛውም ሰው ሊሰራው የሚችል ነው 👉🏿ልምድ | እውቀት| አይጠይቅም 👉🏿ብዙ ገንዘብ ልትሰሩበት ትችላላችሁ NO INVEST ⚡️⚡️⚡️Trust the process 👉 https://t.me/Rea1_airdrop
Show all...
Real airdrops

One way to get free money in the cryptocurrency industry is by participating in airdrop campaigns. so if want real airdrops join us. if u have question dm 👉🏿 @nethnn 👉🏿 @Rea1_airdrop

https://t.me/Rea1_airdrop ኦንላይን ገንዘብ መስራት ከፈለጋቹ join it's real.
Show all...
Real airdrops

One way to get free money in the cryptocurrency industry is by participating in airdrop campaigns. so if want real airdrops join us. if u have question dm 👉🏿 @nethnn 👉🏿 @Rea1_airdrop

#_ይሄ_የመጨረሻው_የዐብይ_ጾም_የንስሐና_የቄደር_ጥምቀት_ነው #_ሼር_ማድረግ_በኃጢአት_ለተጨነቀች_ነፍስ_አድርሱልኝ! ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም ተወዳጆች ሆይ የፊታችን እሑድ ሚያዝያ 13 የዐብይ ጾም የመጨረሻውን የንስሐ እና የቄደር ጥምቀት መርሃ ግብር አዘጋጅተናል። የዐብይ ጾም የመጨረሻው የንስሐ እና የቄደር ጥምቀቱ እሑድ ሚያዝያ 13 ቀን የሆነበት ምክንያት ከፊታችን እሑድ ካለው ቀጥሎ ያለው እሑድ ሆሳዕና ስለሆነ ነው። ወይም ከኒቆዲሞስ ቀጥሎ ያለው የመጨረሻው ሳምንት ሆሳዕና ስለሆነ ነው። ከፊታችን እሑድ እስከ ሆሳዕና ዕለት ያለው አንድ ሳምንት ብቻ ነው። ስለዚህ ለምሳሌ የፊታችን እሑድ ንስሐ ብትገቡ ለአንድ ሳምንት ቀኖና ተቀብላችሁ ወይም የተሰጣችሁን ጾም ጸሎት ስግደት ወዘተ ጨርሳችሁ እሐድ የሆሳዕና ዕለት ለመፈታት ትመጣላችሁ። ከሆሳዕና እለት በኋላ ሰሞነ ሕማማት ስለሆነ በሰሞነ ሕማማት እንኳን ንስሐ መግባት እግዚአብሔር ይፍታ ስለማይባል ያለን ቀን አንድ ሳምንት ብቻ ስለሆነ ይህንን አንድ ሳምንት ንስሐ በመግባት ቄደር በመጠመቅ የነፍስ ዕድላችሁን ተጠቀሙበት። ❤ #_የትራንስፖርት_መምጫው ፦ #_ከመገናኛ አያት መጥተው ከአያት በቦሌ አራብሳ ታክሲ ተሳፍረው አያት አምስት ሰንሻይን አፓርታማ ጋር ወርደው በባጃጅ ቤተ ክርስቲያኑ ደጅ ይወርዳሉ #_ከመገናኛ በአውቶብስ ከሆነ 46 ቁጥር አውቶብስ ተሳፍረው ሰንሻይን አፓርታማ ጋር ወርደው በባጃጅ ቤተ ክርስቲያኑ በር ጋር ይወርዳሉ #_ከቦሌ አያት መጥተው ከዛ የቦሌ አራብሳ ታክሲ ተሳፍረው ሰንሻይን አፓርታማ ጋር ወርደው በባጃጅ ቤተ ክርስቲያኑ ደጅ ይወርዳሉ #_ከቃሊቲ፣ ከቱሉ ዲምቱ፣ ከኮዬ ፈጬ የምትመጡ አያት ወርዳችሁ ከአያት የቦሌ አራብሳ ታክሲ ተሳፍራችሁ አያት አምስት ሰንሻይን አፓርታማ ዳር ወርዳችሁ በባጃጅ ቤተ ክርስቲያኑ ደጅ ትወርዳላችሁ #_ከለገ_ጣፎ አያት መጥታችሁ፣ ከአያት የቦሌ አራብሳ ታክሲ ተሳፍራችሁ አያት አምስት ሰንሻይን አፓርታማ ጋር ወርዳችሁ በባጃጅ ቤተ ክርስቲያኑ ደጅ ትወርዳላችሁ ከጎሮ አያት መጥታችሁ ከአያት አያት አምስት ሳንሻይን አፓርታማ ጋር ወርዳችሁ በባጃጅ ቤተ ክርስቲያኑ ደጅ ትወርዳላችሁ #_በግል_መኪና የምትመጡ ከየትኛውም አቅጣጫ አያት አምስት ሰንሻይን አፓርታማ ደርሳችሁ በመግቢያው ታጥፋችሁ ቀጥታ ቤተ ክርስቲያኑ ደጅ ትደርሳላችሁ ሚያዝያ 11-8-16 ዓ.ም አዲስ አበባ
Show all...
👍 3
🚩የዝሙት አጋንንትና የዝሙት ፈተና በአረጋዊ መንፈሳዊ ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ! ◈ ተወዳጆች ሆይ በመጻሕፍተ መነኰሳት በአረጋዊ መንፈሳዊ ላይ ስለ ዝሙት አጋንንት ክፉኛ ፈተና ተጽፏል። ለአንባቢ እንዲመች ይዘቱን ሳይለቅ አቀራረቡን ብቻ ጥቂት በመቀየር፣ ትንሽ በመጨመር አቅርቤዋለሁ። ከአጋንንት ሁሉ ይልቅ የዚህ የሰይጣን ዝሙት ፈተናው ቡዙ ነው። የዝሙት አጋንንት ሕዋሳታችንን የሚያዝልበት ጊዜ አለ። ልቦናችንን የሚለውጥበት ጊዜ አለ። ሕሊናችንን የሚሰውርበት ጊዜ አለ። ሰውነታችንን ማዘዝ የማንችልበት ጊዜ አለ። ከጸጋ ስጦታ ለይቶ ኅሊናችንን ይለውጣል። ተኝተን ሳለን በዝሙት የሚዋጋን ጊዜ አለ። ◈ የዝሙት አጋንንትን አመጣጡን እንወቅበት። በምን እናውቃለን? ካልን የዝሙት እሳቱ በፊታችን ላይ እንደ እሳት ብልጭ ይልብናል። የዝሙት አጋንንት ሲመጣ ድንግጥ ድንግጥ እንላለን። የዝሙት አጋንንት ሲፈትነን ጸሎታችን፣ ስግደታችን ይከብደናል። እንዳንጸልይ እንዳንሰግድ ከባድ አድርጎ ያሳየናል። የዝሙት አጋንንት ሲፈትነን ጸሎታችንን የአምልኮት ስግደታችንን ትተን ወይም አቋርጠን እንተኛለን። ቆመን ተኝተን ሕዋሳታችንን እንዳብሳለን። እግራችንን እናፋትላለን። ነገር ግን ታግሰን ብንጸልይ የእግዚአብሔር መልአክ ይረዳናል። ብንጸልይ ብንሰግድ ብንተጋ ፈተናው ይቀልልናል ይርቅልናል። ◈ እነዚህ የዝሙት አጋንንት የፈተና ምልክቶች እያሉብን ያለ ጸሎትና ያለ ስግደት መተኛት የለብንም። ያለ ጸሎት ያለ ስግደት ብንተኛ ጠባቂ መልአክ ይርቀናል የዝሙት አጋንንት ቀርቦ ይፈትነናል። የዝሙት አጋንንት በዓይን ይገባል። በዓይን ሲገባ ወደ ሰውነታችን ገብቶ በመቆጣጠር ሕዋሳችንን በእጅ እንድናሽ ያደርገናል። /ይህ አባባል ግለ ወሲብ እንድንፈጽም ያደርገናል ለማለት ነው/ የዝሙት አጋንንት እንዲህ ሲፈትነን በክርስቶስ ኃይል እናማትብበት። ◈ ወደ ተግባረ ዝሙት እንዳይከተን በርትተን መጸለይ መስገድ አለብን። ይህን ካለደረግን የዝሙት አጋንንት ወደ አባለ ዘር ገብቶ ያለ ርህራሄ በዝሙት ፈተና ያስጨንቀናል በዝሙት ይጥለናል። የዝሙት አጋንንት ሰዎችን እንደ ጊንጥ ይነድፋሉ። ቆመንም ቢሆን፣ ተቀምጠንም ቢሆን፣ ሥራም በያዝንበት ጊዜም ቢሆን የዝሙት ስሜት ቢያነሳሳብን በሕሊናችን እንጸልይ እንገስጸው። ◈ ከወትሮ ይልቅ አብዝተን ስንበላ ስንጠጣ የዝሙት ፆር ይጸናብናል። አብዝቶ መብላት መጠጣት እና እላፊ መተኛት የዝሙት አጋንንትን ያቀርበዋል። አብዝተን ስንበላ ስንጠጣ ያኔ የዝሙት አጋንንት ሊዋጋን እንደቀረበ እንወቅ። ሰውነታችንን ለዝሙት ካነሳሳ ያኔ የዝሙት አጋንንት እንደሰለጠነብን እንወቅ። ◈ ወዳጆቼ ብዙዎቻችንን ከንስሐ መንገድ ያራቀን፣ ክብራችንን ቅድስናችንን ያስጣለን፣ ከዓለማዊ እስከ መንፈሳዊ፣ ከምዕመን እስከ አባቶች እናቶች፣ በአምልኮት ሕይወት ከጸኑት፣ በቅዱስ ቁርባን እስከ ተወሰኑት ወዘተ የዝሙት አጋንንት እየፈተነን በቀላሉ እየጣለን ነው። በዚህም ቅድስና ከሕይወታችን ርቋል። ◈ ከዝሙት አጋንንት የሸሸ እግዚአብሔርን ይከተላል። ከዝሙት አጋንንት የሸሸ ጸጋና በረከቱን ይዞ ይኖራል። ከዝሙት አጋንንት የሸሸ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በማዕረግ ያገባል። ከዝሙት አጋንንት የሸሸ ንጽሕናውን ቅድስናውን ይጠብቃል። ከዝሙት አጋንንት የሸሸ ከርኩሰት ይሸሻል። ከዝሙት አጋንንት ሸሽቶ፣ ወደ እግዚአብሔር ተጠግቶ የሚኖር ሰማያዊ ሽልማት ያገኛል። ከዝሙት አጋንንት እና ከዝሙት እንሽሽ። ለዚህም ነው ቅዱስ ጳውሎስ "ከዝሙት ሽሹ" ያለን። /1ኛ ቆሮ 6፥ 18/ ◈ እጅግ በጣም የገረመኝ አረጋዊ መንፈሳዊ "የሰይጣናት ተንኮላቸውን እናገር ዘንድ ከምን ተችሎኝ ላልፈጽመው" በማለት ገና ያላወቅናቸው ነገር ግን በወጥመዱ የተያዝንባቸው፣ በሴራው የወደቅንባቸው ተንኮሎቹ እንዳሉ ይነግረናል። እኛ ግን ስለ ጥንተ ጠላታችን ከገነት ስላስወጣን፣ ከእግዚአብሔር ስለለየን፣ ከዘላለማዊ መንግሥቱ እንድንባረር ስላደረገን ሰይጣን ተንኮሉ ሴራው ውጊያው ሲነገረን ስለ ሰይጣን የተሰበክን መስሎን እንጃጃላለን። ስለ ጠላታችሁ ንቁ እወቁ ሲባሉ ሰይጣን ለምን ተነካ የሚሉ አሉ። ◈ ቅዱስ ጴጥሮስ ግን "ባላጋራችሁ ዲያቢሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሳ አንበሳ ይዞራልና" በማለት ውጊያው ቀላል እንዳልሆነና የማንጸልይ፣ የማንሰግድ፣ ቅዱስ ቁርባን የማንቀበል ከሆነ እንደ አንበሳ፣ በሕይወታችን እያገሳ ስንት ነገራችንን እየነሳ ይኖራል። /1ኛ ጴጥ 5፥8/ ወዳጆቼ ዲያቢሎስ "ፈልጎ እንደሚያገሳ" መባሉን ልብ በሉ። እኛ ባንፈልገውም እሱ ፈልጎ ይዋጋናል። የመንፈሳዊ የጦር ዕቃዎችን ማለትም ጸሎት፣ ስግደት ወዘተ የማያነሳ ሰው ላይ እንደ አንበሳ መሆኑን አንርሳ።
Show all...
🙏 4👍 1🤗 1
"ትሑት ሰው አጋንንትን አይፈራም እግዚአብሔር ሁሉን ያስገዛለታልና።" አባ መቅሪስ 💥🔥
Show all...