ቤተ ኦርያ (ዘቡሩኬ)
Open in Telegram
252
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Data loading in progress...
Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
July '25
July '25
+1
in 0 channels
June '25
+114
in 0 channels
Get PRO
May '25
+138
in 2 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 03 July | 0 | |||
| 02 July | 0 | |||
| 01 July | +1 |
Channel Posts
ቅዱስ ሚካኤልና ሰኔ 12
ሰኔ 12 በዚህች ዕለት የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል፥ የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ፣ የመላእክት አለቃ ኾኖ የተሾመበት በዓለ ሲመቱ ይታሰባል። እንዲሁም ይህ ታላቅ መልአክ የእግዚአብሔር ባለሟል የኾነች ቅድስት አፎምያን ከሰይጣን ፈተና አውጥቶ ሰማያዊ ድልን እንዳስገኛት ይታሰባል። በተጨማሪም የቅዱስ ሚካኤልን በዓል በችግርም፣ በመልካምም ጊዜ ሳያቋርጡ ይዘክሩ የነበሩ ሰዎች ልጅ የኾነውን፣ የተባረከውን ባሕራንን የሞት መልእክት ለውጦ ወደ ሕይወት የመራበትና ቤተክርስቲያኑን እስኪሠራ፣ ሊገድሉት ያሰቡትን ሰዎች ንብረት ያወረሰበት በዘመኑ ሁሉ ያዳነበትና ለሰማያዊ ጸጋ ያበቃበት ይታሰባል። እንዲሁም በእምነት አይሁዳዊ የነበረውን ሕመምተኛ ፈውሶ ወደ ክርስትና የመለሰበት ነው።
በአንድ የታሪክ ሂደት በዚህች ቀን በግብጽ ሀገር ለጣዖት የሚኾን መስዋእት ይቀርብበት የነበረ በዓል ሲኾን እለእስክንድሮስ የተባለ ደግ ሊቀጳጳስ በተሾመ ጊዜ ግን የጣዖቱን መስዋዕት አስቀርቶ፣ መሰዊያውንም አጥፍቶ በታላቅ ሁኔታ የሊቀ መላእክት በዓል እንዲከበር ያደረገበት ይታሰባል። በበዓሉም ድኆች የሚታሰቡበት፣ የመልአኩ ክብሩ፣ ተራዳኢነቱ የሚነገርበት፣ የተራቡ፣ የተጠሙ የሚበሉ የሚጠጡበት ኾነ።
የችግረኞች ፈጥኖ ደራሽ፣ የጻድቃን ሁሉ የተጋድሏቸው ረዳት ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በጸሎቱ በምልጃው ይርዳን፣ ለሳማያዊ ክብርም ያብቃን። ይቆየን!
| 2 | ጌታችን ኢየሱስም ከተነጋገራቸው በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ፥ በአባቱም በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ፡፡ (ማር. 16፡19)
እንኳን ጌታችን በኃይሉና በሥልጣኑ ወደ ሰማይ በክብር ላረገበት በዓል አደረሰን! | 248 |
| 3 | መናኙ ንጉሥና ዘመናችን፤
በዓለም ታሪክ የሰው ልጅ በሀገሩ ሰብዓዊ ክብሩ በመዋረዱ ምክንያት ከሌላ ሀገር ከልብ በመቆርቆር ለእውነተኛ እገዛ የተዘመተባቸው አጋጣሚዎች እጅግ ጥቂት ናቸው። የዛሬን አያድርገውና ኢትዮጵያውያን ነገሥታት ይህንን አድርገዋል። በዛሬው ዕለት እረፍቱ የሚታሰበው ንጉሡ አፄ ካሌብ በናግራን (የዛሬዋ የመን) ሰራዊት አዝምቶ በግፍ ይገደሉና ይሰቃዩ የነበሩ ክርስቲያኖችን በእግዚአብሔር ፈቃድ ረድቶ ነጻ አውጥቷቸዋል። ከድሉ መልስ ጸሎቱን ሰምቶ የረዳው እግዚአብሔርን እንዴት እንደሚያገለግለው አስቦ ወሰነ። የንግሥና ዘውዱን በጌታችን መቃብር ላይ ይቀመጥ ዘንድ ወደ ኢየሩሳሌም ላከ። ቀሪ ዘመኑን “ነፍሱን ሊያድናት የሚፈልግ ያጠፋታል፤ ነፍሱን ስለ እኔ ብሎ የሚያጠፋት ግን ያድናታል። ሰው ዓለምን ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ቢያጠፋ ወይም ቢያጎድል ጥቅሙ ምንድን ነው?” የሚለውን ቃል መሠረት አድርጎ ከዙፋኑ ወርዶ፥ መንኩሶ ገዳም በመግባት፣ በአንዲት ጠባብ ክፍል ተወስኖ፣ በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት፥ከሰው ጋር ሳይገናኝ፥ በአርምሞ ኖረ (ሉቃ 9፥ 24 – 25)። በሰባ ዓመቱ (529 ዓ.ም)፣ በዚህች ዕለት (ግንቦት 20) አረፈ።
ዛሬ ያለንበትን የሞራል ሁኔታ ከዚያ ዘመን ስናነጻጽር የሚደንቅ ልዩነት እናገኛለን። ያኔ በሌላ ሀገር ለተበደለ ለክቡር ሰው ዋጋ ከፍለናል። ዛሬ ግን በሀገራችን ገዳይና ተገዳይ ኾነን በዘመን አመጣሽ መሣርያ በየቀኑ እንሞታለን። ያኔ ፍትሕ በምድር ላይ ይሰፍን ዘንድ እግዚአብሔርን የሚለምኑ መሪዎች ነበሩን። ዛሬ ግን ሕዝባቸውን ለመጨፍጨፍ ባለመሣሪያ ጌቶቻቸውን የሚለምኑ "መሪዎች" አሉን። ያኔ ሁሉን ትቶ ለነፍሱ ብቻ የሚያስብ መሪ ነበረን። ዛሬ ሁሉ ነገር ከሥልጣኑ በታች የሆነ መንግሥት አለን።
አምላካችን እግዚአብሔር በአፄ ካሌብ ጸሎት ይማረን፥ ክፉውን ያርቅልን! | 230 |
| 4 | እውነተኛ እስራኤላዊ/ኢትዮጵያዊ ማን ነው?
በታሪክ የምናውቃቸው አይሁዳዊያን Zealots (ቀናተኞች) ሃይማኖታቸውን ከሮም ቅኝ ገዥዎች ለመጠበቅ ብዙ ተጋድለዋል። Zealot የሚለው ቃልም የዚህ ታሪክ ውጤት ነው። በሂደቱ አስቀድመው ሃይማኖታቸውን ጠንቅቀው ይማራሉ። ቀጥለው ራሳቸውን ከእግዚአብሔርና ከሕጉ ሚዛንነት ውጪ ካሉ ሀሰተኛ ወገንተኝነቶች ነጻ ማውጣት ይጠበቅባቸዋል። በንጹሕ ልብም ከአምላካቸው ጋር እየተነጋገሩ ሃይማኖታቸውን በአፍና በመጽሐፍ ይጠብቃሉ። ከዚያ አልፎ በጉልበት ሃይማኖታቸውንና ሀገራቸውን ሊያጠፋ የመጣውን ጠላት ግን ፊት ለፊት በመፋለም በአምላካቸው ኃይል ያሸንፋሉ። በአደዋ ላይ እንደሆነው ማለት ነው። በዚህ ተጋድሎው የሚታወቀውና ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ናትናኤል (ቀናተኛው ስምዖን) ነው። ይህ ሐዋርያ ስለ ናዝሬቱ ኢየሱስ ተነግሮት ነበር። ጌታችን አስቀድሞ እንዲከተለው በጠራው ሐዋርያ (ፊልጶስ) በኩል። ነገር ግን ጥያቄ ስላበዛ ፊልጶስ እራሱ አይቶ እንዲያምን ጋብዞት ወደ ጌታችን ሄደ። ጌታችንም ናትናኤል ሲመጣ ሲያየው “እነሆ፥ በልቡ ተንኮል የሌለበት እውነተኛ እስራኤላዊ ይህ ነው” ብሎ መሰከረለት (ዮሐ 1፥48)። እርሱ ግን ጌታችንን “በየት ታውቀኛለህ?” ብሎ ጠየቀው እንጂ ጌታችንን አልተቀበለውም። ጌታችንም በአንዲት ቃል ብቻ ሕይወቱን ሁሉ ፈትሾ ልቡ እንዲመለስ አድርጎታል። “ገና ፊልጶስ ሳይጠራህ በበለስ ዛፍ ሥር ሳለህ አይቸሃለሁ” አለው። የአይሁድ ሊቃውንት ሙት ሲያነሣ፣ ሞቶም ሲነሣ፣ ሌሎችንም ተአምራት ሲያደርግ አይተው “አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ” ብለው አላመኑም። ናትናኤል ግን ይህቺን ቃል ብቻ ሲሰማ አመነ። ቤተክርስቲያን ምክንያቶቹን ዘርዝራ ያስቀመጠች ቢሆንም አንዷን ብቻ ላንሣ። ናትናኤል የኦሪት ሊቅ ነውና ከበለስ ዛፍ ሥር ተቀምጦ የተነገረው ትንቢት፣ የተቀጠረው ሱባዔ ደረሰ ወይስ ቀረ እያለ ሲያወጣ ሲያወርድ ይውል ነበርና ይህንን የልቡን ሀሳብ መፈጸሙን ያረጋገጠ የውስጡን ሀሳብ የሚያውቅ መኾኑን በንግግሩ ስላረጋገጠለት ነው። ከዚህ ንግግር በኋላ ሰማዕትነትን እስከተቀበለባት ዕለት (ግንቦት 15) ድረስ በቅድስና እያስተማረ፣ እያጠመቀ፣ ብዙ ነፍሳትን ወደ እውነት መልሶ ወደ ሰማያዊቷ ቤት ተሸጋግሯል።
*እስራኤላዊ/ኢትዮጵያዊ ማለት ሕሊና ዘይሬእዮ ለእግዚአብሔር (የእግዚአብሔርን የሚያይ ሕሊና)፥ ነጻሪ፣ ከሃሊ ምስለ አምላኩ (ከአምላኩ ጋር በሥምረት የሚያይ፣ በአምላኩም ረድኤት ችሎታ ያለው)፤ ሕዝበ እግዚአብሔር (የእግዚአብሔር ሕዝብ) ማለት ነው።
የሐዋርያው በረከት በሁላችን በምናምነው ላይ ይደር!
ገጻችንን ይወዳጁ 👇👇👇
https://t.me/burukie2014
www.youtube.com/@ቤተኦርያ-BeteOria | 1 299 |
| 5 | ቅዱስ ሚካኤል ቅዱሳንን የሚረዳቸው፣ በተጋድሏቸውም የሚያጸናቸው፣ የአገልግሎት ወይም የሰማዕትነት ዘመናቸው እስኪፈጸም ከመከራ ሁሉ የሚያድናቸው መልአክ ነው። በዚህች ዕለት (ግንቦት 12) በምድረ ባቢሎን (ኢራቅ) ለተራቡ አንበሶች በምድር ቤት (ጉድጓድ) ተጥሎ የነበረውን ነብዩ ዳንኤልን ጠያቂ አምጥቶለታል። ነብዩ እንባቆምን ከያዘው ትኩስ ምግብ ጋር ከኢየሩሳሌም በቅጽበት አድርሶ ለዳንኤል የሚመገበውን እንዲሰጠው አድርጓል። ደግሞም መልሶ ወደ ሀገሩ ኢየሩሳሌም አድርሶታል። በዚህች ዕለት ከእግዚአብሔር ቃል ኪዳንን የተቀበለችውን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን የዘመኗ ፍጻሜ እስኪሆን የረዳትም ይህ መልአክ ነው። በዚህች ዕለት የአጽሙ ፍልሰት የሆነውን ጻድቁ አባታችንን አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ከመወለዱ በፊት ወላጆቹን ከጦርነት፣ ከምርኮ፣ ከመከራ ሁሉ ጠብቆ ይህን ጻድቅ እንዲወልዱ የረዳቸው፥ በተጋድሎው ደግሞ ከጠላት ኃይል ሁሉ የጠበቀው ቅዱስ ሚካኤል ነው። በዚህች ዕለት ያረፈው ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅንም በተጋድሎው ሁሉ ያጸነው ይህ መልአክ ነው።
ቅዱስ ሚካኤል ሆይ፥ የቅዱሳንን የጸሎት መሥዋእት ታሳርግ ዘንድ በአብ የመሥዋእት አዳራሽ ለሆነው አኗኗርህ ሰላም እላለሁ! (የግንቦት ድርሳነ ሚካኤል ቁ 48)።
እንኳን ለቅዱስ ሚካኤልና ለረዳቸው ቅዱሳን ሁሉ መታሰቢያ አደረሰን!
ገጻችንን ይወዳጁ 👇👇👇
ቴሌግራም፤ https://t.me/burukie2014 | 2 452 |
| 6 | ትጋትን ከፍጥረት
የቅድስት ቤተክርስቲያንን አምልኮ ሥርዓት ከሠሩልን መካከል ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ዋናው ነው። ይህ ቅዱስ ቤተክርስቲያን የምታዜምበትን ቅዱስ ዜማ ያዘጋጀ ነው። ድጓ፣ ጾመ ድጓ፣ ምዕራፍ፣ ዝማሬና፣ መዋሥዕት የተባሉ የቤተክርስቲያን የአገልግሎት መጽሐፍት የደረሰ ነው። በኢትዮጵያ የክርስትና ታሪክ ፋና ወጊ በሆነችው አክሱም የተወለደው ይህ ቅዱስ በልጅነቱ ትምህርት አልገባው ብሎ ተቸግሮ ነበር። በዚህ ጠባዩም የመናቅ፣ የመገለል፣ በመምህሩም የመቀጣት እጣ ደርሶበት ነበር። በመጨረሻም ተስፋ ቆርጦ ከትምህርት የመኮብለል ጉዙ ጀመረ። በመንገድ ደክሞት ከዛፍ ስር ለእረፍት ተጠለለ። አንዲት ትል ከዛፉ አናት ላይ ፍሬ ለመብላት እየወጣች፥ እስከ ወገቡ እየደረሰች ስትወድቅ አየ። ከብዙ ሙከራዎች በኋላ ከላይ ወጥታ ፍሬውን ስትበላም ተመለከተ። የዚህች ፍጥረት ትጋት የእርሱን ትምህርት መሰልቸት አሳሰበውና ትምህርት ሆነው። ቅዱስ ያሬድ ከዚያ በኋላ ያባከናት ሽርፍራፊ ጊዜ የለችም። ወደ ትምህርት ቤቱ ተመልሶ በአጭር ጊዜ ትምህርቱን ሁሉ አጠናቀቀ። ሕይወቱን ሁሉ ለተጋድሎ አሳልፎ ሰጠ። በዚህም በሥጋ በምድር እየኖረ፣ ሕይወቱ ከሰማይ መላእክትና ከቅዱሳን ጋር ነበር። ከሰማይ የሱራፌልን የምስጋና ዜማ ሰምቶ አመጣልን። ዛሬ እስካለነውም ደረሰ። በምድር ደግሞ እመ አምላክ ደመና ጠቅሳ አባ ሕርያቆስን ከብሕንሳ፣ ቅዱስ ኤፍሬምን ከሶርያ አምጥታ ቅዳሴዋንና ውዳሴዋን እየነገሩት ዜማቸውን አድርሶሷል። ይህ ሁሉ የኾነው ከዛሬ 1450 ዓመታት አካባቢ በፊት ነበር። ይህ ቅዱስ በዚህች ዕለት (ግንቦት 11፣ 571 ዓ.ም) ከዚህች ዓለም እነ ሔኖክና ኤልያስ ወዳሉበት ብሄረ ሕያዋን ተወሰደ።
የቅዱስ ያሬድ የጸሎቱና የትምህርቱ በረከት ይደርብን!
ገጻችንን ይወዳጁ👇👇👇
https://t.me/burukie2014 | 244 |
| 7 | No text... | 252 |
| 8 | በባሕር የተጣለችው ንግሥት
ይህ ቀረሽ የማትባል መልከ መልካም ነበረች። ያለ ኃጢአቷ ባሏ አንሥቶ ወደ ባሕር ወረወራት። ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ አቅፎ በሰላም ወደ ሀገረ ሮሐ አደረሳት (የያኔው ሶርያ)። የአካባቢው ንጉሥ ቁንስጣ ዐያትና ወደዳት። ሚስቱም ሆነች። ጸነሰች። እርሱም በዚያው በሮሐ ትቷት ወደ ግዛቱ ዋና ከተማ በራንጥያ ተመለሰ። ወንድ ልጅንም ወልዳ አሳደገች። ልጇም በአካል፥ ወታደራዊ የአካል ብቃትን ገንብቶ አደገ። በመንፈስ ክርስትያናዊ ሥነ ምግባርን አስተማረችው። በአስተሳሰብ (በጥበብ) ደግ፣ የዋሕ፣ ላመነበት ሟች አድርጋ አሳደገችው። የክርስትና ጥምቀትን ግን አላስጠመቀችውም ነበር። ይህ የኾነው ደግሞ ይህቺ እናት ከእግዚአብሔር ጋር ትነጋገር ነበርና ወቅቱ አለመሆኑን ቢያስረዳት ነው። ቅዱስ ሚካኤልም ረዳቷ ነበር። ልጇ ክርስቲያን ቢሆን ስዕለትን እንድትሳል ነገራት። እርሷም ከ300 ዓመታት በላይ በአይሁድ፣ በኢየሩሳሌም የተቀበረውን የጌታችንን መስቀል ልታወጣ ተሳለች። ልጇ አድጎ በጎለመሰ ጊዜ ወደ አባቱ ላከችው። አባቱም ባየው ጊዜ በሁሉም አድጎ አገኘው። በመንግሥቱም በታላቅ ሥልጣን ሾመው። ከ 2 ዓመታት በኋላም ሞተ። ልጁም ነገሠ። በበራንጥያም ፍትሕን አሰፈነ። ለድኆች የሚራራ፣ ሌቦችን የሚገራ ሆነ። በደግነቱ፥ በፈታሒነቱ፣ በርቱዕነቱ በዓለም ሁሉ መነጋገሪያ ሆነ። በሮም የባርነት አስተዳደር የነበሩት ሁሉ እርዳታውን ናፈቁ። እንዴት እንደሚረዳቸው ሲመረምር በቀትር በሰማይ የመስቀሉ ምልክት ፀሐይን ጋርዷት አየ። በዚያ ምልክትም ጠላቱን እንደሚያሸንፍ አምላካዊ ድምጽን ሰማ። የመንግሥቱም ምልክት አድረገው። በመስቀሉ ኃይል ድል አድርጎ ክርስቲያን ጠል ንጉሥን አሸንፎ በሮም ነገሠ። በዓለምም የክርስትናን ክብር መለሰ። ያኔም የእናቱ ስዕለት ተፈጸመና እናቱም ኢየሩሳሌም ሄዳ ቅዱስ መስቀሉን አወጣች። የዚህ ንጉሥ መሠረቱ እናቱ ናት። ንግሥት ዕሌኒ በዚህች ዕለት አርፋ ወደ አባቷ መንግሥት በክብር ሄዳለች። በዘመናቺንም ልጆቻችሁን በቤታችሁ በፍቅር፣ በሃይማኖት፣ በጥበብ የምታሳድጉ እናቶች ክብር ይገባችኋል።
የንግሥት ዕሌኒ የጸሎቷ በረከት ይደርብን!
ይቀላቀሉ👇👇👇
https://t.me/burukie2014 | 246 |
| 9 | ጌታችን እግዚአብሔር በይባቤ መላእክት በቅዳሴ ዐረገ። ለፈጣሪያችን ምሥጋና አቅርቡ።
ለንጉሣችን ለክርስቶስ ዘምሩ። መዝ 46፥5
እንኳን ለጥንተ ዕርገቱ አደረሰን! | 219 |
| 10 | ቅዱስ አትናቴዎስ በሚታሰብባት በዚህች ዕለት በዘመናችን የነበሩትን የሃይማኖት አርበኛ ክቡር አለቃ አያሌውን ብናስባቸውስ?
አባቷን በሕመም አልጋው ስታስታምም የነበረችው ደራሲ ስምረት አያሌው ታምሩ የአባታችንን የመጨረሻዎቹን ሰዓታት እንዲህ ታስታውሳለች፤
...ቀስ ብዬ የአባቴን ከንፈር ለማርጠብ የሚያስችለኝን ያህል ጥጥ በውኃ ውስጥ ነክሬ አፉን ለመጠራረግ ስሞክር የሚገርም ነገር ገጠመኝ። ከአፉ ከሚወጣው ትንፋሽ የጽጌረዳ አበባ አይነት ሽታ ሸተተኝ። ግራ ተጋባሁ። በአልጋው አካባቢ አንዳች የሚሸት ነገር መኖር አለመኖሩን ለማረጋገጥ ግራና ቀኝ የነበሩትን ኮመዲናዎችና ትራሶች በጥንቃቄና በጥርጣሬ ፈተሽኋቸው። አንዳችም የጽጌረዳ ሽታ ያለው ነገር አልነበረም። በጣም ከመገረሜ የተነሣ የአባቴን ትንፋሽ ደግሜ ለማሽተት ሞከርኩኝ። የጽጌረዳ አበባ መሰሉ ሽታ የሚወጣው ከአባቴ አፍ ውስጥ ነበር። ... በዚህ ግርታ ውስጥ እንዳለሁ እንደ ነፋስ ሽውታ ያለ እንቅስቃሴ በመኝታ ቤቱ ውስጥ ተሰማኝ። ከሽውታው ውስጥ በስም ለይቼ የዚህ አበባ ሽታ ነው የማልለው ልዩና ግሩም የሆነ መዓዛ ሸተተኝ። ... “አይዞሽ አትጨነቂ፥ አትፍሪ፤ እኔ አባትሽ ዓለምን አሸንፌዋለሁ” አለኝ። በጣም ደነገጥሁ።... እያለች ትቀጥላለች።
አባቴና እምነቱ፤ ገጽ 284-286።
የተገለጠ የሃይማኖት ፍሬ ይህ ነው! | 286 |
| 11 | ተጋዳዩ ሐዋርያና ዘመናችን፤
የተወለደው ክርስቲያናዊ ካልሆኑ ቤተሰቦች ነው። ከአካባቢው ልጆች ጋር በነበረው ቀረቤታ ወደ ክርስትና ተሳበ። ተማረ፤ ተጠመቆም የእግዚአብሔር ልጅነትን አገኘ። በትጋትና በቅልጥፍና አገለገለ። ከዲቁና እስከ ጵጵስናም ደረሰ። በዘመኑ ነገረ ተዋሕዶውን አጣሞ ስሁት ትምህርት ሲያስተምር የነበረውን አርዮስን ከ317 ሌሎች ጳጳሳትና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የጉባዔው ጸሐፊ ሆኖ አወገዘ። ቀጥሎም 20ኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ኾኖ በትጋት ማገልገል ጀመረ። አርዮሳዊ ንጉሥ ሲነግሥ ግን እርሱን አባሮ አርዮሳዊ ሊቀ ጳጳሳት በመንበሩ አስቀመጠ። ለአስራ አምስት ዓመታት በእስር፣ በስደት፣ በእንግልት አሳለፈ። ጥፍሩንና የሰውነት ክፍሉን ቢቆራርጡት፥ የቆራረጡትን የአካል ክፍል አሽጎ “እነሆ የሃይማኖት ፍሬ” ብሎ በእምነታቸው ጸንተው እንዲጠብቁ ላከላቸው። በዚህ ሁኔታ የቤተክርስቲያንን እውነተኛ አስተምህሮ ጠብቆ፣ አስጠብቆ ለኛ ትውልድ አሸጋገረልን። ሐዋርያ የተባለው ቅዱስ አትናቴዎስ በዚህች ዕለት (ግንቦት 7) አረፈ።
ዛሬም ቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ በባለሥልጣናት ተጽእኖ ተሾመው እንደ አርዮስ ሁሉ የክህደት ትምህርትን ያለመሸማቀቅ የሚያስተምሩበት ዘመን ላይ ነን። ያው ከትናንቱ የተለየ ነገር የለም። ያኔ እነ ቅዱስ አትናቴዎስ ታስረው፣ ተጋድለው እዚህ ያደረሷት ቤተክርስቲያን ዛሬም የሚጋደሉላትን ትጋብዛለች። የሚጋደሉ ይጋደሉላታል፤ የሚክዱም ይክዷታል። ነገንም ትቀጥላለች። እንደ አርዮስ አይነት ከሃዲ፣ ከእንደ ሁለተኛው አርዮሳዊው ቆስጠንጢኖስ ጋር እያሴረ፥ እንደ አትናቴዎስ አይነት ሃይማኖተኛ እየፈጠረ ዑደቱ ይቀጥላል።
የቅዱስ አትናቴዎስ የተጋድሎውና የጸሎቱ በረከት ከሁላችን ጋር ይኑር!
ይቀላቀሉ! 👇👇👇
https://t.me/burukie2014 | 4 665 |
| 12 | የፈጠረንን አምላክ አስበን፥ ከፊቱ ጸሎትን ማድረስ በራሱ የእግዚአብሔርን ፈቃድና ምሕረት ይፈልጋል።...
ጸሎቴን ያልከለከለኝ፥ ምሕረቱንም ከእኔ ያላራቀ፥ እግዚአብሔር ይመስገን (መዝ 65፥ 20)።
ይቀላቀሉ! 👇👇👇
ቴሌግራም፤ https://t.me/burukie2014
ዩቲዩብ፤ www.youtube.com/@ቤተኦርያ-BeteOria | 2 019 |
| 13 | ነብዩ ኤርምያስና የባቢሎን ምርኮ
ነብየ እግዚአብሔር ኤርምያስ በአይሁድ እጅ ተወግሮ በዚህች ዕለት (ሚያዝያ 5) ሰማዕት ኾነ። የእግዚአብሔርን ቃል በማስተማሩ፣ ከኃጢአታቸው እንዲመለሱ፥ ንስሐም እንዲገቡ በመንገሩ ወገሩት። እግዚአብሔር፥ በነብዩ በኩል ነግሯቸው አልሰማ ያለውን ሕዝብ ለባቢሎኑ ንጉሥ አሳልፎ ሰጣቸው። ሰባ ዓመትም በባርነትም ገዛቸው።
በርኩሰቷ እግዚአብሔርን ያሳዘነችው “ታላቂቱ ከተማ” (ባቢሎን) ቅዱስ ቃሉን አልሰማ ያለን ሁሉ ትማርከዋለች። ባቢሎን እንዲህ ተብሎላታል፤ “የአጋንንት ማደሪያ ኾነች፤ የርኩሳንም መናፍስት ሁሉ መጠጊያ ሆነች፤ አሕዛብ ሁሉ ከዝሙቷ ቁጣ ወይን ጠጅ የተነሣ ወድቀዋልና፤ የምድርም ነገሥታት ከእርሷ ጋር ሴሰኑ፤ የምድርም ነጋዴዎች ከቅምጥልነቷ ኃይል የተነሣ ባለጠጋዎች ሆኑ፤” (ራእይ 18፥ 2-3)።
ሕዝብ ወደ ባቢሎን በመማረኩ ቅዱሳን ያዝናሉ። ደስታቸውም በባቢሎን ላይ እግዚአብሔር የሚሰጠው ፍርድ ነው። “ሰማይ ሆይ! ቅዱሳን ሐዋርያት፥ ነቢያትም ሆይ! በእርሷ ላይ ደስ ይበላችሁ፤ እግዚአብሔር ፈርዶላችኋልና” (የዮሐንስ ራእየ 18)።
አምላካችን እግዚአብሔር ከቤቱ የራቅነውን፣ የቅዱሳንን ቃል ሁሉ ያቃለልነውን በነብዩ ኤርምያስ ጸሎት ከባቢሎን ምርኮ መልሶ በቤቱ አጽንቶ ያኑረን!
ይቀላቀሉ!
ቴሌግራም፤ https://t.me/burukie2014
ዩቲዩብ፤ www.youtube.com/@ቤተኦርያ-BeteOria | 2 592 |
| 14 | መልካሟ ደጅ፥ ኦርያ
ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ልምሾ ኾኖ የተወለደ ሰው ነበር። እግሩ አይቆምለትም፣ ወገቡ አይጸናለትም። ከቦታ ወደ ቦታ የሚያንቀሳቅሰው ሌላ ሰው ነው። ይህ ሰው አንድ ሥራ ብቻ ነበረው። ልመና። ሲነጋ ወስደው ከቤተክርስቲያን ደጅ ላይ ያስቀምጡታል። ከሚገባውና ከሚወጣው ሲለምን ይውላል። ማታ መጥተው፥ ያገኘውን ገንዘብ ተቀብለው፥ ወደ ቤቱ ይወስዱታል።
ወደዚህ ቤተክርስቲያን ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ሁለት ሰዎች ለጸሎት እየገቡ ነው። ሁሉንም እንደሚለምነው ለመናቸው። በትኩረትም ተመለከቱት። ዘልቀው የልቡን ሁሉ ገመና አዩ። ያሰረውን ኃይል፣ የያዘውን ጠላት አስተዋሉ። ቀጥሎም አንደኛው እንዲህ አለው፤ “ወደ እኛ ተመልከት”። የሚሰጡትን ገንዘብ ከእጃቸው ሲፈልግ አየውና “ወርቅና ብር የለኝም፤ ያለኝን ግን እሰጥሃለሁ፤ እነሆ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሥተህ ሂድ” አለው። በቀኝ እጁም ይዞ አስነሣው። ቆመ፣ ዘለለ፣ ሮጠም። እግዚአብሔርንም እያመሰገነ ከእነርሱ ጋር ወደቤተ መቅደስ ገባ። ይህ ታሪክ በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ሦስት የተመዘገበ ነው። “ወደ እኛ ተመልከት” ያለው ቅዱስ ጴጥሮስ ነበር። አብሮትም የነበረው ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ነው። “ወደ እኛ ሃይማኖት ግባ” እያሉ፣ ጥሪ እያቀረቡለት ነበር። እርሱም ፊቱን ወደ እምነቱ መልሷል። በዚህም ተፈውሷል።
ይህንን ያዩ የአካባቢው ሰዎች ተደንቀዋል፤ ይህ የተሠራው በሰቀሉት በጌታችን ስም በመኾኑ ተጸጽተዋል፤ ሐዋርያቱ ስለ ስሙ ኃይልና ሥልጣን አስተምረዋቸዋል። በዚህም አምነው፣ ንስሐ ገብተው፣ ተጠምቀዋል።
ያ የተፈወሰ ሰው የተቀመጠባት ቦታ ኦርያ ትባላለች። ትርጉሟም መልካም ደጅ ማለት ነው። ፈውስ የሚገኝባት፥ ምህረት የሚደረግባት፥ እግዚአብሔር የሚመሰገንባት፥ ወደ እነ ጴጥሮስ ሃይማኖት የመግባት ጥሪ የሚደረግባት ሰናይ ደጅ።
ወደድንም ጠላንም በዚህ ዘመን ከሚዲያ አሠራር ተጽእኖ ነጻ መኾን የማይቻልበት ሁኔታ ተፈጥሯል። የቅድስት ቤተክርስቲያን አስተዳደር ይህንን ሁኔታ ተረድቶ እንቅስቃሴ ከጀመረ ገና ጥቂት ጊዜው ነው። የተቀናጀ አሠራርን ከማስፈንና ሚዲያን በአግባቡ ከመጠቀም አንጻር በጣም ብዙ ወደ ኋላ የቀረንበት ነው። በእርግጥ ሚዲያን መልካም ደጅ የማድረግ ሥራ የሁሉም የቤተክርስቲያን ልጆች ኃላፊነት ነው ብለን እናምናለን። ቤተ ኦርያም እንደ አንድ የሚዲያ አማራጭ ቅድስት ቤተክርስቲያን የምትዘክራቸውን ቅዱሳን ትምህርታቸውን፣ ተጋድሏቸውንና ሕይወታቸውን ካለንበት ነባራዊ ሁኔታ አንጻር እየቃኘች ታቀርባለች።
የሚዲያ አማራጮቻችንን ይቀላቀሉ!
ቴሌግራም፤ https://t.me/burukie2014
ዩቲዩብ፤ www.youtube.com/@ቤተኦርያ-BeteOria
ፌስቡክ፤ https://www.facebook.com/profile.php?id=61574859306729 | 4 157 |
| 15 | እኔ ተኛሁ አንቀላፋሁም፤ እግዚአብሔርም ደግፎኛልና ነቃሁ። ከሚከብቡኝ ከአእላፍ ሕዝብ አልፈራም። መዝ 3፥5
እንኳን ለ4ኛው የጌታችን ትንሣኤ ሳምንት አደረሰን! | 255 |
| 16 | ያለንን ሁሉ ልናጣ እንደምንችል አስበን እናውቃለን? ለዘመናት የገነባነው ቤት፥ ያካበትነው ሀብትና ንብረት በቅጽበት ሊወድም ይችላል። ልጆቻቻንን፥ በቅጽበት ልናጣቸው እንችላለን። ጤናችን ታውኮ መቆም፥ መቀመጥ፥ መተኛትም የማንችልበት ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል። ዘመድ፥ ወዳጅ፥ ጓደኛ፥ ጎረቤት ሁሉ ሁኔታችንን ዐይቶ እንዳልተፈጠርን ሊረሳን ይችላል። በእኛ ዘመን ይህ ሁሉ ሲኾን በተደጋጋሚ እየሰማን፥ እያየንም ነው። ጻድቁ ኢዮብ እኒህን ሁሉ ፈተናዎች በእግዚአብሔር ፈቃድ ተፈትኗቸው ነበር። ሁሉንም አጥቶ ጤናውም ተቃውሶ፣ ሰውነቱ ተበላሽቶ በነበረበት ዘመን የገጠመው የመጨረሻው ፈተና “ይህ ሁሉ ሲኾን እግዚአብሔር ሊረዳህ ሲገባ አልረዳህምና ሰድበኸው ሙት” አይነት ምክር ነበር። እርሱ ግን “እርሱ ሰጠ፤ እርሱ ነሳ። ሲያስገኘኝ ያመሰገንሁትን አምላክ፥ ሲያሳጣኝም አመሰግነዋለሁ” ብሎ በምስጋና ጸና። እግዚአብሔርን የማማረር ቃል አልተናገረም። በመጨረሻም እግዚአብሔር ተገለጠለት፤ ባረከውም። ከነበረው ሁሉ አብልጦ ሰጠው። መቶ ሰባ ሌሎች ዓመታትንም በተድላ፥ በደስታ አኖረው። ዛሬም ራሳቸው ፈተናችን የኾኑት ሰይጣንና የሰይጣን ተላላኪዎች “እንዲህ በመከራ ኾነህ ያላየህ እግዚአብሔር ትክክለኛው ባይኾን ነው፤ቤተክርስቲያኗም ስሁት የምታስተምር ናት፥ እርሱንና እርሷን ስደብና ወደኛ ና፥ እመ አምላክ የምትላትን ተውና ተከተለን” የሚሉ ድምጾች የሚሰሙበት ነው። በዚህች ዕለት (ግንቦት 2) እንዲህ አይነቶችን የምንረታበትን የጻድቁን የኢዮብን ታሪክ እንድናስብ ቤተክርስቲያን ታሳስበናለች።
እንኳን ለጻድቁ ኢዮብ መታሰቢያ በዓል አደረሰን!
ይቀላቀሉ👇👇👇
https://t.me/burukie2014 | 2 106 |
| 17 | ቅዱስ አባታችን አባ ሕርያቆስ የእመቤታችንን ቅዳሴ ያደረሰው የልደቷ ዕለት ነበር። ይህም የታወቀው አንድ ጻድቅ ባሕታዊ እመ አምላክን በጠየቃት አንድ ጥያቄ ነው። እንዲህ ሲል፤
“ከ33ቱ በዓላት ማንን ትወጃለሽ?”
ክብርት እመ አምላክም፤
‹‹ኪዳነ ምሕረትን፣ ልደታን፣ አስተርእዮን፣ ፍልሰታን›› አለችው፡፡
እርሱም ‹‹ከእነዚህ ከአራቱስ ማንን ትወጃለሽ?›› አላት።
እመ ብርሃንም፤
‹‹ከጠባብ ወደ ሰፊ፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን የወጣሁበት ነውና ልደቴን እወዳለው፤ ቀድሞ እኔ ሳልወለድ እናትና አባቴን መባችሁን አንቀበልም ብለዋቸው አዝነው ተክዘው ነበር፡፡ የእነርሱ ሃዘን ሃዘኔ ነውና እኔን ከወለዱ በኋላ መባቸውን ተቀብለዋቸው ደስ ብሎዋቸዋል፡፡ የእነርሱ ደስታ ደስታዬ ነውና›› አለችው፡፡
እንኳን ለዚህች እመ አምላክ ከበዓሎቿ ሁሉ አብልጣ ለምትወዳት የልደቷ በዓል፣ አባ ሕርያቆስም ቅዳሴዋን ላደረሰባት ዕለት አደረሰን!
ይቀላቀሉ👇👇👇
https://t.me/burukie2014 | 3 027 |
| 18 | ሰማዕቱ ሐዋርያ ቅዱስ ማርቆስ፤
የአንድ ጫማ ሰፊን ሕይወት ከመለወጥ ጀምሮ በርዕሰ መንበርነት የቤተክርስቲያን አስተዳደርን በእስክንድርያ መሥርቶ የመራው ቅዱስ ማርቆስ በዚህች ዕለት ሰማዕት ኾነ። እናቱ ቤቷን ለሐዋርያት የጸሎት ቤት አድርጋ የሰጠች ናት። አጎቱ በርናባስ ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር ሰባኪ ነበር። እኒህን የወንጌል አርበኞችም ተከትሎ ጵንፍልያ ወደምትባል ሀገር ሄዶ ነበር። በሐዋርያቱ የሚደርሰውን መከራ ባየ ጊዜ ግን ሸሽቶ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ። ክርስትና በሂደት የሚታደግበት መንገድ ነውና ሐዋርያቱ በእግዚአብሔር ተአምር በሰላም ተመልሰው፥ በመከራው መካከል ተረማምደው ያስመዘገቡትን ድል፣ የለወጡትን ሕይወት በነገሩት ጊዜ አዘነ። እንደገናም አብሮ መሄድ ፈለገ። ቅዱስ በርናባስም አስከትሎት አብሮ ሲሰብክ፣ ሲያስተምርም ቆይቷል። በኋላም በርናባስ ሲሞት ወደ ቅዱስ ጴጥሮስ ሀገረ ስብከት (ሮሜ) ሄዶ አብሮት አገልግሏል። እዚያም ሳለ ቅዱስ ጴጥሮስ እየተረጎመለት ዛሬ የምናነበውን የማርቆስ ወንጌልን ጽፏል። በእግዚአብሔርም ትእዛዝ ወደ እስክንድርያ ሄዶ ከአንድ ቤተሰብ ጀምሮ ብዙዎችን ወደ እውነተኛዋ ሕይወት መልሷል። የኛና የግብጻውያንንም መንበር በእስክንድርያ መሥርቷል። ብዙዎችን አስተምሮ፣ በክርስትና አጽንቶ ሥራውን ሁሉ ከፈጸመ በኋላ፥ እግዚአብሔር ወደ ዘለዓለማዊ መንግሥቱ ሊያሸጋግረው በወደደ ጊዜ በዕለተ ትንሣኤ በከሃድያን እጅ ጣለው። በገመድ አስረውም ብዙ አንገላትተው በዚህች ዕለት (ሚያዝያ 30) ገድለውታል። ሥጋውን ሊያቃጥሉም በሞከሩ ጊዜ እግዚአብሔር በነጎድጓድ፣ በውሽንፍርም በትኗቸዋል። ምእመናንም ክቡር ሥጋውን አንሥተው በክብር አሳርፈውታል።
የሰማዕቱ የቅዱስ ማርቆስ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን!
የቴሌግራም ቤታችንን ይቀላቀሉ።👇👇👇
https://t.me/burukie2014 | 4 978 |
| 19 | ስለ ጌታችን ልደት ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ አለ፤
ምን እላለሁ? ምንስ እናገራለሁ? ከዘመን አስቀድሞ የነበረው እርሱ ሕፃን ሆኗልና፡፡ እኔ ፈጽሜ አደንቃለሁ። ከሰማየ ሰማያት በላይ የሚሆን፣ በዘለዓለማዊ ዙፋን የሚኖር እርሱ በበረት ተጣለ፡፡ ከሥጋዌ አስቀድሞ አይዳሰስ የነበረ አንዱ እርሱ በምድራውያን እጅ ተዳሰሰ፡፡ ኀጢአትን የሚያስተሰርይ እርሱን በጨርቅ ጠቀለሉት፡፡ ይህን ወዷልና፤
(ሃይማኖተ አበው ዘዮሐንስ አፈ ወርቅ፣ ፷፮፥፲፯)፡፡
እንኳን ለጌታችን ልደት መታሰቢያ ወርሐዊ በዓል በሰላም አደረሰን! | 213 |
| 20 | የምስክርነት ዋጋና ሽልማት፤
ሰማዕትነት ላመኑት ምስክር መኾን ማለት ነው። ምስክርነት በአንድ በኩል ዋጋ ያስከፍላል። በሌላ ደግሞ ሽልማት አለው። ሰማያዊ፣ ዘለዓለማዊ ሽልማት። ዋጋውን ከፍሎ ሽልማቱን ለማግኘት ደገሞ ያመኑት ነገር ትክክል መኾን አለበት። ሚያዝያ 28 በዚህች ዕለት ሁለት ቅዱሳን ያመኑበትን ትክክለኛውን ክርስቲያናዊ ሃይማኖታቸውን ትተው በሌላ እንዲያምኑ ተገደው ነበር። የመጀመሪያው አባ ሜልዮስ ይባላል። ኮራሳን ከሚባል ተራራ ላይ ወጥቶ በተጋድሎ ከሚኖርበት የሀገሩ ንጉሥ ሁለት ልጆች ሄደው ለፀሐይና ለእሳት እንዲሰግድ አስገድደውት ነበር። ባልሰማቸውም ጊዜ ከፊትና ከኋላው በወታደሮች ፍላጻዎች ተወግቶ እንዲሞት ኾኖ ሰማዕትነትን ተቀብሏል። ይህ አባት ከመሞቱ በፊት ለገዳዮቹ አንድ ትንቢት ነግሯቸው ነበር። “እኔን በፍላጻ እንዳሰቃያችሁኝ እናንተም እንዲሁ በፍላጻችሁ ትሞታላችሁ” ብሎ። ይህ ቃል ከአንድ ቀን በኋላ ተፈጽሞባቸዋል።
ሁለተኛው ደግሞ አባ ብስጣውሮስ ይባላል። ክርስቲያናዊ ሕይወቱ ያስቀናው ጎረቤቱ “ሃይማኖታችንንና ባሕላችንን አይቀበልም” በማለት ለመኳንንት ከሶታል። እምነቱን እንዲቀይር ብዙ ስጦታዎችን፣ ማታለያዎችን ቢሰጡትም አልተቀበላቸውም። የሚያምነውን ያውቃልና። በሰይፍ አንገቱን ተቆርጦ ሰማዕትነትን ተቀብሏል።
ዓለም በእምነትህ ከቆምህ ሰይፏን ይዛ ትመጣብሃለች። የምታምነው እውነት መሆኑ ከገባህ አንገትህን ትሰጣታለህ። ካልገባህ ደግሞ እየሳቅህ የክህደት ትምህርቷን ትጋታለህ።
አምላከ ቅዱሳን ከስህተት ጠብቆ፣ በእውነተኛዋ ሃይማኖት ያጽናን! | 242 |
