uz
Feedback
Mujib Amino Z islam

Mujib Amino Z islam

Kanalga Telegram’da o‘tish

📈 Telegram kanali Mujib Amino Z islam analitikasi

Mujib Amino Z islam (@mujibbinislam) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 14 469 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 997-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 343-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 14 469 obunachiga ega bo‘ldi.

29 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -95 ga, so‘nggi 24 soatda esa -7 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 16.91% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 8.60% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 2 447 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 245 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 18 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Kanal uchun tavsif kiritilmagan.

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 30 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

14 469
Obunachilar
-724 soatlar
-347 kunlar
-9530 kunlar
Postlar arxiv
photo content
+1

photo content
+9

photo content
+9

photo content
+9

የወደፊትን ዛሬ የሚገነባ መሪና አመራር፤ ዶ/ር ረሻድ ከማል ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ Mujib Amino የማንኛውም የልማት ተቋም ስኬት የሚለካው በሚገነባቸው ፕሮጀክቶች ብዛት ብቻ አይደለም፤ ተቋሙ የሚገነባው ተቋማዊ አቅም፣ የሚያዳብረው የአመራር ባህል፣ የሚፈጥረው የሰው ኃይል ብቃት እና ለህብረተሰቡ የሚያመጣው ዘላቂ ጥቅምም ነው። በዚህ መለኪያ መሠረት፣ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ባለፉት ዓመታት ያከናወነው የተቋማዊ ለውጥ ከተለያዩ ግዙፍ ሀገር በቀል ተቋማት ውስጥ ሊጠቀስ የሚችል ወርቃማ ሂደት ነው። የኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ መድረክ የዓመታዊ ሪፖርት ማቅረቢያ ብቻ አይደለም፤ ያለፈውን በማጠናከር የወደፊቱን በማቀድ የሚጓዝ የአመራር ባህል መገለጫ ነው። እቅድን ማውጣት፣ አፈጻጸሙን መለካት፣ ጉድለቶችን መለየትና እንደገና ማሻሻል የሚችል ተቋም የረጅም ጊዜ ውጤት የማስመዝገብ አቅም ያለው መሆኑን ያሳያል። በዚህ ሂደት ዶ/ር ረሻድ ከማል ያሳዩት የአመራር አቅጣጫ ተቋሙን ከዕለታዊ የሥራ እንቅስቃሴ በላይ ወደ ራዕይ ተኮር አመራር ለማሸጋገር የታሰበ መሆኑን ከቀረቡት መግለጫዎች መረዳት ይቻላል። የተቋማት ስኬት የአንድ ግለሰብ ስኬት ሳይሆን የራዕይ፣ የቁርጠኝነት፣ የቡድን ሥራ እና የመንግሥት ድጋፍ ውጤት ነው። የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ባለፉት ዓመታት ያሳየው የለውጥ ጉዞ፣ የሪፎርም አተገባበር፣ የእቅድ ተኮር አመራር እና የወደፊት የቤት ልማት ራዕይ በቀጣይነት ሊጠናከር የሚገባው ተቋማዊ አቅጣጫ መሆኑን ያመለክታል። ከዚህ አንፃር፣ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ረሻድ ከማል እየመሩት ያለው የለውጥ ጉዞ እና የተቋማዊ ሪፎርም እንቅስቃሴ የተገኙትን ውጤቶች በተጨባጭ መለኪያዎች እየተገመገመ የሚቀጥል ከሆነ፣ መንግሥትም እንዲህ ዓይነቱን የተቋማዊ አመራር ማበረታታት፣ አስፈላጊውን የፖሊሲና የተቋማዊ ድጋፍ መስጠት፣ እንዲሁም ለተመዘገቡ ውጤቶች ተገቢ እውቅና መስጠት ለሌሎች የህዝብ ተቋማትም አበረታች ምሳሌ ሊሆን ይችላል። ስኬታማ የተቋማዊ ሪፎርም እና የልማት አመራር በቀጣይነት እንዲጠናከር የሚያስፈልገው ሽልማት ብቻ ሳይሆን፣ የበለጠ የሥራ ነፃነት፣ ተቋማዊ ድጋፍ፣ የፋይናንስ አቅም እና ለረጅም ጊዜ ዕቅዶች የሚያስፈልጉ ምቹ ሁኔታዎች መፍጠር ነው። ይህ ሲሆን የተቋሙ የወደፊት የቤት ልማት ራዕይ በተሻለ ሁኔታ ወደ ተግባር የመቀየር እድሉ ይጨምራል። በመሆኑም የለውጥ አመራሮችን በተጨባጭ ውጤታቸው መሠረት ማበረታታት፣ እውቅና መስጠት እና የበለጠ የመስራት እድል መፍጠር የአንድ ግለሰብን ስኬት ከማጎልበት በላይ በመላው የህዝብ አገልግሎት ሥርዓት ውስጥ የውጤት፣ የተጠያቂነት እና የላቀ አፈፃፀም ባህልን ለማጠናከር ያስችላል። ይህ ደግሞ በመጨረሻ ተጠቃሚው ህዝብ የተሻለ አገልግሎት እንዲያገኝ እና የሀገሪቱ የልማት ግቦች በተሻለ ፍጥነት እንዲሳኩ አስተዋጽኦ ያበረክታል። የተቋማዊ ሪፎርም ማዕከል በኮርፖሬሽኑ የተተገበረው የሪፎርም ሥራ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግበዋል፣ የለውጥ ፕሮግራሞች በሰነድ ላይ ብቻ የቀሩ ሳይሆን ወደ አሠራር እንዲወርዱ ጥረት መደረጉን ያሳያል። በዘመናዊ የህዝብ ተቋማት አመራር ውስጥ የሪፎርም ትርጉም የሥራ ፍጥነትን ማሳደግ፣ የተጠያቂነት ሥርዓትን ማጠናከር፣ የአገልግሎት ጥራትን ማሻሻል እና ለውጤት ቅድሚያ መስጠት ነው። የፋይናንስ ጥንካሬ እና ዘላቂነት የተቋሙን ገቢ ማሳደግ፣ የሀብት አስተዳደርን ማጠናከር እና ለቀጣይ ፕሮጀክቶች የሚያስፈልገውን የፋይናንስ መሠረት መፍጠር በማንኛውም የልማት ተቋም ውስጥ ወሳኝ ጉዳይ ነው። በዚህም ረገድ ትኩረት መደረጉ ግልፅ ነዉ፤ ይህም የረጅም ጊዜ ዕቅዶችን ለማስፈጸም አስፈላጊ መሠረት ነው። የሰው ሀብት፤ የለውጥ ዋና ኃይል ተቋማት የሚቀየሩት በሰዎች ነው። ስለዚህ ሰራተኞችን ማብቃት፣ የትብብር ባህልን ማጎልበት፣ የውጤት ተኮር አስተሳሰብን ማስረጽ እና ቀጣይ ትውልድ መሪዎችን ማፍራት ዘላቂ ለውጥ የሚያመጡ መሠረታዊ ጉዳዮች ናቸው። ዘመናዊ አሠራርና ተወዳዳሪነት የዘመናዊ አሠራር ሥርዓት ማለት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ብቻ ሳይሆን፣ የውሳኔ አሰጣጥን ማፋጠን፣ የመረጃ ፍሰትን ማሻሻል፣ የአገልግሎት ጥራትን ማሳደግ እና የተቋሙን የውስጥ ቅንጅት ማጠናከር ጭምር ነው። እነዚህ በረጅም ጊዜ የተቋሙን ተወዳዳሪነት ሊያጠናክሩ ይችላሉ። 50 ዓመታትን ወደ አዲስ ምዕራፍ “በአዲስ ምዕራፍ ለተሻለ ነገ” በሚል መሪ ሃሳብ የተከበረው የ50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል ያለፈውን በማክበር ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱ የተሻለ አቅጣጫ ለመቅረጽ የተጠቀመበት አጋጣሚ ነበር። ከጥንካሬዎች ቀጣይነት መውሰድና ከክፍተቶች መማር የሚለው መርህ የተሻለ ተቋማዊ ባህልን ያመለክታል። የቤት አቅርቦት፤ የተቋሙ ዋና ተልዕኮ “የቤት አቅርቦት ፍላጎትን በዘላቂነት ለመመለስ በትኩረት እንሰራለን” የሚለው መልዕክት የተቋሙ ራዕይ በመሠረታዊ የህዝብ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ መሆኑን ያሳያል። የመኖሪያ ቤት ችግር የከተማ ልማት፣ የኢኮኖሚ እድገት እና የማህበራዊ መረጋጋት ጋር በቀጥታ የተያያዘ ስለሆነ፣ በዚህ ዘርፍ ዘላቂ መፍትሄ ማፈላለግ የረጅም ጊዜ የልማት ራዕይን ያሳያል። የትብብር አመራር የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ከመንግሥት፣ ከግሉ ዘርፍ፣ ከፋይናንስ ተቋማትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅርብ ትብብር የሚሰራ ዘርፍ ነው። ስለዚህ የተጠቀሰው የአጋርነት ጥሪ የተቋሙን ችግሮች በጋራ የመፍታት አቅጣጫ ያንጸባርቃል። የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የተቋማዊ ለውጥ ጉዞ የሪፎርም፣ የእቅድ ተኮር አመራር፣ የሰው ኃይል ልማት እና የረጅም ጊዜ የቤት አቅርቦት ራዕይ ላይ ያተኮረ መሆኑን ያመለክታል። ተቋሙ የ2018 አፈጻጸምን በመገምገም እና የ2019 እቅዱን በማዘጋጀት የሚያሳየው አካሄድ፣ የተቋማዊ መሻሻል ሂደት በቀጣይነት እንዲቀጥል የሚያግዝ መሠረት መሆኑን ያሳያል። Abiy Ahmed Ali Federal Housing Corporation - Ethiopia Worku Gachena-ወርቁ ጋቸና

photo content
+1

የሕግ መዘግየት የሁከት መነሻ ነዉ! •የዚህን ፓርቲ ዋና አመራሮች ለፍርድ ታቀርባላችሁ ወይስ? ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ Mujib Amino የዘመናዊ መንግሥት ዋና ተግባር የዜጎቹን መብት ማስከበር ብቻ ሳይሆን የሕዝብን ደህንነት፣ ሰላምና መረጋጋት መጠበቅ ነው። ይህ ኃላፊነት በተለይ መረጃ በሰከንዶች ውስጥ ዓለምን በሚያዞርበት የዲጂታል ዘመን ይበልጥ ከባድ ሆኗል። የሐሳብ ነፃነት የዴሞክራሲ መሠረታዊ እሴት ቢሆንም፣ ያ ነፃነት ወደ ጥላቻ፣ ወደ ሁከት ወይም ወደ ዓመፅ ለመቀስቀስ የሚውል መሣሪያ ሲሆን ወደሕግ ማስከበር ምዕራፍ መሸጋገሩ የግድ ይሆናል። በሕግ የሚመራ መንግሥት ውስጥ የሐሳብ ነፃነትን እና የሕዝብ ደህንነትን በሚዛን መጠበቅ እጅግ አስፈላጊ ነው። የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ሀሳብን በነፃነትን የመግለጽ መብትን ያረጋግጣል። ይሁን እንጂ ማንኛውም መብት ከኃላፊነት እኩል እንጂ ብልጫ የለዉም ወይንም ተመጣጣኝ መብትና ግዴታዎች አሉት። የሌሎችን መብት፣ የሕዝብ ሰላምና የሀገር ደህንነት የሚጎዱ ተግባራት በሕግ ሊገደቡ ይችላሉ። ይህ መርህ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በብዙ የዓለም ሀገራት የሚንፀባረቅ ሕጋዊ መሠረት ነው። የመብት ጥበቃ እና የሕዝብ ደህንነት ተቃራኒ ሳይሆኑ ተደጋጋፊ እሴቶች መሆናቸውን ልብ ይሏል። በ1960ዎቹ ብቅ ያሉት ባለ አፍሮ ፀጉራም ወጣቶች፣ በማርክስ፣ በኤንግልስ እና በሌሊን አስተምህሮቶችና ፍልስፍናዎች የተራቀቁት የኮሚኒስት እና የሶሻሊዝም ርዕዮት የሚያስተጋቡት እኒያ ወጣቶችን በጠማማና ጭካኔ በተሞላበት የፓለቲካ ወጥመድ ዉስጥ አስጥሞ የደም ፓለቲካን ያፋፋመዉ ኢሕአፓ አሁንም ትዉልድን ተሻግሮ ነጭ ሽብርን ለማፋፋም እየሰራ ለመሆኑ በየማሕበራዊ ሚዲያው ተደጋጋሚ ና የለየለት ብጥብጥና ደም የማፋሰስ እቅድ ሲያንፀባርቁ እየተስተዋሉ ነዉ:: አንዴ በሃይማኖት ሌላ ጊዜ ዘር ሲያሻዉ ሕዝብን ለሁከትና ብጥብጥ በማነሳሳት የሀገርን ሰላምና ደህንነት አደጋ ዉስጥ በሚጥል መልኩ በግልፅም በስውርም መልእክቶችን ሲያስተላልፉ ስለምን በዝምታ ታለፈ? ሕግ በወቅቱ፣ በፍትሐዊነት እና በእኩልነት ሲተገበር ዜጎች በተቋማት ላይ እምነት ያድራሉ፤ ሰላምም ይጠናከራል። በተቃራኒው መንግሥት ሕግን ማስከበር ሲዘገይ ወይም የሕግ ጥሰቶች ሳይታረሙ ሲቆዩ፣ የሚፈጠረው ችግር ከአንድ ፓለቲካ ፓርቲ ወይም ከአንድ ክስተት በላይ ሆኖ መላውን ማኅበረሰብ ይጎዳል። በመጀመሪያ የሚጎዳው የሕዝብ በሕግ ላይ ያለው እምነት ነው። ዜጎች ሕግ በሁሉም ላይ በእኩል እንደማይተገበር ሲሰማቸው፣ ቅሬታቸውን በሕጋዊ መንገድ ከማቅረብ ይልቅ ሌሎች መንገዶችን የመፈለግ አደጋ ይጨምራል። ይህ ደግሞ የማኅበራዊ መተማመንን ያዳክማል። ሁለተኛ፣ ሕግን መዘግየት ለሌሎች የተሳሳተ መልዕክት ሊሰጥ ይችላል። ሕግ ጥሰት በወቅቱ ካልታረመ፣ አንዳንድ ሰዎች ያለ ተጠያቂነት መቀጠል እንደሚቻል ሊያስቡ ይችላሉ። ይህ ሁኔታ የሕግ አክብሮትን ሊያዳክም ይችላል። ሦስተኛ፣ ለሕዝብ ደህንነት አደጋ የሚፈጥሩ ድርጊቶች በወቅቱ ካልተያዙ ችግሩ ሊስፋፋ ይችላል። ይህ በተለይ የዓመፅ ጥሪዎች፣ የተደራጁ የወንጀል ተግባራት ወይም በቀጥታ ወደ ጥቃት የሚያነሳሱ ድርጊቶች ሲሆኑ፣ በሕግ መሠረት ፈጣን እና ፍትሐዊ ምላሽ መስጠት የሕዝብን ደህንነት ለመጠበቅ ጠቃሚ ነው። ታሪክ የሚያሳየን አንድ አስፈላጊ እውነት አለ፤ ቃላት ማህበረሰብን ሊገነቡም ሊያፈርሱም ይችላሉ። በ1930ዎቹ በጀርመን የተስፋፋው የጥላቻ ፕሮፓጋንዳ በማህበረሰቡ ውስጥ ጥላቻን በማባባስ ወደ አስከፊ የሰብዓዊ ጥፋት አምርቷል። ይህ ታሪክ የቃላት ኃይል በሕግ ካልተመራ ምን ያህል አደገኛ ሊሆን እንደሚችል ያስታውሰናል። በ1994 በሩዋንዳ የተከሰተው የዘር ፍጅትም በተመሳሳይ መልኩ በጥላቻ ንግግርና በዓመፅ ቅስቀሳ የተቀደመ ነበር። በዚያ ወቅት የተሰራጩ መልዕክቶች ሰዎችን ከጎረቤቶቻቸው ጋር እንዲጋጩ አድርገዋል። ይህ ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ከታሪክ የተማረው ከባድ ትምህርት ነው፤ የጥላቻ ቅስቀሳን በቀላሉ ማለፍ ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍል ይችላል። ኢትዮጵያም በታሪኳ ውስጥ ከፖለቲካ ውጥረቶች፣ ከዘርና ከማንነት ግጭቶች የተነሳ ከባድ ፈተናዎችን አሳልፋለች። ከ1966 አብዮት በኋላ የነበሩት የፖለቲካ ግጭቶች፣ በ1997 ከምርጫው በኋላ የተፈጠሩ ውጥረቶች፣ እንዲሁም በተለያዩ ወቅቶች በሐሰተኛ መረጃና በአነሳሽ መልዕክቶች የተባባሱ ግጭቶች ለሀገሪቱ ሰላምና ለዜጎች ሕይወት ከባድ ዋጋ አስከፍለዋል። ከእነዚህ ታሪካዊ ተሞክሮዎች መማር የወደፊቱን ሰላም ለማስጠበቅ አስፈላጊ ነው። ዘላቂ ሰላም የሚገነባው በፍትሕ፣ በሕግ የበላይነት እና በተጠያቂነት ነው። የሕዝብን ደህንነት በአደጋ ላይ የሚጥሉ የሁከት ቅስቀሳዎች በሕግ ሲገቱ የሚጠበቀው መንግሥት ብቻ ሳይሆን የዜጎች ሕይወት፣ የማህበረሰብ አንድነት እና የሀገር መረጋጋት ነው። የሕግ ጥንካሬ የሚለካው በፍትሐዊነቱ ሲሆን፣ የሀገር ጥንካሬ ደግሞ በሰላም እና በአንድነት ነው። ስለዚህ ስለምና አንድነታችን ይረጋገጥ ዘንድ፤ በቅድሚያ ለሕዝባችን ሰላም ቀጥሎም ለሕግ የበላይነትና የዚህን ፓርቲ ዋና አመራሮች ለፍርድ ታቀርባላችሁ ወይስ? Ethiopian Federal Police Addis Ababa Police FDRE Ministry of Justice/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር

photo content

የምክክር ጉባኤው የነገዋ ኢትዮጵያ በምን ዓይነት መሠረት ላይ መገንባት እንዳለባት ሁላችንም ቆም ብለን እንድናስብ አድርጎናል - ኡስታዝ አህመዲን ጀበል ****** አሁን በሂደት ላይ ያለው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በሀገራችን ለዘመናት ሳይፈቱ የቆዩ ታሪካዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ልዩነቶችን ለመፍታት ትልቅ ዕድል መፍጠሩን የጉባኤው ተሳታፊ የሆኑት ኡስታዝ አህመዲን ጀበል ገለጹ። ኡስታዝ አህመዲን ስለጉባኤው ሂደት በሰጡት አስተያየት፣ ምክክሩ ሁሉንም ችግሮቻችንን በአንዴ ሊያራግፍልን ባይችል እንኳ፣ አጀንዳ ያለው ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል በመድረኩ በመገኘት በዋና ዋና ሀገራዊ ችግሮቻችን ላይ ተወያይቶ የመፍትሔው አካል መሆን እንደሚገባ አሳስበዋል። የምክክር ጉባኤው በተለይ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ፣ የብሔር ብሔረሰቦች እና በአጠቃላይ የዜጎች የውክልና ጥያቄዎች የሚመለሱበትን እና የሕዝቦች አብሮነት የሚጠናከርበትን ማዕቀፍ ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ኡስታዝ አህመዲን ገለጻ፣ በምክክር ጉባኤው እስከ አሁን የተካሄዱት ውይይቶች ሁለት ዋና ዋና አዎንታዊ ፋይዳዎችን አስገኝተዋል፦ አንደኛ፣ ከተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች የተወከሉ ተሳታፊዎች ያሏቸውን ቅሬታዎች በመጋራት እርስ በርስ እንዲተዋወቁና አንዱ የሌላውን ብሶት እንዲረዳ ጉባኤው ሰፊ በር ከፍቷል። በዚህም፣ ቀደም ሲል በየአካባቢው ታፍነው የቆዩ ቅሬታዎች ይፋ በመውጣታቸው የጋራ ግንዛቤ መፍጠር ተችሏል። ሁለተኛ፣ ለረጅም ጊዜ ሳይፈቱ የቆዩ አከራካሪ የሆኑ ጉዳዮችም ጠረጴዛ ላይ ቀርበው ውይይት እንዲደረግባቸው አስችሏል። ውይይቱ ሙሉ መፍትሔ ባያመጣ እንኳ፣ በልዩነቶቹ ዙሪያ መነጋገር መቻሉ በራሱ የመግባባት መንፈስ ይፈጥራል ብለዋል። በተጨማሪም የምክክር ሂደቱ የነገዋ ኢትዮጵያ በምን ዓይነት መሠረት ላይ መገንባት እንዳለባት ሁሉም ወገን ቆም ብሎ እንዲያስብ መንገድ የከፈተ መሆኑን አስገንዝበዋል። በአጠቃላይ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ሁሉንም ወገኖች የመፍትሔ አካል በማድረግ ኢትዮጵያዊ አብሮነትን ለማጠናከር በሚያስችል ተስፋ ሰጪ ሂደት ላይ መሆኑን ኡስታዝ አህመዲን ጀበል ገልጸዋል። በመሐመድ ፊጣሞ #Ethiopia #NationalDialogue #NationalConsensus #EBC

አህመዲን ጀበል https://vt.tiktok.com/ZSXqmNaye/

ጧሪ ያጡ የወንድማችንን ቤተሰቦችና ጭቅላ ሕፃኑን በገንዘብ እንደግፍ! ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ በቅርቡ ሰኔ 28 ቀን 2018 በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ል
+3
ጧሪ ያጡ የወንድማችንን ቤተሰቦችና ጭቅላ ሕፃኑን በገንዘብ እንደግፍ! ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ በቅርቡ ሰኔ 28 ቀን 2018 በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ቡልቡላ አቦ መሻገሪያ ድልድይ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ወንድማችን ዘይኑ ፈድሉ ጨካኞች በጩቤ ደረቱን በመውጋት ህይወቱ እንዲያልፍ አድርገዋል። ፖሊስ ግዳያዉን ፈጽመዋል በሚል 11 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል ወደፍርድ ቤት አቅርቧል። ሟች ወንድማችን በስሩ የሚያስተዳድራቸዉ ቤተሰቡና በግድያዉ ማግስት የተወለደዉን ልጁና ባለቤቱን ጥሎ አልፏል። በተለይም አዲስ የተወለደዉ ጨቅላ ሕፃን ከሁላችንም ድጋፍና አብሮነት ይፈልጋል። አዲሱ የቲም ሕፃን ወደ ዓለም ሲመጣ የአባቱን ፍቅር ባያገኝም፣ የማህበረሰቡን ፍቅርና ድጋፍ እንዲያገኝ የማድረግ የሁላችንም ኃላፊነት በመሆኑ በአራስ ባለቤቱ ስም የተከፈተ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሒሳብ ቁጥርና የቴሌብር ቁጥር ከታች ያያዝን በመሆኑ ሰደቃ እንድታደርጉ በአላህ ስም እንጠይቃለን።፦ 1000782025426 Hayat kedir husen 0959314114 telebirr

photo content

ትናንሾቹ ዲጂታል አምባገነኖች! ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ _Mujib Amino_ አምባገነንነት ሁልጊዜ በመንግሥት ወይም በታጠቀ ኃይል ብቻ አይገለጥም። በዘመናዊ ማህበረሰብ ውስጥ አምባገነንነት በግለሰቦች፣ በፖለቲካ ቡድኖች፣ በማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች፣ በአክቲቪስቶች እና በተለያዩ ቡድኖች ውስጥም ይታያል። የዚህ አይነት አምባገነንነት ዋና መሣሪያው ጠመንጃ ሳይሆን የሀሳብ ነፃነትን ማፈን ነው። •ሀሳብን በእዉቀት ፈንታ በስድብ መመለስ የዲሞክራሲ መሠረት የሀሳብ ውድድር ነው። ነገር ግን ሀሳብን በምክንያት ለመመለስ ፈቃደኝነት ሲጠፋ፣ በስድብ፣ በማጥላላት፣ በግለሰብ ጥቃት እና በስም ማጥፋት የሚተካ ይሆናል። ይህ የሀሳብ ድክመት ብቻ ሳይሆን የዲሞክራሲ ባህል እየተሸረሸረ መሆኑንም ያሳያል። ለዚህ ማሳያዎች በእውነት ላይ ምስረታዉን ያደረገ ተጨባጭ መፍትሄና ጥያቄዎቻችንን በምናቀርብበት የማህበራዊ ድረገፅ መድረክ የሚዘንቡት ስድቦች ፣ ማጥላላት ፣ ጥላቻና የጥፋት መንገድ ምንም እንኳ ቦታ ባንሰጣቸዉም የሆነ ቡድን ምን ያህል የሞራል ልዕልናዉ እንደተቀነጨረ ፣ የስነ ምግባር ኃላፊነቱ እንደወደቀ ፣ ከራሱም ጋር ጭምር እንደማይግባባ ከስድብ ውጪ ስለሚያወራቸዉ ነገሮች እንኳ ዋጋ ቢስ እዉቀት መጨበጡ ነዉ:: ሀሳብን በእዉቀት መተቸትና ማስተካከል ተግባቦትን በመፍጠር በሀሳብ ልዕልና የሚገዛ ማህበረሰብን ለመፍጠር ሚና ቢኖረዉም ከራሳቸዉ ፍላጎት ውጪ ለሌሎች ድንቁርናን የመረጡ ቡድኖችን በዝምታ ማለፍ ሳይሆን ታግሎ ማሸነፍ አሊያም ከትራኩ ውጪ እንዲቆሙ ማድረግ አንዱ የመፍትሄ አቅጣጫ ይሆናል:: እነርሱን መተዉ ንፁሀንን መበከል ይሆናል:: •የሐሰት አካውንቶች እና የፍርሃት ፖለቲካ ማህበራዊ ሚዲያ ለውይይት ታላቅ እድል ቢፈጥርም፣ የሐሰት መለያዎችን በመጠቀም ሌሎችን ማስፈራራት፣ ማሳደብ ወይም ዝም እንዲሉ ጫና ማሳደር የተለመደ ችግር ሆኗል። ዓላማው ብዙ ጊዜ ሀሳብን ማሸነፍ ሳይሆን ሀሳብ የሚያቀርበውን ሰው እንዲፈራና እንዲቆም ማድረግ ነው። የሀሰት አካዉንት መክፈት ለሀሰት ትርክት ፣ ለዉሸት ስርጭት ፣ ለጥላቻ ፣ ለፌዝ ፣ ለማጥቃት ፣••• ዝግጅት ማድረግ መሆኑን አያጠራጥርም:: ጥቂት የማይባሉ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ሀሰተኛ ምስሎችንና ስሞችን በመጠቀም ግለሰብ ላይ ብቻ ሳይሆን ማህበረሰብ ላይም ጭምር ጦርነት ሲያዉጩ ፣ ብጥብጥ ሲጠምቁ ፣ •••ይታያል :: ይሕ ጨቋኝና ከባህልና ወግ ያፈነገጠ ሀሳቦቻቸዉ በማይታዩና በማይታወቁ ምስልና ስም ቢደበቁም ግና የጥላቻ ሀሳቡና ብዕሩ ባለቤት እንዳለዉ እሙን በመሆኑ ለሚወነጨፉ የጥላቻ ቀስቶች ጋሻ ማበጀት ይገባል:: ቀስቶቹ ደካሞችን እንዳያጠቁ! •የድርብ መለኪያ ችግር በፖለቲካና በማህበራዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ብዙ ጊዜ የሚታየው ችግር ለራስ ነፃነት መጠየቅና ለሌሎች ግን ያንኑ መብት አለመቀበል ነው። የሀሳብ ነፃነት የሚለካው የምንስማማበትን ሀሳብ በመፍቀድ ሳይሆን፣ የማንስማማበትን ሀሳብ እንኳ እንዲገለጽ በመፍቀድ ነው። እነርሱ ስለሚጠይቋቸዉ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ፣ ስለሚራመዷቸዉ እርምጃዎች ፣ ስለዉሏቸዉ ፣ ስለፍላጎታቸዉና ሕልማቸው ጭምር ሲፅፉና ሲገልፁ በመልካም ከመመልከት ወይንም በዝምታ ከማለፍ ውጪ(እኛን በተመለከተ ካላነሱ) አንዳችም ባንልም ፤ በሕዝበ ሙስሊሙ የውስጥ ጉዳይ ጭምር እንዲህ ካልሆነልን ብለዉ ኩፊታና ሻል ከሙሰቢሃ ጋር እየጎተቱ ሊመርጡልን መሻታቸዉ ከ2004 ቱ የኢህአዴግ መንግስት የአህባሽ ጠመቃ ጋር ያመሳስላቸዋል:: እነርሱ ስለእኛ መጅሊስ ያቦካሉ ይጋግራሉ:: በራሳችን ተቋም አስተያየት እንኳ እንዳንሰጥ ፍላጎታቸዉን በየሀሳብ መስጫው ሳጥን ዉስጥ ይንፀባረቃ:: እኛ ጣልቃ ሳንገባ ብቻ ሳይሆን አይመለከተንም ብለን በቆምንበት ተጨባጭ እነርሱ ጥያቄም ይሁን ንቅናቄ በሚያራምዱበት ልክ በራሳችን ጎጆ ያጨድነውን ጎተራ ዘርፈን እንብል የሚሉ ቀማኛም ጭምር መሆናቸው ልብ ይሏል:: የፍትህና የእኩልነት ጥያቄ እነርሱ በተስተናገዱበት ልክ ሌላው እድል ማግኘቱን የበታችነት ስሜት መፍለቂያ ምንጭ ያደርጉታል:: እነርሱ በተስተናገዱበት ሜዳ መጫወት የሽንፈት ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ የሀገሪቱ ዉድቀት ለማድረግ ይጥራሉ:: የበጀነን አካሄድ መምረጥ የእኛ እንጂ የእናንተ ፍላጎት አይሆንም! •የተደራጀ የማጥላላት ዘመቻ የፍትህና በተለይ የእኩልነት ሀሳብ ሲቀርብ በተደራጀ መልኩ በጥላቻ የታወረ ወረራ ሊገጥመን ይችላል። ተመሳሳይ ቃላትን በመድገም፣ በስም በማጥፋት ወይም በስድብ ማጥለቅለቅ ሌሎች ሰዎች ያንን ሀሳብ እንዳይዳስሱ የፍርሃት አካባቢ የሚፈጠርባቸዉ መስመሮች ይስተዋላሉ። ይህ የውይይት ሂደትን ይዳክማል፣ ለውጥ ና እውነተኛ እሳቤን ይገድላል ፣ ለሀሰትና ለደቦ ፍርድ ያዘነብላል•••ወዘተ ይህን ባለዘመቻ ቡድን ቆሞ መመልከት ና ለጥላቻ ቀስቶቹ ደረት መስጠት ሳይሆን የእዉነትና የእኩልነት ዘመቻ በማስተባበር ፣ የሀሰት ቀስትን በፍትሕ ጋሻ በመመከት ፣ ለጥላቻ ፍቅርና የእዉነት መንገድን በማመላከት በረሃ ዉስጥ እንደተገኘ በረዶ አቅልጦ ማሸነፍ እንደሚቻል እሙን ነዉ:: የዲጂታል ሚዲያ መድረኮች ለሚሊዮኖች ድምፅ ሰጥተዋል። ይህ የዴሞክራሲ ባህል እድገት ትልቅ እድል ነው። ሆኖም በተመሳሳይ ጊዜ የሀሰት መረጃ፣ የጥላቻ ንግግር፣ የውሸት መለያዎች እና የተደራጁ የስም ማጥፋት ዘመቻዎች እንዲስፋፉ አስችለዋል። በዚህ ሁኔታ ዜጎች ማንኛውንም መረጃ ሳይመረምሩ መቀበል ሳይሆን ከተለያዩ ምንጮች ማረጋገጥ፣ ማስረጃን መፈለግ እና ሂሳዊ አስተሳሰብን ማዳበር ይኖርባቸዋል። እንዲያ ከሆነ ትናንሾቹን አምባገነኖች ቦታ ያጣሉ ፣ ይጣላሉም!

photo content

የብሔራዊ ምክክር ጅምር፦ ለዘላቂ ሰላም የተከፈተ በር ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ Mujib Amino ኢትዮጵያ በረጅም ታሪኳ ውስጥ ብዙ ፈተናዎችን አልፋለች። ከእነዚህ ፈተናዎች መካከል የፖለቲካ አለመግባባት፣ የማንነት ግጭቶች፣ የመተማመን እጦትና የጦርነት አዙሪት በሀገሪቱ ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድረዋል። እንደዚህ ያሉ ጥልቅ ችግሮች በኃይል ወይም በመከፋፈል ሳይሆን በውይይት፣ በመደማመጥና በጋራ መፍትሄ ፍለጋ እንደሚፈቱ የብዙ ሀገራት ተሞክሮ በግልጽ ያሳያል። በደቡብ አፍሪካ የአፓርታይድ ስርዓት መጨረሻ የተከተለው የCODESA ውይይት ሰላማዊ የፖለቲካ ሽግግርን አስቻለ፤ በኬንያ ደግሞ ከ2008 የምርጫ ቀውስ በኋላ የተደረገው የብሔራዊ ስምምነት የግጭት መቀጠልን አቆመ፤ በቱኒዚያም የ2013 የብሔራዊ ውይይት አራት ተቋማት የፖለቲካ ቀውስ እንዳይባባስ አግዘው ሀገሪቱን ወደ ሰላማዊ ሽግግር መልሰዋል። እነዚህ ምሳሌዎች ውይይት በቃል ብቻ ሳይሆን በተግባርም ውጤት እንደሚያመጣ ያሳያሉ። በዚህ አውድ ውስጥ የተጀመረው ብሔራዊ ምክክር የተለያዩ ሀሳቦችን በአንድ ማዕድ ላይ በማሰባሰብ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር የሚደረግ ጥረት ነው። እንደማንኛውም ትልቅ አገራዊ ሂደት፣ ይህም የተለያዩ ድጋፎችንና ትችቶችን ሊያስነሳ ይችላል። የተለያዩ ፖለቲካዊ ኃይሎች ሂደቱን በተለያየ መንገድ ሊያዩት ይችላሉ፤ ይህም በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ የተለመደ ነው። ነገር ግን ልዩነቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲቀርቡና ውይይቱ እንዲቀጥል መደገፍ ለሀገር ጥቅም የሚበጅ ነው። በቱኒዚያ የብሔራዊ ውይይት አራት ተቋማት የተሳካው ምክንያት አካታችነት፣ ግልጽነት እና የሁሉም ወገኖች ተሳትፎ ስለነበረ ነው፤ በኬንያም የተፈጠረው የስምምነት መንግሥት የምርጫ ስርዓት ማሻሻያዎችን አስከትሎ የቀጣይ ግጭት እድልን ቀንሷል። ይህ የተግባር ማስረጃ ብሔራዊ ምክክር በትክክል ሲመራ የሚያመጣው ለውጥ እውነተኛ መሆኑን ያሳያል። ብሔራዊ ምክክር ፍጹም ውጤት ይዞ እንደሚወጣ ማንም አስቀድሞ ማረጋገጥ አይችልም። ሆኖም የመነጋገር ባህልን ማጠናከር፣ የተለያዩ እይታዎችን ማዳመጥና በጋራ መፍትሄ መፈለግ ከግጭት ይልቅ የተሻለ አማራጭ መሆኑ በብዙ ሀገራት ተሞክሮ ተረጋግጧል። የዓለም ባንክ፣ የተባበሩት መንግሥታት እና ሌሎች የልማት ተቋማት በተደጋጋሚ የሚያሳዩት ነገር አንድ ነው፤ ግጭት የቀነሰባቸው ሀገራት በኢኮኖሚ ማገገም፣ በትምህርት ቀጣይነት፣ በጤና አገልግሎት መሻሻል እና በኢንቨስትመንት መሳብ የተሻለ ውጤት ያሳያሉ። ስለዚህ ሰላም ያለበት ሀገር ብቻ ነው ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት፣ ለጤና፣ ለኢንቨስትመንትና ለወጣቶች የሥራ እድል ሊፈጥር የሚችለው። በመሆኑም የብሔራዊ ምክክሩ ሂደት የተሻለ እንዲሆን ሐሳብ ማቅረብ፣ በገንቢ መንገድ መተቸትና ሁሉም ድምፆች በአግባቡ እንዲሰሙ መጠየቅ ጠቃሚ ነው። በደቡብ አፍሪካ የተካሄደው የሽግግር ውይይት የቀድሞ ግጭት እንዳይደገም የሚያግዝ የፖለቲካ መሠረት ፈጥሯል፤ በቱኒዚያም የሲቪል ማህበራት ተሳትፎ ውይይቱን ከፖለቲካዊ ግጭት ወደ ተግባራዊ መፍትሄ አመራው። ይህ ሂደት አካታች፣ ግልጽና ተዓማኒ እንዲሆን መስራት የሁሉም ባለድርሻዎች ኃላፊነት ነው። ኢትዮጵያ የጋራ ሀገራችን ናት። የወደፊት ትውልድ በሰላም፣ በፍትሕና በመተማመን የምትኖርባትን ሀገር ለመገንባት ውይይትን ከግጭት፣ መግባባትን ከመከፋፈል እና የጋራ ጥቅምን ከጠባብ ፖለቲካዊ ፍላጎቶች በላይ ማስቀደም ያስፈልጋል። የሌሎች ሀገራት ተሞክሮ የሚያሳየው አንድ ግልጽ እውነት አለ፤ ውይይት በራሱ መፍትሄ ባይሆንም መፍትሄ የሚያመጣ መንገድ ነው። ብሔራዊ ምክክር ግቡን እንዲመታ የሚያስፈልገው የሁሉም ወገኖች ተሳትፎ፣ መከባበርና ቁርጠኝነት ነው። ልዩነቶችን በውይይት የመፍታት ባህል እየጠነከረ በሄደ ቁጥር የሰላም፣ የአንድነትና የእድገት መሠረት ይበልጥ ይጠናከራል። ይህም ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለመጪው ትውልድም የሚተርፍ አዎንታዊ ቅርስ ይሆናል።

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን የቀድሞ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ከማል በድሪ ወደአኼራ ሔደዋል:: በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከ 1988 እስከ 2000 ፕሬዝዳንት በመሆን
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን የቀድሞ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ከማል በድሪ ወደአኼራ ሔደዋል:: በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከ 1988 እስከ 2000 ፕሬዝዳንት በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት ክቡር አቶ ከማል በድሪ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሐምሌ 08/2018 ከዚህ አለም በሞት እንደተለዩ ታውቋል፡፡ አሏህ በጀነተልፊርዶዉስ ይቀበልዎት። ቀብርዎን ብርሀን፣ ቀብርዎ የሰፋ፣ ቀብርዎ ያማረ፣ አኼራህ የተዋበ ይሁን። አሚን🤲 አሚን 🤲አሚን🤲 ለቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንመኛለን። የቀብር ስነ ስርዓቱ በዛሬው ዕለት ከቀኑ በ9 ሰዓት የሚፈፀም ይሆናል፡፡

photo content
+1

photo content
+9

Addis Ababa Police እናመሰግናለን!!! ወንድማችን ዘይኔ ፈድሉ በአፋልጉኝ ማስታወቂያ ሲፈለግ ቆይቶ በጭካኔ ተገድሎ መገኘቱን አሳውቀን እንደነበር ይታወቃል:: ጉዳዩንም ለአዲስ አበባ ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች አቅርበን የነበረ ሲሆን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጉዳዩን በጥልቀት በመመርመር አፋጣኝ እርምጃዎችን በመዉሰድ በቁጥጥር ስር አውሏል:: የግድያ ወንጀል የፈጸሙ 11 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ዝርዝር ጉዳዩን እንደሚከተለዉ ፖሊስ አቅርቧል:/ *** ሰኔ 28 ቀን 2018 በግምት ከለሊቱ 7:00 ሠዓት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ቡልቡላ አቦ መሻገሪያ ድልድይ እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ ነው የግድያ ወንጀሉ የተፈፀመው። በወቅቱ ማንነቱ ያልታወቀ ግለሠብ ከሳሪስ አቦ ወደ ኮዬ መሄጃ በሚገኝ መንገድ ድልድይ ስር ደረቱ ላይ በስለት ተወግቶ ህይወቱ አልፎ ተገኘ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የሰው መግደል ምርመራ፣ የክትትልና ኦፕሬሽን ቡድኑ በመቀናጀት የሟችን ማንነት ለማወቅ እና ወንጀል ፈፃሚዎችን ለመለየት ባደረገው ጥረት ወንጀሉ በተፈፀመ 48 ሠዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የሟችን ማንነትና እና ወንጀሉን ፈፅመዋል ያላቸውን እንዳለ ተሰማ፣ ኤርሚያስ አሰፋ፣ ያብስራ እንዳለ፣ ዘካሪያስ ለማ፣ ናትናኤል ግርማ፣ ተመስገን ተስፋዬ፣ ብሩክ ኤርሚያስ፣ ኢዮብ ጌታቸው፣ ላምሮት አረጋኸኝ፣ ኤልሻዳይ ዳዊት እና ኤዶሚያስ ወንድወሰን የተባሉ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገልጿል። ፖሊስ በተያዙት ተጠርጣሪዎች ላይ ባደረገው ምርመራ ሟች ዘይኑ ፈድሉ በመንገድ እየተጓዘ ባለበት ወቅት አንገቱን በመያዝና ደረቱን በጩቤ በመውጋት ህይወቱ እንዲያልፍ በማድረግ ይዞት የነበረውን ሳምሰንግ ስልክ ወስደዋል። የሟችን አስክሬን ኤርሚያስ አሠፋ በተባለው ግለሠብ የሠሌዳ ቁጥር ኮድ 3-B 83677 አ/አ ቪትስ ኮምፓክት ተሽከርካሪ ኮፈን ውስጥ በመክተት ሌሎቹ ተጠርጣሪዎች ደግሞ ኮድ 3-71724 አ/አ በሆነ ቪትስ ተሽከርካሪ በመሆን ተከታትለው በመሄድ የሟችን አስክሬን ድልድይ ስር ጥለውት መሄዳቸውን በምርመራ ወቅት ገልጸዋል። ተጠርጣሪዎቹ ወንጀሉን በፈጸሙ 48 ሠዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በፖሊስ እንደተያዙ እና በራሳቸው ፍላጎት ወንጀሉን እንዴት እንደፈፀሙ መርተው ማሳየታቸውን ከምርመራ ክፍሉ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ፖሊስ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ባደረገው ምርመራ የማስፋት ስራ ለወንጀሉ መፈፀሚያ የሚጠቀሙበት 2 ጩቤ፣ 3 ሽጉጥ መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ገልፆ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ምርመራው እንደቀጠለ ገልጿል። የሟች ዘይኑ ፈድሉ ቤተሰቦች በበኩላቸው በወንድማቸው ህልፈት እጅጉን ማዘናቸውን ገልጸው ፖሊስ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወንጀል ፈፃሚዎቹን በቁጥጥር ስር በማዋሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።