ቅዱሳት መጻሕፍት
Open in Telegram
በዚህ ቻናል 👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ:: 👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ:: 👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ። ⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️ @Holy_scriptures
Show more7 833
Subscribers
+724 hours
+357 days
+15630 days
Posts Archive
7 834
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“በበጎ ሥራ በመጽናት ምስጋናንና ክብርን የማይጠፋንም ሕይወት ለሚፈልጉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸዋል፤”
ሮሜ 2፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 834
⁉️ትወደኛለህን?
ምላሽ የሚያሻው የክርስቶስ ጥያቄ - ትወደኛለህን? (ዮሐንስ 21)
ይህን ጥያቄ ስናነብ ወደ አእምሮአችን በቶሎ የሚመጣው ምንድን ነው? ምናልባት ምን ዐይነት ጥያቄ ነው? ብለን እናስብ ይሆናል፤ ወይም ጥያቄው የአፍቃሪ ጥያቄ አንደሚሆን ልንገምት እንችላለን። አሊያ እንደዚህ ተብሎ ይጠየቃል ወይ? ብለን ልንጠይቅም እንችላለን። ጥያቄው ረጅም ጊዜ ዐብሮን ከኖረ ሰው፥ በጣም ከሚያውቀንና ከምናውቀው ሰው፥ ለምሳሌ፥ ከባለቤታችን ወይም ከጓደኛችን ቢመጣስ ምን ይሰማናል? ያለ ጥርጥር ምን አይቶብኝ ይሆን? ወይም ምን አይታብኝ ይሆን? ምን ሰምቶብኝ/ምን ሰምታብኝ ይሆን? የሚሉ ጥያቄዎችን ሊያጭርብን ይችላል።
ጥያቄው “አዎን እወድሃለሁ” የሚል ምላሽን ለማግኘት ወይም መወደድን ለማወቅ የተጠየቀ ጥያቄ አይደለም። ጥያቄው ከፍቅረኛ፥ ከትዳር አጋር ወይም ከጓደኛ የመጣ ሳይሆን ከጌታችንና ከመድኀኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ በተለይም ለጴጥሮስ የቀረበ ጥያቄ ነው። ሐዋርያው ዮሐንስ በወንጌሉ በ21ኛው ምዕራፍ አንደ ዘገበልን፥ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጴጥሮስን ሦስት ጊዜ ያህል “ትወደኛለህን?” ሲል ጠይቆታል።
እወድሃለሁ
“ትወደኛለህን?” የሚለው ጥያቄ ፍቅርን ለማወቅ ወይም ለማረጋገጥ የሚጠየቅ ጥያቄ ቢሆንም፥ ዮሐንስ እንደ ጻፈው ጥያቄው ከዚያ የሚያልፍ መልእክት አለው። በርግጥ ትወደኛለህን? ተብሎ ሲጠየቅ ምላሹ አልወድህም የሚል አይሆንም። በክርስቶስና በጴጥሮስ መካከል የነበረውን ግንኙነት መለስ ብለን ስናስታውስ፥ ጌታ ደቀ መዛሙርቱን በሥጋ ሊለያችሁ ነው፤ ልሄድ ነው ብሎ በነገራቸው ጊዜ፥ ጴጥሮስ ‘ተለይተኸን ወዴት ትሄዳለህ? የትም ብትሄድ ዐብሬህ እሄዳለሁ፤ ሞት እንኳ ቢመጣ ከአንተ አልለይም’ ያለው ሰው ነበር (ዮሐ. 13፥36-38)። ጌታ ለጴጥሮስ ንግግር የሰጠው ምላሽ፥ ‘እንኳ ነፍስህን ልትስጠኝ፥ ዶሮ ከመጮኹ በፊት ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ’ የሚል ነበር።
ፍቅር እንዴት ይገለጣል?
እንደሚታወቀው በዓለም ላይ የፍቅር መገለጫ አንድ ዐይነት አይደለም፤ ከማኅበረሰብ ማኅበረሰብ፥ ከባህል ባህል ይለያያል። የፍቅር መግለጫ ቋንቋ፥ የጋለ ጭብጨባ፥ እንባ፥ የቃል ንግግር፥ አበባ ማበርከት፥ መተቃቀፍ፥ መጨባበጥ፥ መሳሳም ሊሆን ይችላል። ከእነዚህ በአንዱ ወይም በሌሎች መንገዶች ፍቅር ይገለጣል። ጌታ ጴጥሮስን ሦስት ጊዜ መላልሶ ሲጠይቀው፥ ጴጥሮስም ሦሰት ጊዜ መላልሶ እወድሃለሁ ብሎታል። እንዲሁም በኋላ ላይ ግራ የገባው በሚመስል መልክ፥ በማዘንም ጭምር እንደምወድህ አንተ ታውቃለህ ብሎታል።
ፍቅርና ተግባር
በአጠቃላይ በወንጌል በተለይም በጌታችን ትምህርትና ሕይወት ውስጥ እንደምንመለከተው፥ የፍቅር ዋና መገለጫ ቃላት ሳይሆኑ ተግባር ነው። ጴጥሮስ “እወድሃለሁ” ቢልም በተግባር ግን ይህን ፍቅር ማሳየት አልቻለም፤ እወድሃለሁ ያለውን ጌታውን ክዶታል። ጌታችን ኢየሱስ በዮሐንስ ወንጌል 15፥13 ላይ ነፍሱን ለወዳጆቹ ከመስጠት የበለጠ ፍቅር እንደሌለና ነፍስን መስጠት የፍቅር ጣሪያ መሆኑን እንዳስተማረ፥ በተግባርም ነፍሱን በመስጠት ፍቅሩን አሳይቷል። ከዚህ በኋላ ነው ጌታ ጴጥሮስን “ትወደኛለህን?” ሲል መላልሶ የጠየቀው። ጴጥሮስም እንደ ቀድሞው፥ “ከአንተ ጋር መሞት እንኳ የሚያስፈልገኝ ቢሆን፥ ከቶ አልክድህም” (ማቴ. 26፥35) አላለም። የራሱን ምላሽ ከመስጠት ይልቅ “እንድወድህ አንተ ታውቃለህ” ነበር ያለው። ጴጥሮስ ፍቅሩን በተግባር መግለጽ ባይችልም፥ ኢየሱስ ፍቅሩን በተግባር ከገለጠና፥ የካደውን ጴጥሮስን በዚህ ፍቅር እንደ ገና ከመለሰው በኋላ አልከሰሰውም። ይልቁንም ሲመልሰውና ወይም እንደ ገና ሲያድሰው፥ ኀላፊነትንም ሲሰጠው እንመለከታለን።
መልእክቱ
“ትወደኛለህን?” የሚለው የጌታ ጥያቄ “አዎን እወድሃለሁ” ከሚል ምላሽ ያለፈ ቀጥተኛ መልእክት አለው። መልእክቱም የምትወደኝ ከሆነ አደራዬን ተወጣ የሚል ነው። ጌታ ሦስት ጊዜ፥ “ትወደኛለህን?” ሲል ከጠየቀው በኋላ ጴጥሮስ “አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ” የሚል ምላሽ መስጠቱን ተከትሎ፥ ግልግሎቼን አሰማራ፤ ጠቦቶቼን ጠብቅ፤ በጎቼን አሰማራ የሚል ግልጽ አደራ ሰጥቶታል (ዮሐ 21፥15-17)። ይህ ኀላፊነት ወይም አደራ የሕይወት መሥዋዕትነትን የሚጨምር እንደሚሆን ቀጥሎ በተጻፈው ቃል ውስጥ እናነባለን። “እውነት እውነት እልሃለሁ፥ አንተ ጒልማሳ ሳለህ ወገብህን በገዛ ራስህ ታጥቀህ ወደምትወደው ትሄድ ነበር፤ ነገር ግን በሸመገልህ ጊዜ እጆችህን ትዘረጋለህ፥ ሌላውም ያስታጥቅሃል፤ ወደማትወደውም ይወስድሃል አለው። በምን ዐይነት ሞት እግዚአብሔርን ያከብር ዘንድ እንዳለው ሲያመለክት ይህን አለ።” የዚህ ክፍል መልእክት በእኛም ሕይወት ሊተገበር የሚገባው ነው። ምክንያቱም ክርስቶስ በዕለታዊ ሕይወታችን ተግባራዊ ምላሽን ይጠብቃል። ትወደኛለህን? ለሚለው ጥያቄ በቃል “እወድሃለሁ!!” የሚለውን ምላሽ ከመስጠት ይልቅ፥ ራሳችንን መልሰን መጠየቅ የተሻለ ሳይሆን አይቀርም። በርግጥ ጌታን እንወደዋለን ወይ?
ምንጭ:- dejebirhan.blogspot.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 834
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ዘመኑ ቀርቦአልና የሚያነበው፥ የትንቢቱን ቃል የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፈውን የሚጠብቁት ብፁዓን ናቸው።”
ራእይ 1፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 834
ነገረ ፍጻሜ (Eschatology)
ክፍል-2
Premillennialism (ቅድመ ሚሊኒየም)
ቅድመ ሚሊኒየም ስለ ሚሊኒየም (በራዕይ 20፥1-6 ላይ የተገለጸውን የክርስቶስን "የሺህ ዓመት ግዛት") በተመለከተ ከሦስቱ ዋና ዋና የክርስትና አመለካከቶች አንዱ ነው። ቅድመ ሚሊኒየም(premillennialism) የሚለው ቃል የመጣው ከላቲን ሲሆን “pre” (ቅድመ ወይም በፊት) እና “millennium” (ሺህ ዓመት) ሲሆን ይህም ኢየሱስ ክርስቶስ የሺህ ዓመት መንግሥት ከመቋቋሙ በፊት እንደሚመለስ ያለውን እምነት ያመለክታል።
በዚህ አመለካከት መሠረት፣ የአሁኑ ዘመን በክህደት፣ በመከራ እና የክርስቶስ ተቃዋሚ መምጣትን ያጠቃልላል። ከዚያም ክርስቶስ ጠላቶቹን ለማሸነፍ፣ ሰይጣንን ለማሰር፣ መንግሥቱን በምድር ላይ ለአንድ ሺህ ዓመታት ለማቋቋም እና እንደ ንጉሥ ለመንገሥ በገሃድ በሚታይ መልኩ እና በክብር ይመለሳል። ከሺህ ዓመቱ በኋላ፣ ሰይጣን ለመጨረሻው ዓመፅ ይለቀቃል፤ ከዚያም ክርስቶስ በፍፁም ያሸንፈዋል፤ ከዚያም የመጨረሻው ፍርድ እና የአዲሱ ሰማይ እና የአዲሱ ምድር መፈጠር (ራእይ 20-22) ይሆናል።
ቅድመ ሚሊኒየም አስተምህሮ የመጽሐፍ ቅዱስን ትንቢት በቁም ነገር ይመለከተዋል እና በአጠቃላይ ብዙ ትንቢታዊ ምንባቦችን ከሌሎች የሺህ ዓመት እይታዎች ይልቅ ቃል በቃል ወይም በታሪካዊ ሰዋሰዋዊ መንገድ ይተረጉማል። ሆኖም፣ ሁሉም ቅድመ ሚሊኒየም አማኞች ትንቢትን በትክክል በተመሳሳይ መንገድ አይተረጉሙም። ከጊዜ በኋላ፣ ሁለት ዋና ዋና የቅድመ ሚሊኒየማዊነት ዓይነቶች ተፈጥረዋል፤ እነዚህም “Historic Premillennialism” ታሪካዊ የቅድመ ሚሊኒየማዊነት እና “Dispensational Premillennialism” የዲስፔንሽናል ቅድመ ሚሊኒየማዊነት ናቸው።
1. Historic Premillennialism (ታሪካዊ ቅድመ ሚሊኒየማዊነት)
ታሪካዊ ቅድመ ሚሊኒየማዊነት ጥንታዊ የቅድመ ሚሊኒየማዊነት አይነት ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ ከታላቁ መከራ በኋላ ከሺህ ዓመት ግዛት በፊት እንደሚመለስ ያስተምራል። አማኞች በመከራ ያልፋሉ፤ በመከራ ታማኝ ሆነው ይቆያሉ፤ ከዚያም ወደ ክርስቶስ በሚታየው መመለሱ ይሰበሰባሉ። ክርስቶስ ምድራዊ መንግሥቱን ይመሰርታል፤ ለሺህ ዓመት ይነግሣል፤ ከዚያም የመጨረሻውን ፍርድ እና የዘላለሙን መንግሥት በሙላት ያመጣል።
ከዲስፔንሽናል በተለየ መልኩ፣ ታሪካዊ ቅድመ ሚሊኒየማዊነት እስራኤልን እና ቤተክርስቲያንን በፍፁም አይለያያቸውም። በምትኩ፣ ቤተክርስቲያንን የእግዚአብሔር የቃል ኪዳን ሕዝብ ቀጣይነት እና ፍጻሜ እንደሆነች አድርጎ ይመለከታታል ይህም ሆኖ እግዚአብሔር ለተስፋዎቹ ታማኝ መሆኑን አሁንም የተረጋገጠ እንደሆነ ያስተምራሉ።
ታሪካዊ ቅድመ ሚሊኒየማዊነት ዋና ዋና ባህሪያት
👉ክርስቶስ ከሺህ ዓመቱ በፊት ይመለሳል።
👉ቤተክርስቲያን ታላቁን መከራ ገፈት ቀማሽ ትሆናለች።
👉መነጠቅና የክርስቶስ ዳግም መምጣት አንድ ጊዜ የሚከሰት ለሁሉም በገሃድ የሚታዩ ክስተት ነው።
👉ክርስቶስ በምድር ላይ ተጨባጭ፣ ነባራዊ የሆነ ግልጽ መንግሥትን ይመሰርታል።
👉በሺህ ዓመት ጊዜ ሰይጣን ይታሰራል።
👉ከሺህ ዓመቱ በኋላ የመጨረሻው ፍርድና የክርስቶስ ዘላለማዊ መንግሥት በሙላት ይመጣል።
የመጽሐፍ ቅዱስ ድጋፍ
ታሪካዊ የቅድመ ሚሊኒየም ሊቃውንት በተለምዶ የሚከተሉትን ጥቅሶች እንደማስረጃ ያመጣሉ፡-
👉ራእይ 19–20
👉ማቴ. 24፥29–31
👉ሐዋ. 1፥6–11
👉1 ተሰ. 4፥16–17
👉1 ቆሮ. 15፥20–28
ይቀጥላል . . .
Blaising, C. A., & Bock, D. L. (Eds.). (1993). Progressive dispensationalism. Baker Academic.
Erickson, M. J. (2013). Christian theology (3rd ed.). Baker Academic.
Grudem, W. (2020). Systematic theology: An introduction to biblical doctrine (2nd ed.). Zondervan Academic.
Ladd, G. E. (1974). The presence of the future: The eschatology of biblical realism. Eerdmans.
Ryrie, C. C. (2007). Dispensationalism (Rev. and expanded ed.). Moody Publishers.
Walvoord, J. F. (1959). The millennial kingdom. Zondervan.
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 834
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔር ሙታንን የሚያስነሣ እንደ ሆነ ስለ ምን በእናንተ ዘንድ የማይታመን ነገር ሆኖ ይቈጠራል?”
ሐዋርያት 26፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 834
በነገረ ፍጻሜ (eschatology) ላይ ካሉት አስተምህሮዎች ውስጥ በሚስጥራዊ ንጥቀት (secret rapture) የሚያምነው የቱ ነው?
7 834
የቀጠለ...
ውስጥን የሚለውጥ መንፈሳዊ እርምጃ
ሁላችንም የምንታገልባቸው ብዙ ነገሮች አሉን፡፡ያብዛኞቻችን ህይወት ከያእቆብ ጋር በሚገባ ይመሳሰላል፡፡ የያእቆብ ልቡ፣አካሄዱ እና ስሙ እንደተለወጠ ጌታ ሊለውጠንና የፍሬ ሰዎች ሊያደርገን ይፈልጋል፡፡ ግን አንድ ነገር ከእኛ ይፈልጋል ብዬ አምናለሁ-በበቂ ሁኔታ መገኘታችንን!!
ያእቆብ ከእግዚአብሔር ጋር ታግሎ አሸነፈ የሚለው ሀሳብ እግዚአብሔርን ማሸነፉ ሳይሆን ለእግዚአብሔር ሙሉ በሙሉ መሰጠቱ እና መገዛቱ ነው እንደ ማሸነፍ የተቆጠረለት፡፡ እውነተኛ መንፈሳዊ ለውጥን ፈለገ! እግዚአብሔር በህይወታችን የበላይ መሆኑም የአሸናፊነታችን ሁሉ ምንጭ ነውና ያእቆብ ከሰውም ከእግዚአብሔርም ጋር ታግለህ አሸነፍክ ተባለ፡፡የወሰዳቸው እርምጃዎቹ እና ያሳለፈው ያ ድንቅ የሌሊት ትግል እግዚአብሔርን ፊት ለፊት እንዲያይ አደረገው፡፡
እኛም በእንደዚህ አይነት ውሳኔና ረሀብ በፊቱ ብንሆን እና ሳናቅማማ እራሳችንን በፊቱ ብንጥል እናየውና ተለውጠን እንቀራለን ብዬ አምናለሁ፡፡አለበለዚያ ግን ህይወት የሌለን፣ሀይማኖተኛ፣ግብዝ፣አስመሳይ እና ከእውነት የራቅን ነው የምንቀረው፡፡በላይ በተጠቀሱት መንፈሳዊ ሂደቶች ውስጥ ስናልፍ ግን እምነታችን ይጠነክራል ያድጋል ብሎም ግትረኝነት እልህ ከህይወታችን ይወገዳል፤ እውነተኛ የልብ መሰበርና ትህትናም መገለጫችን ይሆናል፡፡
አሳዛኙ ነገር በህይወታችን ብዙ ጊዜ ዋናው ፍላጎታችን “ኤሳው”እንዲለወጥ ነው የምንፈልገው ቢሆንም አንዱ “ኤሳው” ከህይወታችን ቢወገድ ሌላው ይመጣል በምድር እስካለን ድረስ፡፡ነገር ግን እግዚአብሔር በማንኛውም የህይወት ውጣ ውረድ ነጥሮ የሚወጣ ማንነትን ሊሰጠን ስለሚፈልግ እኛን ከውስጥ መለወጥ ነው የሚፈልገው፡፡ለዚህ ደግሞ የእኛን ፈቃደኝነት ይፈልጋል፡፡ስለዚህ እሺ እንበለው፡፡እጆህ ይስሩኝ ያበጃጁኝ እንበለው መስራትና መለወጥ ያውቅበታልና!‹‹እንዳላሸነፈውም ባየ ጊዜ የጭኑን ሹልዳ ነካው››እንደሚል ሰባብሮ የራሱ ሊያደርገን እና ትሁት አድርጎ የሚጠቅም የክብር እቃ ሊያደርገን ይመኛልና እንፍቀድለት፡፡
በመጨረሻም መሰረት የሆነኝ ሀሳብ ላይ ልናገር እና ጽሁፌን ልጨርስ፡፡ ያእቆብ ካደረጋቸው እርምጃዎች እጅግ የሚያስደስተኝ “ያእቆብም ለብቻው ቀረ” የሚለው ሀሳብ ነው፡፡ በዛች አመሻሽ ቀን በሀሳብ እና በጉልበት ሊረዱት የሚችሉ ሰዎችን ሁሉ አሻግሮ ለብቻው ሆነ፡፡እውነተኛ ውስጣዊ ለውጥን ፈልጎአልና ውጫዊ ከበባን አስወገደ፡፡ አዎ በዚህ ግርግር በበዛበት እና የሰውን ቀልብ በተለያየ መልኩ የሚስቡ ነገሮች በበዙበት አለም ብቻን በመሆን ለጌታ መገኘት የሚቻልባቸው አጋጣሚዎች የጠበቡ ቢሆንም እንደ አጋጣሚ እንደዚህ አይነት ጊዜዎች ሲገኙ መታለፍ የለባቸውም ባይ ነኝ፡፡ በነዚህ ጊዜዎች የምናሳልፋቸው በርከት ያሉ ሰኣታት ወደ ፊት የሚኖረን ህይወትና አገልግሎት በእጅጉ ይወስኑታልና ያለመሰሰት እራሳችንን እግሩ ስር እንጣል፡፡ እግዚአብሔር ሆይ እንደ ያእቆብ በፊትህ የከበረን ጊዜን ስጠን!!
ምንጭ:- bekedesa7.blogspot.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 834
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ወደ እርሱ ቅረቡ ያበራላችሁማል፥ ፊታችሁም አያፍርም።”
መዝሙር 34፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 834
ነገረ ፍጻሜ (eschatology)
ክፍል-1
የክርስትናን የነገረ ፍጻሜ (eschatology) ጥናት ስንመረምር በሺህ ዓመቱ ትርጓሜ ላይ አብዛኛው ክርክሩ ያተኩራል። ይህ ጽንሰ-ሀሳብ፣ በራዕይ 20 ላይ የተመሠረተ፣ የክርስቶስና የቅዱሳኑ የ1,000 ዓመት ግዛትን ይገልጻል። ሚሊኒየም የሚለው ቃል የሚያመለክተው በራዕይ 20፥1-6 ላይ የተጠቀሰውን የክርስቶስን የሺህ ዓመት አገዛዝ ነው። በቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ፣ ክርስቲያኖች የክርስቶስን ዳግም መምጣት በተመለከተ የዚህን መንግሥት ተፈጥሮና ጊዜ ለመረዳት ሞክረዋል። በዚህ መሠረት ሦስት ዋና ዋና አመለካከቶች አሉ። እነርሱም ቅድመ ሚሊኒየም (premillennialism)፣ ድህረ ሚሊኒየም (postmillennialism) እና አልቦ-ሚሊኒየም(amillennialism) ናቸው። ሦስቱም ምልከታቸው የተለያዩ ቢሆኑም፣ ሁሉም የክርስቶስን አካላዊ መመለስ፣ የሙታንን ትንሣኤ እና የእግዚአብሔርን ዘላለማዊ መንግሥት የመጨረሻ መመስረት ያረጋግጣሉ። እስቲ አንድ በአንድ እንመልከታቸው።
ቅድመ ሚሊኒየም (Premillennialism)
ይህ አስተምህሮ ክርስቶስ ከሺህ ዓመቱ በፊት እንደሚመለስ እና በምድር ላይ የከበረ ግዛት እንደሚጀምር ያስተምራል። በዚህ የሚያምኑ (ብዙውን ጊዜ “chiliasm” ተብለው ይጠራሉ) የቤተክርስቲያን አባቶች የሂራፖሊስ ፓፒያስ፣ ጀስቲን ሰማዕቱ እና የሊዮንስ ኢራኒየስ ይገኙበታል። በዘመናችን፣ ቅድመ ሚሊኒየማዊነት በተለይ በብዙ ወንጌላዊ፣ ባፕቲስት እና በጴንጤቆስጣሎች ዘንድ የተለመደ ነው።
ድህረ ሚሊኒየም (Postmillennialism)
ድህረ ሚሊኒየም አስተምህሮ ወንጌል ዓለምን ቀስ በቀስ ይለውጣል፤ ረጅም የጽድቅና የሰላም ዘመንን ያመጣል፤ ከዚያም በኋላ ክርስቶስ ይመለሳል ይላል። ምንም እንኳን በቀደሙት አባቶች ዘንድ በስፋት ይህ አስተምህሮ ባይወከልም፣ ይህን አመለካከት እንደ ጆናታን ኤድዋርድስ ዘንድ ጎልቶ ይታያል። ዛሬ በዋናነት በአንዳንድ የተሐድሶ እና የፕሪስባይቴሪያን ክርስቲያኖች ዘንድ ይገኛል። ድህረ ሚሊኒየም አመለካከት የወንጌልን ድል አድራጊ ኃይል እና የቤተክርስቲያን በታሪክ ውስጥ ተልዕኮዋን አጉልቶ ያሳያል።
አልቦ ሚሊኒየም (Amillennialism)
አልቦ ሚሊኒየም ራዕይ 20 ላይ ያለው የአሁኑን የቤተክርስቲያን ዘመን እንደሚገልጽና “ሺህ ዓመት” የተባለውም ምልክት(symbolical) እንደሆነ እንጂ በእርግጥም አንድ ሺህ ዓመት እንዳልሆነ አድርገው ይተረጉሙታል። ይህ አመለካከት ከታዋቂው የቤተክርስቲያን አባት ኦገስቲን ትምህርት ጋር የተያያዘ ሲሆን አስተምህሮው የምዕራባውያንን ክርስትና በጥልቅ የቀረጸው ነው። አልቦ ሚሊኒየም በሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን፣ በምስራቅ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን፣ በሉተራን አብያተ ክርስቲያናት (መካነ ኢየሱስ) እና በብዙ የተሐድሶ ቤተ እምነቶች ውስጥ ይፋዊ ወይም ዋና አመለካከት ወይም አስተምህሮ ነው። ክርስቶስ አሁንም እንደነገሰ እና መንግሥቱ አሁንም እንደሚገኝ እና በዳግም መመለሱ መንግሥቱ በሙላት እንደምትመጣ አፅንዖት ይሰጣል።
ይቀጥላል . . .
Erickson, M. J. (2013). Christian theology (3rd ed.). Baker Academic.
Hoekema, A. A. (1979). The Bible and the future. Eerdmans.
Ladd, G. E. (1974). The presence of the future. Eerdmans.
McGrath, A. E. (2017). Christian theology: An introduction (6th ed.). Wiley-Blackwell.
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 834
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ፥ ከኃጢአተኞች በደረሰበት እንዲህ ባለ መቃወም የጸናውን አስቡ።”
ዕብራውያን 12፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 834
#እራሳችንን_እንመርምር
እግዚአብሔርን መታመም ዋጋ የሚያስከፍል ነገር ነው። እንዲሁም ደግሞ ተስፋ ያስቆርጣል። እና እግዚአብሔር ምን እያደረግን እንጠብቀው?
“እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ፤ በርታ፥ ልብህም ይጽና፤ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ።”
መዝሙር 27፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 834
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ነፍሴ፦ እግዚአብሔር እድል ፈንታዬ ነው፤ ስለዚህ ተስፋ አደርገዋለሁ አለች።”
ሰቆ. 3፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 834
"ሐዋሪያ" እና "ነቢይ" በአሁን ዘመን አለ? እንዲህ አይነት ሹመትስ ይሰጣል? መጽሐፍ ቅዱስ ስለዚህ ጉዳይ ምን ይላል?
ክፍል-11
ከኢየሱስ ለመማር ይከተለው የነበረው ሕዝብም እርሱን እንደ ነቢይ ተቀብሎት እንደነበረ ከወንጌላት እንማራለን (ማቴ 16፥14፣ 21፥46፣ ሉቃ 7፥16)። ለዚህም ከእናቱ ማህጸን ጀምሮ ዓይነ ሥውር የነበረ፣ በኢየሱስ እጅ ከተፈወሰ በኋላ “እርሱ ነቢይ ነው!” በማለት የሰጠው ምስክርነት ለአብነት ሊጠቀስ ይችላል (ዮሐ 9)፡፡ በእግዚኣብሔር ዘንድ ቃል የነበረ፤ በኋላም ሥጋ በመልበስ ጸጋና እውነትን ተሞልቶ በሰዎች መካከል በመገኘት እግዚኣብሄር አብን የገለጠልን እርሱ ነውና (ዮሐ 1)፡፡
በመጨረሻው ዘመን ለምንኖር ለእኛ ደግሞ ነቢያት ራሳቸው ትንቢት እየተናገሩለት ራሳቸውም ሊያዩት ይናፍቁ የነበረ፣ እግዚኣብሔር ለእኛ የተናገረበት የመጨረሻ መልዕክትና መልዕክተኛው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። “እርሱን ስሙት" የሚለው ከአብ ዘንድ የመጣው ቃል ኢየሱስ በሥጋ የተገለጠ የእግዚኣብሔር ጥበብ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ይመሰክራል(1 ቆሮ 1፥30)፡፡ ሙሴ በትንቢት "እርሱን የማትሰማ ነፍስ ትጠፋለች" ያለው እርሱ የእኛ ነቢይ መሆኑንና እርሱን ብቻ እንድንሰማ እንደብሉይ ኪዳን ነቢያት በትንቢት ተስፋ የምንኖርበት ጊዜና ዘመን አይደለም፡፡ የእነርሱ ትንቢት እንደሞግዚት ሆኖ ወላጅ እስኪመጣ ይጠብቅ ነበርና፡፡ አሁን ግን በክርስቶስ በኩል የተሰወረው የእግዚኣብሔር ጥበብ ተገልጧልና (ቆላስ 2፥3)።
ከላይ እንዳሳነው የጥንቱ ነቢያት መልዕክቶቻቸውን የሚቀበሉት ከጠራቸው እግዚአብሔር ከራሱ በቀጥታ ነበር (ዘጸ 3፥1-4፤ ኢሳ 6፥6-8)፡፡ በአንጻሩም ሥልጣንንና ክብርን በመመኘት ሐሰተኛ ነቢያት በራሳቸው ሥልት ወደ ነቢይነት ቦታ ወይም አገልግሎት ሰግስገው ራሳቸውን ያስገቡ እንደነበረ ቅዱሳት መጻሕፍት በግልጽ ያስረዳሉ (ኤር 14፥14፣ 23፥21)፡፡ ነቢያት በሰዎች ፊት ቆመው ሲናገሩ በእግዚአብሔር ፊት እንደቆሙ ይቆጠራል (1 ነገሥ 17፥1፤ 18፥15)፡፡ ነቢያት በራሳቸው ፍላጎት ሲሾሙ ወይም ራሳቸውን ሲሾሙ ማየት መጽሐፍ ቅዱሳዊ አለመሆኑን ማንም ቅንጣት ያህል ሊጠራጠር አይገባም፡፡ እግዚአብሔር እነ ሙሴን ፤ ኤልያስን፣ ኤርምያስን፣ አሞጽንና ዮናስን ሲጠራ ጥሪውን ላለመቀበል መከራከራቸው ፈቃደኛ ካለመሆን አልነበረም፡፡ ነገር ግን አገልግሎቱ ታላቅና በኃላፊነት የሚያስጠይቅና እነርሱም በራሳቸው ከራሳቸው የሆነ ብቃት የሌላቸው መሆናቸውን በመገንዘባቸው ነው፡፡
ከአገልግሎታቸው መካከል የሚበዙቱ ነገሥታትን እስኪፈታተኑ ድረስ ስለፍትህ መጓደል በገሃድና በአደባባይ የወቀሳና የማስጠንቀቂያ መልእክት ማስተላለፍ ነበር፡፡ ለዚህም ነቢዩ ናታን ንጉስ ዳዊትን ከኦርዮን ሚስት ጋር ስለማመንዘሩ፣ እንዲሁም መጥምቁ ዮሐንስ በዘመነ የሮም ተወካይ የነበረውን የይሁዳ አገረ ገዥ ሄሮድስን የወንድሙን ሚስት ስለመውሰዱ ማውገዙ ለአብነት ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡ ይህንና ይህንን የመሳሰሉት አገልግሎቶች መስጠታቸው ነቢያትን ተወዳጆች ሳይሆኑ ተሰዳጆች አድርጎኣቸዋል፡፡ አንዳንዶች መከራቸው ሞትን እስኪመኙ ድረስ አንገሽግሾኣቸዋል፡፡ እውነትን በእውነትና በፍጹም ቅድስና በድፍረት ፊት ለፊት ተናግረዋልና፤ በጊዜያዊ ድለላና ጥቅምም አልተረቱምና፡፡ ነቢይ በመሆናቸውም ከተገልጋዩ ሕዝብ ልዩ ክብርና ረብ አልጠበቁም፡፡
ስለዚህ ከብሉይ ክዳነ ታሪክ እንደምንረዳው ነቢይነት ግለሰቦች ፈልገው የሚቀበሉት አገልግሎት ሳይሆን እግዚኣብሔር በፈለገው ጊዜና ለፈለገው ሰው ለመንግስቱ አገልግሎት ሲል የሚሰጥ ነበር፡፡ የጥንቱ ነቢያት አገልግሎት በእርግጥ ማህበራዊና ብሄራዊ ነክ ጉዳዮችንም ጭምር ይዳስስ ስለነበረ ነገሥታት ሳይቀሩ ይፈሩኣቸው፣ ይጠሎአቸውና፣ ያሳድዱኣቸው እንደነበር የነቢያት አገልግሎት ታሪክ ይመሰክራል። ዛሬም ቤተ ክርስቲያን ትንቢታዊ መልአእክት የማስተላለፍን አገልግሎት ከቤተ ክርስቲያን ግድግዳዎችና ከምዕመናን መንፈሳዊ ሕይወትና ሥጋዊና ማህበራዊ ብልጽግና ባለፈ መልኩ በማህበረሰብና በአመራር ባሉት ደረጃ ዘልቆ እንዲስማ ጥረት ማድረግ አለባት፣ ማህበራዊና ብሔራዊ ነክ ጉዳዮች የእግዚኣብሔር ጉዳዮች ናቸውና፡፡ ሙስና በሰፈነበት፣ ሥልጣንን ያለአግባብ መጠቀም በበዛበት የደካሞች መብት በተረገጠበት ጊዜና ቦታ ሁሉ ቤተክርስቲያን ትንቢታዊ ድምፅዋን ማሰማት ይጠበቅባታል! ጥሪዋም ነው፡፡ ነገር ግን ቤተክርስቲያን በብሉይ ኪዳን ዘመን እንደነበረው ዓይነት ነቢያትን መድባ ለመንግስታትና ለሕዝቦች ትንቢት እንዲናገሩ አታሰማራም፡፡ ራስዋ ቤተ ክርስቲያን ትንቢታዊ ቃል አላትና በሚመቻት መንገድ ሁሉ ትንቢታዊ ድምጽዋን ታሰማለች፡፡
ይቀጥላል. . .
ምንጭ፦
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የሚሲዮንና ሥነመለኮት ቦርድ ስመተ-ሐዋሪያንና ሲመተ- ነቢያን በሚመለከት ለቤተክርስቲያኒቱ 18ኛው የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ የቀረበ የሥነ መለኮታዊ አቋም አስተያየት፤ ታህሳስ 14-18 2003 ዓ.ም፤ አባሪ 2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
7 834
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እናቱም ለአገልጋዮቹ፦ የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው።”
ዮሐንስ 2፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 834
👉ርዕስ፦ ድል አድራጊ ሁን!
እርግጠኛና ክቡር ከሆነው የክርስቶስ ምጽአት የተነሣ፣ ክርስቲያን አሸናፊ ነው!
የዮሐንስ ራእይ መልእክት ጥናት
✍️ጸሐፊ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ
🗣ትርጉም፦ ግርማዊ
✏️እርማት፦ ዓቢይ ደምሴ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
