en
Feedback
ኤዞፕ መጻሕፍት

ኤዞፕ መጻሕፍት

Open in Telegram

ኤዞፕ ነባርና ቀደምት መጻሕፍት መገኛ የከተማችን ፈርጥ ቤተ መጽሐፍት። #ቁጥር _1 ሚኒልክ አደባባይ ቴምር ሪልስቴት ፊት ለፊት የአራዳ ጊዮርጊስ ቤተ/ን ህንፃ አቢሲኒያ ባንክ ያለበት 2ኛ ፎቅ ላይ #ቁጥር_2 አራት ኪሎ አባድር ሱፐር ማርኬት ፊት ለፊት የድሮ ጆሊ ባር ጋ ስልክ:- 09 11 72 36 56 0911185548 ለማዘዝ @Azop_mesi @Mesay21

Show more
8 941
Subscribers
+924 hours
+237 days
+8230 days
Posts Archive
photo content
+6

photo content

photo content
+9

photo content
+3

photo content
+9

photo content
+9

photo content

photo content
+3

photo content
+8

#ፈላስፋው_ሰማዕት:ሰማዕት #ቅዲስ:ዩስጢኖስ #ሕይወቱና_ሥራዎቹ ( ክርስትና በውስጣዊና ውጫዊ መከራ ሲፈተን የኖረ፣ አሁንም የሚፈተን፣ እስከ ዓለም ፍጻሜ ፈ ተ ና የ ማይቀርለት፣ ነገር ግን በፈተናዎች ሁሉ አሸናፊነቱበ ክ ር ስ ቶስ የተረጋገጠለት እምነት ነው። የዚህ መጽሐፍ ባለቤት የሆነው ሰማዕቱ ቅዱስ ዩስጢኖስ እነዚህን ውስጣዊ ፈተናዎች እምነትና አመክንዮን በመጠቀም ለመወደር ይነሣል። “ወንእመን እንበለ ተኀሥሦ ” የሚለውን መር ሕ ሳይለቅ ነገር ግን “መጽሐፍ ለሚጠይቋችሁ መልስ ይኸውም በእናንተ ዘንድ ላለው የመዳን ቃል መስጠት እንድትችሉ ሁል ጊዜ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ”( 1 ኛ ጴጥ. 3 ÷ 1 5 ) ያለውን ተከትሎ ክ ር ስ ት ና ው ላይ በተለያየ መነሻ ለሚነሡ ጥያቄዎች በአመክንዮ የተደገፈ መልስ ይሰጣል። ፍልስፍናን የክርስትና አገልጋይ ያደርጋታል። የፍልስፍና ካባውን ሳያወልቅ ፍልስፍናን ክርስትና ያነሣታል። ቅዱስ ዩስጢኖስ ሰማዕት “ክርስትናን ከአመክንዮ ጋራ ያስታረቀ ቀዳሚው የቤተ ክርስቲያን ሊቅ” ስለመሆኑ ጸሐፍት መስክረውለታል። ቅዱስ ዩስጢኖስ ከቢጽ ሐሳውያንና ከቤተ አይሁድ ለተነሡ ጥያቄዎች የተደራጀ ምላሽ በመስጠት ቀዳሚ ዐቃቤ እምነት ስለመሆኑ ይነገርለታል። በዚህ መጽሐፍ ትሪፎ ከተባለ ይሁዲ ጋራ የሚያደርገው ምልልስ በተዋሥኦ መልክ ሲሆን፥ ይህም አርኣያነቱ በኋላ ዘመን በቅዱስ ቄርሎስ ጰላድዮስ ጭምር የምናየው ነው። የተዋሥኦ መልክ ያላቸው የዕቅበተ እምነት ሥራዎች የተከራካሪን ጥያቄ ሳያድበሰብሱ የተሟላ መልስ ምላሽ ይቀርብባቸዋል። በዚህ መጽሐፍም ያንን እናያለን። በምዕራቡና በምሥራቁ ዓለም የገነነው ቅዱስ ዩስጢኖስ ሰማዕት በእኛ ቤተ ክርስቲያን ስሙ እምብዛም አለመታወቁና ላለመታወቁ ምክንያት ሊሆኑ የሚችሉ መላ ምቶች በዚህ መጽሐፍ የራሳቸው የራሳቸው ክፍል ተሰጥቷቸው ተተንትነዋል። የምንባባቱ አሻራዎች በጠቅላላው በቤተ ክርስቲያን ታሪክና ምንባባት በኩል መድረሳቸው አይቀርም። የቅዱሱ ተጽዕኖ በእስክንድርያዎቹ እነ ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ፣ አርጌንስና አቴናጎረስ ዘንድ መታየቱ አልቀረም። ቅዱሱ የብሉይ ኪዳን ምንባባትን በአንጻረ ክርስቶስ ጥላና አካል እያደረገ በመተርጐም ለክርስትና የአንድምታ ትርጓሜ ትልቅ መሠረት የጣለ ነው። ስለሆነም በስም ባይሆንም በተዘዋዋሪ በግብር መታወቁ አልቀረም። እንዲህ ያሉ ቀደምት ሥራዎች መተርጐም የቀደምት ክርስቲያኖችን ታሪክ ተጋድሎ ለመረዳት፣ መሠረተ እምነቶቻችንና የክርስትና ቃላት እንዴት በጊዜ ኺደት ይዘት ገላጭ በሆነ ሽግግር እንዳለፉ፣ ክርስትና ከመነሻው የነበረበትን ፈተና፣ ለዚያ ፈተና የተሰጡትን ምላሾች ይዘት እያየን፥ ዛሬያችንን በትናንት መነጽርም ለመመልከት ዕድል እናገኝበታለን። ቅዱሱ በሁሉም ትውፊታውያን አብያተ ክርስቲያናት በቅድስና የሚጠራ እንደመሆኑ መጠን ሥራውን መተርጐም፣ መጻፍ፣ ማንበብና መስማት በረከትም ይገኝበታል። ለአጥኚዎችም ግሩም ማጣቀሻ ይሆናል። ተርጓሚው ለኅሊናውና ለነባሩ ቅጂ በመታመን በጥሩ ገላጭ ዐማርኛ ያቀረበበት መንገድ የሚያስመሰግን ነው። ስለሆነም ታናሽ ወንድማችንን በጥበብና በሞገስ ያሳድግልን እያልን አንባብያንን ወደሰፊው የፈላስፋው ሰማዕት ጉባኤ እንዲታደሙ እንጋብዛለን! በአማን ነጸረ (ደብተራና የሕግ ባhሞያ)

photo content

photo content

photo content

photo content
+4

photo content
+5

photo content
+9

photo content
+8

photo content
+2

photo content
+9

photo content
+3