en
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Open in Telegram
1 741
Subscribers
+224 hours
+37 days
-730 days
Posts Archive
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ የአምራች ኢንዱስትሪውን ፍላጎት ለመለየት የተዘጋጀ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ለባለድርሻ አካላት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ:: አምራች ኢንዱስትሪው የሚጠይቀውን ብቁና የሰለጠን የሰው ሀይል በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ አሰልጥኖ ለማቅረብ ታሳቢ ያደረገ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በተቋም ደረጃ የተጠና ሲሆን ወጣቶች ጊዜው የሚጠይቀውን የአጫጭር ስልጠና ምርጫቸው ከማድረጋቸው ጋር ተያይዞ የአምራች ኢንዱስትሪውን የሙያ ፍላጎት መሰረት ያደረገ የአጫጭር ስልጠና ፕሮግራም ለመቅረፅ የጥናት ቡድኑ ከኢንዱስትሪ አድቫይዘሪግ ቦርድ አባላት ጋር በቅንጅት መስራቱም ተገልፇል:: በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ትኩረት ተደርጎባቸው ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል ለኢንዱስትሪው ግብዓት የሚሆኑ ብቁ ባለሙያዎችን የማፍራቱን ሂደትን መደገፍ ዋነኛው መሆኑ የተገለፅ ሲሆን የፕሮጀክቱ ባለሙያዎች ከትምህርትና ስልጠና ዘርፉ ጋር በመቀናጀት ባዘጋጁት የኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሰረት ያደርገ የአጫጭር ስልጠና ፕሮግራም ላይ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ሲያደርግም ቆይቷል:: በፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱ መሰረት ውጤታማነታቸው ታምኖበት የተለዩ የአጫጭር ስልጠና ፕሮግራሞችን የጥናት ቡድኑ በዝርዝር ያቀረበ ሲሆን በተጨማሪም ለስልጠና ፕሮግራሞቹ እየተዘጋጁ ሚገኙት ማሰልጠኛ ሞጁሎች ላይም ለባለድርሻ አካላት ገለፃ አድርገዋል:: በመድረኩ በቀረቡት አጠቃላይ ሰነዶች መነሻነት ውይይት የተካሄደ ሲሆን ተሳታፊዎች በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ የበቃ የሰው ሀይል ከማሟላት አኳያ በጥናቱ ያልተዳሰሱና ሊካተቱ ይገባል ያሏቸውን ጉዳዮች ለጥናት ቡድኑ አመላክተዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በInnovative Pedagogy ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል:: ለኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን የተሰጠ የሚገኘው የInnovative Pedag
+9
ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በInnovative Pedagogy ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል:: ለኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን የተሰጠ የሚገኘው የInnovative Pedagogy ስልጠና በፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር አዘጋጅነት ከፌደራል TVET ኢንስቲትዩት በመጡ የዘርፉ ባለሞያዎች እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን የስልጠናው ዋና ዓላማም የተለመደውን የማሰልጠኛ ስነ-ዘዴ ለማሻሻልና ጊዜው የደረሰበትን ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ትምህርትና ስልጠናውን ለማዘመን ያለም ስልጠና እንደሆነም ተገልፇል:: ይህ በኮሌጁ ለ5 ቀናት የሚቆየው ስልጠናም ባለፉት 15 ቀናት አሰልጣኝ መምህራኑ በOnline ሲከታተሉት የነበረውን የ Innovative Pedagogy ስልጠና በተግባር የሚሰለጥኑበት እንደሆነው ተመላክቷል:: ስልጠናው በሀገሪቱ በሚገኙና የEASE ፕሮጀክት በሚተገበባቸው 24 ፖሊቴክኒኮች ላይ ለሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን አየተሰጠ እንደሚገኝም ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግንቦት 11/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ሀገር አቀፍ የካይዘን ውድድርን አስመልክቶ በኮሌጁ ምልከታ ተካሄደ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በካይዘን ፅንሰ-ሃሳብ መነሻነት እያከናወናቸው የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ተግባራትና ወቅታዊ አፈፃፀም ላይ ከፌደራል በመጡ ባለሙያዎች በዛሬው እለት ግምገማ ተካሂዷል:: የሀገር አቀፍ የካይዘን ውድድር አካል በሆነውና ከፌደራል በመጡ ባለሙያዎች በተካሄደው ምዘና በኮሌጁ የስራ ቦታን ምቹ ከማድረግ ፤ ብክነትን ከመቀነስ፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ፍጥነትን ከማሻሻል አኳያ በተቀመጡ መመዘኛዎች የተከናወኑ ተግባራትንም ገምግሟል:: የምልከታ ቡድኑ በኮሌጁ የካይዘን ትግበራ አጠቃላይ የአፈፃፀም ሪፖርትን የተመለከት ሲሆን ከ8ቱ የውጤት አመላካች አኳያ የተገኙ ውጤቶችን በሪፖርቱ ተመልክተዋል:: በማስቀጠል ቡድኑ በተቋሙ የሚገኙ የስራ ክፍሎችና የስልጠና ወርክሾፖች ላይ የተከናወኑ የካይዘን ትግበራዎችን ከመመልከት በተጨማሪ የካይዘን ትግበራው ውጤታማነትና የተገኘውን ለውጥ የሚያመላክቱ ሰነዶችን በዝርዝር የገመገመ ሲሆን በኮሌጁ በትግበራ ወቅት የተገኙ ምርጥ ተሞክሮችንም መመልከት ችሏል:: "ዛሬን እናሻሽል፤ ብክነትን እንቀንስ፤ ጥራትና ፍጥነትን እንጨምር፤ ነገን እንገንባ"!! የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓትን (ICSMIS) እና የመንግሥት ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ (Civil Servant Data Verification) ምንነትና አስፈላጊነት ======================== ኢትዮጵያ የመንግሥት ሠራተኞችን መረጃ በማዕከላዊ ዲጂታል ሥርዓት ለማስተዳደር ያላትን ፍላጎት ለማሳካት እና ቀደም ሲል የነበረውን ችግር በዘላቂነት መቅረፍ በሚያስችል መልኩ የሰው ሀይል መረጃን ወደ ዘመናዊ የሰው ኃይል አስተዳደር ስርዓት ለመሸጋገር በርካታ እርምጃዎችን እየወሰደች ነው። እንደ ሀገር እየተወሰዱ ካሉ እርምጃዎች መካከል አንዱ የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓትን (ICSMIS) ተግባራዊ ማድረግ ሲሆን ይህንኑ መሰረት በማድረግም የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን እና የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት በጋራ በመሆን የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ቬሪፊኬሽን ስራ ተጀምሯል። የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓትን (ICSMIS) እና የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ቬሪቪኬሽን ስራዎች የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች በውስጣቸው ይይዛሉ:- 1. የICSMIS ፍቺ እና አላማ ይህ ስርዓት በመንግሥት ተቋማት ውስጥ ያሉ ሠራተኞችን ብዛት፣ የሥራ መደብ፣ ዕድሜ፣ ትምህርት ደረጃ፣ ደመወዝ እና ሌሎች መረጃዎች በማዕከላዊ መረጃ ቋት ለማስተዳደር የተዘጋጀ አገር አቀፍ የመረጃ ስብስብ ነው። በአብዛኛው የሚመራው በPublic Service and HR Directorate ወይም በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ነው። 2. የመረጃ ማረጋገጫ (Verification) አስፈላጊነት ከዚህ ቀደም የሠራተኛ ፋይሎች በተቋማት ተበትነው ስለነበር፣ ትክክለኛ ማዕከላዊ መረጃ ቋት አልነበረም። ስለዚህ የሚከተሉትን ለማስፈጸም የሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ አስፈለገ፦ · ትክክለኛ የመንግሥት ሠራተኞች ዳታቤዝ መፍጠር · የደመወዝ ክፍያ ሥርዓት ማሻሻል · የሰው ኃይል እቅድ ማውጣት · ዘመናዊ የሰው ኃይል አስተዳደር መሠረት መጣል · ተደጋሚ ወይም ክፍት የሥራ መደቦችን ለይቶ ለወደፊት ዕቅድ መረጃ ማግኘት 3. የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ሚና ኮሚሽኑ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ በተለያዩ ሕጎች መሠረት የተቋማትን አደረጃጀት እና የሰው ኃይል አስተዳደር በበላይነት ሲያስተዳድር ቆይቷል። ኮሚሽኑ የሲቪል ሰርቪስን የሰው ኃይል መረጃ ሥርዓት በወጥነት እና በዘመናዊነት ተግባራዊ ለማድረግና ማዕከላዊ የመረጃ ምንጭ ሆኖ ለማገልገል ይሠራል። 4. ያጋጠመ ተግዳሮት ኮሚሽኑ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ዘመናዊ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት ሳዘረጋ በመቅረቱ፣ ከአገልግሎት ጥራትና ቅልጥፍና አንጻር ተፈላጊውን ደረጃ ላይ መድረስ አልቻለም። 5. መፍትሔ እና ወቅታዊ እንቅስቃሴ አሁን ላይ ኮሚሽኑ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማስገኘት በርካታ የለውጥ ፕሮግራሞችን በመተግበር ላይ ይገኛል። እንዲሁም የመንግሥት አገልግሎት እና አስተዳደር ፖሊሲ ሰነድ አዘጋጅቶ እንዲጸድቅ ተደርጓል። 👉የኢስሚስ (ICSMIS) ትግበራ፣ ችግሮች፣ እና የመረጃ ማረጋገጫ (verification) አስፈላጊነት ዋና ዋና ነጥቦች፦ 1. የዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ አስፈላጊነት የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ ግብ ለማሳካት፣ የሲቪል ሰርቪስ የሰው ኃይል መረጃ አያያዝ ሥርዓት በወጥነት እና በዘመናዊነት እንዲተገበር ዲጂታል ቴክኖሎጂ መደገፍ አስፈለገ። ከፖሊሲው ሰባት አምዶች አንዱ ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ መገንባት ሲሆን፣ ለዚህም የዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ ገብቷል። 2. የICSMIS ትግበራ ታሪክና ተግዳሮት · ከ2004 በጀት ዓመት ጀምሮ ሥርዓቱን ማስፋፋት ተጀምሯል። · ነገር ግን በቂ ክትትልና ተግባራዊነት ባለመኖሩ በወቅቱ ሙሉ በሙሉ ሊተገበር አልቻለም። · ከ2006 ጀምሮ በፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ደረጃ ተቋቁሞ ሥራዎችን ማከናወን ጀምሯል። 3. እስካሁን ያሉ ሥሪቶች (Versions) · 1ኛ ሥሪት (1st version ICSMIS) – በአንዳንድ የክልልና የፌዴራል ተቋማት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። · 2ኛ ሥሪት (2nd version ICSMIS) – በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር እየተጠቀመ ይገኛል። · አዲሱ ሥሪት – ብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ)ን መነሻ በማድረግ በአገር አቀፍ ደረጃ ለመተግበር የቅድመ-ዝግጅት ሥራ እየተከወነ ነው። 4. የመረጃ ማረጋገጫ (Verification) አስፈላጊነት ሥርዓቱ በአገር አቀፍ ደረጃ ሙሉ በሙሉ ባለመተግበሩ የሚከተሉት ችግሮች ተፈጥረዋል፦ · የመንግሥት ሠራተኞች መረጃ በአንድ ቦታ ባለመደራጀቱ ለፖሊሲ ጥናት የሚሆን ግብአት ማቅረብ አልተቻለም። · በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን እና በገንዘብ ሚኒስቴር መካከል ስለ መንግሥት ሠራተኞች ቁጥር ጉልህ ልዩነት አለ። ለዚህም መፍትሔ እንዲሆን አገር አቀፍ የመንግሥት ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ (Civil Servant Data Verification) በመካሄድ ላይ ነው። ግቡም ትክክለኛውን የሠራተኞች ቁጥርና ተጓዳኝ መረጃ በኦንላይን ወደ ICSMIS ማስገባት ነው።

ለሥራ ፈላጊዎች የወጣ ማስታወቂያ በተለያዩ የውጭ አገራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ለምትፈልጉ ዜጎች የኢትዮጵያ መንግስት ከአገራቱ ጋር በፈጠረው ስምምነት እድሉ ተመቻችቷል። በዚህም እስከ ሚያዚያ 2
+2
ለሥራ ፈላጊዎች የወጣ ማስታወቂያ በተለያዩ የውጭ አገራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ለምትፈልጉ ዜጎች የኢትዮጵያ መንግስት ከአገራቱ ጋር በፈጠረው ስምምነት እድሉ ተመቻችቷል። በዚህም እስከ ሚያዚያ 26/2018 ዓ.ም ባሉት የሥራ ቀናት በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ እና በሁሉም የአስተዳደሩ ወረዳ የሥራና ክህሎት ማስተባበሪያዎች በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

በኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚዘጋጁ ኤክስፖዎች ለአገር በቀል አምራቾች የእርስበርስ ትስስርን መፍጠር እንደሚያችሉ ተገልፀ: "ድሬ ታምርት፤ ኢትዮጵያ ትበልፅግ” በሚል መሪ ቃል ከሚያዝያ 15 እስከ 20 ቀን
+7
በኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚዘጋጁ ኤክስፖዎች ለአገር በቀል አምራቾች የእርስበርስ ትስስርን መፍጠር እንደሚያችሉ ተገልፀ: "ድሬ ታምርት፤ ኢትዮጵያ ትበልፅግ” በሚል መሪ ቃል ከሚያዝያ 15 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆየው አራተኛው የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ሀገር አቀፍ ንቅናቄና የኢንዱስትሪ ኤግዚቢሽንን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል የአስተዳደሩ ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀርና ከአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በዛሬ እልት በደማቅ ሁኔታ ተከፍቷል። በዛሬው እለት ጅማሮውን ባድረገው ኤግዚቢሽን እና ባዛር ላይ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅም እየተሳተፈ የሚገኝ ሲሆን በዚህም በኮሌጁ የተሰሩና የማህበረሰቡን ችግር ፈቺ የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን እንዲሁም ኢንዱስትሪዎች ምርትና ምርታማነታቸውን በይበልጥ እንዲያሳድጉ ለማስቻል የተሰሩ ተኪ ምርቶችንም ይዞ ቀርቧል:: ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሚያዝያ 15/2018 ዓ.ም ድሬዳ

እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ!! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሳሣኤው አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታና የመተሳሰብ በዓል ይሆንላ
እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ!! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሳሣኤው አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታና የመተሳሰብ በዓል ይሆንላችሁ ዘንድ ከወዲሁ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ። አቶ ታደለ አሰፋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን

ለኢንተርፕራይዞች ስኬትና ዘላቂነት፦ የጀማሪ ኢንተርፕራይዞችን አቅም በመገንባት ውጤታማና ተወዳዳሪ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግርና እንዱስትሪ ኤክስ
+6
ለኢንተርፕራይዞች ስኬትና ዘላቂነት፦ የጀማሪ ኢንተርፕራይዞችን አቅም በመገንባት ውጤታማና ተወዳዳሪ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግርና እንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት በአስተዳደሩ ከተለያዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ:: ለኢንተርፕራዝ አንቀሳቃሾች የአቅም ግንባታ ስልጠናውን የሰጡት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ሀላፊ አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ የስልጠናው ዋና አላማ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ውጤታማ፣ ተወዳዳሪና ዘላቂነት እንዲኖራቸው ለማስቻል የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልፀው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከትንሽ ተነስተው ትልቅ ቦታ ለመድረስ ያላቸውን ራዕይ አጠናክረው በቁርጠኝነት ሊተጉ እንደሚገባም ተናግረዋል:: በእለቱ ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የተሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠናው በዋናነት..... - የንግድ ስነ-ምግባር.. - የገበያ ጥናት.. - የፋይናንስ አያያዝ.. - የቴክኖሎጂ ሽግግርና ካይዘን.. - የስራ ፈጠራና የንግድ ኢንኩቤሽን እና.. - የደንበኞች አያያዝ ላይ ያተኮረ ስልጠና በሰፊው ግንዛቤ የተሰጠበት መድረክም ነበር:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መጋቢት 30/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት በአስተዳደሩ ዋሂል ክላስተር በSolar PV Installation & Maintenance ስልጠናዋን ተከታትላ ላጠናቀቀች ወጣት በፀሀይ ሀይል የሚሰራ ዘመናዊ ማብሰያ(Solar Cooker) ድጋፍ አደረገ:: ድጋፉ በዋናነት በBMZ ADRA, Germany አማካኝነት የተገኘ ሲሆን ይህም 1.1 KW የሚያመነጭ የSolar PV System ዝርጋታ እና በሶላር የሚሰራ ማብሰያ ምድጃ(Solar Cooker) ያካተተ እንደሆነም ተገልፇል:: በፕሮጀክቱ ድጋፍ የተደረገላት ወጣት ፎዚያ ባጋጠማት የአካል ጉዳት ሳትበገር ከምትኖርበት ከዋሂል ክላስተር ጁጁማ ወረዳ ተነስታ ኮሌጅ ድረስ ለስድስት ወራት 20 ኪሎ ሜትሮችን እየተመላለሰች ስትሰለጥን የቆየች ብርቱ ሴት ስትሆን የአድራ ኢትዮጵያ ፕሮጀክትም የዚህችን ወጣት ድካም በመረዳት በአካባቢዋ የራሷን ቢዝነስ ሰርታ ገቢ ምታገኝበትን የSolar PV System ዝርጋታ እንዲሁም በፀሀይ ሀይል የሚሰራ ዘመናዊ ማብሰያ(Solar Cooker) በድጋፍ መልክ አበርክቷል:: የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በSolar PV Installation Maintenance ወጣቶችን አሰልጥኖ የሙያ ባለቤት ከማድረግም ባሻገር ተደራጅተው ወደ ስራ እንዲገቡ አስፈላጊ ድጋፎችን ሁሉ በማድረግ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ያስታወሱት የADRA Germany ዋና ሀላፊ አቶ ዳዊት መሀሪ ሲሆኑ በድሬዳዋ ገጠር ክላስተር ላይ ለእህታችን ፎዚያ የተደረገው ድጋፍም ፕሮጀክቱ ለሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ተደራሽና አካታች መሆኑን ማሳያ ከመሆኑም በተጨማሪም የፕሮጀክቱ ከላይ እስከታች የሚገኙ ሀላፊዎች ከባለድርሻ አካላት ጋር ተናቦ የመስራት ድምር ውጤት እንደሆነም ገልፀዋል:: ወጣት ፎዚያ በበኩሏ የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ከብዙ ድካም እንግልት እንዳሳረፋት በመግለፅ በተደረገላት ድጋፍም የተለያዩ ገቢዎችን በማመንጨት የራሷንም ሆነ የቤተሰቦቿን ህይወት እንደምታሻሽል የገለፀች ሲሆን በአጠቃላይ ይህ ድጋፍ እውን እንዲሆን ያደረጉ ለADRA ፕሮጀክት ሀላፊዎችንና አስተባባሪዎች በሙሉ ምስጋናዋን አቅርባለች:: በእለቱ በነበረው የድጋፍ ርክክብ ላይ የADRA Germany, የADRA Ethiopia ሀላፊዎች እንዲሁም የፕሮጀክቱ አስተባባሪዎችና የኮሌጁ አመራሮች በቦታው ተገኝተው የተደረገውን ድጋፍ ውጤታማነት የተመለከቱ ሲሆን ወጣቷንም አበረታተዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መጋቢት 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ