en
Feedback
Nikodimos Christian center

Nikodimos Christian center

Open in Telegram

Nikodimos Show is a unique program which is hosted by the famous Ethiopian Gospel Singer Tigist Ejigu, https://www.facebook.com/tigist.ejigu.5 This show is working on creating awareness on sensitive Christian issues inside the Church of Ethiopia.

Show more
6 506
Subscribers
-124 hours
-247 days
-4830 days
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+5
in 0 channels
August '26
+70
in 1 channels
Get PRO
July '26
+108
in 0 channels
Get PRO
June '26
+114
in 0 channels
Get PRO
May '26
+132
in 0 channels
Get PRO
April '26
+145
in 0 channels
Get PRO
March '26
+263
in 1 channels
Get PRO
February '26
+222
in 0 channels
Get PRO
January '26
+176
in 1 channels
Get PRO
December '25
+275
in 0 channels
Get PRO
November '25
+400
in 0 channels
Get PRO
October '25
+699
in 0 channels
Get PRO
September '25
+1 887
in 0 channels
Get PRO
August '25
+14
in 0 channels
Get PRO
July '25
+19
in 0 channels
Get PRO
June '25
+16
in 0 channels
Get PRO
May '25
+21
in 1 channels
Get PRO
April '25
+29
in 0 channels
Get PRO
March '25
+32
in 0 channels
Get PRO
February '25
+31
in 0 channels
Get PRO
January '25
+64
in 0 channels
Get PRO
December '24
+57
in 0 channels
Get PRO
November '24
+58
in 0 channels
Get PRO
October '24
+170
in 0 channels
Get PRO
September '24
+142
in 0 channels
Get PRO
August '24
+652
in 0 channels
Get PRO
July '24
+16
in 0 channels
Get PRO
June '24
+17
in 0 channels
Get PRO
May '24
+178
in 0 channels
Get PRO
April '24
+552
in 0 channels
Get PRO
March '24
+2 030
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
02 September+2
01 September+3
Channel Posts
2
https://youtu.be/Ek1Ole0TaZ0?si=kq46TDu1Z0XdUPeL
479
3
No text...
500
4
356ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ 7 - 9 የዩ
356ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ  ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ  7 - 9 የዩቱብ  የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች  ታገኛላችሁ👇 YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316 TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu TIKTOK#2:-  tiktok.com/nikodimoschrstiancenter TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow
559
5
#ና! #4_ቀናት_ብቻ_ቀሩን! "ንጉሣችን ይመጣል! እኛም ዝግጁ እንሁን!" መስከረም 1 ዘፍጥረት 1 ብለን የጀመርነው ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስን የማንበብ ጉዞአችን በእግዚአብሔር ፈቃድና እርዳታ እነሆ ራእይ
#ና! #4_ቀናት_ብቻ_ቀሩን! "ንጉሣችን ይመጣል! እኛም ዝግጁ እንሁን!" መስከረም 1 ዘፍጥረት 1 ብለን የጀመርነው ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስን የማንበብ ጉዞአችን በእግዚአብሔር ፈቃድና እርዳታ እነሆ ራእይ 22 ብለን ነሐሴ 30፣ 2018 ልንጨርስና በአካል ልንገናኝ 4 ቀናት ብቻ ቀርተውናል። ቀን ፡- ነሐሴ 30/2018 ሰዓት :- ከ 8:00 ጀምሮ ቦታ :- ዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን ቦሌ አጥቢያ #ጌታ_ኢየሱስ_ሆይ_ና! #መስከረም1_ዘፍጥረት1_ጿግሜ5_ራዕይ22 ኒቆዲሞስ ክርስቲያን ሴንተር
601
6
4 ቀን ብቻ ቀረው!
4 ቀን ብቻ ቀረው!
598
7
https://youtu.be/TCppo_VC9FM
669
8
https://youtu.be/V8AtWeXsJSI
670
9
https://youtu.be/ztlgigP4q_o?si=r8GhoUVBVkmFv9I5
647
10
355ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ 4 - 6 የዩ
355ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ  ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ  4 - 6 የዩቱብ  የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች  ታገኛላችሁ👇 YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316 TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu TIKTOK#2:-  tiktok.com/nikodimoschrstiancenter TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow
659
11
#ና! #5_ቀናት_ብቻ_ቀሩን! "ኢየሱስ ይመጣል እኛንም ይወስደናል ለዘላለም ከእርሱ ጋር እንሆናለን!" መስከረም 1 ዘፍጥረት 1 ብለን የጀመርነው ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስን የማንበብ ጉዞአችን በእግዚአብሔር
#ና! #5_ቀናት_ብቻ_ቀሩን! "ኢየሱስ ይመጣል እኛንም ይወስደናል ለዘላለም ከእርሱ ጋር እንሆናለን!" መስከረም 1 ዘፍጥረት 1 ብለን የጀመርነው ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስን የማንበብ ጉዞአችን በእግዚአብሔር ፈቃድና እርዳታ እነሆ ራእይ 22 ብለን ነሐሴ 30፣ 2018 ልንጨርስና በአካል ልንገናኝ 5 ቀናት ብቻ ቀርተውናል። ቀን ፡- ነሐሴ 30/2018 ሰዓት :- ከ 8:00 ጀምሮ ቦታ :- ዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን ቦሌ አጥቢያ #ጌታ_ኢየሱስ_ሆይ_ና! #መስከረም1_ዘፍጥረት1_ጿግሜ5_ራዕይ22 ኒቆዲሞስ ክርስቲያን ሴንተር
663
12
 በእግዚአብሔር ምድር አይቀመጡም፤ኤፍሬም ወደ ግብፅ ይመለሳል፤የረከሰውንም ምግብ በአሦር ይበላል።”(አ.መ.ት)   ግብፅ የባርነትና ወደ ኋላ የመመለስ ተምሳሌት ናት ፡ በእግዚአብሔር የተዋጀና ነፃ የወጣ ህዝብ ባለመታዘዝ ከፀና ወደ ነበረበት ሊመለስ ይችላል   ወደ ገላትያ ሰዎች 5 1 በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ።   2 ጴጥሮስ 5 20ጌታችንንና አዳኛችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በማወቅ ከዓለም ርኵሰት ካመለጡ በኋላ እንደ ገና ተጠላልፈው ቢሸነፉ ከመጀመሪያው ይልቅ የኋለኛው ሁኔታቸው የከፋ ይሆንባቸዋል። (አ.መ.ት)   ሀጢአት ነፃነት ሰጣችኋለሁ ቢለንም ወደ ባርነት ነው የሚመልሰን   7-9 ነቢዩ እንደሞኝና እንደ እብድ ተቆጥሯል   እስራኤል አመፃቸው በዝቶ መልዕክቱን በመቀበል ፈንታ መልዕክተኛው ላይ ጥቃት ይሰነዝሩ ጀመር   የደነደነ ልብ ተግሳፅን በመቀበል ፈንታ በሚገስፀው ላይ ዞሮ ጠላት ይሆንበታል   የሐዋርያት ሥራ 7 52 -53 ከነቢያትስ አባቶቻችሁ ያላሳደዱት ማን ነው? የጻድቁንም መምጣት አስቀድሞ የተናገሩትን ገደሉአቸው፤ በመላእክት ሥርዓት ሕግን ተቀብላችሁ ያልጠበቃችሁት እናንተም አሁን እርሱን አሳልፋችሁ ሰጣችሁት ገደላችሁትም።   መልክተኛውን የሚቃወም መልዕክቱንና ላኪውን ይቃወማል   “10እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ “እስራኤልን ባገኘሁ ጊዜ የወይን ዘለላን ከምድረ በዳ እንደ ማግኘት ነበር፤ የቀድሞ አባቶቻችሁን ባየሁ ጊዜ ቀድሞ የጐመራውን የበለስ ፍሬ እንደማየት ነበር፤ ወደ በዓል ጴዖር በደረሱ ጊዜ ግን ራሳቸውን ለዚያ አሳፋሪ ጣዖት ለይተው አቀረቡ፤ እነርሱም እንደዚያ እንደሚወዱት ጣዖት የረከሱ ሆኑ።”(አ.ት)   እግዚአብሔር እስራኤልን መውደዱን አላቋረጠም ፡ ህዝቡ ግን ልቡን ለጣኦታት ፍቅሩን ለሌሎች አማልክት ሰጠ   የዮሐንስ ራእይ 2 4 ዳሩ ግን የምነቅፍብህ ነገር አለኝ የቀደመውን ፍቅርህን ትተሃልና።   11-14 ክብር እንደወፍ በረረ   “11. የኤፍሬም ክብር እንደ ወፍ በሮ ይጠፋል፤መውለድ፣ ማርገዝና መፀነስ የለም።” (አ.መ.ት)   የህጉ እርግማን የሆኑት ፡ መካንነት ፡ ማጣት ፡ ጭንገፋ እና መገደል  ይደርስባቸዋል ፡ ይህ ደግሞ በእነርሱ ላይ ብቻ ሳይሆን በልጆቻቸውም ላይ ጉዳት ያስከትላል   ሀጢአት ግለሰብን ብቻ ሳይሆን ትውልድንም ይጎዳል   15-17 አሳድዳቸዋለሁ !   “17እርሱን ስላልታዘዙ አምላኬ ይጥላቸዋል፤ እነርሱም በአሕዛብ መካከል በመንከራተት ይኖራሉ።”(አ.መ.ት)   የእስራኤል ችግር እውነትን አለማወቅ ወይንም ሀይማኖታዊ ስርአቶችን አለመፈፀም አይደለም ፡ በሚያውቁት እውነት አለመሄድ (አለመታዘዝ) ነው እንጂ   ወደ ዕብራውያን 3 15 እየተባለ። ዛሬ ድምጹን ብትሰሙት፥ በማስመረር እንደሆነ ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ።   መታዘዝ የሌለበት መስማት አይጠቅምም   ምን እንማር   1.       መንፈሳዊ ጤንነታችንን በምድራዊ ስኬት (ብልፅግና) አንለካ   2.      ሀጢአት ወደ ነፃነት ሳይሆን መልሶ ወደ ባርነት ነው የሚያስገባን   3.      ለጌታ ያለንን የመጀመሪያ ፍቅራችንን እንጠብቀው(አናስነካው)   4.      የእግዚአብሔርን ተግሳፅ ሰምቶ ለመመለስ ያልደነደነ ልብ እንዲኖረን እንትጋ ትንቢተ ሆሴዕ ምዕራፍ 10   እስራኤል በብልፅግናዋ ታበየች   1-2 የእግዚአብሔርን በረከት አግባብ ላልሆነ አላማ አዋሉት   እግዚአብሔር አብዝቶ በባረካቸው ቁጥር ወደ እግዚአብሔር በመጠጋትና እርሱን በማክበር ፈንታ ጣኦታትን ያበዙ ነበር   ባራኪውን በበረከቱ ተክተውት ነበር   “ልባቸው አታላይ ነው”   የሰው ልጅ ዋናው ችግር ያለው ልቡ ላይ ነው   የእግዚአብሔር በረከት ወደ እግዚአብሔር ሊያስጠጋን እንጂ ሊያርቀን አይገባም   3-8 ጣኦቶቻቸው ይፈራርሳሉ   “3ሕዝቡ “እግዚአብሔርን መፍራት ስለ ተውን ንጉሥ አጥተናል፤ ንጉሥ ቢኖረንስ ምን ያደርግልናል?” ይላሉ።”(አ.ት)   በእግዚአብሔርና እርሱ በሚሰጣቸው አመራር ሳይሆን በጣኦቶቻቸው ተማምነው ነበር   የታመኑባቸው ጣኦቶቻቸው ከእነርሱ ጋር ይማረካሉ እስራኤል በጣኦቶቹ ይኖራል !   9-10 በጊብአ የሰራችሁት ሀጢአት ይታሰባል   መሳፍንት ምዕራፍ 19-21 ያለውን ታሪክ ያስታውሳቸዋል ፡ ጊብአ የእርኩሰት የአንገት ደንዳናነት እና ንስሀ ያለመግባት ምሳሌ ነው   እስራኤል በዚያው አይነት ሀጢአት እስከዚህ ጊዜ ፀንተዋል እንጂ አልተለወጡም   ተናዘን ያልተውነው (ችላ ያልነው) ሀጢአት በህይወታችን እየደጋገመ ይመጣል እንጂ በራሱ ጊዜ አያልፍም   11-13 መዝራትና ማጨድ   ፅድቅን ዝሩና ፅኑ ፍቅርን እጨዱ ብያችሁ ነበር እናንተ ክፋትን ዘርታችሁ ግፍን አጨዳችሁ አዝመራውን ያልወደደ ዘሩን ነው መቀየር ያለበት   የያዕቆብ መልእክት 3 18 የጽድቅም ፍሬ ሰላምን ለሚያደርጉት ሰዎች በሰላም ይዘራል።   ድንገተኛ አዝመራ የለም   “እዳሪውን መሬት እረሱ”   የደነደነውን ልብ አለስልሱ ማለት ነው   14-15 ፍርድ እየመጣ ነው!   እግዚአብሔር ፅድቅን ዝሩ ፡ ልባችሁን ገር አድርጉ ፡ እኔን ፈልጉ ሲላቸው ወደ ፍርድ እንዳይገቡ ሊያስጠነቅቃቸው ነው ፡ ሰምተው ካልታዘዙ ግን የእግዚአብሔር ማስጠንቀቂያ ማስፈራሪያ ስላልሆነ እንደተናገረው መፈፀሙ አይቀርም   ምን እንማር ?   1.       የእግዚአብሔር በረከት በጥንቃቄ ካልተያዘ ከእግዚአብሔር ሊያርቀን ይችላል “በረከቴ ወደ የት እየሳበኝ ነው?”   2.      ሀጢአትን ተናዘን በመተው እንጂ ችላ በማለት ከህይወታችን አናስወግደውም   3.      የምንዘራውን እንጂ የምናጭደውን መምረጥ አንችልም   4.      የእግዚአብሔር ማስጠንቀቂያ የምህረቱና የፍቅሩ መገለጫ እንጂ ተራ ማስፈራሪያ አይደለም
588
13
የዮሐንስ ራእይ 3 15 በራድ ወይም ትኩስ እንዳይደለህ ሥራህን አውቃለሁ። በራድ ወይም ትኩስ ብትሆንስ መልካም በሆነ ነበር። 16 እንዲሁ ለብ ስላልህ በራድም ወይም ትኩስ ስላልሆንህ ከአፌ ልተፋህ ነው።   “የሙሉ ጊዜ አዳኝ የሚፈልግ የትርፍ ጊዜ ክርስቲያን አንሁን”   “9. እንግዶች ጒልበቱን በዘበዙ፤እርሱ ግን አላስተዋለም።ጠጒሩም ሽበት አወጣ፤እርሱ ግን ልብ አላለም።”(አ.መ.ት)   እስራኤል ጉልበቱ እየተበዘበዘ (እየደከመ) ግን አላወቀም   ሀጢአት ቀስ በቀስ መንፈሳዊ ህይወታችንን ሲበዘብዝና ሲያደክም አይታወቀንም   መንፈሳዊ ድካም አደገኛነቱ እንደ አካላዊ ድካም ፈጥኖ አለመታወቁ ነው   የዮሐንስ ራእይ 3 17 ሀብታም ነኝና ባለጠጋ ሆኜአለሁ አንድም ስንኳ አያስፈልገኝም የምትል ስለ ሆንህ፥ ጐስቋላና ምስኪንም ድሀም ዕውርም የተራቆትህም መሆንህን ስለማታውቅ፥   እራስን ማታለል አደገኛ መንፈሳዊ ችግር ነው   10-12 እስራኤል አዕምሮ እንደሌላት እርግብ ነው   እርዳታ ፍለጋ ወደ እግዚአብሔር በመጮህ ፋንታ አንዴ ወደ ግብፅ አንዴ ደግሞ ወደ አሶር ይጮሀሉ   ስንፈራ መጀመሪያ የምንጮኸው ወደ ማን ነው ?   እግዚአብሔር አስቀድመን ወደ እርሱ እንድንጣራ ይፈልጋል   13-16 ከልባቸው ወደ እኔ አይጮሁም   ያስቅሳሉ ፡ የሚያስለቅሳቸው ግን የመከራው ብዛት ነው እንጂ ለንስሀ አይደለም   ከችግር ለመውጣት ማልቀስና እውነተኛ ንስሀ የተለያዩ ነገሮች ናቸው   “15. እኔ አሠለጠንኋቸው፤ አጠነከርኋቸውም፤እነርሱ ግን አደሙብኝ።”(አ.መ.ት)   እግዚአብሔር በሰጠን ነገር እግዚአብሔርን እናክብር   ምን እንማር   1.        አንዳንድ ጊዜ ለመፈወስ መታመም አለ   2.      እግዚአብሔር በግማሽ ልብ የምንከተለው አምላክ አይደለም   3.      ሀጢአት ሳያሳውቅ እንደ ምስጥ መንፈሳዊ ህይወትን ይቦረቡራል   4.      እርዳታን ከእግዚአብሔር ውጪ መፈለግ አእምሮ እንደሌለው እርግብ እንደመሆን ነው ትንቢተ ሆሴዕ ምዕራፍ 8   እስራኤል አውሎ ንፋስን ታጭዳለች   1-3 የማስጠንቀቂያ መለከት   ጠላት በእስራኤል ላይ እንደንስር እየመጣ ስለሆነ “መለከትን በአፍህ ላይ አድርግ”   “2. እስራኤልም፣ ‘አምላካችን ሆይ፤ እኛ እናውቅሃለን’ እያሉ፣ወደ እኔ ይጮኻሉ።”(አ.መ.ት)   እግዚአብሔርን ማወቅ ከንግግር ያለፈ የሚኖር ህይወት ነው   የማቴዎስ ወንጌል 7 21 በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም። 22 በዚያ ቀን ብዙዎች። ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል። 23 የዚያን ጊዜም። ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ።   ወደ ቲቶ 1 16 እግዚአብሔርን እንዲያውቁ በግልጥ ይናገራሉ፥ ዳሩ ግን የሚያስጸይፉና የማይታዘዙ ለበጎ ሥራም ሁሉ የማይበቁ ስለ ሆኑ፥ በሥራቸው ይክዱታል።   ስለ እግዚአብሔር ማወቅ እግዚአብሔርን ማወቅ አይደለም   “4. ያለ እኔ ፈቃድ ነገሥታትን አነገሡ፤እኔንም ሳይጠይቁ አለቆችን መረጡ፤በብራቸውና በወርቃቸው፣ለገዛ ጥፋታቸው፣ጣዖታትን ለራሳቸው ሠሩ።”(አ.መ.ት)   “ያለኔ ፍቃድ…እኔን ሳይጠይቁ”   የእግዚአብሔርን ጥቅሙን እንጂ ጌትነቱን አይፈልጉም   5-6 እጅ የሰራው ይህ ጥጃ አምላክ አይደለም   የተፈጠረ (እጅ የሰራው ነገር) አምላክ እንዳይሆንብን ልንጠነቀቅ ያስፈልጋል   “7. “ነፋስን ይዘራሉ፤ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ፤አገዳው ዛላ የለውም፤ዱቄትም አይገኝበትም፤እህል አፍርቶ ቢገኝም፣ባዕዳን ይበሉታል።”(አ.መ.ት)   አዝመራ (አጨዳ) ሁልጊዜም ከተዘራው ዘር በብዙ እጥፍ ይበዛል   ክፉም ይሁን መልካም የተዘራ ነገር መብቀሉ አይቀርም ሲበቅል ደግሞ የተዘራውን ያህል ብቻ አይደለም   ወደ ገላትያ ሰዎች 6 7 አትሳቱ፤ እግዚአብሔር አይዘበትበትም። ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና፤ 8 በገዛ ሥጋው የሚዘራ ከሥጋ መበስበስን ያጭዳልና፥ በመንፈስ ግን የሚዘራው ከመንፈስ የዘላለምን ሕይወት ያጭዳል።   የያዕቆብ መልእክት 1 14 ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ምኞት ሲሳብና ሲታለል ይፈተናል። 15 ከዚህ በኋላ ምኞት ፀንሳ ኃጢአትን ትወልዳለች፤ ኃጢአትም ካደገች በኋላ ሞትን ትወልዳለች።   8-10 እስራኤል ለእርዳታ ወደ አህዛብ ጮሁ   “ለብቻው እንደሚባዝን የዱር አህያ …ሆነዋል”   ከእግዚአብሔር ተለይቶ በራስ ለመቆም (እራስን ለመቻል) መሞከር ነፃነት ሳይሆን ባርነት ነው   የዮሐንስ ወንጌል 15 5 እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።   አፈጣጠራችን ከእርሱ ጋር ለመጣበቅና በእርሱ ለመደገፍ ነው እንጂ በራሳችን ለመቆም አይደለም   11-13 መሰዊያ ብታበዙም ሀጢአታችሁ ይበዛል !   ሀይማኖተኝነታቸው እየከረረ ህይወታቸው ግን ከእግዚአብሔር እየራቀ ይሄድ ነበረ   የማቴዎስ ወንጌል 15 8 ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል፥ ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፤ 9 የሰውም ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል ብሎ በእውነት ትንቢት ተናገረ።   እግዚአብሔር በሀይማኖት ሳይሆን በእውነትና በመንፈስ የሚያመልኩትን ይሻል   14“የእስራኤል ሕዝብ ለራሳቸው ታላላቅ ቤተ መንግሥቶች ሠርተዋል፤ እኔን ፈጣሪአቸውን ግን ረስተዋል፤ የይሁዳም ሕዝብ ብዙ የተመሸጉ ከተሞችን ሠርተዋል፤ ስለዚህ ከተሞቻቸውንና ምሽጎቻቸውን የሚያቃጥል እሳት እልክባቸዋለሁ።” (አ.ት)   “እስራኤል ፈጣሪያቸውን ረስተዋል”   የችግራቸው ሁሉ ምንጭ አለማወቅ ሳይሆን መርሳት ነው   አብዛኛውን ጊዜ የእግዚአብሔር ህዝብ የሚገባበት ወጥመድ ከመነሻው ግልፅ የሆነ አመፅ ሳይሆን ቀስ በቀስ የሚከሰት እግዚአብሔርን መርሳት ነው   እስራኤል ሀይማኖታዊ ስርአቶችን አስታውሰው ይፈፅማሉ ፡ እግዚአብሔርን ግን ረስተዋል   ወደ ዕብራውያን 2 1 ስለዚህ ከሰማነው ነገር ምናልባት እንዳንወሰድ፥ ለእርሱ አብልጠን ልንጠነቀቅ ያስፈልገናል።   መንፈሳዊ ውድቀት በድንገት (በአንድ ጊዜ) ሳይሆን ቀስ በቀስ ነው የሚከሰተው   ምን እንማር   1.       ኢየሱስን እንደ አዳኝ ብቻ ሳይሆን እንደ ጌታም እንቀበለው   2.      ክፉም ይሁን መልካም የምንዘራው ነገር በዝቶ ስለምናጭደው ምን እንደምንዘራ እንጠንቀቅ   3.      ከጌታ ተለይቶ በራስ መቆም ነፃነት ሳይሆን እውነተኛ ባርነት ነው   4.      እግዚአብሔርን መርሳት የመንፈሳዊ ውድቀት ስር ነው ትንቢተ ሆሴዕ ምዕራፍ 9   በእስራኤል ላይ የሚደርሰው ቅጣት   1-2 እስራኤል ሆይ ….. እንደ ሌሎች ህዝቦች ደስ አይበልሽ   እስራኤል ለእግዚአብሔር ጀርባዋን ሰጥታ በምድራዊ ብልፅግና ሀሴት እያደረገች ነበር   ጥሩ አዝመራ ማግኘታቸውን ሁሉ ሰላም እንደሆነና እግዚአብሔር እንደተቀበለው ማረጋገጫ አድርገው ወስደውታል   ውጫዊ ስኬት ሁልጊዜ የመንፈሳዊ ጤንነት ማረጋገጫ ተደርጎ ሊወስድ አይችልም   “2ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲህ ከዐውድማችሁ እህልን፥ ከመጭመቂያችሁም የወይን ጠጅን ከቶ አታገኙም፤ አዲስ የወይን ጠጅም አይገኝም።”(አ.ት)   እንደ ማረጋገጫ የወሰዱትን ነገር አጠፋዋለሁ አላቸው   አንዳንድ ጊዜ ምድራዊ ስኬት መንፈሳዊ ውድቀታችንን እንዳናይ ሊጋርድብን ይችላል   3-6 ስደት (ምርኮ) እየመጣባችሁ ነው   “3.
424
14
ትንቢተ ሆሴእ ምእራፍ 6-10 ሆሴዕ(መዳን ፡ ያድናል)ማለት እንደሆነ አይተናል   722 አ.አ. (አሶር እሰራኤልን ከማፍለሷ ጥቂት ቀደም ብሎ የሰሜኑን መንግስት (እስራኤልን) ያገለገለ ነቢይ ነው   ዋና ሀሳቡ የእግዚአብሔር የኪዳን ፍቅር ታማኝ ላልሆነችው እስራኤል የሚል ነው   በሆሴዕ መጽሐፍ ላይ እግዚአብሔር ኪዳኑን ላልጠበቀው ህዝብ ፍርድ ብቻ ሳይሆን አስደናቂ ፍቅር እንዳለውም እናያለን   ሆሴዕ በትዳሩ አማካኝነት ለህዝቡ መልዕክት ያስተላለፈ ሰው ነበረ ፡ ሆሴዕ ለኪዳኑ ታማኝ እንደሆነው እንደ እግዚአብሔር ፡ ጎሜር(ሚስቱ) ደግሞ እንደ አመንዝራዋ እስራኤል ሆነው ቀርበዋል   ጎሜር በተደጋጋሚ ሆሴዕን እንደምትክደውና ጥላው እንደምትኮበልል እስራኤልም በእግዚአብሔር ላይ እንዲሁ ታደርግ ነበረ ፡ ሆሴዕ ጎሜርን በተደጋጋሚ ተከታትሎ የራሱ እንደሚያደርጋት ሁሉ እግዚአብሔርም ለእስራኤል እንዲሁ ያደርግ ነበረ   ቁልፍ ቃሉ ፡ “የኪዳን ፍቅር” ነው   ቁልፍ ጥቅሱ ሆሴዕ 6፡6 ነው ሆሴዕ 6 6. ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን፣ከሚቃጠልም መሥዋዕት ይልቅ እግዚአብሔርን ማወቅ እሻለሁና። (አ.መ.ት)   ጌታ ኢየሱስ ይህንን ቁልፍ ጥቅስ ለፈሪሳውያን ጠቅሶታል   የማቴዎስ ወንጌል 9 13 ነገር ግን ሄዳችሁ። ምሕረትን እወዳለሁ መሥዋዕትንም አይደለም ያለው ምን እንደ ሆነ ተማሩ፤ ኃጢአተኞችን ወደ ንስሐ እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁምና አላቸው።   የማቴዎስ ወንጌል 12 7 ምሕረትን እወዳለሁ መሥዋዕትንም አይደለም ያለው ምን እንደሆነ ብታውቁስ ኃጢአት የሌለባቸውን ባልኰነናችሁም ነበር።   ትንቢተ ሆሴዕ ምዕራፍ 6   እግዚአብሔር ባዶ የሀይማኖት ልምምድን ሳይሆን እውነተኛ ልብን ነው የሚፈልገው   1-3 ኑ ወደ እግዚአብሔር እንመለስ   “1. “ኑ፤ ወደ እግዚአብሔር እንመለስ፤እርሱ ሰባብሮናል፤እርሱም ይጠግነናል፤እርሱ አቊስሎናል፤እርሱም ይፈውሰናል።”(አ.መ.ት)   ሰብሮ መጠገን የእረኞች ልምምድ ነው ፡ እየባዘኑ (እየጠፉ) የሚያስቸግሩ በጎችን ጠፍተው እንዳይቀሩና የአውሬ እራት እንዳይሆኑ እረኛው ሰብሮ ይጠግናቸዋል ቁስላቸው እስከሚድን ከእረኛው አጠገብ ስለማይለዩ እረኛቸውን ማወቅ ይሆንላቸዋል   “2. ከሁለት ቀን በኋላ ያነቃናል፤በእርሱም ፊት እንድንኖር፣በሦስተኛው ቀን ያስነሣናል።”(አ.መ.ት)   ሀጢአታቸው ከተፈረደበት በኋላ ስለሚኖረው ተሀድሶ (restoration) የሚናገር ሲሆን በሌላ አቅጣጫ ደግሞ ትንሳኤን በሩቅ እንድናይ የሚያደርግ ነው   ሀጢአት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በክርስቶስ መስቀል ላይ ከተፈረደበት በኋላ በሶስተኛው ቀን ክርስቶስ ተነስቷል !   “3. እግዚአብሔርን እንወቀው፤የበለጠ እናውቀውም ዘንድ እንትጋ፤እንደ ንጋት ብርሃን፣በእርግጥ ይገለጣል፤ምድርን እንደሚያረሰርስ የበልግ ዝናብ፣እንደ ክረምትም ዝናብ ወደ እኛ ይመጣል።” (አ.መ.ት)   የንጋት ብርሀን ሳይመጣ ቀርቶ እንደማያውቅ ሁሉ እግዚአብሔርም ሊያውቁት ለሚተጉ በእርግጥ ይገለጣል! እንደ በልግ ዝናብ ጥማታቸውን ያረካል   “4እግዚአብሔርም እንዲህ ይላል፦ “የእስራኤልና የይሁዳ ሕዝብ ሆይ! እናንተን ምን ላድርጋችሁ? እናንተ ለእኔ ያላችሁ ፍቅር እንደ ማለዳ ጉምና እንደ ጠዋት ጤዛ ፈጥኖ ይጠፋል።”(አ.ት)   ስሜታዊ ሆነው ንስሀ ቢገቡም በንስሀቸው ፀንተው መቆምና መለወጥ አይታይባቸውም   ንስሀ በገባንበት ጉዳይ ፀንተን እንዳንቆም የሚደርጉ ተግዳሮቶች እንዳሉ ማወቅና መጠንቀቅ ያስፈልጋል   1.       ቃሉ በልባችን ስር አለመስደዱ   2.      የዚህ አለም ሀሳብና የሀብት ፍቅር   “6. ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን፣ከሚቃጠልም መሥዋዕት ይልቅ እግዚአብሔርን ማወቅ እሻለሁና።”(አ.መ.ት)   ይህ የመጽሐፉ ቁልፍ ጥቅስ ነው   እግዚአብሔር እራሱ የሰጠውን የመስዋዕት ስርአት እየተቃወመ ሳይሆን ከልብ ያልሆነ (የላይ የላይ የሆነ) ባዶ ሀይማኖታዊ ስርአት አይጠቅምም እያለ ነው   ማቴዎስ 9 13. ሄዳችሁ፣ ‘ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን እወዳለሁ፤’ የሚለውን ቃል ትርጕም አጢኑ፤ ኀጢአተኞችን እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁምና።”(አ.መ.ት) ማቴዎስ 12 7. ‘ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን እወዳለሁ’ የሚለው ቃል ምን ማለት እንደሆነ ብታውቁ ኖሮ፣ በንጹሐን ላይ ባልፈረዳችሁ ነበር። (አ.መ.ት)   ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ግንኙነት አኗኗራችንንና ከሌሎች ጋር ያለንን ግንኙነት ሊቀርፅ ይገባል   “7. እንደ አዳም ቃል ኪዳንን ተላለፉ፤በዚያም ለእኔ ታማኝ አልነበሩም።”(አ.መ.ት)   አዳም በኤደን ገነት ተፈትኖ እንደወደቀ እሰራኤልም በተስፋይቱ ምድር ወድቃለች   የሰው ዘር ከአዳምም ከእስራኤልም የተሻለ ወኪል (ተፈትኖ የሚያልፍ አዳኝ) ያስፈልገው ነበር   ወደ ሮሜ ሰዎች 5 19 በአንዱ ሰው አለመታዘዝ ብዙዎች ኃጢአተኞች እንደ ሆኑ፥ እንዲሁ ደግሞ በአንዱ መታዘዝ ብዙዎች ጻድቃን ይሆናሉ።   8-11 አመፅ በሁሉም ስፍራ ተንሰራፍቷል !   ክፋት ፡ ጥቃት ፡ ደም መፍሰስ ፡ የካህናት ወንጀል ዝሙትና እርኩሰት ምድሪቱን ሞልቷታል !   ውጫዊ የሀይማኖት ስርአቶችን መፈፀም ባያቋርጡም ውስጣቸው ግን ተበክሏል   ሀይማኖታዊ ልምምድ ውስጣዊ ብክለትን አያፀዳም   ምን እንማር ?   1.       ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ግንኙነት ልማዳዊ ነው ? ወይንስ ልባዊ ? የሚለውን እንመርምር   2.      ሀይማኖታዊ ስርአቶችን መፈፀም የመንፈሳዊ ህይወታችን ጤንነት ማረጋገጫ አይደለም   3.      እለት እለት እግዚአብሔርን ለማወቅ እንጠማ   4.      ንስሀችን እንደማለዳ ጤዛ እንዳይሆን በቃሉ ስር እንስደድ የሀብት ፍቅርን እናስወግድ ትንቢተ ሆሴዕ ምዕራፍ 7   ልቡ ከእግዚአብሔር የራቀ ህዝብ የሚገጥመው ውድቀት   1-2 ክፋታችሁን እገልጣለሁ   “እስራኤልን በምፈውስበት ጊዜ…..ሀጢአታቸውና ክፋታቸው ይገለጣል”   እውነት ከመፈወሱ በፊት ያሳምማል ፡ ስለዚህ አንዳንድ ጊዜ ለመፈወስ መታመም አለ   “2. ነገር ግን ክፉ ድርጊታቸውን ሁሉ እንደማስታውስ፣እነርሱ አይገነዘቡም፤ኀጢአታቸው ከቦአቸዋል፤ሁልጊዜም በፊቴ ናቸው።”(አ.መ.ት)   ከእግዚአብሔር አይን የተሰወረ አንዳች ነገር የለም   ወደ ዕብራውያን 4 13 እኛን በሚቆጣጠር በእርሱ ዓይኖቹ ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው እንጂ፥ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም።   እግዚአብሔር የተገለጠውን ድርጊታችንን ብቻ ሳይሆን የተሰወረ መነሻ ሀሳባችንንም ይመለከታልና በፍርዱ አይሳሳትም   3-7 የረከሱ መሪዎችና የረከሰ ህዝብ   ንጉሳቸው ፡ አለቆቻቸውና ገዢዎቻቸው ረክሰዋልና ህዝቡም ደግሞ ለዝሙት ፡ ለሴራና ደም ለማፍሰስ ልባቸው እንደምድጃ የጋለ ነው   እግዚአብሔርን ከመካከሉ ያስወጣ ማህበረሰብ ይህንን ይመስላል   ብዙ ማህበራዊ ቀውሶች መነሻ ችግራቸው መንፈሳዊ ነው   “8 ፤ ኤፍሬም ከአሕዛብ ጋር ተደባለቀ፤ ኤፍሬም እንዳልተገላበጠ ቂጣ ነው።”   ያልተገላበጠ …. በአንዱ በኩል የበሰለና በሌላኛው በኩል ሊጥ የሆነ ለምንም የማይጠቅም ሆነዋል   በአንዱ በኩል ለእግዚአብሔር በሌላ በኩል ለጣኦት የተሰጠ የማይጠቅም ህዝብ ሆነዋል   እግዚአብሔርንም ይፈልጋሉ (ጥበቃውን አቅርቦቱን ምሪቱን) ደግሞም የአህዛብን ጣኦታት ይከተላሉ   እግዚአብሔር በግማሽ ልብ የምንከተለው አምላክ አይደለም   የማቴዎስ ወንጌል 6 24 ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ማንም የለም፤ ወይም አንዱን ይጠላል ሁለተኛውንም ይወዳል፤ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል ሁለተኛውንም ይንቃል፤ ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም።  
424
15
12 -13 ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤   በዚህ ዘመን ያለው አመንዝራነት የሚገለፀው በመጎምጀት ነው እግዚአብሔር በማይከብርበት ህይወት ብዙ ጊዜ ስንጎመጅ ይታያል ይሔ መንፈሳዊ ምንዝርና ነው   ወደ ቆላስይስ ሰዎች 3 5 እንግዲህ በምድር ያሉቱን ብልቶቻችሁን ግደሉ፥ እነዚህም ዝሙትና ርኵሰት ፍትወትም ክፉ ምኞትም ጣኦትንም ማምለክ የሆነ መጎምጀት ነው።   ከቁጥር 14-19 የጣኦት አምልኮ በመካከላቸው እንዴት እንደተስፋፋ እናያለን   “16. እስራኤላውያን እንደ እልኸኛ ጊደር፣እልኸኞች ናቸው፤ታዲያ እግዚአብሔር እነርሱን በመልካም መስክ ውስጥ እንዳሉ የበግ ጠቦቶችእንዴት ያሰማራቸዋል?(አ.መ.ት) ትንቢተ ሆሴዕ ምዕራፍ 5   በእስራኤል ላይ የተነገረ ፍርድ   “1. “እናንተ ካህናት፤ ይህን ስሙ!እናንት እስራኤላውያን፤ አስተውሉ!የንጉሥ ቤት ሆይ፤ ስሙ!ይህ ፍርድ በእናንተ ላይ ነው፤በምጽጳ ወጥመድ፣በታቦርም ላይ የተዘረጋ መረብ ሆናችኋልና።(አ.መ.ት)   እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ እስራኤላዊ ስሙኝ ይላቸዋል   “3. ስለ ኤፍሬም ሁሉን ዐውቃለሁ፤እስራኤልም ከእኔ የተሰወረች አይደለችም፤ኤፍሬም፣ አንተ አሁን አመንዝረሃል፤እስራኤልም ረክሳለች።(አ.መ.ት)   ከእግዚአብሔር የተሰወረ ሀጢአት የለም   እግዚአብሔር ድካማችንን ያውቃል የተሻለ ሀጢአት የለም   “4. “የሠሩት ሥራ፣ ወደ አምላካቸው እንዲመለሱአይፈቅድላቸውም፤የአመንዝራነት መንፈስ በልባቸው አለ፤ እግዚአብሔርንም አያውቁትም።(አ.መ.ት)   ወደ እግዚአብሔር መመለስ ያልቻሉበት 3 ምክንያት   1 በህዝቡ ላይ በሚሰራው የዝሙት መንፈስ ምክንያት   2 እግዚአብሔርን ስለማያውቁ   3 ስራቸው ያሳፍራል!   በሀጢአት መፅናትና ሀጢአትን ማድረግ የተለያዩ ነገሮች ናቸው   የንስሀ ተቃራኒ በሀጢአት መፅናት ነው   “6. እግዚአብሔርን ለመሻት፣የበግና የፍየል መንጋ እንዲሁም የቀንድ ከብቶቻቸውን ነድተው ሲሄዱ፣እርሱ ስለ ተለያቸው፣ሊያገኙት አይችሉም።(አ.መ.ት)   ለእግዚአብሔር መስዋዕት አድርገው ለመቅረብ ቢፈልጉም አላገኙትም   እግዚአብሔርን በሰጠን ነገር አታለን ወደ ራሳችን አንመልሰውም   እግዚአብሔር የሁሉም ነገር ባለቤት ነው በሰጠን ነገር ወደ እርሱ መቅረብ አንችልም እርሱ የሚፈለግው የተሰበረን ልብ ነው   እግዚአብሔርን አናታልልም እርሱ ሁሉን ያውቃል
437
16
ት)   እግዚአብሔር አሁንም እስራኤልን ይወዳታል እርሱ በህዝቡ ተስፋ ቆርጦ አያውቅም   በምድረበዳ ከእግዚአብሔር ውጪ የሚረዳ ማንም የለም በምድረበዳ ከእግዚአብሔር ውጪ ማንም ላይ መደገፍ እንደሌለባት ተምራ ትወጣለች   ከቁጥር 16-19 ከእስራኤል ጋር ያለውን ግንኙነት በኪዳን ሲያድስ እናያለን   “19. ለእኔ እንድትሆኚ ለዘላለም አጭሻለሁ፤በጽድቅና በፍትሕ፣በፍቅርና በርኅራኄም አጭሻለሁ። 20. በታማኝነት አጭሻለሁ፤አንቺም እግዚአብሔርን ታውቂያለሽ።(አ.መ.ት)   እግዚአብሔር ማወቅ ማለት 2 ትርጉም አለው   1 የመጀመሪያው "ሎሀኪር" የሚል ሲሆን ትርጉሙም የሆነ ነገር እንዳለ ማወቅ ማለት ነው   2 ሌላው "ለዳ" የሚል ቃል ነው ይሄም ማለት የግል የሆነ ጥብቅ ቁርኝነት ያለው እውቀት ማለት ነው:: የዚህም ቃል መገለጫው ትዳር ነው   እግዚአብሔርን ታውቂዋለሽ ማለት መኖሩን ፍጥረትን አይተሽ ታውቂያለሽ ማለት ሳይሆን ከእግዚአብሔር ጋር የተለየ ግንኙነት ይኖርሻል ማለት ነው ትንቢተ ሆሴዕ ምዕራፍ 3   የሆሴዕ ከሚስቱ ጋር መታረቅ   ትዳር ኪዳን ነው በዚህ ምዕራፍ ሆሴዕ ከሚስቱ ጋር ያለውን ኪዳን ሲያድስ እናየዋለን   “1. እግዚአብሔር እንዲህ አለኝ፤ “እርሷ በሌላ ሰው የምትወደድ አመንዝራ ብትሆንም፣ አሁንም ሂድና ሚስትህን ውደዳት፤ ወደ ሌሎች አማልክት ዘወር ቢሉና ለእነርሱም የተቀደሰውን የዘቢብ ጥፍጥፍ ቢወዱም፣ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን እንደ ወደዳቸው አንተም እርሷን ውደዳት።”(አ.መ.ት)   ይህቺ ሴት ለሆሴዕ ሚስቱ ነች ልጆችን ወልዳለች የሆነ ጊዜ ላይ ግን ሌላ ሰው ወዳ ትታው ሄዳለች እግዚአብሔር ይቺን ሴት ነው መልሰህ ውደዳት የሚለው   ሆሴዕ ይህችን ሴት ለመተው ሙሉ በሙሉ መብት ነበረው   እግዚአብሔር የወደደን ሀጢአተኞች ስላልሆንን ወይም የተሻልን ሰዎች ስለሆንን አይደለም እንዲሁ ነው!   ጎሜር ከሆሴዕ ቤት ወጥታ ባሪያ ነው የሆነችው   ከእግዚአብሔር ተለይተን የምንሆነው ምንም ጥሩ ነገር የለም:: ባሪያ ብቻ ነው መሆን የምንችለው አለም የምትሰጠን መልካም ነገር የላትም   ሆሴዕ ዋጋ ከፍሎ ይወስዳታል   “2. ስለዚህ በዐሥራ አምስት ሰቅል ጥሬ ብርና በአንድ ቆሮስ ተኩል መስፈሪያ ገብስ ገዛኋት።(አ.መ.ት)   ለክርስቲያን ነፃነቱ ስርአቱ ነው ስርአት ማጣት ነፃ የመሆን መገለጫ አይደለም   ሆሴዕ በባሪያ ዋጋ የገዛ ሚስቱን ገዛ   1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 1 18 -19 ከአባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከከንቱ ኑሮአችሁ በሚያልፍ ነገር በብር ወይም በወርቅ ሳይሆን፥ ነውርና እድፍ እንደ ሌለው እንደ በግ ደም በክቡር የክርስቶስ ደም እንደ ተዋጃችሁ ታውቃላችሁ።   ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1 7 በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት።   ሆሴዕ የተከበረ የእግዚአብሔር ነቢይ ሆኖ ሳለ የገዛ ሚስቱን ፍለጋ ባሮች የሚሸጡበት መንደር ይሄዳል ይህም ኢየሱስ እኛን የፈለገበትን መንገድ በምሳሌ ያሳየናል   ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2 6 እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም፥ 7 ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥   “3. እኔም፣ “ከእኔ ጋር ብዙ ቀን ተቀመጪ፤ አታመንዝሪ ወይም ሌላ ሰው አትውደጂ፤ እኔም ከአንቺ ጋር እኖራለሁ” ብዬ ነገርኋት።(አ.መ.ት)   ሆሴዕ እንደዚያ ያደረገችውን ሚስቱን አላፈረባትም ነይ ከእኔ ጋር ኑሪ ይላታል   እግዚአብሔር ከነበርንበት ጨለማ ሲጠራን አላፈረብንም   “4. እስራኤላውያን ለብዙ ዘመን ያለ ንጉሥና ያለ አለቃ፣ ያለ መሥዋዕትና ያለ ዐምደ ጣዖት፣ ያለ ኤፉድና ያለ ጣዖት ምስል ይኖራሉና። 5. ከዚያ በኋላ እስራኤላውያን ተመልሰው አምላካቸውን እግዚአብሔርንና ንጉሣቸውን ዳዊትን ይፈልጋሉ፤ በመጨረሻውም ዘመን በመንቀጥቀጥ ወደ እግዚአብሔርና ወደ በረከቱ ይመጣሉ።(አ.መ.ት)   ለእስራኤል የተነገረ ትንቢት ነው   እስራኤላውያን ኢየሱስ መሲህ ሆኖ ሲመጣ አልተቀበሉትም   ትንቢተ ዘካርያስ 12 10 ፤ በዳዊትም ቤት ላይ፥ በኢየሩሳሌምም በሚኖሩት ላይ፥ የሞገስንና የልመናን መንፈስ አፈስሳለሁ፤ ወደ እርሱም ወደ ወጉት ይመለከታሉ፤ ሰውም ለአንድያ ልጁ እንደሚያለቅስ ያለቅሱለታል፥ ሰውም ለበኵር ልጁ እንደሚያዝን በመራራ ኀዘን ያዝኑለታል። ትንቢተ ሆሴዕ ምዕራፍ 4   በእስራኤል ላይ የቀረበ ክስ   “1. በምድሪቱ በምትኖሩ በእናንተ ላይ እግዚአብሔር የሚያቀርበው ክስ ስላለው፣እናንት እስራኤላውያን ይህን የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤“ታማኝነት የለም፤ ፍቅርም የለም፤እግዚአብሔርንም ማወቅ በምድሪቱ የለም።(አ.መ.ት)   እግዚአብሔርን ማወቅ ዋና ነገር ነው ከነገሮች መካከል አንዱ ነገር አይደለም   እግዚአብሔርን ማወቅ በህይወት የሚገለጥ ነገር ነው   ህይወታችን ብዙ ሀብትን ፡ ቤተሰብን የተለያዩ ነገሮችን የምናከማችበት ነገር ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔርን አላማ አውቀን የምኖረውም ነው   እግዚአብሔርን ባወቅነው ቁጥር እንገዛለታለን   ማሪያም የመረጠችው አንድ ነገር እግዚአብሔርን ማወቅ ነው ይሄም በጎ እድል ተብሎ በጌታ አፍ የተነገረ ነው   የሉቃስ ወንጌል 10 42 የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፤ ማርያምም መልካም ዕድልን መርጣለች ከእርስዋም አይወሰድባትም አላት።   እግዚአብሔር እርሱን እንድናውቀው ይፈልጋል እራሱን ድብቅ አላደረገም   የዮሐንስ ወንጌል 17 3 እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።   ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 3 10 -11 እርሱንና የትንሣኤውን ኃይል እንዳውቅ፥ በመከራውም እንድካፈል፥ ወደ ሙታንም ትንሣኤ ልደርስ ቢሆንልኝ፥ በሞቱ እንድመስለው እመኛለሁ።   እግዚአብሔርን ማወቅ አስፈላጊ ነገር ነው   ከቁጥር 2-6 እግዚአብሔርን ባለማወቅ የመጣባቸው ነገርን እናያለን   “6. ሕዝቤ ዕውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል።“ዕውቀትን ስለናቃችሁ፣እኔም ካህናት እንዳትሆኑ ናቅኋችሁ፤የአምላካችሁን ሕግ ስለ ረሳችሁ፣እኔም ልጆቻችሁን እረሳለሁ።(አ.መ.ት)   እውቀት ሳይኖር ቀርቶ ሳይሆን ስለናቁት ነው መከራ የመጣባቸው   ከቁጥር 7-14 ካህናቱ ላይ የወጣውን ቁጣ እናያለን   “7. ካህናት በበዙ ቊጥር፣በእኔ ላይ የሚያደርጉት ኀጢአት በዝቶአል፤ክብራቸውንም በውርደት ለውጠዋል።(አ.መ.ት)   ካህናትን ያበዛው እግዚአብሔር ቢሆንም እነርሱ ግን በተቃራኒው መንገድ ሲሄዱ እናያለን   “8. የሕዝቤ ኀጢአት ለመብል ሆኖላቸዋል፤ርኵሰታቸውንም እጅግ ወደዱ።(አ.መ.ት)   ለሀጢአት መስዋዕት የሚቀርበውን ለራሳቸው ጥቅም ማዋል ጀመሩ:: ስለዚህ እነርሱ እንዲበለፅጉ ህዝቡ ሀጢአትን እንዲሰራ ማበረታት ጀመሩ   እግዚአብሔር ዝም የሚለው የንስሀ ጊዜን ሰጥቶ እንጂ ከሀጢአት ጋር እየተባበረ አይደለም   “12. የሕዝቤ ማስተዋል ተወሰደ፤ከዕንጨት የተሠራውን ጣዖት ምክር ይጠይቃሉ፤ዘንጋቸውም ይመልስላቸዋል።የአመንዝራነት መንፈስ ያስታቸዋል፤ለአምላካቸውም ታማኝ አልሆኑም።(አ.መ.ት)   የዝሙት መንፈስ ከእግዚአብሔር ያርቃል ደጋግሞ በሀጢአት ውስጥ መኖር ማስተዋል እንዲወስድባቸው ያደርጋል   ወደ ቲቶ 2 11 ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤
414
17
ትንቢተ ሆሴዕ መግቢያ   ሆሴዕ ታናናሽ ነቢያት ተብለው ከሚታወቁት ውስጥ ነው   ታናሽና ታላቅ ነቢይ የተባሉበት ምክንያት በምዕራፉ ርዝመት እንደሆነ አይተናል   ሆሴዕ ለ 40 አመታት የእስራኤልን ህዝብ ያገለገለ ነቢይ ነው   በአዲስ ኪዳን ከሆሴዕ ላይ 10 ጊዜ ቃል ተጠቅሶ ተነግሯል   የመጽሐፉ አላማ ፡-   እግዚአብሔር ከእስራኤል ጋር ያለውን ግንኙነት በባልና በሚስት መካከል ያለው ግንኙነት አይነት እንደሆነ ማሳየት ነው   እስራኤል ህጉን በመታለለፏ ምክንያት ፍርድ እንደመጣባት ያሳያል   ስለፍርድ ብቻ ሳይሆን ስለ ተሀድሶም መጽሐፉ ይናገራል   እግዚአብሔርን ማወቅ በጣም ወሳኝ ነገር እንደሆነም ያስተምራል   ማዕከላዊ ሃሳቡ እስራኤል መንፈሳዊ ግልሙትና ውስጥ በመግባቷ እግዚአብሔር እንደ ባል ደስተኛ እንዳልሆነ የሚያሳይ ነው   ሆሴዕ 3 ልጆች ነበሩት ሶስቱም ታድያ ስማቸው ትርጉም ነበረው ይሄም ከመጽሐፉ አላማ ጋር ይያያዛል   1 ኢዝራኤል ማለት ትርጉሙ እግዚአብሔር ይበትናል ማለት ነው   2 ሎ ሩሃማ ማለት ምህረት የማይገባት ማለት ነው   3 ሎ አሚ ማለት ደግሞ ህዝቤ አይደላችሁም ማለት ነው   3ቱንም ስም ያወጣው እግዚአብሔር ነው ከእስራኤል ጋር ያለውን ህብረት በሆሴዕ ቤትና ልጆቹ ላይ ገልጧል   ከዚህ መጽሐፍ ውስጥ እግዚአብሔር በምን አይነት ፍቅር እስራኤልን እንደወደዳት እንማራለን   እስራኤል ቃልን ሰምታ የምትመለስበት ጊዜ ላይ ስላልነበረች እግዚአብሔር በሆሴዕ ትዳር ሊያስተምራት ሲነሳ እናያለን   ከዚህ መጽሐፍ የምንማራቸው ነገሮች   ከእግዚአብሔር የሚበልጡብንን ነገሮች እያበጀን ሀይማኖታዊ ስርአትን መፈፀም የመንፈሳዊ ግልሙትና መገለጫ ነው   እግዚአብሔር ሀጢአትን ይቀጣል   እግዚአብሔር ከሀይማኖታዊ ስርአት ይልቅ የልብ ልብ ግንኙነት እንደሚፈልግ እንማራለን   ቁልፍ ጥቅሱ ከምዕራፍ 6፡1-3 እና ቁጥር 6 ላይ ያለው ነው   “1. “ኑ፤ ወደ እግዚአብሔር እንመለስ፤እርሱ ሰባብሮናል፤እርሱም ይጠግነናል፤እርሱ አቊስሎናል፤እርሱም ይፈውሰናል። 2. ከሁለት ቀን በኋላ ያነቃናል፤በእርሱም ፊት እንድንኖር፣በሦስተኛው ቀን ያስነሣናል። 3. እግዚአብሔርን እንወቀው፤የበለጠ እናውቀውም ዘንድ እንትጋ፤እንደ ንጋት ብርሃን፣በእርግጥ ይገለጣል፤ምድርን እንደሚያረሰርስ የበልግ ዝናብ፣እንደ ክረምትም ዝናብ ወደ እኛ ይመጣል።” 6. ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን፣ከሚቃጠልም መሥዋዕት ይልቅ እግዚአብሔርን ማወቅ እሻለሁና።”(አ.መ.ት)   ትንቢተ ሆሴዕ ምዕራፍ 1   ሆሴዕ ባገለገለበት ዘመን ውስጥ 7 ነገስታት አልፈዋል ከ7ቱ አምስቱ ተጠቅሰዋል   ሆሴዕ በታማኝነት እግዚአብሔርን ሲያገለግል የነበረ ነቢይ ነው   “2. እግዚአብሔር በሆሴዕ መናገር በጀመረ ጊዜ፣ እግዚአብሔር “ምድሪቱ ከእግዚአብሔር ተለይታ ታላቅ ምንዝርና እያደረገች ስለ ሆነ፣ ሄደህ አመንዝራ ሴት አግባ፤ የምንዝርና ልጆችንም ለራስህ ውሰድ” አለው።”(አ.መ.ት)   እግዚአብሔር ብዙ ጊዜ ከህዝቡ ጋር ያለውን በትዳር ይመስለዋል   ክርስቶስና ቤተክርስቲያንም በዚህ ዘመን እንዲህ አይነት የጠበቀ ቁርኝት አላቸው   ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5 31 ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይተባበራል ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ። 32 ይህ ምሥጢር ታላቅ ነው፥ እኔ ግን ይህን ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ ክርስቲያን እላለሁ።   ሆሴዕ አግባ የተባለው መጀመሪያም አመንዝራ የሆነች ሴትን ነው   እግዚአብሔር እስራኤልን ሲመርጣት ጻዲቅ ስለነበረች አይደለም   ይህቺ ሴት በእስራኤል ባህል ከሰፈር ውጪ የምትኖር ባል የማግባት ምንም አይነት እድል የሌላትን ነው እግዚአብሔር አግባት ያለው   በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ብንሆን እግዚአብሔር ይወደናል የኛ ሀጢአት ከእግዚአብሔር ፍቅር አይበልጥም   ሆሴዕ ጎሜርን አገባት 3 ልጆችም ወለደች የልጆቹም ስም በቀጥታ እግዚአብሔር ከእስራኤል ጋር ያለውን ህብረት የሚያሳይ ስም ነው   1 ኢዝራኤል ማለት ትርጉሙ እግዚአብሔር ይበትናል ማለት ነው   2 ሎ ሩሃማ ማለት ምህረት የማይገባት ማለት ነው   3 ሎ አሚ ማለት ደግሞ ህዝቤ አይደላችሁም ማለት ነው   “10. “ይሁን እንጂ እስራኤላውያን ሊሰፈርና ሊቈጠር እንደማይችል እንደ ባሕር አሸዋ ይሆናሉ፤ ‘ሕዝቤ አይደላችሁም’ በተባሉበት ቦታ፣ ‘የሕያው አምላክ ልጆች’ ተብለው ይጠራሉ። 11. የይሁዳ ሕዝብና የእስራኤል ሕዝብ እንደ ገና አንድ ይሆናሉ አንድ መሪም ይሾማሉ፤ አንድ ሆነውም በምድሪቱ ይገናሉ፤ የኢይዝራኤል ቀን ታላቅ ይሆናልና።(አ.መ.ት)   እግዚአብሔር በዚህ ሁኔታ ውስጥም ሆነው እንደገና ተስፋ ይሰጣቸዋል   ወደ ሮሜ ሰዎች 9 25 እንዲሁ ደግሞ በሆሴዕ። ሕዝቤ ያልሆነውን ሕዝቤ ብዬ፥ ያልተወደደችውንም የተወደደችው ብዬ እጠራለሁ፤ 26 እናንተ ሕዝቤ አይደላችሁም በተባለላቸውም ስፍራ በዚያ የሕያው እግዚአብሔር ልጆች ተብለው ይጠራሉ ይላል።   ህዝቡን ሁሉ አንድ የሚያደርገው ያ መሪ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ትንቢተ ሆሴዕ ምዕራፍ 2    የእስራኤል መቀጣትና መመለስ   “3. አለበለዚያ ገፍፌ ዕርቃኗን አስቀራታለሁ፤እንደ ተወለደችበትም ቀን አደርጋታለሁ፤እንደ ምድረ በዳ፣እንደ ደረቅም ምድር አደርጋታለሁ፤በውሃ ጥምም እገድላታለሁ።(አ.መ.ት)   በአይሑድ ባህል ዕርቃን መሆን የሀጢአተኝነት ልብስ መደረብ ደግሞ የጽድቅ ምልክት ተደርጎ ይወሰዳል   ትንቢተ አሞጽ 8 11 ፤ እነሆ፥ በምድር ላይ ራብን የምሰድድበት ዘመን ይመጣል፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ እርሱም የእግዚአብሔርን ቃል ከመስማት እንጂ እንጀራን ከመራብና ውኃን ከመጠማት አይደለም።   ለስጋችን ውሃና ምግብ እንደሚያስፈልገን ለነፍሳችን ደግሞ የእግዚአብሔር ቃል መስማት ያስፈልጋል   “5. እናታቸው አመንዝራ ነች፤በውርደትም ፀንሳቸዋለች፤እርሷም፣ ‘እንጀራዬንና ውሃዬን ይሰጡኛል፤ሱፌንና የሐር ልብሴን፣ ዘይቴንና መጠጤን ይሰጡኛል፤ስለዚህ ውሽሞቼን ተከትዬ እሄዳለሁ’ አለች።(አ.መ.ት)   እስራኤል ከእግዚአብሔር ዞር ብላ ይሄን የውሸት አቅርቦት አምና ያመለከችውን ጣኦትን ተከትላ ትሄዳለች   ለመኖር ግዴታ የሚያስፈለገውን ነገር ሳይሆን የቅንጦትን ኑሮ አገኛለው ብላ ነው የኮበለለችው   ሰይጣን ብዙ ጊዜ ሰዎችን በዚህ መንገድ ያጠምዳቸዋል ለመኖር የሚያስፈለግውን ሳይሆን ከዚያ የሚበልጥ ድሎትን ለሰዎች በማቅረብ ወጥመድ ውስጥ ይከታቸዋል   8. እርሷም እህል፣ ዘይትና አዲስ የወይን ጠጅ የሰጠኋት፣ለበኣል አምልኮ ያደረጉትን፣ብርንና ወርቅን ያበዛሁላት፣እኔ እንደሆንሁ አላወቀችም። (አ.መ.ት)   ሰጪው እግዚአብሔር ሆኖ ሳለ እሷ ግን ለባእድ አምልኮ ተጠቀመችበት   እግዚአብሔር የሰጠንን ነገሮች በሙሉ ለምን እየተጠቀምነው እንደሆነ ማወቅ ያስፈልጋል   “12. ከውሽሞቼ የተቀበልሁት ዋጋ ነው የምትለውን፤የወይን ተክሎቿንና የበለስ ዛፎቿን አጠፋለሁ፤ጫካ አደርገዋለሁ፤የዱር አራዊትም ይበሉታል።(አ.መ.ት)   እስራኤል እርሻ አርሰው ምርትን ሲያገኙ በአል የተባለው ጣኦት የባረካቸው ይመስላቸዋል ነበር   “13. ለበኣል አማልክት፣ ዕጣን ስላጠነችባቸው ቀናትእቀጣታለሁ፤በጌጣ ጌጥና በቀለበቶች ራሷን አስጊጣለች፤ውሽሞቿንም ተከትላ ሄዳለች፤እኔን ግን ረስታለች”ይላል እግዚአብሔር።(አ.መ.ት)   የዚህ ሁሉ ጥፋት ምክንያት እግዚአብሔርን መርሳቷ ነው   እግዚአብሔር ስላደረጉት ጥፋት ስለዚህ እፈርድባታለሁ አይልም ድጋሚ ደግሞ ሲራራ እናየዋለን   “14. “ስለዚህ እነሆ፤ አባብላታለሁ፤ወደ ምድረ በዳም እወስዳታለሁ፤በፍቅር ቃል አነጋግራታለሁ።(አ.መ.
556
18
https://youtu.be/dlT1hTxk-3M
662
19
https://youtu.be/gijNhCsBEW4
632
20
354ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ 1 - 3 የዩ
354ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ  ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ  1 - 3 የዩቱብ  የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች  ታገኛላችሁ👇 YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316 TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu TIKTOK#2:-  tiktok.com/nikodimoschrstiancenter TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow
684