1 739
Subscribers
-124 hours
+17 days
-730 days
Posts Archive
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባለፋት ቀናት በስራ ሂደቶችና ስራ ክፍሎች ላይ ሲያካሂደው የቆየውን የ2016 ዓ.ም የመጀመርያ 6ወር አፈፃፀም ድጋፍና ክትትል ግብረ መልስና ማጠቃለያ ሪፖርት መድረክ አካሄደ::
በግብረ መልስ አሰጣጥ መድረኩ ላይ ድጋፍና ክትትል ሲደረግባቸው የነበሩ ዋና ስራ ሂደቶች እና ስራ ክፍሎች የተገኙ ሲሆን በዲን ፅ/ቤት የሚመራው የድግፍና ክትትል ቡድንም ትግበራውን በማጠናቀቅና ግብረ መልሶችን በማዘጋጀት በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ለተሳታፊዎች ቀርቧል::
በመድረኩ በቀረበው ማጠቃለያ ግብረ መልስም ዋና ስራ ሂደቶና ስራ ክፍሎች በድጋፍና ክትትል ወቅት ከተሰጣቸው ተልዕኮ አንፃር የታዩባቸውን ክፍተቶችና ጥሩ ተመኩሮዎች በዝርዝር በማስቀመጥ ግብረ መልስ መስጠት ተችሏል::
በተጨማሪም በሪፖርት መልክ ከተሰጠው ግብረ መልስ በተጨመማሪ ለሁሉም ስራ ሂደቶችና ስራ ክፍሎች በተደረገው ድጋፍና ክትትል መሰረት የፅሁፍ ግብረ መልስ የተሰጣቸው ሲሆን በዚህም የታዩ ክፍተቶችን በቀጣይ አፅኖት ሰተው ለመተግበር እንደ መነሻ ይሆናልም ተብሏል::
በመጨረሻም በተቋሙ ካሉት የስራ ሂደቶችና ክፍሎች በክትትልና ድጋፍ ወቅት በአንፃራዊነት ልቆ የተገኘው የ አይ.ሲ.ቲ ትምህርትና ስልጠና ክፍል በመድረኩ ለሌሎች የስራ ሂደቶችና ክፍሎች ተሞክሮውን እንዲያክፍል የተደረገ ሲሆን ይህም የስራ ክፍሎቹ በቀጣይ የነበሩ ውስንነቶችን በመቅረፍ እንደ ተቋም ለሚመዘገው ውጤት ጉልህ አስተዋፇ እንዲያበረክቱ እንደሚያግዝም ታምኖበታል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
የካቲት 27/2016 ዓ.ም
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
ላለፉት 2 ቀናት “ከዕዳ ወደ ምንዳ” በሚል ርዕስ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እና ሁለቱ የመንግስት ኮሌጅ አስተዳደር ሰራተኞች እና አሰልጣኝ መምህራን ሲሰጥ የቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቀቀ።
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ስልጠናው በተለያዩ ሀገራዊ እና አስተዳደራዊ የመንግስት ነባራዊ ሁኔታዎችን መሰረት በማድረግ በተዘጋጁ የስልጠና ሰነዶች ዙሪያ ላይ ያተኮረ ሲሆን የመንግስት ሠራተኛውን አቅም በማጎልበት ኢትዮጵያ ብሎም አስተዳደሩ ለጀመሩት የእድገትና ለውጥ ጉዞ ወሳኝ ሚናቸውን እንዲወጡ የሚያስችላቸው ግንዛቤ እንዲይዙ የሚያስችል አቅም የተፈጠረበት ስልጠና ነው ብለዋል።
በተመሳሳይ የቢሮው ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የቢሮው የመንግሥት ሠራተኞች በአጠቃላይ ስልጠናው ሠራተኛው ራስን ከመምራት ጀምሮ ህዝብን በሚገባ ማገልገል እንዲችልና በሠራተኛው ዘንድ የተግባርና የሀሳብ አንድነት በማምጣት ቀጣይነቱ የተረጋገጠ ጥራት ያለውና ፍትሀዊ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችልና የሚያስረዳ ግንዘቤ መፍጠሩን ተናግረዋል።
በስልጠናው ማጠናቀቂያ ሰልጣኝ የቢሮውና የኮሌጆች አስተዳደር ሠራተኞች እና አሰልጣኝ መምህራን በስልጠናው የቀረቡ ሰነዶች ላይ ግልጽነት የሚያስፈልጋቸውን ነጥቦች በማንሳትና በመጠየቅ ከመድረክ ሰፊ ማብራሪያ እና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል በመጨረሻም ሰልጣኞች በተሰጣቸው የግንዛቤ ማጎልበቻ ስልጠና መደሰታቸውን ገልጸው መንግስት የጀመረውን እድገትና ለውጥ እንዲያስቀጥል በማሳሰብ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 7/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
''ከዕዳ ወደ ምንዳ'' በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ የአቅም ግንባታ ስልጠና በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እና ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ስር ለሚገኙ የአስተዳደር ሰራተኞችና አሰልጣኝ መምህራን መሰጠት ጀመረ፤
በአቅም ግንባታ ስልጠናው ላይ በክብር እንግድነት በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የድሬዳዋ ብልጽግና ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ እንደተናገሩት ይህ ስልጠና የመንግስት ሰራተኛው የመንግስትን አቅጣጫ በመረዳትና መግባባትን በመፍጠር የአስተዳደራችንን አልፎም የሀገራችንን ብልጽግና በማረጋገጥ ሂደት ላይ አቅም የሚፈጥር ነው ብለዋል፤
የቢሮው አስተዳደር ሰራተኞች እና አሰልጣኝ መምህራን ዛሬን ጨምሮ ለሚቀጥሉት 2 ተከታታይ ቀናት "ሀብት እና ብልፅግናን መፍጠር እና ማስተዳደር እንዲሁም አገልጋይና ስልጡን ሲቪል ሰርቪስን መገንባት" በሚሉ ርዕሶች በቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ስልጠናው ለተከታታይ ሁለት ቀናት ከየካቲት 6-7/2016 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 6/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከሻሎም ኢንጂነሪንግ ድርጅት ጋር በመተባበር ላሰለጠናቸው ሰልጣኞች ተማሪዎች እውቅና ሰጠ::
ስልጠናው የተሰጠው በኮንስትራክሽን ዘርፍ በBasic General constraction በአጫጭር ስልጠና መርሃ-ግብር ሲሆን በዚህ ስልጠናም 16 የሚሆኑ ሰልጣኝ ተማሪዎች ስልጠናቸውን በብቃት በማጠናቀቅ በራሳቸው በሰልጣኞች ተሰርቶ በተጠናቀቀው ግንባታ ውስጥ በኮሌጁ የእውቅናና ሰርተፊኬት ፕሮግራም ተደርጎላቸዋል::
ይህ ስልጠና ከግብ እንዲደርስም ሻሎም ኢንጂነሪንግ ድርጅት የስልጠና ግብዓቶችን ከማቅርብ ጀምሮ አስፈልጊውን ድጋፍና ክትትል በማድረግ ጉልህ ሚና የተወጣ ሲሆን የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በበኩሉ ለስልጠናው ብቁ የሆኑ ሰልጣኞችን ከመመደብ ጀምሮ ሰልጣኞቹ የሰለጠኑትን በተግባር የሚሰሩበት ሳይት በማመቻቸት ሰልጣኞች በሁሉም ረገድ ብቁና ተፈላጊ ሞያተኛ ሆነው እንዲወጡ ና ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ ትልቁን ድርሻ ተወጥቷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
የካቲት 4/2016 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ ለሚገኙ ዋና ስራ ሂደቶችና ክፍሎች የ2016 ዓ.ም ሁለተኛ ሩብ ዓመት የድጋፍና ክትትል መርሃ-ግብር በማካሄድ ላይ ይገኛል::
የድጋፍና ክትትል መርሃ-ግብሩን እያደረገ የሚገኘው በኮሌጁ ዲን የሚመራ የድጋፍና ክትትል ቡድን ሲሆን በድጋፍና ክትትሉ ወቅትም ስራ ሂደቶችና ክፍሎች በበጀት አመቱ የእቅድ አፈፃፀም ግምገማና ሪፖርት፣ በመረጃ እደረጃት፣ በQMS አተገባበር ያሉበት ደረጃ፣ በስራ አካባቢ ያላቸው የካይዘን አተገባበር እንዲሁም በግብአት አጠቃቀም ያሉበትን ቁመና የሚገመግም ሲሆን በተጨማሪም ስራ ሂደቶችና ክፍሎች እንደየስራ ባህርያቸው መፈፀም ከሚገባቸው ተግባራት ምን ያህሉን ተግባራዊ አድርገዋል ሚለው ላይም ያተኮረ የድጋፍና ክትትል መሆኑ ተገልጿል::
የድጋፍና ክትትል ቡድኑ በድጋፍና ክትትሉ ወቅት ለስራ ሂደቶችና ክፍሎች በቃል ግብረ መልስ የሚሰጥ ሲሆን የድጋፍና ክትትሉ ማብቂያ ላይም ለሁሉም በፅሁፍ ግበረ መልስ የሚሰጥም ይሆናል::
የዚህ ድጋፍና ክትትል ዋና አላማ በተቋሙ የሚገኙ ስራ ሂደቶችና ክፍሎች በአፈፃፀም ጉድለት የሚታይባቸውን ተግባራቶች ለይቶ ትኩረት እንዲሰጣቸው የማድረግና የተሻለ አፈፃፀም ለታየባቸው ስራ ሂደቶችና ክፍሎች ደግሞ ለሌሎች ተሞክሮ እንዲሆኑ በማለም ሲሆን በቀጣይም ድጋፍና ክትትሉ በቀሩት ስራ ሂደቶችና ክፍሎችም የሚቀጥል ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
የካቲት 2/2016 ዓ.ም
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
