Mujib Amino Z islam
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Mujib Amino Z islam
تُعد قناة Mujib Amino Z islam (@mujibbinislam) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 562 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 981 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 323 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 562 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 08 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -90، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -7، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 27.70%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 9.61% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 033 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 400 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 17.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 09 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
14 562
المشتركون
-724 ساعات
-47 أيام
-9030 أيام
أرشيف المشاركات
14 562
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን
ወንድማችን ዘይኔ ፈድሉ ተገድሎ አስክሬኑ በጫካ ውስጥ ተገኝቷል!
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
ከቀናት በፊት ወንድማችን ዘይኔ ፈድሉ ከቤት እንደወጣ ሳይመለስ መቅረቱን በመግለጽ የአፋልጉኝ ማስታወቂያ አጋርተን ነበር።
ሆኖም በሚያሳዝን ሁኔታ በዛሬዉ እለት አስክሬኑ በአዲስ አበባ ከተማ ከቡልቡላ ወደኮዬ ፈጬ በሚወስደዉ አዲሱ መንገድ ጫካ ዉስጥ ሕይወቱ አልፎ ተገኝቷል።
ወንድማችን ዘይኔ በመልካም ባህሪው የሚታወቅ፤ በአከባቢዉ ማህበረሰብ የሚወደድ ወጣት የነበረ ሲሆን ሕይወቱ በዚህ መልኩ ማለፉ አስደንጋጭ ክስተት ሆኗል። ባለቤቱ ነፍሰጡር መሆኗና እርሱ በሚሰራዉ ስራ መተዳደራችዉ ቤተሰቡ ላይ ከባድ ሀዘን ፈጥሯል።
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን
አላህ ጀነተልፊርደውስን እንዲያጎናፅፈዉ፣ ቀብሩንም የጀነት ጨፌ እንዲያደርግለት፤ ለቤተሰቦቹም መጽናናትን እንመኛለን።
አሚን 🤲
14 562
💫ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም
🎙አቅራቢ: ኡስታዝ ማህሙድ ሀሰን
🔥ርዕስ : ወጣትነት እና ትርፍ ጊዜ
📅ቀን:እሁድ 28/10/2018
🕰ሰዓት :የዙሁር ሰላት እንደተሰገደ
አድራሻ: 🕌አብነት ከፍ ብሎ በሚገኘው ዑመር ኢብኑል ኸጣብ(26)መስጂድ
📌 አቡ አል-ዓታሂያ እንዲህ ይላሉ ፡
«ወጣትነት፣ ባዶ ጊዜ እና ብዙ ሀብት ለሰው እጅግ የሚያበላሹ ናቸው»
14 562
የአፋልጉኝ ማስታወቂያ‼
ወንድማችን ዐብዱልሃዲ ኸይረዲን ኑሪ በ19/10/2018 አንፎ ደንበል መስጂድ አካባቢ ከሚገኘው ቤታቸው እንደወጡ አልተመለሱም ። አቶ ዐብዱልሃዲ ኸይረዲን የልጆች አባት እና የቤተሰብ አስተዳዳሪ ነው። ቤተሰብ በጣም ጭንቀት ላይ ስለሆነ ያየ ወይም ያለበትን የሚያውቅ ቢያሳውቀን ወሮታ ከፋይ ነን ይላሉ ቤተሰቦቹ
ስልክ: 0911235477።
14 562
የንጹሐን ደም ምንም ዓላማ አያጸድቀውም
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
Mujib Amino
ሃይማኖት የሰላም፣ የእርቅ፣ የፍቅር እና የሰብዓዊነት እሴቶችን የሚያስተምር ተቋም ነው። እነዚህን እሴቶች የሚያስተምሩ የሃይማኖት መሪዎችን በጥይት ማጥቃት ወይም መግደል ደግሞ በአንድ ግለሰብ ላይ ብቻ የተፈጸመ ጥቃት ሳይሆን፣ በሰላም፣ በሃይማኖት ነፃነት እና በማህበረሰብ አንድነት ላይ የተቃጣ ጥቃት ነው።
የፅንፈኝነት ዋና መለያው ልዩነትን አለመቀበል፣ ሃሳብን በኃይል ለማስገደድ መሞከር እና ፍርሃትን እንደ መሣሪያ መጠቀም ነው። የሃይማኖት አባትን ዒላማ ማድረግም የዚህ አስተሳሰብ አደገኛ መገለጫ ነው፤ ምክንያቱም ዓላማው አንድን ሰው መጉዳት ብቻ ሳይሆን ሰፊ ማህበረሰብን በፍርሃት እና በውጥረት ውስጥ ማስገባት ሊሆን ይችላል።
ማንኛውም ዓላማ የሰውን ሕይወት ከመከበር በላይ ሊቆም አይችልም። ንጹሐንን መግደል በማንም አካል ቢፈጸም ሊወገዝ የሚገባ ወንጀል ነው። የንጹሐን ደም ምንም ዓላማ አያጸድቀውም፤ የሚያስከትለው ሀዘን፣ ፍርሃት እና ተጨማሪ ግጭት ብቻ ነው። ዘላቂ መፍትሔ የሚገኘው በሕግ የበላይነት፣ በፍትሕ እና በሰላማዊ ውይይት እንጂ በጥይት አይደለም።
በማንኛውም ፖለቲካዊ፣ ሃይማኖታዊ፣ ወይም በሌላ ምክንያት ንጹሐንን ማጥቃት ወይም መግደል ፈጽሞ ሊያፀቅ አይችልም። የሚነገር ዓላማ ምንም ያህል ትልቅ ቢመስልም፣ የሰው ደም በላዩ ሲፈስ ሞራላዊ እና ሕጋዊ ተቀባይነቱን ያጣል።
ፅንፈኛ ከሀሳብ ተሻግሮ በተግባር ወደ ግድያ፣ ወደ ማስፈራራት እና ወደ ማኅበረሰብ መከፋፈል ሲያመራ የሚጎዱት በአብዛኛው ንጹሐን ዜጎች ናቸው። ታጣቂ ቡድኖችም ሆኑ ሌሎች ኃይል የሚጠቀሙ አካላት የሲቪል ሰዎችን ኢላማ ማድረግ በሕግም ሆነ በሰብዓዊ እሴት ተቀባይነት የለውም።
በአማራ ክልል ዳንግላ ከተማ ቀበሌ 02 በሚገኘው የኹጥባ መስጂድ ኢማም ሸይኽ ሱፍያን አደም የ 4 ልጅ አባት የነበሩና በማህበረሰቡ ዘንድ ክቡርና ወጣቶችን በመልካም ስነ ምግባር በማነፅ የሚታወቁ
የነበሩ የሃይማኖት መሪ በትላንትናዉ እለት ሰኔ 20/10/18 እለተ ቅዳሜ ምሽት ላይ የዒሻ ሶላታቸዉ ምዕመናኑ በማሰገድ ሲወጡ በአማራ ክልል ስር እየሰደደ የመጣዉ ፅንፈኝነትና የሽብር ግብረ ኀይል በጥይት በመምታት ግድያ ፈፅሟል::
ፋኖ ተብሎ የሚጠራዉ ፅንፈኛና ሙስሊም ጠል ቡድን በዚሁ ክልል ና በተለያዩ አከባቢዎች በርካታ ነዋሪዎችን እምነታቸዉን ምክንያት በማድረግ ብቻ እንግልትና ግድያ በተደጋጋሚ ፈፅሟል:: በጥቂት ጊዜያት ዉስጥ ብቻ እንደማሳያ:-
ሸይኽ መሐመድ ነጃው በአማራ ክልል በጎንደር ከተማ ፒያሳ ቀበሌ 11 በሚገኘው ሼህ መሐመድ ደሴ መስጂድ ላይ ኢማም ፅንፈኛዉና ባለሽብር ካባዉ ፋኖ ሚያዚያ 18 ቀን 2014 ገድ*ሏቸዋል::
በአማራ ክልል ጎንደር ዙሪያ ወረዳ እንፍራንዝ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሚያዚያ 10 እና 11 ቀን 2016 በፅንፈኛዉ ፋኖ ምክንያት የሸይኽ ኢብራሂም መህሊ የሃይማኖት እውቀት ማዕከል ላይ ሙዓዚኑን ጨምሮ 4 የሃይማኖት ትምህርት ተማሪዎች ተሰዉተዋል::
ሸይኽ ሲራጅ አብድሬ በአማራ ክልል ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ደንቢያ ወረዳ አየንባ ቀበሌ ውስጥ የመስጂድ ኢማም ግንቦት 10 ቀን 2016 የመግሪብ ሶላትን አሰግደው ሲወጡ፣ በፅንፈኞቹ ፋኖዎች ህይወታቸዉ አልፏል::
ሸይኽ ጀማል ከማል ኢሳ በደቡብ ወሎ ዞን፣ ቦረና ወረዳ፣ መካነ ሰላም ከተማ ቀበሌ 2 ውስጥ የሚገኘው አንጋፋው የኑር ሃጂ ነስሩ መስጂድ ኢማም የነበሩ ሲሆን
መስከረም 23 ቀን 2018 ዓ.ል በፋኖ ታጣቂዎች በተሰነዘረ አሰቃቂ ጥቃት መስጂድ ውስጥ እያሉ በግፍ በጥይት ተመትተው ተገድለዋል።•••ወዘተ የሽብር ዶሴዎች!
ፅንፈኝነት የሚሸነፈው በቁጣ ወይም በበቀል ሳይሆን፣ በፍትሕ፣ በጠንካራ ተቋማት እና በሕግ የበላይነት መሆኑን በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል። ስለዚህ መንግሥት በግልጽና በተጠያቂነት ሕግን ማስከበር ሲኖርበት፣ ማኅበረሰቡም ለሰላም፣ ለመቻቻል እና ለፍትሕ በመቆም የበኩሉን ኃላፊነት ሊወጣ ይገባል። ይህ ነው የአመፅና የፅንፈኝነት ዑደትን ለማስቆም ዘላቂ መንገድ የሚሆነዉ::
ከዚህ ጎን ለጎን የጥቃቱ ተደጋጋሚ ሰለባ የሆነዉ ሙስሊም ማህበረሰቡ ራሱን ፋኖ ብሎ የሚጠራዉን ፅንፈኛና ፀረ ኢስላም ቡድን ከበፊቱ በተሻለ ሁኔታ ነቅቶና ተደራጅቶ እንዲታገል ፣ የእርስ በእርስ ግንኙነቱንና ማህበራዊ ሕይወቱን በአንድነት ገመድ ማስተሳሰር ፣ ለነገ የማይባል የዛሬ ስራችንና ትግበራችን ሊሆን ይገባል::
በዚሁ አጋጣሚ ይሕ ፅንፈኛ ቡድን የማህበረሰብን አንድነት ለመናድና የዘመናት አብሮ የመኖር እሴትን ለማፈራረስና ለመበጠስ ሲል የአንድንት እምነት ተቋም መገለጫዎችና ቃላትን በመጠቀም ጠበቃ ና አገልጋይ በመምሰል ዉዥንብ ቢፈጥርም እዉነታዉ ግን ቆምኩለት የሚለዉን የእምነት ተቋም የሃይማኖት አባቶችን ጭምር በግፍ የሚገድል በመሆኑ የዚህ ሽብር እንቅስቃሴ ባለቤት ቡድኑ እንጂ ሃይማኖቶችና ተቋማቱ እንዳልሆኑ ልንገነዘብ ይገባል:: በእርግጥ አንዳንድ መምህራን ተብዬዎች ቀን የሰላም ባንዲራ ምሽት ላይ ጦርነት መጎሰም ስራቸዉ ያደረጉ ከፅንፈኛዉ ሃይልጋር አብረው የሚሰሩ መኖራቸዉ አያጠራጥርም:: እንዲያም ሆኖ እምነቱን የማይወክሉ ተርብ ናቸው::
ኢማማችንን አላህ ይዘንላቸው። ማረፊያቸውንም ጀነት ያድርግልን:: አሚን 🤲
Abiy Ahmed Ali
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
Ethiopian Federal Police
Prosperity Party - ብልፅግና
Amhara Prosperity Party /APP/
14 562
አፋልጉን
ከታች በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ህጻን ሙሀመድ ሁሴን ይባላል::
ትላንት ሰኔ 20/2018 እለተ ቅዳሜ በግምት ከቀኑ
8:00 ሰዓት አከባቢ ኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው መብራት ሀይል ተብሎ በሚጠራዉ በሚኖርበት ስፍራከልጆች ጋር እየተጫወተ እንደነበርና ቤተሰቦቹ ፓሊስ ጣቢያም የሕክምና ተቋማትም ጭምር ሲፈለጉት ማግኘት አልቻሉም::
ህፃን ሙሀመድ ሁሴን ያያችሁ ወይንም ያለበትን የምታዉቁ እባካችሁ ከታች በተቀመጡት ስልክ ቁጥሮች አሳዉቁን ያላሉ ቤተሰቦቹ:-
📲091 310 1614
📲 0911622758
14 562
ይህ የክረምት የዑምራ ፓኬጅ እንዳያልፋችሁ!
በ150ሺ ብር ሙሉ የዑምራ ፓኬጅ
* ቪዛና የደርሶ መልስ ቲኬት
* ለ2ቱም ሀረሞች ቅርብ የሆኑ ጥራታቸውን የጠበቁ ሆቴሎች
* ሙሉ የትራንስፖርት ወጪ
* በመካና በመዲና የታሪካዊ ቦታዎች ጉብኝት
* የዑምራ አደራረግ ቅድመ ስልጠና እና የልምድ ልውውጦች
* ሾፒንግ ያካተተ ፓኬጅ
-------------
0967237373
ይደውሉ
14 562
በአገራችን ድምጽ አልባው የትዳር ገዳይ
/ትምህርት ሰጪ በመሆኑ: ይሕን አጭር ፁሁፍ ጋብዣለሁ/
ትዳር በሁለት ሰዎች የሚጀምር ቢሆንም፣ በአገራችን ብዙ ጊዜ በብዙ ሰዎች የሚመራ ሆኗል። ይህም ለብዙ ቤተሰቦች መፍረስ፣ ለልጆች መበተን እና ለማኅበረሰባችን በጣም ከባድ ማኅበራዊ ቁስል ሆኗል። ባልና ሚስት በፍቅር ተዋውቀው፣ በተስፋ ተጋብተው አዲስ ሕይወት ይጀምራሉ። በሠርጋቸው ቀን ስለ ደስታ፣ ስለ ፍቅር፣ ስለ ልጆች እና ስለ ወደፊት ሕይወታቸው ያልማሉ። ነገር ግን ከተጋቡ በኋላ ትዳራቸው በራሳቸው እጅ እንዲመራ ከመተው ይልቅ ቀስ በቀስ ወደ ወላጆች፣ ወደ እህቶች፣ ወደ ወንድሞች እና ወደ ሌሎች ዘመዶች እጅ ይገባል።
መጀመሪያ ምክር በሚመስል ነገር ይጀምራል። "እንዲህ አድርጉ።" "እንዲያ አታድርጉ።" "ልጃችን እንዲህ አይደረግበትም።" "እኛ የምናውቀው ይሻላል።" ከዚያ ግን ምክር ወደ ቁጥጥር ይቀየራል። ቁጥጥሩም ወደ ጣልቃ ገብነት ያድጋል። በመጨረሻም ባልና ሚስት የራሳቸውን ሕይወት ለመወሰን የማይችሉ ሰዎች ይሆናሉ።
በብዙ ቤቶች ውስጥ ችግሩ በባልና ሚስት መካከል አይደለም። ችግሩ የሚፈጠረው ከቤቱ ውጭ ነው። ባል ለሚስቱ የነበረውን ቅሬታ ለእናቱ ይናገራል። ሚስትም ለቤተሰቦቿ ትናገራለች። ከዚያም ሁለቱ ችግሩን ለመፍታት ከመቀመጥ ይልቅ የየራሳቸውን ወገን ማሰባሰብ ይጀምራሉ።
በዚህ ጊዜ ትዳሩ ከፍቅር ወደ ውድድር ይቀየራል። ከመግባባት ወደ ወገንተኝነት ይሄዳል። ከመደማመጥ ወደ መከሳሰስ ይለወጣል።
የሚያሳዝነው ግን በዚህ ግጭት ውስጥ የማይናገሩት ልጆች ናቸው። በየምሽቱ የእናትና የአባት ጭቅጭቅ የሚሰሙ ልጆች፣ አንድ ቀን አባት ከቤት ሲወጣ የሚያዩ ልጆች፣ በፍቺ መካከል የሚጎዱ ልጆች ማንንም አይከሱም፤ ግን ቁስሉን ዕድሜ ልካቸውን ይሸከማሉ። ብዙ ጊዜ ትዳር ሲፈርስ ሰዎች ባልን ወይም ሚስትን ይወቅሳሉ። ነገር ግን እውነቱ አንዳንድ ጊዜ ትዳሩን የገደለው ሰው በውስጡ ሳይሆን በዙሪያው የነበረ ሰው ነው። ወላጆች ልጆቻቸውን መውደድ አለባቸው። ዘመዶች መደገፍ አለባቸው። ጓደኞችም መርዳት አለባቸው። ነገር ግን ትዳርን መምራት ያለባቸው ባልና ሚስት ብቻ ናቸው።
ትዳር የቤተሰብ ፕሮጀክት አይደለም። ትዳር የዘመዶች ኮሚቴ አይደለም። ትዳር የሁለት ሰዎች ቃል ኪዳን ነው። በአገራችን የትዳር መፍረስን ለመቀነስ የመጀመሪያው መፍትሄ ባልና ሚስት ችግራቸውን በራሳቸው መፍታት መማር ነው። ወላጆች መካሪ እንጂ አስተዳዳሪ መሆን የለባቸውም። ዘመዶች ደጋፊ እንጂ ዳኛ መሆን የለባቸውም። ቤት የሚገነባው በፍቅር ነው። የሚፈርሰው ግን ብዙ ጊዜ በከመጠን በላይ በሆነ ጣልቃ ገብነት ነው። ዛሬ የምናድነው አንድ ትዳር ከሆነ፣ ነገ የምናድነው አንድ ትውልድ ይሆናል።
14 562
ተፈላጊ- አህመድ ሽኩር
እድሜ- 16
ነዋሪነቱ ጉሬጌ ዞን ጌቶ ወረዳ ልዩ ስሙ ቀቡል
በቀን 29/9/18 ጠዋት ከቤት እንደወጣ አልተመለሰም።
ተፈላጊ አህመድ ሽኩርን ያየ ወይንም ያለበትን የሚያዉቅ ከታች በተቀመጡት ስልክ ቁጥሮች እንድታሳውቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፦
📲0923 75 40 04
📲0925 75 61 79
14 562
ለሀሰተኞች ህመም ይሆን ዘንድ ሼር ይደረግ!
እዉነታዉን ሁሉም ይወቅ! ሁሉም ይረዳ!
በአርሲ ዞን 2 የክርስትና እና 1 የእስልምና ተከታይ ናቸው የተገደሉት-ኢሰመኮ
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ በተፈጸመ ጥቃት የሦስት ሲቪል ሰዎች ሕይወት ማለፉን ኢሰመኮ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች መገደል በተጨማሪ ከ2 ሺሕ 650 በላይ የሚገመቱ የአካባቢው ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገልጿል።
ኮሚሽኑ ግንቦት 23 እና 24 ቀን 2018 የተፈጸመውን ይህንን ጥቃት በተመለከተ ባካሄደው ክትትልና ምርመራ፤ ጥቃቱ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ በሚጠራውና “በተለምዶ ኦነግ ሸኔ” በሚባለው ታጣቂ ቡድን መፈጸሙን ጠቁሟል።
በዚህም የሰው ሕይወት መጥፋቱን፣ መፈናቀል፣ የንብረት ውድመት እና ቃጠሎ መድረሱን ከዐይን እማኞች፣ ከተጎጂዎች፣ ከቤተሰቦቻቸውና ከመንግሥት አካላት ባሰባሰበው መረጃ ማረጋገጡን ገልጿል።
ኢሰመኮ ከደቂቃዎች በፊት ባወጣው መግለጫ፣ በአሰኮ ወረዳ ደለተ ጫፋ ቀበሌ አካባቢ ከግንቦት 22 ቀን 2018 . ጀምሮ የታጣቂዎች እንቅስቃሴ በመስተዋሉ የአካባቢው ሚሊሻዎችና የኦሮሚያ ጸረ ሽምቅ ውጊያ ፖሊስ አባላት በስፍራው ተሰማርተው ነበር ብሏል።
በዚህም ሳቢያ በታጣቂ ቡድኑ እና በጸጥታ አካላቱ መካከል ግጭት የተፈጠረ ሲሆን፣ ግጭቱን ተከትሎ ታጣቂ ቡድኑ በሰነዘረው ጥቃት ከአካባቢው መሸሽ ያልቻሉት ኃይሉ ንጉሴ እና ሰሙ አባይነህ የተባሉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንዲሁም በአካባቢው ከብቶች በመጠበቅ ላይ የነበረ ባቶ ሰፈኖ የተባለ የእስልምና እምነት ተከታይ በድምሩ የሦስት ንጹሐን ዜጎች ሕይወት አልፏል።
ከሰው ሕይወት መጥፋት በተጨማሪ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ የመኖሪያ ቤቶችና የንግድ መደብሮች ላይ በመደዳ ዘረፋና ቃጠሎ መፈጸሙን ኮሚሽኑ በምርመራው አረጋግጧል።
በዚሁ ጥቃት የጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን መቃጠሉን፣ የቢዮ ቡጡሌ የሼክ ሙስተፋ መስጅድ አጥር ላይ ጉዳት መድረሱን እና የደለተ ጫፋ ጤና ጣቢያ መዘረፉን የገለጸው ኢሰመኮ፣ በሽርካ፣ በአሰኮ፣ በአንቆሎ ዋቤ፣ ጉና እና መርቲ ወረዳዎች ላይ መሰል ጥቃቶች ዳግም እንዳይከሰቱ በተለያዩ ጊዜያት ማሳሰቡን አስታውሷል።
በአሁኑ ወቅት በጥቃቶቹ ምክንያት ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ነዋሪዎች በመንግሥትና በአጋር አካላት በቂ የአስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ እንዲቀርብና በዘላቂነት የሚቋቋሙበት ሁኔታ እንዲመቻች ኮሚሽኑ አሳስቧል።
ይዘቱ በአግባቡ ሳይረጋገጥ የሚሰነዘሩ ፍረጃዎችና ቅስቀሳዎች ተጨማሪ ግጭት ሊቀሰቅሱ ስለሚችሉ ማናቸውም ተቋማትና ግለሰቦች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ጥሪ ያቀረበው ኮሚሽኑ፣ ጉዳዩን አስመልክቶ ዝርዝር የምርመራ ሪፖርት በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ በዜጎች ላይ በደረሰው ሞትና ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ኃዘን ገልጸው፣ የተፈጸሙት የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች እጅግ አሳሳቢ መሆናቸውን አስረድተዋል።
ዋና ኮሚሽነሩ መንግሥት ሁኔታውን ለማረጋጋት የጀመራቸውን ጥረቶች በማጠናከር በአስቸኳይ ተጨማሪ የጸጥታ ኃይሎችን እንዲያሰማራ፣ የነዋሪዎችን በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደኅንነትና የንብረት መብቶች እንዲያስጠብቅ ጠይቀዋል።
14 562
የክረምትን ወቅት ዉድ ልጆችዎ የት ያሳልፉ ይሆን ብለዉ እንዳያስቡ!
ፈጥነው ልጆችዎን ለክረምት ያስመዝገቡ!
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
የ 15 አመታት ልምድ ያካበተዉ አዱርቱ አል መክኑና የተርቢያና የቁርአን ማዕከል ከፊት ለፊታችን ያለዉን የክረምት ጊዜያት ዉድ ልጆችዎ(ወንድም፤ ሴትም) ከቁርኣንና ከሀዲሶች ፣ ከተፍሲርና ከአረብኛ ቋንቋ፣ ከሲራና ከፊቅህ ጋር ያላቸዉን ቁርኝት ለማዳበርና በዲን ትምህርት መሰረት እንዲይዙ ለማድረግ የትምህርት ካሪኩለም ቀርጾ እናንተን እየጠበቀ ይገኛል።
አዱርቱ አል መክኑና የተርቢያና የቁርአን ማዕከል ከ 1000 በላይ ሁፋዞችን ለሀገሪቱ አ ስተምሮ ያበቃና በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄዱ የቁርኣንና የሀዲስ ዉድድሮች ላይ ከፊት የተስለፉት አሸናፊዎችን አስተምሮ ያበቃም ጭምር በመሆኑ ልምድና ብቃት፣ ስናምግባርና የእንክብካቤ ጉዳዮችን በሙሉ እኛ እንደወላጅ ተቀብለን እንደምናስተናግድ እርግጠኞች ነን። ኢንሻ አላህ።
በተቋማችን ስር ተምረዉ መዉጣትና እውቀት መሸመት ብቻ ሳይሆን፤ የአዱርቱ አል-መክኑና የተርቢያና የቁርአን ማዕከል ባስተማራቸዉ መሰረት የራሳቸዉን የቁርኣን ማዕከል ከፍተዉ በርካቶችን እያሰለጠኑ መገኘታቸዉ ለትምርት ጥራታችን ምን ያህል እንደምንጨነቅ ማሳያ ነዉ።
የክረምት ጊዜያት ምዝገባ እየተከናውነና በአጭር ጊዜ ዉስጥም ያሉን ውስን ቦታዎች እየተገባደዱ ስለሆነ ፈጥነው በመመዝገብ ለልጆችዎ የዲን መሰረት ይጣሉ። ኢንሻ አላህ
ለበለጠ መረጃ :-
📲0910769303
📲0921123712
📲0940505065
አድራሻ
አንፎ አልቢር መስጂድ ከፍ ብሎ እና
በአዲስ አበባ የተለያዩ ቅርንጫፎች
14 562
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ/EHRC) ምን እንዳጣራ ሰማችሁ? በእዉነቱ በተወስነ ደረጃ የዘገየ ቢሆንም ሪፖርቱ መዉጣቱ ለሀሰተኞች ቅጣት ነዉ።
ምን ተብሎ ነበር?
14 562
የ‹‹ነጭ ሽብር›› አዋጅን እናስቁም!
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️
Mujib Amino
በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዋና ተግባራቸው በፖሊሲ፣ በልማት አጀንዳ እና በህዝብ ፍላጎት ዙሪያ አማራጮቻቸዉን በማቅረብ መወዳደር ነው። ሃይማኖትን የፖለቲካ መሳሪያ በማድረግ ወይም ለአንድ ሃይማኖት ብቻ ወግኖ ሌሎችን ማግለል ግን የማህበራዊ አንድነትን የሚያዳክም እና በዜጎች መካከል የጥርጣሬ እና የመከፋፈል መንፈስ የሚፈጥር አደገኛ አካሄድ ነው። የሃይማኖት ተቋማት የእምነት፣ የሰላም እና የሥነ-ምግባር ማዕከላት እንጂ ፓለቲካ ፓርቲዎች የፉክክር መድረኮች ሊሆኑ ፈፅሞ አይገባም።
በቅርቡ ሀገር አቀፍ 7ኛዉ ምርጫ መካሄዱ ይታወሳል:: በምርጫ ሂደት ውስጥ ህዝብ የሰጠውን ውሳኔ በአክብሮት መቀበል የፖለቲካ ብስለት መለኪያ ሆኖ ሳለ ኢሕአፓን የመሳሰሉ አንዳንድ ፓርቲዎች ግን በሕዝባችን የደረሰባቸውን የምርጫ ውጤት ወይም ሽንፈት በግልጽ ራስ-ግምገማ ከመቀበል ይልቅ፣ የሃይማኖት ጉዳዮችን በመቀስቀስ ትኩረትን ለማሳት የሚሞክሩበት ሁኔታ ታይቷል። ይህ አካሄድ የፖለቲካ ችግርን ወደ ሃይማኖታዊ ግጭት በመቀየር ህዝብን ለመከፋፈል የሚያመራ በመሆኑ በብርቱ ሊወገዝ ብቻ ሳይሆን መንግስት ለሕግ ሊያቀርብም ጭምር ይገባል።
ሃይማኖትን እና ፖለቲካን በማቀላቀል የሚገኝ ጊዜያዊ የፖለቲካ ትርፍ ቢኖርም፣ የሚያስከትለው ማህበራዊ ጉዳት ግን እጅግ ከባድ ነው። ዜጎች በእምነታቸው ሳይሆን በዜግነታቸው እና በጋራ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እንዲተባበሩ ማድረግ የፖለቲካ ኃይሎች ኃላፊነት ነው። ማንኛውም ፓርቲ የፖለቲካ ድክመቱን ወይም የምርጫ ሽንፈቱን በሃይማኖት ጉዳይ ለመሸፈን ከሞከረ፣ ያ የዴሞክራሲ መንፈስን የሚጎዳ እና የህዝብን አንድነት የሚፈታተን ተግባር መሆኑን ማህበረሰቡ በግልጽ ሊረዳ ይገባል።
ኢሕአፓና መሰሎቹ ከምርጫ ማግስት ከአዲስ አበባ በርካታ ኪ.ሜ አቋርጠዉ አርሲ የከተሙበት ፈጣን መንገድ ዝግጅት ና እቅድ የወለደዉ እንጂ በድንገት የተፈጠረ አለመሆኑ ፓለቲካዊ ቁመናዉን ቀብሮ በቀጥታ የሃይማኖት ካርድ በመሳብ ለአንድ እምነት ተከታዮች ብቻ ጥብቅና ቆሟል::
በአርሲ በርካቶች ሕይወታቸዉ አልፎ ለሰብዓዊነትን ክብር ያለዉ የሀገሪቷ ሕዝብ ሁሉ በሀዘን ላይ ሳለ : እምነት ምርመራ ዉስጥ የገባዉ ኢሕአፓና መሰሎቹ የሌሎቹን የግዑዝ ሞት ይሁን ብለዉ ፈርጀዋል::
እኛ ከቆምንለት እምነት ውጪ ለእናንተ ሞትና መፈናቀል ግድም አይሰጠንም ብለዉ በዘመናዊዉ አለም በሕዝባቸዉ የነጭ ሽብር ጥቃት ፈፅመዋል::
በ1960ዎቹ ብቅ ያሉት ባለ አፍሮ ፀጉራም ወጣቶች፣ በማርክስ፣ በኤንግልስ እና በሌሊን አስተምህሮቶችና ፍልስፍናዎች የተራቀቁት የኮሚኒስት እና የሶሻሊዝም ርዕዮት የሚያስተጋቡት እኒያ ወጣቶችን በጠማማና ጭካኔ በተሞላበት የፓለቲካ ወጥመድ ዉስጥ አስጥሞ የደም ፓለቲካን ያፋፋመዉ ኢሕአፓ ነጭ ሽብርን ለማፋፋም ይሆን እጅና እግሩን የሃይማኖት ተቋማት ዉስጥ የሰደደው?
የሀገር ጥንካሬ የሚገነባው በመቻቻል፣ በህግ የበላይነት እና በእምነት ነጻነት ላይ እንጂ ሃይማኖትን ለፖለቲካ ፍጆታ በማዋል አይደለም። ስለዚህ ሁሉም የፖለቲካ ተዋናዮች የሃይማኖት ተቋማትን ሊያከብሩ፣ ከጣልቃ ገብነት ሊቆጠቡ እና የፖለቲካ ውድድራቸውን በሃሳብ፣ በፕሮግራም እና በህዝብ ጥቅም ላይ መመስረት ይገባቸዋል። ይህ ብቻ ነው ዘላቂ ሰላምን፣ አንድነትን እና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን የሚያጠናክረው። በነጭ ሽብር አዋጃቸዉ መሰረት ከእነሱ ህሳብና ምልከታ ብቻ ሳይሆን የተለይ እምነት ያላቸዉ ዜጎቻችን እየተመረጡ ይወገዱ?•••ለዚህ መልዕክት ሕዝብና መንግስት በትብብር ና በአንድነት መቆም ይገባቸዋል:: መንግስትና የፀጥታ አካላት በሕዝባችን ላይ የነጭ ሽብርን ለመፈፀም የተንቀሳቀሰን አካል ስለምን ይታገሳል? ‹‹ከችግሮችና ከምስቅልቅሎች በኃላ ለመፍትሄ እንዘጋጅ ወይስ ቅድሚያ እንከላከል?›› የሚለዉን መልዕክቴን የሚመለከተዉ አካል ይውሰድ!
