382
Subscribers
-124 hours
+77 days
+4330 days
Posts Archive
382
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
የሬሜዲያል መቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደረገ።
የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የሚያስችል የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደርጓል፡፡
በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያላስመዘገቡ ነገር ግን ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣቸውን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተማሪዎች የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የሚያስችላቸው የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደርጓል፡፡
በዚህም መሰረት በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 30 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ማለትም (210 ከ 700፣ 180 ከ 600 እና 150 ከ500) የተቆረጠ መሆኑ ተመላክቷል።
ከላይ በተራ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የRemedial ፕሮግራም የሚከታተሉት የሚከተሉትን መቁረጫ ነጥብ ያሟሉ ብቻ እንደሚሆኑ ተጠቁሟል፡፡
☑ የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 255 ያመጡ
☑ የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 234 ያመጡ
☑ የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች ከ600 ነጥብ 218 ያመጡ
☑ የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች ከ600 ነጥብ 200 ያመጡ
☑ ታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 224 ያመጡ
☑ ታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 210 ያመጡ
☑ ታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ600 192 ያመጡ
☑ ታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ600 ነጥብ 180 ያመጡ
☑ አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 210 ያመጡ
☑ አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 210 ያመጡ
☑ አርብቶ አደር አካባቢ የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ600 ነጥብ 180 ያመጡ
☑ አርብቶ አደር አካባቢ የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ600 ነጥብ 180 ያመጡ
☑ ዓይነ ስውራን ማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ500 ነጥብ 150 ያመጡ
☑ ዓይነ ስውራን ማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ500 ነጥብ 150 ያመጡ መሆን አለባቸው ተብሏል።
መረጃውን ትምህርት ሚኒስቴርን ዋቢ በማድረግ ያሰራጨው ኤፍ ቢ ሲ ነው።
@tikvahethiopia
382
Repost from Ethiopian Digital Library
የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መጽሀፍ ከ KG -12
New Curriculum Student Text Books from KG -12
382
☞ የተማሪዎችን ውጤት [#Exam_Result, #Report_Card] በትምህርት ቤት መገኘታቸውን [#Attendance] መከታተል የሚያስችላችሁን እንዲሁም ወሳኝ የሆነ መልእክት የምንልክበት #መተግበሪያ [Android Application] ስለምንልክ መተግበሪያውን አስቀድማችሁ በማውረድ አገልግሎቱን ስንጀምር እንድትጠቀሙ ይሁን::
382
☞ የተማሪዎችን ውጤት [#Exam_Result, #Report_Card] በትምህርት ቤት መገኘታቸውን [#Attendance] መከታተል የሚያስችላችሁን እንዲሁም ወሳኝ የሆነ መልእክት የምንልክበት #መተግበሪያ [Android Application] ስለምንልክ መተግበሪያውን አስቀድማችሁ በማውረድ አገልግሎቱን ስንጀምር እንድትጠቀሙ ይሁን::
382
እናስታውስዎ
ቀን7/2/2016
የ2016 ዓ/ም የአንደኛው ተርም የመክፈያ ጊዜ ከጥቅምት 1_10/2/2016 ዓ/ም ብቻ ስለሆነ ቀኑ እንዳያልፍብዎት ልናስታውስዎ ወደድን ።
የክፍያ መጠኑ ከ9_10ኛ =8820
.. .................. ከ11_12ኛ=9198
በዳሸን ባንክ መሆኑንም እናስታውስዎ!
ጣሳቸው ጫኔ
ር/መምህር
382
Repost from Ethiopian Digital Library
በ12ኛ ክፍል ውጤት ቅሬታ ካላችሁ እስከ ጥቅምት 05/2016 ዓ.ም አመልክቱ
በ2015 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተያ ውጤት ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተፈታኞች eaes.et ላይ እስከ ጥቅምት 05/2016 ዓ.ም ከቀኑ 11:30 ድረስ ቅሬታችሁን በኦንላይን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አግልግሎት ገልጿል።
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
382
ቀን 2/2/2016
ሰላም ወላጆች እንደምን አደራችሁ
የትራንስፖርት (ሰርቪስ) ተጠቃሚዎች ለሾፌሮች በቀጥታ የሚከፈል ክፍያ አይኖርም ። ስለሆነም በተከፈተው አካውንት ብቻ ገቢ እንዲሆን እናሳስባለን ።
