en
Feedback
Mujib Amino Z islam

Mujib Amino Z islam

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Mujib Amino Z islam

Channel Mujib Amino Z islam (@mujibbinislam) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 253 subscribers, ranking 6 017 in the Religion & Spirituality category and 2 397 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 253 subscribers.

According to the latest data from 04 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -184 over the last 30 days and by -2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 12.75%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 6.53% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 1 818 views. Within the first day, a publication typically gains 931 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

14 253
Subscribers
-224 hours
-437 days
-18430 days
Posts Archive
photo content

ሊያፈርሷት ቢፈልጉም፣ ኢትዮጵያ በጽናት ቆማለች! 🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹 ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ Mujib Amino ሀገር ማለት በካርታ ላይ የተሰመረ ድንበር ብቻ አይደለም። ሀገር ማለት የትውልዶች ትዝታ፣ የአባቶች ውለታ፣ የእናቶች ትዕግስት፣ የሕዝቦች ባህልና እምነት፣ የሥልጣኔ አሻራ እና ለቀጣዩ ትውልድ የምናስረክበው አደራ ነዉ። ሀገር ማለት ትውስታ፣ ታሪክ፣ ባህል፣ ቋንቋ፣ የአባቶች ትግል፣ የእናቶች እንባ፣ የትውልድ ትስስር እና የነገ ትውልድ ተስፋ ነው። አንዳንድ 'መሳይ መኮንን'ን የመሰሉ ቆሞቀር ቅዥታሞች እንደሚሉት ሳይሆን እኛ ሀገር አልባ ያልሆንን ረጅም ታሪክ ያላት ዉድ ሀገር አለችን። ያልፈረሰና የማይፈርስ ግን ደግሞ የምትሰራና የምትገነባ ዉድ ሀገር አለችን! እኛ ሀገር አልባ አይደለንም። ከረጅም ዘመን ታሪክ የተወለደች ዉብና ዉድ ሀገር አለችን። በብዙ ዘመናት የተሻገረ ሥልጣኔ፣ በትውልድ የተላለፈ ባህል እና ለሀገር ሉዓላዊነት የተከፈለ ዋጋ አለን። ኢትዮጵያ የቀደሙት ትውልዶች ብቻ ያስተላለፉልን ቅርስ አይደለችም፤ እኛም ለሚመጣው ትውልድ የምናስረክባት አደራ ናት። በባሌ የሚገኘው ሶፍኡመር ዋሻ የተፈጥሮ አስደናቂነት ብቻ ሳይሆን፣ የአካባቢውን የቆየ ታሪክና የሕዝቦች ባህላዊ ትውስታ የሚያስታውስ ልዩ ቅርስ ነው። ከዚያ በላይ፣ በአፋር የተገኙት የጥንታዊ የሰው ልጅ ቅሪተ አካላትና በኦሞ ሸለቆ የተገኙ ቅሪተ አካላት የሰው ልጅን ታሪክን ለመረዳት ኢትዮጵያ ያላትን ሚና ያሳያሉ። አክሱም ስንል- መንግሥት፣ ንግድ፣ ሥነ-ሕንፃ፣ ጽሑፍ እና ሳንቲም የነበረውን ጥንታዊ ሥልጣኔ እናስታውሳለን። የአክሱም ሐውልቶች እና ቅርሶች ዛሬም የዚያን ዘመን ልማት ይመሰክራሉ። የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት የኢትዮጵያ የሥነ-ሕንፃ፣ የሥልጣኔ ታሪክ ልዩ ምስክሮች ናቸው። የኢትዮጵያ ታሪክ የክርስቲያናዊ ቅርሶችና የኢስላማዊ ሥልጣኔ ውህድ በሀገራችን ያለው ታሪክ በጥልቀት የሚያሳይ ግርማ ነዉ:: ሐረር ጀጎል የዚህ ጥንታዊ ታሪክ አንዱ ታላቅ ምስክር ነው። በግንብ የተከበበችው የሐረር ከተማ፣ መስጂዶቿ፣ ጥንታዊ ቤቶቿ እና የንግድ መስመሮቿ የኢስላማዊ ባህልና ሥልጣኔ በኢትዮጵያ ላይ ያሳረፈውን ጥልቅ አሻራ ያመለክታል። ነጃሺ መስጂድና አካባቢ የኢስላማዊዉን ታሪክ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ጥንታዊ ትስስር የሚያስታውሱ ናቸው። ኢትዮጵያ ለሙስሊሞች መጠጊያ መሆኗ ደግሞ በኢስላማዊ ታሪክ ውስጥ የሀገራችንን ልዩ ቦታ ያስቀምጣል። የጎንደር ቤተ-መንግሥቶች፣ ግንቦችና ታሪካዊ ሕንፃዎች የኢትዮጵያን የመንግሥት፣ የሥነ-ሕንፃ እና የባህል ታሪክ የሚያሳዩ የተለየ ቅርሶች ናቸው። በእርግጥ አያሌ የታሪክ ገጾች ያሉን ህዝቦችን ነን:: የይሐ ጥንታዊ ሥልጣኔ፣ የአዳል ሱልጣኔት ታሪክ፣ የኦሮሞ ገዳ ሥርዓት ፣ የስልጤ ጉራጌና የሲዳማ ባህላዊ ቅርሶች፣የሶማሌ ባህላዊ ቅርሶች፣ የአፋር ታሪካዊ ትውፊቶች እና በሀገሪቱ የተለያዩ ሕዝቦች የተገነቡ ብዙ ባህላዊና ታሪካዊ ቅርሶች አሉን። እነዚህ ሁሉ የተለያዩ ገጾች ሆነው አንድ ታላቅ መጽሐፍ ይጽፋሉ፤ የኢትዮጵያን ታሪክ። ይህ ታሪክ የአንድ ብሔር ብቻ አይደለም ፤ የአንድ አከባቢ ብቻ አይደለም ፤ የአንድ ሃይማኖትም ብቻም አይደለም። የእኛ የጋራ ታሪካችን ነው። የኢትዮጵያዊያኖች! የአክሱምን ሐውልት ስናይ፣ የላሊበላን ድንጋይ ስንመለከት፣ የሐረርን ጁጎል ስንጎበኝ፣ የነጃሺን ታሪክ ስናስብ፣ የጎንደርን ቅርስ ስንመለከት፣ የሶፍኡመርን ዋሻ ስንጎበኝ—•••የተለያዩ ታሪኮችን ሳይሆን የአንዲት ሀገርን ብዙ ገፆችን እየተመለከት ነው። እኛ ሀገር አልባ አይደለንም። ታሪክ አለን። ሥልጣኔ አለን። ቅርስ አለን። ከሁሉም በላይ—የጋራ ቤት አለን። የትናንት ትውልድ ሀገርን በትጋትና በመስዋዕትነት አስረክቦናል፤ ዛሬ ደግሞ ይህንን አደራ በሰላም፣ በአንድነት፣ በመከባበርና በልማት ማስቀጠል የእኛ ድርሻ ነው። የሀገር ፍቅር በቃል ብቻ አይገለጽም፤ በተግባር ይረጋገጣል። ታሪካችንን ማክበር፣ ቅርሶቻችንን መጠበቅ፣ ልዩነታችንን በመከባበር መሻገር እና ለሚመጣው ትውልድ የተሻለች ሀገር መገንባት ነው። የተረከብናትን ኢትዮጵያ ከመጠበቅ በላይ፣ የተሻለች ኢትዮጵያን ለሚመጣው ትውልድ ማስረከብ አለብን። ሀገር መጠበቅ የትውልዳችን አደራ ነው:: በርካታ ታሪኮችን በጋራ ያቆየን፣ የጋራ ቅርሶችንና ትውስታዎችን የምንጋራ፣ ዛሬን በጋራ የምንኖርና ለወደፊትም አብረን ለመጓዝ ብዙ ምክንያቶች ያሉን ህዝቦች ነን። የሚያገናኙን ብዙ ነገሮች እያሉ፣ የሚለያዩንን ልዩነቶች ምክንያት አድርገን እርስ በርስ መራራቅ ሳይሆን፣ የጋራ ታሪካችንን መሠረት አድርገን የጋራ ነገያችንን መገንባት ይገባናል። ትናንት በጋራ ነበርን፤ ዛሬ በጋራ ነን፤ ነገም በጋራ መጓዝ አለብን። የውስጥ ባንዳዎች ከውጭ ጠላቶች ጋር ተባብረው፣ ሀገር ፈርሳለች ብለው ቢያወሩም፤ የኢትዮጵያ ጽናት ከእነሱ የተሳሳተ ትንበያ የበለጠ ነው። ኢትዮጵያ በችግር ጊዜ ትፈተናለች እንጂ አትሰበርም፤ በመከራ ውስጥ ትጠነክራለች እንጂ አትጠፋም። የሀገራችን ታሪክ የሚመሰክረውም ይሄንኑ ነው። ዛሬም ልዩነታችንን በመቻቻል፣ ችግሮቻችንን በውይይት፣ የሀገራችንን እድገት በጋራ ትጋት እውን እናደርጋለን። ኢትዮጵያ የማንም የጥፋት ፕሮጀክት ሳትሆን፣ የልጆቿ የጋራ ቤት ናት። #ሀገር_አልባ_አይደለንም #ኢትዮጵያ #የጋራ_ታሪካችን #ሀገር_ፍቅር #ቅርሳችን_ማንነታችን #አንድነት Abiy Ahmed Ali Ethiopian National Dialogue Commission/የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን Worku Gachena-ወርቁ ጋቸና Office of the Prime Minister-Ethiopia

ኢና ሊላሂ ወዒና ኢለይሂ ራጂዑን የወንድማችን ኡስታዝ አህመዲን ጀበል ወላጅ እናት ወደ አኼራ ሄደዋል:: የእናታችን ስርዓተ ቀብርም ነገ ቅዳሜ ከዝሁር ሰላት ቡኃላ ሰናተል ጀናዛ ተሰግዶባቸው በኮልፌ የሙስሊሞች መካነ መቃብር የሚፈፀም ይሆናል:: አላህ ይዘንላቸው፣ ማረፊያቸውንም በጀነተል ፊርዶስ ያድርግላቸው ለኡስታዝ አህመዲን ጀበል እና ለመላው ቤተሰቦቹ አላህ ሰብሩን ይወፍቃችሁ🤲

photo content

photo content
+9

🌿ዘመናዊ ቴክኖሎጂ፣ ብቁ የሕክምና ባለሙያዎች፣ ታካሚን ያማከለ እንክብካቤ!🌿 ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ጤና በተመለከተ ምርጫ ሲደረግ፣ የታካሚው ደህንነት፣ ትክክለኛ ምርመራ፣ የሕክምና ብቃት እና የቴክኖሎጂ ደረጃ ዋና መለኪያዎች ናቸው። በዚህ መርህ ላይ በመመሥረት New Leaf Medical Complex (NLMC) በአዲስ አበባ ለቡ ሙዚቃ ሰፈር፣ ቶሞካ ቡና ፊት ለፊት የዘመናዊ ሕክምና አገልግሎትን በአዲስ ራዕይ እያቀረበ ይገኛል። የላቀ የሕክምና ቴክኖሎጂ በአንድ ማዕከል NLMC ከሚለይባቸው ዋና ጥንካሬዎች አንዱ የላቀ የሕክምና ምርመራና ሕክምና ቴክኖሎጂዎችን ማቀናጀቱ ነው። 🩻 PET/CT — የዘመናዊ ምርመራ ቴክኖሎጂ በተቋሙ የሚገኘው PET/CT የሞለኪውላር ኢሜጂንግን ከአናቶሚካል ኢሜጂንግ ጋር በማጣመር የበሽታ እንቅስቃሴንና የሚገኝበትን ቦታ በተቀናጀ መልኩ ለመገምገም የሚያግዝ የላቀ የምርመራ ቴክኖሎጂ ነው። በተለይ በኦንኮሎጂ ዘርፍ የካንሰር ስርጭትን ለመገምገም፣ ለሕክምና ውጤት ክትትል እና ለሕክምና ዕቅድ የሚሰጠው መረጃ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው። ❤️ Advanced Cath Lab — የልብ ሕክምና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ Advanced Cardiac Catheterization Laboratory (Cath Lab) ደግሞ የልብና የደም ቧንቧ ችግሮችን ለመመርመርና የተወሰኑ የinterventional cardiology ሂደቶችን ለማከናወን የሚያግዝ የላቀ የሕክምና አቅም ነው። ይህ የልብ ሕክምና አገልግሎትን ከተለመደው የምርመራ ደረጃ ወደ የተራቀቀ የinterventional care አቅም ለማሸጋገር የሚያግዝ መሠረተ ልማት ነው። 🎗️3D Mammography (Digital Breast Tomosynthesis) New Leaf Medical Complex ዘመናዊውን 3D Mammography (Digital Breast Tomosynthesis) ማሽን በማስገባት የጡት ጤና ምርመራ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። የጡት ካንሰርን በቀድሞ ደረጃ ለመለየት የሚያግዝ የላቀ የጡት ኢሜጂንግ ቴክኖሎጂ ነዉ። ይህ የላቀ የጡት ኢሜጂንግ ቴክኖሎጂ የጡት ውስጥ ያሉ ሕዋሳትን በዝርዝር ለመመርመርና የተለያዩ የጡት ውስጣዊ አካላትን ለውጦችን ለመለየት ያግዛል። 🧲 Latest Model MRI MRI (Magnetic Resonance Imaging) የሰውነት ውስጣዊ አካላትንና ሕብረቶችን በዝርዝር ለማየት የሚጠቅም የምስል ምርመራ ቴክኖሎጂ ነው። ይህ ቴክኖሎጂ በተቋማችን ዉስጥ ሌተስት ሞዴሉን ስንገጥም በደስታና ለታካሚዉ ፈጣንና ዘመናዊ አገልግሎት በማሰብም ነዉ:: MRI በተለይ ምን ይመረምራል? * 🧠 አእምሮና የነርቭ ሥርዓት — የአእምሮ እጢ፣ ስትሮክ እና ሌሎች ችግሮች * 🦴 አከርካሪና መገጣጠሚያዎች — የዲስክ ችግር፣ ጉዳት፣ ጅማትና ጡንቻ ችግሮች * ❤️ ልብና የደም ሥሮች * 🫁 የደረት እና የሆድ ውስጥ አካላት * 🩺 ጉበት፣ ኩላሊት፣ ፓንክሪያስ እና ሌሎች አካላት * 👩 ጡትና የማህፀን/የዳሌ አካባቢ * 🎗️ የተለያዩ እጢዎችን (tumors) ለመለየትና ለመከታተል ይረዳል:: 🩻 ዘመናዊ CT Scan በNew Leaf Medical Complex New Leaf Medical Complex ዘመናዊ CT Scan ቴክኖሎጂን በመጠቀም የአእምሮ፣ የደረት፣ የሆድ፣ የአጥንትና የተለያዩ የሰውነት ክፍሎችን ዝርዝር የምስል ምርመራ ያቀርባል። በተለይም ጉዳቶችን፣ የደም ሥር ችግሮችን፣ እጢዎችንና ሌሎች የጤና ሁኔታዎችን ለመገምገም የሚረዳ የላቀ የምርመራ አቅም ነው። ••• 👨‍⚕️ ቴክኖሎጂ ከባለሙያ ጋር ሲጣመር የዘመናዊ ማሽን መኖር ብቻ ጥራት ያለው ሕክምናን አያረጋግጥም። ከቴክኖሎጂው ጎን ለጎን በየሙያው የሰለጠኑ ሐኪሞች፣ ነርሶች፣ ቴክኖሎጂስቶች እና ሌሎች የጤና ባለሙያዎች ወሳኝ ናቸው። NLMC በአስቸኳይና ከፍተኛ ክትትል፣ ICU፣ NICU፣ Pediatrics፣ Surgery፣ Operating Room፣ GYN/Midwifery፣ Pharmacy እና Physiotherapy የመሳሰሉ ዘርፎችን በማቀናጀት የተቀናጀ የታካሚ እንክብካቤን ለማጠናከር እየሰራ ይገኛል። ይህም ለታካሚዎች ከምርመራ እስከ ሕክምናና ክትትል ድረስ በተቀናጀ የጤና አገልግሎት ሥርዓት የመታገዝ ዕድልን ያሳድጋል። 🏥 ታካሚን ያማከለ የሕክምና እንክብካቤ (Patient-Centered Care) New Leaf Medical Complex የሚያተኩረው በማሽንና በሕክምና አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ታካሚን ያማከለ የእንክብካቤ ባህል በመገንባት ላይም ነው። ትክክለኛ ምርመራ፣ ፈጣን የሕክምና ውሳኔ፣ የታካሚ ደህንነት፣ ሚስጥራዊነት እና ለታካሚው የሚሰጥ ግልጽ ማብራሪያ—እነዚህ ሁሉ የጥራት ሕክምና መሠረቶች ናቸው። 📍 ለአዲስ አበባ የዘመናዊ ሕክምና አዲስ አቅም New Leaf Medical Complex በለቡ የተቋቋመ ብቻ ሳይሆን፣ በዘመናዊ የሕክምና ቴክኖሎጂ፣ በባለሙያ ብቃትና በተቀናጀ የታካሚ እንክብካቤ የአዲስ አበባን የጤና አገልግሎት ከፊት ለማስቀመጥ የሚችል የሕክምና ተቋም እንደሆነ ሊታይ ይችላል። ይህም ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች በከተማቸው ውስጥ የላቀ ምርመራና ሕክምና የሚያገኙበትን አማራጭ ያሰፋል። ስለዚህ የጤና አገልግሎት ሲያስፈልግ፣ ከሐኪም ምክርና ከታካሚው የጤና ሁኔታ ጋር በማጣጣም New Leaf Medical Complexን ቀዳሚ ምርጫዎ ያድርጉ:: 📍 አድራሻ New Leaf Medical Complex (NLMC) አዲስ አበባ፣ ለቡ ሙዚቃ ሰፈር — ቶሞካ ቡና ፊት ለፊት ☎️ ለበለጠ መረጃ 8565 🌿 New Leaf Medical Complex “ዘመናዊ ቴክኖሎጂ፣ ብቁ ባለሙያ፣ ታካሚን ያማከለ እንክብካቤ — ለጤናዎ አዲስ ገጽ!” New Leaf Medical Complex — በለቡ፣ የዘመናዊ ሕክምና አዲስ መዳረሻ። Mujib Amino

photo content
+1

የለውጥ ሰዎችን ካልጠበቅን፣ የለውጥ ተቋማትን ካላጠናከርንና የተሳካ ተሞክሮን ካላስፋፋን፣ ለውጥ የግለሰቦች ጉዞ ሆኖ ይቀራል። ነገር ግን ብቁ አመራርን ከተቋማዊ ሥርዓት፣ ከቴክኖሎጂና ከሀገራዊ ፖሊሲ ጋር ካጣመርን፣ ለውጡ ከግለሰብ ተሞክሮ ወጥቶ ወደ ተቋማዊ ባህልና ዘላቂ ሀገራዊ አቅም ይሸጋገራል። ስለዚህ፣ ዶ/ር ረሻድ ከማልን ማጠናከር ማለት አንድን ግለሰብ ማጠናከር አይደለም፤ የለውጥ አመራርን ማጠናከር ነው። የለውጥ አመራርን ማጠናከር ደግሞ የሀገርን አቅም ማጠናከር ነው። ይህ ነው የለውጡ አሻራ፤ ይህም ለሀገር መጠበቅና ማስቀጠል የሚገባው አቅም ነው። የለውጡ ምልክት የሆነውን አቅም መደገፍ የግለሰብ ሽልማት ሳይሆን፣ ለሀገር የሚደረግ ስትራቴጂያዊ ኢንቨስትመንት ነው። Office of the Prime Minister-Ethiopia Worku Gachena-ወርቁ ጋቸና Federal Housing Corporation - Ethiopia

የለውጡ ምልክትና አሻራ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ Mujib Amino ከራዕይ ወደ ተግባር፣ ከተቋም ለውጥ ወደ ሀገራዊ አቅም የአንድ ሀገር ለውጥ በመሪው ራዕይ ይጀምራል፤ የለውጡ እውን መሆን ግን የሚለካው ራዕዩ ከንግግር ወጥቶ ወደ ተቋማዊ አሠራር፣ ወደ ተግባራዊ አፈጻጸምና በመጨረሻም ወደ ዜጎች የሚታይ ውጤት ሲለወጥ ነው። በዚህ መስፈርት የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን (FHC) ያሳለፈው የለውጥ ጉዞ በተቋም ደረጃ የለውጥ ራዕይ እንዴት ወደ ተግባር ሊወርድ እንደሚችል ከሚያሳዩ ምሳሌዎች አንዱ ሆኖ ይታያል። የጠቅላይ ሚኒስትር Abiy Ahmed Ali የለውጥ አቅጣጫ ዋና መርሆዎች መካከል ተቋማትን ማጠናከር፣ ሀብትን በብቃት መጠቀም፣ ምርታማነትን ማሳደግና የሀገርን የኢኮኖሚ አቅም ማስፋት ይገኛሉ። ይህንን ራዕይ በተቋም ደረጃ ተቀብሎ ወደ ተጨባጭ የሥራ አፈጻጸም ማሸጋገር የሚችል አመራር ደግሞ የለውጡ ወሳኝ አካል ነው። በዚህ አንፃር የFHC ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ረሻድ ከማል አመራር በልዩ ትኩረት ሊመረመር ይገባል። ⸻ 🏘️ ከ“ቤት አስተዳዳሪ” ወደ “የልማት አንቀሳቃሽ” የFHC የቅርብ ዓመታት ለውጥ በአንድ ሐረግ ቢገለጽ፣ “ያለንን ሀብት መጠበቅ ብቻ ሳይሆን፣ ሀብቱን ወደ አዲስ ሀብት መቀየር” የሚል ነው። ኮርፖሬሽኑ ከ20,000 በላይ የመንግሥት ቤቶችንና ሰፊ የሪል እስቴት ፖርትፎሊዮን የሚያስተዳድር ተቋም በመሆኑ፣ ይህንን ሀብት በተሻለ አጠቃቀም ወደ ልማት ማስገባት የተቋሙን ሚና ከንብረት አስተዳደር ወደ ልማት አንቀሳቃሽነት ያሸጋግረዋል። በዚህ ሂደት የዶ/ር ረሻድ ከማል አመራር የሚታየው ሀብትን እንደ ተቀማጭ ንብረት ሳይሆን፣ እንደ ልማት ካፒታል በመመልከት ነው። ይህ አስተሳሰብ በራሱ የለውጥ አመራር አንዱ መገለጫ ነው። ⸻ 💰 የለውጡ መለኪያ፦ የገቢ አቅም የለውጥ አመራር በንግግር ሳይሆን በውጤት ሲመዘን ነው አሳማኝ የሚሆነው። ከኮርፖሬሽኑ ሁለንተናዊ ለውጥ ማሳያዎች አንዱ የገቢ ዕድገቱ ነው። በሪፎርሙ መጀመሪያ ወቅት ከነበረበት ደረጃ በመነሳት በ2017 ዓ.ም. ከ9.34 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መድረሱ፣ በ2018 ዓ.ም. የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡና በበጀት ዓመቱ መጨረሻ ወደ14 ቢሊዮን ብር ለማድረስ የታቀደው ግብ፣ የተቋሙ የገቢ አመንጪነት አቅም መሻሻሉን ያመለክታል። እዚህ ላይ ዋናው ነጥብ ቁጥሩ ብቻ አይደለም። ቁጥሩ የሚያሳየው ንብረትን ወደ ገቢ፣ ገቢን ወደ አቅም፣ አቅምንም ወደ ልማት የመቀየር አቅጣጫ መፈጠሩን ነው። ⸻ 🏗️ ከፕሮጀክት ወደ የፕሮጀክት ባህል የFHC ለውጥ በገቢ ቁጥር ብቻ አይለካም። በተለያዩ ሥፍራዎች የተካሄዱ የቤት ልማት ሥራዎች፣ በ12 የተለያዩ ሥፍራዎች የተከናወኑ ፕሮጀክቶችና አንዳንድ ሥራዎች በአንጻራዊ አጭር ጊዜ መጠናቀቃቸው፣ በተቋሙ የፕሮጀክት አፈጻጸም ባህል መሻሻል መኖሩን ያመላክታል። በተለይ የገርጂ ዘመናዊ መንደር ፕሮጀክት ዘመናዊ የግንባታ አሠራርን ለመጠቀም የተደረገውን ጥረት ያሳያል። የሶማሌ ተራ ሳይት 3B+G+21 የሆነ ሕንፃ በ4,000 ካሬ ሜትር ይዞታ ላይ መገንባቱም የተቋሙ የግንባታ አቅም እየተስፋፋ መምጣቱን ያመላክታል። ስለዚህ ለውጡ “ብዙ ሕንፃ መገንባት” ብቻ ሳይሆን “በተሻለ ቴክኖሎጂ፣ በተሻለ ፍጥነትና በተሻለ አሠራር መገንባት” ወደሚለው አዲስ የአፈጻጸም ባህል መሸጋገሩን ያሳያል። ⸻ 🤖 ቴክኖሎጂ፦ የለውጡ አዲስ ፊት 3D Concrete Printing፣ Aluminium Formwork እና ሌሎች ዘመናዊ የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ሥራ ማስገባት የተቋሙ የሥራ አስተሳሰብ ከባህላዊ አሠራር ወደ ዘመናዊነት እየተሸጋገረ መሆኑን ያሳያል። ይህ ጉዳይ ከFHC ድንበር በላይ የሀገር አቀፍ ትርጉም አለው። ኢትዮጵያ የቤት ፍላጎቷን ለመመለስ ከፈለገች፣ የግንባታ ጊዜንና ወጪን ለመቀነስ፣ ምርታማነትንና ጥራትን ለማሳደግ ቴክኖሎጂን በስፋት መጠቀም ግዴታ ይሆናል። በዚህ መስክ FHC የሚወስደው አቅጣጫ ተቋማዊ ለውጥ ብቻ ሳይሆን፣ ለሀገሪቱ የግንባታ ዘርፍ የሚሰጥ የሙከራና የማሳያ ሚና ነው። ⸻ 🤝 ከመንግሥት ብቻ ወደ የጋራ አቅም(የግል ዘርፍን ማሳተፍ) የቤት ፍላጎት ከፍተኛ በሆነባት ሀገር መንግሥት ብቻውን በመገንባት ችግሩን መፍታት አይችልም። ስለዚህ FHC ከግል ዘርፍ፣ ከኮንትራክተሮች፣ ከአማካሪዎችና ከቴክኖሎጂ ተቋማት ጋር የሚፈጥረው ትብብር ከተቋሙ አሠራር በላይ የሚሄድ ትርጉም አለው። ይህም የመንግሥት ሀብትን ከግል ካፒታል፣ ከቴክኖሎጂና ከሙያ እውቀት ጋር በማጣመር በጋራ አቅም ውጤት የማምጣት አዲስ የልማት አስተሳሰብ መፈጠሩን ያሳያል። ⸻ 🌍 ከአገር ውስጥ ገበያ ወደ ክልላዊ ዕድል የFHC አቅም ከኢትዮጵያ የግንባታ ገበያ አልፎ ወደ ክልላዊ ገበያ ለመስፋፋት መጀመሩ ሌላው የለውጡ ጠንካራ ምልክት ነው። በደቡብ ሱዳን ጁባ ውስጥ ዘመናዊ የመኖሪያና የንግድ ሕንፃዎችን ለመገንባት የተያያዙ ስምምነቶች እውን ከሆኑ፣ ይህ የአንድ ተቋም የንግድ ስፋት ብቻ አይሆንም፤ የኢትዮጵያ የግንባታ እውቀት፣ የሰው ኃይልና የአፈጻጸም አቅም ወደ ውጭ ገበያ መውጣት ማለት ነው። ይህም ከ“የአገር ውስጥ ተጠቃሚ” ወደ “ክልላዊ ተወዳዳሪ” የሚደረግ ሽግግር ነው። ከዚህ አንፃር የFHC ልምድ በተሳካ ሁኔታ ከተስፋፋ፣ ለኢትዮጵያ የውጭ ገበያ ተሳትፎ፣ የሙያ አገልግሎት ኤክስፖርትና የክልላዊ ተፅዕኖ ማሳደግ አቅም ይፈጥራል። ⸻ ዶ/ር ረሻድ ከማል፦ ከአመራር በላይ የለውጥ ምልክት እዚህ ላይ ዋናው ጥያቄ፣ “ዶ/ር ረሻድ ምን ፕሮጀክት ሠሩ?” ብቻ መሆን የለበትም። ዋናው ጥያቄ፣ “ተቋሙን ከየት ወደ የት አሸጋገሩ?” መሆን አለበት። ✅ከቤት አስተዳደር ወደ ቤት ልማት፤ ✅ከቋሚ ንብረት ወደ ንቁ ሀብት፤ ✅ከባህላዊ ግንባታ ወደ ቴክኖሎጂ፤ ✅ከመንግሥት ብቻ ወደ የጋራ አቅም፤ ✅ከአገር ውስጥ ገበያ ወደ ክልላዊ ዕድል፤ ✅ከንብረት አስተዳደር ወደ የልማት አንቀሳቃሽነት። ይህ የአንድ ሰው የሥራ ዘመን ብቻ ሳይሆን፣ የተቋም አሠራር አቅጣጫ መቀየር ነው። ይህንንም የሚመራ አመራር በትክክል የለውጥ አመራር ተብሎ ሊገለጽ ይችላል። ዶ/ር ረሻድ ከማል በዘርፉ ያካበቱት ልምድ፣ የሙያ እውቀትና የአመራር ብቃት ሲደመር፣ ለአንድ ተቋም ብቻ የሚወሰን አቅም ሳይሆን ለሀገር የሚጠቅም የሙያና የአመራር ካፒታል ይሆናል። ⸻ የለውጡን ሰዎች ማጠናከር የለውጡን ራሱን ማጠናከር ነው የኢትዮጵያ ለውጥ የሚለካው በተቀረጹ ፖሊሲዎች ብቻ አይደለም፤ እነዚያን ፖሊሲዎች ወደ ተግባር የሚቀይሩ ተቋማትና አመራሮች በመኖራቸውም ይለካል። ስለዚህ እንደ ዶ/ር ረሻድ ከማል ያሉ በሙያ፣ በልምድና በተግባር የተፈተኑ አመራሮችን ማበረታታት የግለሰብ ሞገስ ወይም የግል ሽልማት ሊሆን አይገባም። ይህ የሀገር የልማት አቅምን የማሳደግ ስትራቴጂያዊ አጀንዳ ነው። ስለዚህ መንግሥት የዶ/ር ረሻድን አቅም በልዩ ትኩረት ማጠናከር ካስፈለገው፣ ይህ የአንድ ግለሰብን ሥራ ለማስቀጠል ብቻ ሳይሆን በFHC የተፈጠረውን የለውጥ ሞዴል ወደ ሌሎች ተቋማት ለማስፋፋት፣ የሀገሪቱን የግንባታ አቅም ለማሳደግ፣ የኢትዮጵያን የሙያ አቅም ወደ ክልላዊ ገበያ ለማስገባትና የለውጡን ፍጥነት ለማስቀጠል ነው።

photo content
+5

photo content
+9

photo content
+9

photo content
+9

photo content
+9

እንኳን ደስ አላችሁ! ኒው ሊፍ፤ በጤና ላይ የተጻፈ አዲስ ተስፋ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ Mujib Amino አዲሱን የኒው ሊፍ ሜዲካል ኮምፕሌክስን ክብርት አዳነች አቤቤ መርቀዉ ስራ አስጀመሩ! አንድ ከተማ የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለመሆን የምትሻ ከሆነ፣ የላቀ ሕክምና በከተማዋ ውስጥ እንዲገኝ ከማድረግ በላይ የጥራት፣ የቴክኖሎጂና የሙያ ብቃት ባህልን መገንባት ያስፈልጋል። በዚህ ረገድ ዛሬ ተመርቆ ሥራ የጀመረው New Leaf Medical Complex (NLMC) አዲስ ሆስፒታል በአዲስ አበባ የጤና ዘርፍ ውስጥ አዲስ አቅም የጨመረ ጉልህ ክንውን ነው። New Leaf Medical Complex ቀደም ሲል በተከፈተው ቅርንጫፉ ትኩረቱን በፈርቲሊቲ ሕክምና ላይ የሚሰራ አገልግሎት ያለው ሲሆን፣ ዛሬ የተመረቀው አዲሱ ሆስፒታል የሕክምና አገልግሎትን በሰፊ ስፔሻሊቲዎች ለማቅረብና የላቀ የምርመራና የሕክምና አቅምን በሀገር ውስጥ ለማስፋት የታለመ ነው። ✅ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በሀገር ውስጥ የአዲሱ ሆስፒታል ልዩ መለያ ከሆኑት ነገሮች አንዱ የላቀ የሕክምና ቴክኖሎጂን ማስገባቱ ነው። የአዲስ አበባ ከንቲባ ክብርት አዳነች አቤቤ በዛሬው እለት መርቀዉ ሆስፒታሉን ክፍት ባደረጉበት መድረክ -''ተቋሙ በኢትዮጵያ ከላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቀጥሎ ሁለተኛው PET-CT Scan እና Cath Lab የተሟላለት ማዕከል ነው''ብለዋል:: እንዲህ ያሉ የላቁ መሣሪያዎች መኖራቸው የምርመራና የሕክምና አማራጮችን በማስፋት፣ ታካሚዎች ለከፍተኛ ደረጃ ሕክምና ወደ ውጭ አገር የሚጓዙበትን ጫና ለመቀነስ የሚያግዝ አቅም ይፈጥራል። ይህም ሕክምናን ወደ ሕዝብ ማቅረብ ብቻ ሳይሆን፣ ሀገር ውስጥ ያለውን የሕክምና እውቀትና ቴክኖሎጂ ደረጃ ማሳደግ ነው። ✅የግሉ ዘርፍ፤ የጤና ልማት አጋር የጤና ሥርዓት ግንባታ የመንግስት ብቻ ኃላፊነት አይደለም። የግሉ ዘርፍ የገንዘብ አቅሙን፣ የፈጠራ አቅሙንና የቴክኖሎጂ ምርጫውን ወደ ጤናው ዘርፍ ሲያመጣ፣ የሀገሪቱ የሕክምና አቅም በተመጣጣኝ መልኩ ይሰፋል። የአዲሱ ሆስፒታል ምረቃም ይህንኑ እውነታ የሚያሳይ ነው። ከተማዋን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተያዘው ግብ በመንግስት ጥረት ብቻ የሚሳካ እንዳልሆነ ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመግለጽ፣ የግሉ ዘርፍ በጤና ላይ ለሚያደርገው ኢንቨስትመንት የከተማ አስተዳደሩ ድጋፉን እንደሚያጠናክር አስታውቀዋል። ይህ አቅጣጫ በጤና ላይ ኢንቨስት ማድረግ በአንድ በኩል የዜጎችን የጤና ፍላጎት ለማሟላት፣ በሌላ በኩል ደግሞ አዲስ የሥራ፣ የሙያ ልማትና የጤና ቱሪዝም ዕድሎችን ለመፍጠር የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ኢንቨስትመንት ነው። ✅የሕዝብ ጤናን ከተስፋ ጋር የሚያገናኝ ኢንቨስትመንት የሕክምና ተቋም ዋጋው በግንባታው ውበት ወይም በመሣሪያዎቹ ብዛት ብቻ አይለካም። በሚያድናቸው ሕይወቶች፣ በሚመልሳቸው ተስፋዎችና በሚቀይራቸው የሕይወት ጥራቶች ነው የሚለካው። በዚህ መነጽር የNew Leaf Medical Complex አዲሱ ሆስፒታል መከፈት ከአንድ የንግድ ፕሮጀክት በላይ የሚታይ ነው። የሀገር ውስጥ የሕክምና አቅምን ለማጠናከር፣ የላቀ ሕክምናን ወደ ዜጎች ለማቅረብና ኢትዮጵያ በጤና ዘርፍ ያላትን የተወዳዳሪነት አቅም ለማሳደግ የሚያግዝ ኢንቨስትመንት ነው። ✅ለመስራቾቹ የሚገባ ምስጋና የዛሬው ቀን የተቋሙን በር ለሕዝብ የከፈተበት ቀን ብቻ ሳይሆን፣ በጤና ዘርፍ ላይ ትልቅ ራዕይ ያላቸው ግለሰቦች ያደረጉት ጥረት ለሀገር የሚያበረክተውን ዋጋ የሚያሳይበትም ነው። ለዚህም የNew Leaf Medical Complex መስራችና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ኢማን አብዱልራህማን እና ባለቤታቸው አቡበከር መሐመድ ሳላህ ልዩ ምስጋናና አድናቆት ይገባቸዋል። በጤና ዘርፍ ኢንቨስትመንት ማድረግ ከባድ የገንዘብ፣ የሙያና የኃላፊነት ጫናን የሚጠይቅ ቢሆንም፣ ዶ/ር ኢማን አብዱልራህማንና አቡበከር መሐመድ ሳላህ ይህን ፈተና በራዕይና በቁርጠኝነት በመቀበል ዛሬ ለሕዝብ የተከፈተ ዘመናዊ የሕክምና ማዕከል ለማቆም በቅተዋል። ይህ ሥራ የግል ስኬት ብቻ ሳይሆን ለሀገር የሚተርፍ አስተዋፅኦ ነው። የግል ካፒታልን ወደ የሕዝብ ጤና ፍላጎት በመቀየር፣ ለሕክምና ባለሙያዎች የሥራና የሙያ ዕድል በመፍጠር፣ በሀገር ውስጥ የላቀ ሕክምና እንዲገኝ በማድረግ የሚያበረክቱት አስተዋፅኦ የሚመሰገን ነው። ለዶ/ር ኢማን አብዱልራህማንና ለአቡበከር መሐመድ ሳላህ፤ ለዚህ ታላቅ ራዕይ፣ ለወሰዳችሁት የልማት እርምጃ እና ለሀገር ያበረከታችሁት የጤና አስተዋፅኦ ከልብ የመነጨ ምስጋና ይድረሳችሁ። የዛሬው ሥራችሁ የነገው ትውልድ የሚያየው የልማት አሻራ ነው። እንኳን ደስ አላችሁ! ✅ከዛሬ ወደ ነገ የNew Leaf Medical Complex አዲስ ሆስፒታል ሥራ መጀመር በአዲስ አበባ የጤና ዘርፍ የተከፈተ አዲስ ገጽ ነው። ገጹ የሚሞላው ግን በሕንፃና በቴክኖሎጂ ብቻ ሳይሆን፣ በሚድኑ ሕይወቶች፣ በሚመለሱ ተስፋዎችና በሚገነባ የሕክምና ልህቀት ነው። የዛሬው ምረቃም እንዲሁ የአንድ ሆስፒታል መከፈት ብቻ ሳይሆን፣ የአዲስ አበባን የጤና ትልም በተጨባጭ እውን ለማድረግ የተወሰደ አዲስ እርምጃ ነው። ኒው ሊፍ ሜዲካል ኮምፕሌክስ —አዲስ ሆስፒታል፤ አዲስ አቅም፤ ለጤናማ ነገ አዲስ ተስፋ።

photo content

የምክክሩ እውነተኛ ድል የሚለካው በሰነዱ ርዝመት ሳይሆን፣ በዜጎች ሕይወት በሚፈጥረው ለውጥ ነው። የሙስሊሙ ጥያቄ ወደ እኩል ዜግነት ሲቀየር፣ የሌሎች ማኅበረሰቦችም ጥያቄ በተመሳሳይ መርህ ሲመለስ፣ ሕግ እና ተግባር ሲገናኙ፣ ዜጎች ማንነታቸውን ሳይደብቁ በእኩል ክብር መኖር ሲችሉ ነው ምክክሩ ከውይይት ወደ ታሪካዊ ለውጥ የተሸጋገረው። የምክክሩ የመጨረሻ መዳረሻ ስምምነት ሳይሆን እኩል ዜግነት ነው፤ የስምምነቱ ትልቁ ፈተናም ትግበራ ነው። «የምክክሩ ድል መቼ ነው? መልሱ—እኩል ዜግነት ሲረጋገጥ!»

የምክክሩ ድል መቼ ነው? ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ Mujib Amino ኢትዮጵያ በረጅም የታሪክ ጉዞዋ ውስጥ ብዙ ፈተናዎችን፣ ልዩነቶችንና የአመለካከት ግጭቶችን አሳልፋለች። እነዚህን ችግሮች በጉልበት ወይም በመገፋፋት ለመፍታት የተሞከሩባቸው ዘመናት አያሌ ናቸዉ። የችግሮቿ መነሻ ብዙ ጊዜ ልዩነት መኖሩ ሳይሆን፣ ልክ እንደአሁኑ መድረክ ያለውን ልዩነት በመነጋገርና በመደማመጥ ለማስተናገድ የተሟላ የጋራ መድረክ አለመፍጠሩና ዝግጁ አለመሆንም ጭምር ነው። በዚህ የታሪክ ዳራ ውስጥ የተካሄደው ሀገራዊ ምክክር ኢትዮጵያ ከግጭትና ከመከፋፈል ይልቅ በውይይት፣ በመደማመጥና በስምምነት ወደ ዘላቂ መፍትሔ ለመሄድ የጀመረችው አዲስ ጉዞ ነው። ይህ ሂደት ራሱ አንድ ትልቅ ጅምር ድል ነው። ምክክር ማለት ሁሉም በአንድ አስተሳሰብ መግባባት ሳይሆን፣ በልዩነት ውስጥ የሚያገናኘንን የጋራ ነገር መፈለግ ነው። ይህንንም ማድረግ መቻል ራሱ ለኢትዮጵያ ታሪካዊ የፖለቲካ ባህል ለውጥ ነው። በምክክሩ የተለያዩ ድምፆች የተደመጡበት፣ ብዙ የቆዩ ቅሬታዎችና የመብት ጥያቄዎች በጋራ ጠረጴዛ ላይ የቀረቡበት እና በልዩነቶች መካከል የጋራ መፍትሔ ለመፈለግ የተሞከረበት መሆኑ ትልቅ ቱሩፋት ነው። በተለይም በሂደቱ 400 ምክረ ሀሳቦች ቀርበው 396 ላይ ስምምነት መድረሱ እንደቀረበው መረጃ ከሆነ፣ በጥልቅ ሲታይ የልዩነት መኖር ችግር ሳይሆን ልዩነትን በሰላማዊ ውይይት ማስተናገድ መቻል እንደሚቻል ያሳየ አመላካች ነው። የምክክሩ ሌላው ታሪካዊ ቱሩፋት የተለያዩ ማንነቶች የሚያነሷቸው ጥያቄዎች ወደ አንድ ሀገራዊ የፍትሕና የእኩል ዜግነት አጀንዳ ሊቀየሩ መቻላቸው ነው። የሙስሊሙ ማኅበረሰብ የሚያነሳቸውን ጨምሮ የተለያዩ የመብት፣ የውክልና፣ የሃይማኖት ነፃነት፣ የፍትሕና የአካታችነት ጥያቄዎች በሀገራዊ የምክክር መድረክ መነሳታቸው፣ “የእኛ ጉዳይ” ከሚለው አስተሳሰብ ወደ “የሁላችንም የጋራ ጉዳይ” ለመሸጋገር የተከፈተ በር ነው። ሆኖም የሀገራዊ ምክክሩ እውነተኛ ድል የሚለካው በተጻፈው ሰነድ ርዝመት፣ በተዘረዘሩት የምክረ ሀሳቦች ብዛት ወይም በተደረሰባቸው ስምምነቶች ቁጥር ብቻ አይደለም። እውነተኛው ድል የሚጀምረው በምክክሩ የተነሱ የዜጎች ጥያቄዎች ከውይይት መድረክ ወጥተው ወደ ሕግ፣ ፖሊሲና ተግባር ሲቀየሩ ነው። በተለይም የሙስሊሙን ጥያቄ ጨምሮ የተለያዩ ማኅበረሰቦች ያነሷቸው የመብት፣ የውክልና፣ የእኩልነትና የክብር ጥያቄዎች በተጨባጭ ወደ እኩል ዜግነት መቀየራቸው ነው የምክክሩን ዘላቂ ውጤት የሚወስነው። ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ከምክክሩ የሚጠብቀው ልዩ መብት አይደለም። የሚጠይቀው በሕግ የተረጋገጠው መብት በተግባርም እንዲከበር ነው። ሂጃብ ማድረግ፣ ሰላትን በነፃነት መስገድ፣ የጁምዓን ሰላት በአግባቡ ማከናወን፣ የሃይማኖት በዓላትን ማክበር፣ የሂጅራ አቆጣጠርን መጠቀም፣ የዐረብኛ ቋንቋን መማር፣ የወለድ ነፃ የፋይናንስ አማራጮችን ማግኘት ወይም በመንግሥታዊና ማኅበራዊ ተቋማት በእኩልነት መወከል የሚለው ጥያቄ ከሌሎች ዜጎች የሚለይ ልዩ ዜግነት ለመፍጠር የሚቀርብ ጥያቄ አይደለም። የመብት ተጠቃሚነት እና ልዩ መብት ሁለት የተለያዩ ነገሮች ናቸው። እኩል ዜግነት ማለት ሁሉም ዜጎች በተመሳሳይ ነገር ብቻ እንዲኖሩ ማስገደድ ሳይሆን፣ የራሳቸውን ማንነትና እምነት ሳይጥሱ በሕግ ፊት እኩል እድልና ክብር እንዲያገኙ ማድረግ ነው። ስለዚህ የሙስሊሙ ጥያቄ ሲረጋገጥ የሌሎች ዜጎች መብት የሚጎዳ ካልሆነ፣ ይህ ለአንድ ማኅበረሰብ የተሰጠ ልዩ ስጦታ ሳይሆን የእኩል ዜግነት መጠናከር ነው። ✅የምክክሩ ትልቁ ፈተና፦ ከሰነድ ወደ ተግባር ምክክሩ የሚለካው ከዛሬ ጀምሮ በሚፈጠረው የተግባር ለውጥ ነው። በሰነዱ ላይ የተጻፈ መብት በትምህርት ቤት ካልተከበረ፣ በዩኒቨርሲቲ ካልተተገበረ፣ በሥራ ቦታ ካልተጠበቀ፣ በመንግሥታዊ ተቋም ካልታየ እና በዜጎች ዕለታዊ ሕይወት ላይ ለውጥ ካላመጣ፣ የምክክሩ ውጤት በወረቀት ላይ ብቻ የቀረ ውጤት ይሆናል። ስለዚህ ዋናው የትግበራ ጥያቄ “ምን ተስማማን?” የሚለው ብቻ ሳይሆን፣ “የተስማማንበትን እንዴት እንተገብራለን?” የሚለው መሆን አለበት። ይህም ግልጽ የሆነ የትግበራ ሥርዓት ይፈልጋል። ምክረ ሀሳቦቹ ወደ ተገቢ ሕጎችና ፖሊሲዎች መቀየር፣ ተጠያቂ ተቋማትን በግልጽ መለየት፣ የጊዜ ገደብ ማስቀመጥ፣ የትግበራ ሂደቱን በየጊዜው መገምገምና ለሕዝብ ተጠያቂ የሆነ አሠራር መፍጠር ያስፈልጋል። ✅ከሙስሊሙ ጥያቄ ወደ ሀገራዊ መፍትሔ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ያነሳቸው ጉዳዮች ለሙስሊሙ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም እምነቶች በሙሉ ማድረግ የምክክሩ አንዱ ትልቅ ውጤት ነዉ። ለምሳሌ የእምነት ነፃነትን ማስጠበቅ ለሙስሊሙ ብቻ ሳይሆን ለሁሉም እምነቶች ዋስትና ይሆናል። የሃይማኖት ቅርሶችን መጠበቅ የአንድ ሃይማኖት ቅርስን ብቻ ሳይሆን የሀገርን የተለያየ ታሪካዊ ቅርስ ማስጠበቅ ነው። በተመሳሳይ፣ በመንግሥት ተቋማት የተለያዩ ማንነቶች በፍትሐዊነት እንዲወከሉ መጠየቅ ለሙስሊሙ ብቻ የሚያገለግል አይደለም። ይህ የሁሉም ዜጎች የመሳተፍና የመወከል መብትን ያጠናክራል። የቁጥር አናሳ እምነቶች መብት እንዲጠበቅ የሚደረግ ሕግም በመጨረሻ የሙስሊሙን ጨምሮ የሁሉንም ዜጎች የሃይማኖት ነፃነት ያጠናክራል። ይህ ነው የምክክሩ እውነተኛ የለውጥ አቅም፤ የአንድ ማኅበረሰብ ተለይቶ የተነሳ ጥያቄ ወደ ሁሉም ዜጎች የሚጠቅም የሕግና የፍትሕ መርህ መቀየር። ✅እኩል ክብር፦ ከሕግ በላይ የሚታይ ውጤት! እኩል ዜግነት በሕግ መጻፉ ብቻ በቂ አይደለም። ዜጋው እኩል እንደሆነ በዕለት ተዕለት ሕይወቱ ሊሰማው ይገባል። ሙስሊም ተማሪው በእምነቱ ምክንያት እንዳይገለል፣ ሙስሊም ሴት በሂጃቧ ምክንያት እንዳትዋረድ፣ ሠራተኛው በእምነቱ ምክንያት እንዳይጎዳ፣ የሃይማኖት በዓል የሚያከብር ዜጋ ከሌሎች ያነሰ እንዳይቆጠር ሲሆን ነው እኩል ክብር ተጨባጭ የሚሆነው። በዚህ መልኩ የምክክሩ ስኬት በሰነዱ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዜጋው ልምድ ውስጥ ይታያል። ዜጋው “መብቴ በሕግ ተጽፏል” ብቻ ሳይሆን “መብቴ በተግባር ይከበራል” ማለት ሲችል ነው የምክክሩ ውጤት እውነተኛ የሚሆነው። ✅የሙስሊሙ ጥያቄ የኢትዮጵያ የጋራ ጥያቄ ሲሆን ኢትዮጵያ ብዙ ማንነቶች፣ ቋንቋዎች፣ ባህሎችና እምነቶች የሚኖሩባት ሀገር ናት። ይህን ልዩነት ማስወገድ አይቻልም፤ የሚጠየቀው ግን ልዩነቶቹ የግጭት ምንጭ ሳይሆኑ የጋራ ሀገራዊ ሕይወት አካል እንዲሆኑ ማድረግ ነው። ስለዚህ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ሲጠይቅ “የእኛ መብት ይከበር” ማለቱ ብቻ ሳይሆን፣ በውስጡ ያለው የጋራ መልዕክት “የማንም ዜጋ መብት በማንነቱ ምክንያት እንዳይገደብ” የሚል መርህ ነው። ይህ መርህ በተግባር ሲሰራ ሙስሊሙም፣ ክርስቲያኑም፣ ሌላ እምነት ያለውም፣ የተለያየ ብሔርና ባህል ያለውም ዜጋ በእኩል ክብር ይኖራል። ✅ስለዚህ ቀጣዩ የሚጠየቀው ትግበራ ነው የምክክሩ ውጤት በተግባር እንዲወርድ ከሁሉም ወገን ትዕግሥት፣ ኃላፊነትና ቁርጠኝነት ያስፈልጋል። መንግሥት የተስማማባቸውን ጉዳዮች በግልጽ የትግበራ እቅድ ማስቀመጥ አለበት፤ ማኅበረሰቡም ሂደቱን በኃላፊነት መከታተልና በሰላማዊ አግባብ ተጠያቂነትን መጠየቅ አለበት። በተለይ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ከምክክሩ የተገኙትን ውጤቶች እንደ “የሙስሊሞች ድል” ብቻ ከማቅረብ ይልቅ፣ “የእኩል ዜግነት ድል” እንደሆኑ ማቅረቡ የበለጠ ሀገራዊ ትርጉም ይሰጠዋል። ይህም የሙስሊሙን ጥያቄ ከሌሎች ማኅበረሰቦች ጥያቄ ጋር ያገናኛል፤ የጋራ የሆነ የፍትሕ አጀንዳም ይፈጥራል።

photo content
+9

ከ1447 የሐጅ ስኬት ወደ 1448 ዓ•ሂ ልህቀት ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ የ1448 ሐጅ ዝግጅት፦ ትብብር፣ ተቋማዊ ቅንጅትና የሐጃጆች አገልግሎት ማሻሻያ Mujib Amino የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሐጅና ዑምራ ጉዳዮች ቢሮ፣ በዶ/ር ሙሀመድ ሷሊህ Dr.Mohammed Salih መሪነት፣ ከኢትዮጵያ ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ጋር ያደረገው ውይይት በመሠረቱ የ1448 ዓ•ሂ ሐጅን ከቀድሞው የተሻለ፣ ቀልጣፋና ለምዕመናን ተደራሽ ለማድረግ የተያዘ አቅጣጫ ያሳያል። ጉዳዩ የሐጅ ምዝገባን ብቻ የሚመለከት ሳይሆን፣ ከሐጃጆች የጉዞ ሰነዶች አዘገጃጀት ጀምሮ እስከ መውጫ ሂደት ድረስ ያሉ አገልግሎቶችን በተቋማት መካከል በተቀናጀ መንገድ ለማስኬድ የሚያስችል አቅም መገንባትንም ያካትታል። 1. ከችግር መፍትሔ ወደ ቅድመ ዝግጅት በሐጅ ጉዳይ ላይ አንድ ነገር ግልጽ ነው፤ የተሳካ ሐጅ አገልግሎት የሚጀምረው ሁጃጆች ከሀገር ሲወጡ ሳይሆን ከዚያ በፊት ነው። የምዝገባ ሂደት፣ ፓስፖርት፣ መታወቂያ፣ የጉዞ ሰነዶችና ሌሎች መስፈርቶች በጊዜ ከተዘጋጁ በኋላ በመጨረሻ ደቂቃ የሚፈጠሩ መጨናነቆችን መቀነስ ይቻላል። ስለዚህ የ1448 ዓ•ሂ ሐጅ ዝግጅትን ቀደም ብሎ ማስጀመር ከፍተኛ ተቋማዊ ጠቀሜታ አለው። 2. የሁለቱ ተቋማት ትብብር ለሁጃጆች ምን ያመጣል? ሐጅ አንድ ተቋም ብቻ ሊያስፈጽመው የሚችል አገልግሎት አይደለም። የሐጅና ዑምራ ጉዳዮች ቢሮ የሐጅ ሂደቱን ሲመራ፣ ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ደግሞ ለጉዞው ወሳኝ የሆኑ የፓስፖርትና የሰነድ አገልግሎቶችን ይይዛል። ስለዚህ በሁለቱ መካከል የተጠናከረ ቅንጅት ማለት ለሐጃጆች የተቀናጀ፣ ፈጣንና በተቻለ መጠን ያለ የአሰራር መደጋገም አገልግሎት ማለት ነው። 3. የ1447 ዓ•ሂ ልምድን ወደ 1448 ማሻገር በውይይቱ የ1447 ዓ•ሂ ሐጅ አገልግሎት ስኬት መጠቀሱ እጅግ ጠቃሚ ነው። የተቋም ስኬት የሚለካው በማጠናቀቁ ብቻ ሳይሆን፣ ከተገኘው ልምድ ትምህርት በመውሰድ ቀጣዩን ዙር የበለጠ ማሻሻል በመቻሉ ነው። ስለዚህ የ1447 ሂደት ምን ጥሩ ነገር አስገኘ? የት ችግር ተፈጠረ? የት የአሰራር ክፍተት ነበር? የትኛው አገልግሎት በሕዝብ ዘንድ የተሻለ ምላሽ አገኘ? የሚሉት ጥያቄዎች ተመርምረው ወደ 1448 ማሻሻያ መቀየር ይገባል። 4. የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ቀጣዩ ትልቅ እርምጃ ነው የኢሚግሬሽን አገልግሎቱ በበርካታ ማዕከላት አገልግሎት መስጠቱና የቴክኖሎጂ አጠቃቀሙ መጠናከሩ አዎንታዊ እርምጃ ነው። በተለይ ሀጃጆች ከሚገኙበት አካባቢ ሳይርቁ የፓስፖርት አገልግሎት ማግኘት ከቻሉ የጊዜ፣ የወጪና የጉዞ ጫናን ይቀንሳል። ነገር ግን ቀጣዩ ደረጃ የተለያዩ ተቋማት የሚጠቀሙባቸውን ሂደቶች በተቻለ መጠን በዲጂታልና በተቀናጀ አሰራር ማስተሳሰር ነው። ይህ የሁጃጆችን የሰነድ ሂደት የበለጠ ሊያቀል ይችላል። 5. እኩልነትና ተደራሽነት—ዋናው የአገልግሎት መለኪያ የኢሚግሬሽን ተቋሙ “ዜጎችን በእኩልነት ማገልገል” የሚለውን መርህ ማስቀመጡ አስፈላጊ ነው። ሐጅ የሚፈጽሙ ምዕመናን ከተለያዩ ክልሎችና አካባቢዎች የሚመጡ በመሆናቸው አገልግሎቱ በአዲስ አበባ ብቻ የተገደበ መሆን የለበትም። በአካባቢ የሚገኙ ማዕከላትን በብቃት መጠቀም የሐጅ አገልግሎቱን የበለጠ ሕዝባዊና ተደራሽ ያደርገዋል። 6. የዶ/ር ሙሀመድ ሷሊህ አመራር የሚያሳየው አቅጣጫ በዚህ ውይይት የሚታየው አመራር ከተቋማዊ ድንበር ወጥቶ ለአንድ የጋራ ውጤት የተለያዩ ተቋማትን ማስተሳሰር ላይ ያተኮረ ነው። ሀጃጆች ለሚፈልጉት አገልግሎት ተቋም በተቋም እየተጓዙ ከመጨነቅ ይልቅ፣ ተቋማቱ እርስ በርስ ተቀናጅተው የሕዝቡን ጊዜና ጉልበት እንዲቆጥቡ ማድረግ ዘመናዊ አመራር የሚጠይቀው ነው። 7. የሚቀጥለው ፈተና፦ ከውይይት ወደ ተጨባጭ ተግባር የዛሬው ውይይት ጠቃሚ ቢሆንም፣ ዋናው መለኪያ የሚሆነው ውጤቱ ነው። በቀጣይ፦ ✅የሐጅ ምዝገባን ቀድሞ ማስጀመር፣ ✅የፓስፖርትና ሌሎች ሰነዶችን በጊዜ ማሟላት፣ ✅የአገልግሎት ማዕከላትን በተገቢው መጠቀም፣ ✅የተቋማትን ቅንጅት ማጠናከር፣ ✅የዲጂታል አሰራርን ማስፋት፣ ✅ለሁጃጆች ግልጽና ወቅታዊ መረጃ መስጠት የሚሉት ጉዳዮች በተግባር ከተፈጸሙ የ1448 ሐጅ አገልግሎት ከ1447 የበለጠ የተደራጀና ቀልጣፋ ሊሆን ይችላል። በአጠቃላይ፣ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሀጅና ዑምራ ዳይሬክተር ዶ/ር ሙሀመድ ሷሊህ የሚመራው የሐጅና ዑምራ ጉዳዮች ቢሮ ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ጋር ያደረገው ውይይት የ1448 ሐጅን በቅድመ ዝግጅት፣ በተቋማዊ ትብብርና በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር ለማስኬድ የተያዘ አቅጣጫ ነው። የሐጅ ስኬት የሚለካው በሁጃጆች ቁጥር ወይም በተጓዙበት ጊዜ ብቻ ሳይሆን፣ ከምዝገባ ጀምሮ እስከ መመለሻቸው ድረስ ያገኙት አገልግሎት በምን ያህል ቀላል፣ ፈጣን፣ ፍትሐዊና ተደራሽ እንደነበር ነው። ይህ ከሆነ፣ 1448 ዓ•ሂ ሐጅ የቀድሞ ስኬትን የሚደግም ብቻ ሳይሆን፣ ከስኬት ወደ የተሻለ የአገልግሎት ደረጃ የሚወስድ አዲስ ምዕራፍ ሊሆን ይችላል። ኢንሻ አላህ::