ru
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Открыть в Telegram
1 739
Подписчики
+224 часа
+17 дней
-430 день
Архив постов
የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓትን (ICSMIS) እና የመንግሥት ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ (Civil Servant Data Verification) ምንነትና አስፈላጊነት ======================== ኢትዮጵያ የመንግሥት ሠራተኞችን መረጃ በማዕከላዊ ዲጂታል ሥርዓት ለማስተዳደር ያላትን ፍላጎት ለማሳካት እና ቀደም ሲል የነበረውን ችግር በዘላቂነት መቅረፍ በሚያስችል መልኩ የሰው ሀይል መረጃን ወደ ዘመናዊ የሰው ኃይል አስተዳደር ስርዓት ለመሸጋገር በርካታ እርምጃዎችን እየወሰደች ነው። እንደ ሀገር እየተወሰዱ ካሉ እርምጃዎች መካከል አንዱ የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓትን (ICSMIS) ተግባራዊ ማድረግ ሲሆን ይህንኑ መሰረት በማድረግም የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን እና የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት በጋራ በመሆን የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ቬሪፊኬሽን ስራ ተጀምሯል። የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓትን (ICSMIS) እና የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ቬሪቪኬሽን ስራዎች የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች በውስጣቸው ይይዛሉ:- 1. የICSMIS ፍቺ እና አላማ ይህ ስርዓት በመንግሥት ተቋማት ውስጥ ያሉ ሠራተኞችን ብዛት፣ የሥራ መደብ፣ ዕድሜ፣ ትምህርት ደረጃ፣ ደመወዝ እና ሌሎች መረጃዎች በማዕከላዊ መረጃ ቋት ለማስተዳደር የተዘጋጀ አገር አቀፍ የመረጃ ስብስብ ነው። በአብዛኛው የሚመራው በPublic Service and HR Directorate ወይም በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ነው። 2. የመረጃ ማረጋገጫ (Verification) አስፈላጊነት ከዚህ ቀደም የሠራተኛ ፋይሎች በተቋማት ተበትነው ስለነበር፣ ትክክለኛ ማዕከላዊ መረጃ ቋት አልነበረም። ስለዚህ የሚከተሉትን ለማስፈጸም የሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ አስፈለገ፦ · ትክክለኛ የመንግሥት ሠራተኞች ዳታቤዝ መፍጠር · የደመወዝ ክፍያ ሥርዓት ማሻሻል · የሰው ኃይል እቅድ ማውጣት · ዘመናዊ የሰው ኃይል አስተዳደር መሠረት መጣል · ተደጋሚ ወይም ክፍት የሥራ መደቦችን ለይቶ ለወደፊት ዕቅድ መረጃ ማግኘት 3. የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ሚና ኮሚሽኑ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ በተለያዩ ሕጎች መሠረት የተቋማትን አደረጃጀት እና የሰው ኃይል አስተዳደር በበላይነት ሲያስተዳድር ቆይቷል። ኮሚሽኑ የሲቪል ሰርቪስን የሰው ኃይል መረጃ ሥርዓት በወጥነት እና በዘመናዊነት ተግባራዊ ለማድረግና ማዕከላዊ የመረጃ ምንጭ ሆኖ ለማገልገል ይሠራል። 4. ያጋጠመ ተግዳሮት ኮሚሽኑ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ዘመናዊ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት ሳዘረጋ በመቅረቱ፣ ከአገልግሎት ጥራትና ቅልጥፍና አንጻር ተፈላጊውን ደረጃ ላይ መድረስ አልቻለም። 5. መፍትሔ እና ወቅታዊ እንቅስቃሴ አሁን ላይ ኮሚሽኑ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማስገኘት በርካታ የለውጥ ፕሮግራሞችን በመተግበር ላይ ይገኛል። እንዲሁም የመንግሥት አገልግሎት እና አስተዳደር ፖሊሲ ሰነድ አዘጋጅቶ እንዲጸድቅ ተደርጓል። 👉የኢስሚስ (ICSMIS) ትግበራ፣ ችግሮች፣ እና የመረጃ ማረጋገጫ (verification) አስፈላጊነት ዋና ዋና ነጥቦች፦ 1. የዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ አስፈላጊነት የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ ግብ ለማሳካት፣ የሲቪል ሰርቪስ የሰው ኃይል መረጃ አያያዝ ሥርዓት በወጥነት እና በዘመናዊነት እንዲተገበር ዲጂታል ቴክኖሎጂ መደገፍ አስፈለገ። ከፖሊሲው ሰባት አምዶች አንዱ ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ መገንባት ሲሆን፣ ለዚህም የዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ ገብቷል። 2. የICSMIS ትግበራ ታሪክና ተግዳሮት · ከ2004 በጀት ዓመት ጀምሮ ሥርዓቱን ማስፋፋት ተጀምሯል። · ነገር ግን በቂ ክትትልና ተግባራዊነት ባለመኖሩ በወቅቱ ሙሉ በሙሉ ሊተገበር አልቻለም። · ከ2006 ጀምሮ በፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ደረጃ ተቋቁሞ ሥራዎችን ማከናወን ጀምሯል። 3. እስካሁን ያሉ ሥሪቶች (Versions) · 1ኛ ሥሪት (1st version ICSMIS) – በአንዳንድ የክልልና የፌዴራል ተቋማት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። · 2ኛ ሥሪት (2nd version ICSMIS) – በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር እየተጠቀመ ይገኛል። · አዲሱ ሥሪት – ብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ)ን መነሻ በማድረግ በአገር አቀፍ ደረጃ ለመተግበር የቅድመ-ዝግጅት ሥራ እየተከወነ ነው። 4. የመረጃ ማረጋገጫ (Verification) አስፈላጊነት ሥርዓቱ በአገር አቀፍ ደረጃ ሙሉ በሙሉ ባለመተግበሩ የሚከተሉት ችግሮች ተፈጥረዋል፦ · የመንግሥት ሠራተኞች መረጃ በአንድ ቦታ ባለመደራጀቱ ለፖሊሲ ጥናት የሚሆን ግብአት ማቅረብ አልተቻለም። · በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን እና በገንዘብ ሚኒስቴር መካከል ስለ መንግሥት ሠራተኞች ቁጥር ጉልህ ልዩነት አለ። ለዚህም መፍትሔ እንዲሆን አገር አቀፍ የመንግሥት ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ (Civil Servant Data Verification) በመካሄድ ላይ ነው። ግቡም ትክክለኛውን የሠራተኞች ቁጥርና ተጓዳኝ መረጃ በኦንላይን ወደ ICSMIS ማስገባት ነው።

ለሥራ ፈላጊዎች የወጣ ማስታወቂያ በተለያዩ የውጭ አገራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ለምትፈልጉ ዜጎች የኢትዮጵያ መንግስት ከአገራቱ ጋር በፈጠረው ስምምነት እድሉ ተመቻችቷል። በዚህም እስከ ሚያዚያ 2
+2
ለሥራ ፈላጊዎች የወጣ ማስታወቂያ በተለያዩ የውጭ አገራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ለምትፈልጉ ዜጎች የኢትዮጵያ መንግስት ከአገራቱ ጋር በፈጠረው ስምምነት እድሉ ተመቻችቷል። በዚህም እስከ ሚያዚያ 26/2018 ዓ.ም ባሉት የሥራ ቀናት በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ እና በሁሉም የአስተዳደሩ ወረዳ የሥራና ክህሎት ማስተባበሪያዎች በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

በኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚዘጋጁ ኤክስፖዎች ለአገር በቀል አምራቾች የእርስበርስ ትስስርን መፍጠር እንደሚያችሉ ተገልፀ: "ድሬ ታምርት፤ ኢትዮጵያ ትበልፅግ” በሚል መሪ ቃል ከሚያዝያ 15 እስከ 20 ቀን
+7
በኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚዘጋጁ ኤክስፖዎች ለአገር በቀል አምራቾች የእርስበርስ ትስስርን መፍጠር እንደሚያችሉ ተገልፀ: "ድሬ ታምርት፤ ኢትዮጵያ ትበልፅግ” በሚል መሪ ቃል ከሚያዝያ 15 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆየው አራተኛው የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ሀገር አቀፍ ንቅናቄና የኢንዱስትሪ ኤግዚቢሽንን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል የአስተዳደሩ ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀርና ከአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በዛሬ እልት በደማቅ ሁኔታ ተከፍቷል። በዛሬው እለት ጅማሮውን ባድረገው ኤግዚቢሽን እና ባዛር ላይ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅም እየተሳተፈ የሚገኝ ሲሆን በዚህም በኮሌጁ የተሰሩና የማህበረሰቡን ችግር ፈቺ የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን እንዲሁም ኢንዱስትሪዎች ምርትና ምርታማነታቸውን በይበልጥ እንዲያሳድጉ ለማስቻል የተሰሩ ተኪ ምርቶችንም ይዞ ቀርቧል:: ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሚያዝያ 15/2018 ዓ.ም ድሬዳ

እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ!! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሳሣኤው አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታና የመተሳሰብ በዓል ይሆንላ
እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ!! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሳሣኤው አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታና የመተሳሰብ በዓል ይሆንላችሁ ዘንድ ከወዲሁ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ። አቶ ታደለ አሰፋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን

ለኢንተርፕራይዞች ስኬትና ዘላቂነት፦ የጀማሪ ኢንተርፕራይዞችን አቅም በመገንባት ውጤታማና ተወዳዳሪ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግርና እንዱስትሪ ኤክስ
+6
ለኢንተርፕራይዞች ስኬትና ዘላቂነት፦ የጀማሪ ኢንተርፕራይዞችን አቅም በመገንባት ውጤታማና ተወዳዳሪ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግርና እንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት በአስተዳደሩ ከተለያዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ:: ለኢንተርፕራዝ አንቀሳቃሾች የአቅም ግንባታ ስልጠናውን የሰጡት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ሀላፊ አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ የስልጠናው ዋና አላማ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ውጤታማ፣ ተወዳዳሪና ዘላቂነት እንዲኖራቸው ለማስቻል የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልፀው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከትንሽ ተነስተው ትልቅ ቦታ ለመድረስ ያላቸውን ራዕይ አጠናክረው በቁርጠኝነት ሊተጉ እንደሚገባም ተናግረዋል:: በእለቱ ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የተሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠናው በዋናነት..... - የንግድ ስነ-ምግባር.. - የገበያ ጥናት.. - የፋይናንስ አያያዝ.. - የቴክኖሎጂ ሽግግርና ካይዘን.. - የስራ ፈጠራና የንግድ ኢንኩቤሽን እና.. - የደንበኞች አያያዝ ላይ ያተኮረ ስልጠና በሰፊው ግንዛቤ የተሰጠበት መድረክም ነበር:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መጋቢት 30/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

photo content
+9

በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት በአስተዳደሩ ዋሂል ክላስተር በSolar PV Installation & Maintenance ስልጠናዋን ተከታትላ ላጠናቀቀች ወጣት በፀሀይ ሀይል የሚሰራ ዘመናዊ ማብሰያ(Solar Cooker) ድጋፍ አደረገ:: ድጋፉ በዋናነት በBMZ ADRA, Germany አማካኝነት የተገኘ ሲሆን ይህም 1.1 KW የሚያመነጭ የSolar PV System ዝርጋታ እና በሶላር የሚሰራ ማብሰያ ምድጃ(Solar Cooker) ያካተተ እንደሆነም ተገልፇል:: በፕሮጀክቱ ድጋፍ የተደረገላት ወጣት ፎዚያ ባጋጠማት የአካል ጉዳት ሳትበገር ከምትኖርበት ከዋሂል ክላስተር ጁጁማ ወረዳ ተነስታ ኮሌጅ ድረስ ለስድስት ወራት 20 ኪሎ ሜትሮችን እየተመላለሰች ስትሰለጥን የቆየች ብርቱ ሴት ስትሆን የአድራ ኢትዮጵያ ፕሮጀክትም የዚህችን ወጣት ድካም በመረዳት በአካባቢዋ የራሷን ቢዝነስ ሰርታ ገቢ ምታገኝበትን የSolar PV System ዝርጋታ እንዲሁም በፀሀይ ሀይል የሚሰራ ዘመናዊ ማብሰያ(Solar Cooker) በድጋፍ መልክ አበርክቷል:: የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በSolar PV Installation Maintenance ወጣቶችን አሰልጥኖ የሙያ ባለቤት ከማድረግም ባሻገር ተደራጅተው ወደ ስራ እንዲገቡ አስፈላጊ ድጋፎችን ሁሉ በማድረግ ውጤታማ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ያስታወሱት የADRA Germany ዋና ሀላፊ አቶ ዳዊት መሀሪ ሲሆኑ በድሬዳዋ ገጠር ክላስተር ላይ ለእህታችን ፎዚያ የተደረገው ድጋፍም ፕሮጀክቱ ለሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ተደራሽና አካታች መሆኑን ማሳያ ከመሆኑም በተጨማሪም የፕሮጀክቱ ከላይ እስከታች የሚገኙ ሀላፊዎች ከባለድርሻ አካላት ጋር ተናቦ የመስራት ድምር ውጤት እንደሆነም ገልፀዋል:: ወጣት ፎዚያ በበኩሏ የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ከብዙ ድካም እንግልት እንዳሳረፋት በመግለፅ በተደረገላት ድጋፍም የተለያዩ ገቢዎችን በማመንጨት የራሷንም ሆነ የቤተሰቦቿን ህይወት እንደምታሻሽል የገለፀች ሲሆን በአጠቃላይ ይህ ድጋፍ እውን እንዲሆን ያደረጉ ለADRA ፕሮጀክት ሀላፊዎችንና አስተባባሪዎች በሙሉ ምስጋናዋን አቅርባለች:: በእለቱ በነበረው የድጋፍ ርክክብ ላይ የADRA Germany, የADRA Ethiopia ሀላፊዎች እንዲሁም የፕሮጀክቱ አስተባባሪዎችና የኮሌጁ አመራሮች በቦታው ተገኝተው የተደረገውን ድጋፍ ውጤታማነት የተመለከቱ ሲሆን ወጣቷንም አበረታተዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መጋቢት 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

photo content
+9

#ዜና| በፀሐይ ሀይል እየተገኘ ያለው ለውጥ እና ስኬት ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለፀ #DireTvአማርኛ | መጋቢት 25 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከአድራ (ADRA) ኢትዮጵያ ጋር በመሆን በሶላር (በፀሐይ ሀይል )የሚሰሩ የተለያዩ የምርት ውጤቶችን የሚያስገኙ መሳሪያዎችን በመስራት በይፋ አስመርቆ ሥራ አስጀምሯል። በወቅቱም ከጀርመን እና ከኢትዮጵያ አድራ የመጡ የፕሮጀክቱ ኃላፊዎች ፤ የኮሌጁ አመራሮች እና ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ የመጡ ኃላፊዎች የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ የሆኑት በማህበር የተደራጁ ሰራተኞችም ተገኝተዋል። በምርቃት መርኃግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አድራ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ወደ ኮሌጁ ከመጣ በኋላ መጀመሪያ ላይ በፀሐይ ኃይል ( በሶላር ) የሚሰራ ወፍጮ በመስራት ይፋ ማድረጉን አስታውሰው አሁን ደግሞ ለኮሌጁ እና ለአካባቢው ማኅበረሰብ የሚጠቅም በፀሐይ ኃይል የሚሰራ የውሃ መሳቢያ ፓንፕ ፣ የዘይት መጭመቂያ መሳሪያ እና የተለያየ አካል ጉዳት ያለባቸው በማኅበር ተደራጅተው የሚጠቀሙበት የመኪና ማጠቢያ (ላቪያጆ ) በመስራት ርክክብ እንዳደረጉ ገለፀዋል። ዲኑ አያይዘውም በተለይ በኮሌጁ ቅጥር ግቢ ውስጥ በፀሐይ ኃይል የወጣው ውሃ ኮሌጁ የነበረበትን ከፍተኛ የሆነ የውሃ እጥረት ችግር ቀርፏል ነው ያሉት። ውሃውም ከኮሌጁ አልፎ ለአካባቢው ማኅበረሰብ ብሎም በግቢው ውስጥ በመኪና አጠባ ሥራ ለተደራጁት ማኅበራት የስራ እድል መፍጠር የተቻለበት አቅም ፈጥሯልም ብለዋል። ዲኑ አድራ ኢትዮጵያም ድጋፉን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። የአድራ ኢትዮጵያ ዳሬክተር ዶ/ር ዘሪሁን አዋኖ በወቅቱ እንደገለፁት የድሬዳዋ ኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በፀሐይ ኃይል አጠቃቀም በኩል በገጠርም በኮሌጁም እየደረገ ያለው ስራ እጅግ በጣም የሚበረታታ ነው ብለዋል። ዳይሬክተሩ አያይዘውም የፀሐይ ኃይል ማመንጫውን በዘላቂነት ለመጠቀም ኮሌጁ በአጫጭር ስልጠና ያስተማራቸውን የሶላር ጥገናና ተከላ ባለሞያዎችንም በማፍራት በማህበር በማደራጀት ወደስራ ማስገባቱ የሚደነቅና ስራው ቀጣይነት እንዲኖረው የሚያደርግ ነው ብለዋል። ይህም በፀሐይ ሓይል የሚሰራ ስራ መቀጠል አለበት በማለት ጨምረው ገልፀዋል። የጀርመኑ አድራ ዳሬክተር አቶ ዳዊት መሐሪ በድሬዳዋ ኢትዮጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያየነው ተጨባጭ ተግባር ተደስተናል። በቀጣይም በሌላ ፕሮጀክት አብሮነታችን ይቀጥላል ብለ፥ ይህ ስራም ኮሌጁ ከራሱ አልፎ አሁንም ለሌሎች መትረፍ አለበት በማለት አሳስበዋል። በመርኃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይም በፀሐይ ኃይል የሚሰሩት መሳሪዎች ርክክብና ስራ ማስጀመሪያ ፊርማ የተከናወነ ሲሆን እንዲሁም በመኪና አጠባ ለተደራጁት አካል ጉዳተኞች የስራ ማስጀመሪያ የሚሆን አጫጭር ስልጠና ስልጥነው ያጠናቀቁበት የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።

photo content
+9

photo content
+9

ለድሬዳዋ አስተዳደር ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የባዮሜዲካል ሰልጣኝ ተማሪዎች በቀዝቃዛ ሰንሰለት የሚሠሩ የህክምና መሣሪያዎች (ColdChain equipment management) ቅድመ-ሥራ ላይ ሰልጠና ተሰጠ። የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከጤና ሚኒስቴር እና ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በቀዝቃዛ ሰንሰለት የሚሠሩ የህክምና መሣሪያዎች (ColdChain equipment management) ቅድመ-ሥራ ላይ ሰልጠና ለባዮሜዲካል ሰልጣኝ ተማሪዎች ሰልጠና ሰጥቷል። በስልጠናው ማጠናቀቂያ የተገኙት በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የፈውስ ህክምና ተሃድሶ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብዶ ሙሜ ስልጠናውን በአብሮነት ለሰልጣኞች እንዲሰጥ ያደረጉትን ጤና ሚ/ርን እና ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክን በማመስገን የባዮሜዲካል ዘርፍ ባለሞያዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ አነስተኛ በመሆናቸውና የባለሞያ እጥረት በመኖሩ ሰልጣኞች በዚህ በየጊዜው እራሱን እያዘመነ ባለው የሞያ ዘርፍ ስልጠና መውሰዳችሁ ላለው የባለሞያ እጥረት በጥቂቱም ቢሆን መፍትሄ የሚሰጥ ነው ሲሉ ተናግረዋል። አቶ አብዶ ጨምረውም ሰልጣኞች ከወሰዳችሁት ስልጠና ባሻገር በግላችሁም በየጊዜው ከወቅቱ ጋር እራሳችሁን በማናበብና በዘርፉ ለአዳዲስ ነገሮች በማዘጋጀት የጤና ተቋማትን የባለሞያ ችግር በመፍታት በስነ-ምግባር የተቃኘ ሙያዊ አገልግሎት መስጠት ይጠበቅባችኋል ያሉ ሲሆን ቢሮውም በሚያስፈልጓችሁ ሞያዊ እገዛዎች ከጎናችሁ ይሆናል ብለዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው የምንሰጠውን ትምህርትና ስልጠናዎችን የሚደግፍ እንደ ጤና ቢሮ ያለ ተቋም ማግኘታችን እጅግ ዕድለኝነት ነው ያሉ ሲሆን ሰልጣኞች የባዮሜዲካል ስልጠናን ከጤና ቢሮ በመጡና በቀጥታ የሞያው ባለቤት በሆኑ ስልጠናውን ማግኘት ለሰልጣኞች የበለጠ አቅም የሚሰጥ መሆኑንና ሰልጣኞች የወሰዱትን ስልጠና መሰረት በማድረግ ወደ ጤና ተቋማት በመሄድና ተከታታይነት ያለው አገልግሎት በመስጠት እራሳቸውን ሊያበቁ እንደሚገባም ተናግረዋል አቶ ታደለ። በስልጠናው የተሳተፉ ተማሪዎች በበኩላቸው በተሰጣቸው ስልጠና ደስተኞች መሆናቸውንና በተለይ በጤና ተቋማት በተማሩበትና ጤና ቢሮ ባመቻቸላቸው ዕድል በሰለጠኑበት የሞያ ዘርፍ አገልግሎት እንዲሰጡ ለተገባላቸው ቃል በማመስገን በቀጣይም ጤና ቢሮና ኮሌጃችን መሰል ስልጠናዎችን የምናገኝበትን ሁኔታዎች እንዲያመቻቹልን እንጠይቃለን ብለዋል። ስልጠናው ከክፍል ባሻገር በተግባር የተደገፈ ስልጠና እንደነበር የስልጠናው አስተባባሪዎች ተናግረዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን 21/07/2018 ዓ.ም

photo content
+9