cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Skyline media

Show more
Advertising posts
50 169Subscribers
-2124 hours
-1917 days
-91730 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

በፅንፈኛው የፋኖ አመራርና አባላት ላይ እርምጃ ተወሰደ፡፡ የፅንፈኛው አመራርና አንድ የቡድኑ አባል ሲገደሉ አንደኛው በቁጥጥር ስር ውሏል ፡፡ *** የፅንፈኛው ቡድን አባላት የሆኑት ናሁሰናይ አንድአርጌ ታረቀኝ ፣ አቤኔዜር ጋሻው አባተ እና ሀብታሙ አንድአርጌ ተሰማ የተባሉት የፅንፈኛው ፋኖ ቡድን አባላት በከተማችን አዲስ አበባ የሽበር ጥቃት ለመፈፀም ተልዕኮ ይዘው እየተንቃሰቀሱ መሆኑን የፀጥታ አካላት ባደረጉ ክትትል ይድረሱበታል፡፡ አሸባሪዎቹ የሽብር ተግባራቸውን ሳይፈፅሙ በቁጥጥር ስር ለማዋል የፖሊስ አባላት እንቅስቃሴ እያደረጉ ባለበት ሁኔታ ሚያዚያ 4 ቀን 2016 ዓ/ም ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው ሚሊኒዬም አዳራሽ አካባቢ ፅንፈኞቸ እጃቸውን እንዲሰጡ ቢጠየቁም ፍቃደኛ ባለመሆን በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2C 14373 አ/አ አይነቷ አይሱዙ ዲዛዬር መኪናን በመጠቀም ከፖሊስ አባላት ጋር ቶክስ በመክፈታቸው የፅንፈኛው ፋኖ መሪ ናሁሰናይ አንዳርጌ ታረቀኝ ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ ሲሞት ፅንፈኛው ሀብታሙ አንዳርጌ ተሰማ በተኩስ ልውውጡ መሃል ተገድሏል፡፡ አቤኔዘር ጋሻው አባት የተባለው የቡድኑ አባል ሳይቆስል በቁጥጥር ስር መዋሉን አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡ ፅንፈኞቹን በቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገ እንቅስቃሴ ሳጅን አራርሳ ተሾመ እና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ ሲቆስሉ አቶ እንዳሻው ጌትነት የተባሉ ግለሰብ ፅንፈኞቹ በመኪናቸው እንዲጭኗቸው ቢያስገድዷቸውም ግለሰቡ አልተባበር በማለታቸው በፅንፈኛው አባላት ተገድለዋል፡፡ አቶ እንደሻው ሲያሽከርክሯት የነበረቸው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2 አ/አ 80457 በጥይት ጉዳት እንደረሰባት አዲስ አበባ ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል ፡፡ በቀጣይ ፖሊስ የደረሰበትን ዝርዝር መረጃ እንደሚገልፅ አስታውቋል፡፡
Show all...
👍 20👎 1
በኢትዮጵያ እርግጥ ሁለት ዜግነት ተፈጥሯል? ከህግ በላይ የሆነስ አለን?
Show all...
👎 9👍 2 1
Repost from Natnael Mekonnen
ለህግ ይቅረብ‼️ ከጀርባው ልክ እንደሱ የባለገና ጭፍን ጥላቻ ያለው ባለስልጣን ሳይኖር እንዲህ ሊናገር አይችልም:: ይህ ያልኩበት ምክንያት ቲክቶኩን በጥቆማ ገብቼ አብዛኛው ፎቶና ቪዲዮዎቹን ስመለከት ከተለያዩ አመራዎች ጋር ፎቶ አለው:: በኦሮሚያ ክልል ድሬድዋ ይመስለኛል ወይም ሃረር የብልጽግና ቢሮ ውስጥ ስብሰባ እንደሚመራ ሰው ተቀምጦ የተነሳቸው ምስሎች አሉ:: ልጁ ነዋሪነቱ በአሜሪካን ሃገር ሜኖሶታ ሲሆን አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ያለው:: በዚህ ቪዲዮ ላይ የሚናገረው መረን የለቀቀና እጅግ አጸያፊ አንድ ማህበረሰብን የሚያንቋሽሽ አብሮ የመኖርን እሴት የሚሸረሽር አጸያፊ ስድቦችን የሚሳደብበትን ቪዲዮን ደግሜ እዚህ ላይ መለጠፍ ይቅርና ሰምቶ ለመጨረስም ያማል!!! እጅግ ይሰቀጥጣል:: ኢትዮጵያ ውስጥ ተቀምጦ በቀጥታ (Live) ይህን ሲናገር መስማት እጅጉን ያማል‼️ የኦሮሚያ ክልል መንግስት የፌደራል ፖሊስ አዲስ አበባ ፖሊስ የብሔራዊ መረጃ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ከወዴየት ነው ያላችሁት? ምንስ እየተከናወነ ነው???????!!!
Show all...
👍 5
Show all...
anteneh123(antenehabrahamb) is LIVE | TikTok

ከልብ እንነጋገር. Check out anteneh123(antenehabrahamb) LIVE videos on TikTok! Watch, follow, and discover the latest content from anteneh123(antenehabrahamb).

7👍 4
Repost from Zehabesha
ታዋቂው እና ዝነኛው የቀድሞ ድምፃዊ ሙሉቀን መለሰ ከዚህ አለም በሞት ተለየ::
Show all...
የፀሐይ ግርዶሹ በርካታ የአሜሪካ ከተሞችን በእኩለ ቀን አጨልሟቸዋል **************************** የፀሐይ ግርዶሹ በርካታ የአሜሪካ ከተሞችን በእኩለ ቀን ሙሉ በሙሉ እንዳጨለማቸው ተገልጿል፡፡ ሙሉ የጸሐይ ግርዶሹ ማዛትላን የተባለችውን የሜክሲኮ ከተማ ጨለማ አልብሷት ካለፈ በኃላ ወደ ዳላስ፣ ቴክሳስ እና ሌሎች የአሜሪካ ግዛቶች ተሸጋግሯል፡፡ በአንዳንድ የአሜሪካ ግዛቶች የጸሐይ ግርዶሹ እስከ 4 ደቂቃ መቆየቱም ተመላክቷል፡፡ የጸሐይ ግርዶሹ በሚቀጥሉት ሰዓታት ወደ ሰሜን አሜሪካ ሰሜናዊ እና ምስራቃዊ ክፍሎች እንደሚዞርም ተጠቁሟል፡፡ በሰሜን አሜሪካ ክስተቱን ለማየት በ10 ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች አደባባይ መውጣታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ክስተቱን በልዩ ሁኔታ እየተከታተለ የሚገኘው የአሜሪካ የጠፈር ምርምር ተቋም (ናሳ) ያለ ጸሐይ መነጽር ግርዶሹን ለማየት መሞከር የዓይን ብርሃንን እስከማሳጣት የሚያደርስ የጤና ችግር ሊያስከትል እንደሚችል በማስገንዘብ ላይ ነው፡፡
Show all...
👍 13 3
ወጣት ሶፎኒያስ አስራትን ገድለው ተሽከርካሪውን ዘርፈው የተሰወሩ ማንነታቸው ያልታወቁ ወንጀል ፈፃሚዎችን በ48 ሰዓት ውስጥ ከዘረፉት ተሽከርካሪ ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል ሟች ወጣት ሶፎኒያስ  መጋ24 ከንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ ወረዳ 1 ናሆም ሆቴል አካባቢ ከሌሊቱ 8፡00 ሰዓት ላይ ማንነታቸው የማይታወቁ ሦስት ግለሰቦችን አሳፍሮ ወደ ቦሌ ሚካኤል ለማድርስ መሄዱን ጉዳዩን ለመከታተል የተቋቋመው የፖሊስ የምርመራና የክትትል ቡድን አባላት ባደረጉት ክትትል አረጋግጠዋል ወንጀል ፈፃሚዎቹ ወንጀል ለመፈፀም አቅደው እና ተደራጅተው የትራንስፖርት አገልግሎት ፈላጊ መስለው ሹፌሩን በመቅረብ ከተሳፈሩ በኋላ አንገቱን በገመድ አንቀው በመግደል አስክሬኑን በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ ከ ወረዳ 5 አሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ አካባቢ ወደ አቦ ቤተክርስቲያን በሚወስደው መንገድ ላይ በመጣል  አይነቷ ቪትዝ የሴሌዳ ቁጥር ኮድ 2A 93488 ተሽከርካሪ ጨምሮ 2 ሞባይል ስልኮችን ዘርፈው ይሰወራሉ ፖሊስ ሌት ተቀን ባደረገው ብርቱ ክትትል ወንጀል ፈፃሚዎቹ የሰረቁትን ተሽከርካሪ ለመሸጥ እየተስማሙ መሆኑን በበቂ ማስረጃ ካረጋገጠ በሗላ ክትትሉን በመቀጠል ሦስቱን ዋና ወንጀል ፈፃሚዎች የሰረቁትን መኪና በቦሌ ክ/ከ  ልዩ ቦታው ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ለመሸጥ እየተደራደሩ እንዳለ በቁጥጥር ስር በማዋል የተሰረቀችውን መኪና ፣ 2 ሞባይል ስልኮችን ልዩ ልዩ ኤግዚቢቶችን ይዞ ምርመራውን መቀጠሉን ገልጿል ፖሊስ ባደረገው ክትትልና ምርመራ ማንነታቸው የማይታወቁ ወንጀል ፈፃሚዎችን በ48 ሰዓት ጊዜ ውስጥ በመለየት 3 ዋና ወንጀል ፈፃሚዎችንና 3 ግብራበሮቻቸውን በቁጥጥር ስር ማዋሉ ታውቋል የምርመራ ሥራው እንዳበቃ የፍርድ ሂደት ውጤቱን በቀጣይ ለህዝብ እንደሚገለፅ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል
Show all...
👍 23 5