en
Feedback
ቅዱሳት መጻሕፍት

ቅዱሳት መጻሕፍት

Open in Telegram

በዚህ ቻናል 👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ:: 👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ:: 👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ። ⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️ @Holy_scriptures

Show more
7 842
Subscribers
+1024 hours
+417 days
+14330 days
Posts Archive
መጽሐፈ ምሳሌ፣ አዲስ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጽሑፍ ጋር ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

መጽሐፈ ምሳሌ፣ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

👉ርዕስ፦ ድል አድራጊ ሁን! እርግጠኛና ክቡር ከሆነው የክርስቶስ ምጽአት የተነሣ፣ ክርስቲያን አሸናፊ ነው! የዮሐንስ ራእይ መልእክት ጥናት ✍️ጸሐፊ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ 🗣ትርጉም፦ ግርማዊ ✏️እርማት፦ ዓቢይ ደምሴ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፤ ማርያምም መልካም ዕድልን መርጣለች ከእርስዋም አይወሰድባትም አላት።” ሉቃስ 10፥
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፤ ማርያምም መልካም ዕድልን መርጣለች ከእርስዋም አይወሰድባትም አላት።” ሉቃስ 10፥42 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

👉ርዕስ፦ መጽሐፈ ምሳሌ በባይብል ፕሮጀክት፣ በአማርኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

https://www.youtube.com/watch?v=2FZbIytmt2M ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ውስጥን የሚለውጥ መንፈሳዊ እርምጃ በህይወታችን እውነተኛ መንፈሳዊ ለውጥ እንዲመጣ ካስፈለገ ከምር መወሰን ይኖርብናል፡፡ብዙ ጊዜ ውጫዊ ነገሮች በመቀየራቸው ብቻ እውነተኛ መንፈሳዊ እድገት ላይ ያለን እየመሰለን ልንታለል እንችላለን፡፡ እንደ ያእቆብ ማንንም እያታለልንና እያስመሰልን ዘመናችንን ልንጨርስም እንችል ይሆናል፡፡የእግዚአብሔር ዘላለማዊ ሀሳብ ግን ውስጣችን በትክክል ተለውጦ እና እርሱን አንግሶ ከዚህ በሚመነጭ ፍሬ እርሱን በዙሪያችን አስከብረን እንድናልፍ ነው፡፡ለዚህ አይነት ውጤት የጨከነ ማንነት እና ሁለንተናችንን በጸጋው ዙፋን ፊት መጣል ይኖርብናል፡፡እንደዚያ ስናደርግ ብቻ ነው እውነተኛ ፍሬን በህይወታችን ማየት የምንችለው፡፡ ከላይ ለተጠቀሰው የለውጥ እርምጃ እንደ ሞዴል የሚሆነን ዘፍ 32፡22-32 ላይ ያለው ያእቆብ በህይወቱ የወሰደው እርምጃ እና ውጤቱ ነው፡፡ለዚህ ክፍል ዳራ የሚሰጠን በዘፍጥረት መጽሀፍ የተለያዩ ክፍሎች ያእቆብ ያሳለፋቸው ውጣ ውረዶች ናቸው፡፡በነዚያ የህይወት ውጣ ውረዶቹ ፡- ያእቆብ አታላይ ነበር ያእቆብ ከማናኛውም አይነት ሁኔታ ላይ ማትረፍ የሚወድ ራስ ወዳድ ሰው ነበረ ያእቆብ አስቸጋሪ ነገሮችን ከመጋፈጥ ይልቅ ይሸሽ ስለነበር እውነተኛ ሕይወት አልነበረውም ያእቆብ በራሱ በመደገፍ ማንኛውንም ጉዳይ በእራሱ የመፍታት አካሄድ ነበረው በመጨረሻም ያእቆብ በምድራዊ ሀብት ደረጃ ባለጸጋ ሆኗል ነገር ግን ያልተፈቱ ችግሮች ነበሩት በዚህ ክፍል ያእቆብ ወደ እናት አባቱ ምድር ለመመለስ ጉዞ እያደረገ ነው፡፡ከፊት ለፊቱ ኤሳው ወንድሙ እንደ ትልቅ ጋሬጣ በመንገዱ ላይ አለ፡፡ይህንንም ጋሬጣ እንዴት እንደሚያልፍ ጭንቅ ስለሆነበት በዘፍጥረት ምእራፍ 32 ላይ አንዴ ይጸልያል፣አንዴ በእጅ መንሻ ለማምለጥ ይዘይዳል፣አብረውት ያሉትን ባሪዎቹንና ንብረቶቹን ለሁለት ከፍሎ ይህንን አስቸጋሪ ሁኔታ ለማለፍ የሚችለውን ያህል መፍትሄ እያበጀ ነው ያለው፡፡ግን ይህ ሁሉ ዝየዳ መጨረሻ ላይ እንደማይጠቅመው ከተረዳ በኋላ አስደናቂ እርምጃዎችን ማድረግ ጀመረ፡- አብረውት ያሉትን ሁሉ  ከፊት አስቀድሞ የያቦቅን ወንዝ አሻግሮአቸው ለብቻው ቀረ፡፡ያቦቅ ማለት እራስን ባዶ ማድረግ ማለት ነው -በእንግሊዝኛው በቀጥታ ሲተረጎም እንዲህ ነው፡-‘emptying’ ካንድ ሰውም ጋር  እስከ ንጋት ይታገል ነበር፡፡ብዙ የመጽሀፍ ቅዱስ አዋቂዎች ይህ ሰው ኢየሱስ ነው ይላሉ ሊነጋ አቀላልቶአልና ልቀቀኝ ሲለው ያእቆብ “ካልባረክኸኝ አልለቅህም ” አለ-እጅግ በህይወታችን የሚያስፈልገን ድንቅ ውሳኔ እና ጸሎት ለመጀመሪያ ጊዜ እውነተኛ ማንነቱን ተናገረ፡፡ሰውየው  ስምህ ማን ነህ ሲለው ያእቆብ ነኝ አለ ያእቆብ ማለት አታላይ ማለት ነው-እውነተኛ ለውጥ ፈላጊም እንደሆነ አስመሰከረ ይህ ያእቆብ የታገለው ትግል ኢየሱስ በጌተሰማኒ ከጸለየው እና እራሱ ለሀጥያት መስዋእት አድርጎ ለመስጠት ካማጠበት እና ከቃተተበት የጸሎት ትግል ጋር ተመሳሳይነት እንዳለው የመጽሀፍ ቅዱስ አዋቂዎች ይናገራሉ፡፡ከዚህም ምጥና መስዋእት በኋላ ያፈራውን ፍሬ ኢሳ 53፡11 እንዲህ ይገልጸዋል፡-‹ነፍሱን ስለ ሀጢያት መስዋእት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል እድሜውም ይረዝማል የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል፡፡ከነፍሱ ድካም ብርሀን ያያል ደስም ይለዋል…..››  ያእቆብ ከዚህም መንፈሳዊ ትግል የተነሳ ስሙ ተለወጠ፡፡እስራኤል ማለት “ከእግዚአብሔር ታግሎ ያሸነፈ” ማለት ሲሆን በእንግሊዝኛው እንዲህ ይተረጎማል፡- "Triumphant with God" ወይም “who prevails with God” ከዚያ አስደናቂ ትግል በኋላ ሲመሰክርም “እግዚአብሔርን ፊት ለፊት አየሁት ሰውነቴም ድና ቀረች”ብሎ ውጤቱን ተናገረ፡፡ምእራፍ 33 ላይ እንደምናየው ከኤሳውም ጋር በሰላም ነው ተሳስመው የተተላለፉት-ከእግዚአብሔር ጋር ስንስማማ ጠላቶቻችን እንኳ ከእኛ ጋር እንዲስማሙ ማድረግ ይችላልና ነው፡፡ ያእቆብ የወሰዳቸው እርምጃዎች እግዚአብሔርን በህይወቱ ፊት ለፊት እንዲያይ አድርገውታል፡፡በእኛም ህይወት እንዲህ አይነት ጊዜዎች እንዳይኖሩን እራሳችንን መከልከል የጠለቀ ግንኙነት እንዳይኖረን ያደርጋል፡፡ያለ እውነተኛ መንፈሳዊ ትግልም ለውጥ የለም፡፡በእርሱ ፊት እራሳችንን ባዶ የምናደርግበት ፣በፊቱ ወድቀን እውነተኛ መዳሰስ እንዲመጣ ፊቱን ከምር የምንፈልግባቸው ጊዜያት ያስፈልጉናል-አንዴ ሳይሆን በርከት ያሉ ጊዜያት! ይቀጥላል... ምንጭ:- bekedesa7.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል። እናንተ ኃጢአተኞች፥ እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ፥ ልባችሁን አ
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል። እናንተ ኃጢአተኞች፥ እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ፥ ልባችሁን አጥሩ።” ያዕቆብ 4፥8 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

በደቡብ ያለው መናገሻውን ኢየሩሳሌም ያደረገው መንግሥት የትኛው ወገን ነበረበት?
Anonymous voting

የቀጠለ... ከሰማይ እውቀት መጉደል • አምላካቸው በዙሪያቸው ያሉ አህዛብ እንደሚያመልኩዋቸው አማልክት አይነት እንዳልሆነ ሊያውቁና ሊያምኑ ይገባል (ኢሳ.43:11-13 ይመልከቱ) ይህ እውቀት እስራኤልን ከአህዛብ አማልክትና ወገን ለይቶ ወደ ህያው አምላክ ጥላ ያስገባ ነው፡፡ እውቀቱ የእስራኤልን ልብ በሙሉ ጠይቆአል፣ በዚህ እውቀት ምክኒያት ነፍሱ ያለ አንዳች ማወላወል (መቶ በመቶ) አምላክ አንድ ብቻ መሆኑን ልትቀበለውና ልታምነው የተገባ መሆኑን አውጆአል፣ ሀይል የተባለ ሰው ያለው መንፈሳዊ ጉልበትና የአምልኮ መሰጠት ለሌላ ለማንም አምልኮ ሳይውል ይህን እውቀት ለገለጠው አምላክ ብቻ እንዲሆን እግዚአብሄር እስራኤልን አስተምሮአል፡፡ • እግዚአብሄር ብቻ ገዢ እንደሆነ አስተውለው ሊከተሉት የሚገባ መሆኑን ተናግሮአል (ኢሳ.43:14-16 ይመልከቱ ) የእግዚአብሔር ህዝብ ሲፈራ አይኑን ከአምላኩ እንደሚያነሳና በሁኔታዎች ላይ እንደሚደገፍ የሚታይ ክስተት ነው፡፡ የደነገጠን ልብ የሚያደፋፍርና የሚያጽናና አምላክ መጥቶም ህዝቡ ያስፈራውን ጠላት እንዳይቀበል፣ መፈራት የሚገባው ግን ንጉሱ አምላክ እርሱ ብቻ እንደሆነ ያስረዳል፡፡ ጠላት ምንም ያህል ቢጋፋ ማስፈራራቱ የሚቀጥለው ንጉሱ አምላካችን እስኪገለጥ ድረስ ብቻ ነው፤ ነገር ግን አሰራሩን ያስተዋሉ በትእግስት የእግዚአብሄርን ስራ እየሰሩ እየታገሱና ጨክነው እየጠበቁ ይቆያሉ፡፡ እርሱ በፍጻሜው ሲደርስ ያስፈራሩ ጎረቤቶች፣ ሀሰተኛ ነቢያቶችም ሳይቀሩ በእግዚአብሄር መምጣት ይደነግጣሉ፣ ያፍራሉም፡፡ የነነህሚያ ታሪክ ያንን ያስተምረናል ነህ.6፥9-16። በነህሚያ ታሪክ ውስጥ እንደሚታየው የጠላቶቹ አሰራር መራቀቅና የሴራቸው ስውርነት መብዛት ቢጎላም እግዚአብሄር መጥቶ ህዝቡን እስኪረዳ ድረስ የነርሱ ዛቻ ከማስፈራራት አልፎ ሊሄድ አልቻለም፡፡ እግዚአብሄርንና አሰራሩን በማወቅ ስንቆም የሚታየን መምጣቱ እንጂ እየመጣ የሚሄደው የጠላት ፈተና፣ ስውር አሰራር እንዲሁም የሚከታተለው የመከራ ጫና አይደለም፡፡ ድል ድል ነው፣ ማሸነፍ ማሸነፍ ነው! ከዚህ ውጪ ስለጠላት ሁኔታ ማውጣትና ማውረድ የሚፈጥረው ልብን የሚያሸፍትና እግዚእብሄርን ከመጠበቅ የሚያንሸራትት መንፈስ ውስጥ መስጠም ነው፡፡ ንጉስ ዳዊት የእግዚአብሄር እርዳታ እስኪመጣለጥ ድረስ በብዙ ትእግስት እግዚአብሄርን ጠበቀ፣ ሲጠብቅ ግን ነፍሱን እያበራታ፣ ስትዝል እየገሰጸ፣ የአምላኩን ታላቅነት እያሰላሰለ፣ በእምነት እየተናገረም ነበረ፤ የርሱ ማሸነፍ ይሄን ታላቅ ተጋድሎ ጠይቆአል፡- መዝ.18፥1-6 ”አቤቱ ጕልበቴ ሆይ፥ እወድድሃለሁ። እግዚአብሔር ዓለቴ፥ አምባዬ፥ መድኃኒቴ፥ አምላኬ፥ በእርሱም የምተማመንበት ረዳቴ፥ መታመኛዬና የደኅንነቴ ቀንድ መጠጊያዬም ነው።ምስጋና የሚገባውን እግዚአብሔርን እጠራለሁ፥ ከጠላቶቼም እድናለሁ።የሞት ጣር ያዘኝ፥ የዓመፅ ፈሳሽም አስፈራኝ፤የሲኦል ጣር ከበበኝ፤ የሞት ወጥመድም ደረሰብኝ።በጨነቀኝ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት፥ ወደ አምላኬም ጮኽሁ፤ ከመቅደሱም ቃሌን ሰማኝ፥ ጩኸቴም በፊቱ ወደ ጆሮው ገባ።” መዝ.30፥8-12 ”አቤቱ፥ ወደ አንተ ጠራሁ፥ ወደ አምላኬም ለመንሁ። ወደ ጥፋት ብወርድ በደሜ ምን ጥቅም አለ? አፈር ያመሰግንሃልን? እውነትህንም ይናገራልን? እግዚአብሔር ሰማ ማረኝም፤ እግዚአብሔር ረዳቴ ሆነኝ። ክብሬ ትዘምርልህ ዘንድ ዝምም እንዳትል ልቅሶዬን ለደስታ ለወጥህልኝ፥ ማቄን ቀድደህ ደስታንም አስታጠቅኸኝ። አቤቱ አምላኬ፥ ለዘላለም አመሰግንሃለሁ።” መዝ.121፥1-3 ”ዓይኖቼ ወደ ተራሮች አነሣሁ፤ ረዳቴ ከወዴት ይምጣ? ረዳቴ ሰማይና ምድርን ከሠራ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው። እግርህን ለመናወጥ አይሰጠውም፤ የሚጠብቅህም አይተኛም።” ከመነሻው እንደተባለው ሰማያዊ እውቀት ሲጎድል ብዙ ጉዳትና መንፈሳዊ ስብራት እንደሚገለጠው ሁሉ ከላይ እንደምናየው እንደ ንጉሱ ዳዊት ያለ መረዳት ያለበት መለኮታዊ እውቀት ከእግዚአብሄር ጋር እንደሚያኖር፣ ምህረትንና በረከትን እንደሚያስከትል ማስተዋል ይገባናል፡፡ ካለማስተዋል መጉደል እንደሆነው አይሆንም፣ እርግጡን ካለመረዳት በሚመጣ መምታታት አይከሰትም፣ የልኡል እውቀት እስካገዘን ድረስ የማስተዋል እጦት አይገጥመንም፣ አካሄዱን እስከተረዳን ድረስ የጉዳት ጠባሳ በህይወታችን ውስጥ አይታተምም፣ ከዚህ ይልቅ የእውቀቱ ብርታት ይለውጥና መለኮታዊ ጸጋን ያስገኝልናል፣ ምህረትና ደህንነት ገንዘባችን ይሆናል፡፡ መለስ ስንል ይህ እውቀት እስራኤልን ሊያድን፣ ርስታቸው ላይ ሊያኖርና ሊያጸና የሚችል መለኮታዊ እውቀት ሆኖ ሳለ እስራአላውያን ከዚህ እውቀት ጋር ስላልተዋሀዱ በብዙ ሲታገሉትና ሲወድቁም ታሪካቸውን እንደሞሉት የምናየው ነው፡፡ የሚያስተውልም ትምህርቱ እኔንም ይመለከተኛል ይበል፡፡ ብዙ እውቀት በምድር ላይ ቢኖርም ሰማያዊው እውቀት ግን የላቀና አምላካዊ ፈቃድ ያለበት ነው፡፡ ምድር ላይ የተከማቸ እጅግ የበዛ እውቀት የምድርን ምስጢር ይገልጥ ይሆናል፤ ነገር ግን ይህ ጥበብ ለእግዚአብሄር ምስጢር ፍጹም ባዳ እንደመሆኑ ወደ የትኛውም መንፈሳዊ ከፍታ የሰውን ልጅ ማድረስ አይቻለውም፡፡ በዳን.2:20-22 ውስጥ ”ዳንኤልም ተናገረ እንዲህም አለ፡- ጥበብና ኃይል ለእርሱ ነውና የእግዚአብሔር ስም ከዘላለም እስከ ዘላለም ይባረክ፤ ጊዜያትንና ዘመናትን ይለውጣል፤ ነገሥታትን ያፈልሳል፥ ነገሥታትንም ያስነሣል፤ ጥበብን ለጠቢባን እውቀትንም ለአስተዋዮች ይሰጣል። የጠለቀውንና የተሠወረውን ይገልጣል፤ በጨለማ ያለውን ያውቃል፥ ብርሃንም ከእርሱ ጋር ነው።” ምንጭ፦ tsionvoice.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ነገር ግን በተፈረደብን ጊዜ ከዓለም ጋር እንዳንኮነን በጌታ እንገሠጻለን።” 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥32 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ነገር ግን በተፈረደብን ጊዜ ከዓለም ጋር እንዳንኮነን በጌታ እንገሠጻለን።” 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥32 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

የእስራኤል የመጀመሪያው መስፍን ማን ነው?
Anonymous voting

ከሰማይ እውቀት መጉደል ከሰማያዊ እውቀት መጉደል የሚያመጣውን መምታታት፣ የሚፈጥረውን የማስተዋል እጦት፣ የሚጥለውን የጉዳት ጠባሳ፣ የሚያስቀረውን መለኮታዊ ጸጋ፣ ተመትቶ ማንከስ ወይም ተቆርጦ መንገድ ላይ መቅረትን ለመገንዘብ በግልጽ ከአይሁድ የህይወት ተሞክሮ በማየት መማር እንችላለን፡፡ ሰማያዊ እውቀት ምንድነው? የእውቀቱ መታጣት እንዴት አስከፊ ቢሆን ነው የዚህን ያህል ጉድለትና ጥፋት የሚያስከትለው? የምንል ልንኖር እንችላለን፡፡ ቅድሚያ በዘኊ.24:15-16 ላይ የሚገኘው በለአም የተባለ ሰው ስለ መለኮታዊ እውቀት ያስተዋለውን ነገር እንመለከታለን፡- ”የቢዖር ልጅ በለዓም እንዲህ ይላል፥ ዓይኖቹም የተከፈቱለት ሰው እንዲህ ይላል፤ የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰማ፥ የልዑልንም እውቀት የሚያውቅ፥ ሁሉን የሚችል የአምላክን ራእይ የሚያይ፥የወደቀው፥ ዓይኖቹም የተከፈቱለት እንዲህ ይላል።…” ከላይ ባለው ጥቅስ መሰረት ሰማያዊ እውቀት መለኮታዊ እውቀት/የልዑል እውቀት እንደሆነ እንመለከታለን፡፡ እውቀት የሚባል የሰው ልጅ ነፍስ ልታስተውለው የተገባ ይህ መለኮታዊ እውቀት አስፈላጊነቱ ከፍ ያለ ነው፡፡ ነፍሳችን አምላኩዋን ታውቅ ዘንድ ከፈጠራት ከርሱ የተላለፈ ትእዛዝ በመሆኑ እርሱን ባለማወቅዋ የሚከተላት ጥፋትና እጦት እስከ ሞት የሚያደርሳት ነው፡፡ በለአም ግን የእግዚአብሔርን ቃል ሲሰማ የልዑልን እውቀት እንዳወቀ ዓይኖቹም ሲከፈቱለት ሁሉን የሚችል የአምላክን ራእይ እንዳየ ይመሰክራል፡፡ ነቢዩም በኢሳ.43:10 የእግዚአብሄርን ድምጽ እንዲህ ያስተላልፋል፡- ”ታውቁና ታምኑብኝ ዘንድ እኔም እንደሆንሁ ታስተውሉ ዘንድ፥ እናንተ የመረጥሁትም ባሪያዬ ምስክሮቼ ናችሁ ይላል እግዚአብሔር፤ ከእኔ በፊት አምላክ አልተሠራም ከእኔም በኋላ አይሆንም።” ሰው ላለመፍራት ዋስትናው ምንድነው? ቃሉ በግልጽ እንደሚለን እርሱን ማወቅ ነው፤ እውቀቱም ምድራዊ ሳይሆን መለኮታዊ ነው፡፡ ነፍስን ከዘላለም ህይወት ያጎደላት ያለማስተዋል ዋና ከአምላክዋ የመለየትዋ ችግር ከሆነ እርሱን በማወቅ መንቃትና ከእርሱ ጋር ዳግም መገናኘት በሆነላት ወቅት መዳንን ትጎናጸፋለች ማለት ነው፡፡ እግዚአብሄር ለእስራኤላውያን አትፍሩ እኔ አምላካችሁ ነኝ ሲል ያጽናናቸዋል፡፡ እነዚህ ህዝቦች በእግዚአብሄር ተመርጠው ሳለ በሆነ ወቅት ከእርሱ ኮብልለው በባእድ አማልክት ስር ሲወድቁና ለጠላቶቻቸው ተላልፈው ሲሰጡ እጅግ ተስፋ ያጡና የተጠቁ ሆነው ይኖሩ ነበር፡፡ እግዚአብሄርም ይሄን አይቶ እኔን እወቁና ወደ እኔ ተመለሱ እንጂ የሚያስፈራችሁ አንዳች ጠላት ሊኖር አይችልም የሚል ዋስትና ሲሰጣቸው እንመለከታለን፡፡ እኛም ብንሆን ከሰማይ እውቀት ጎድለን ያለተስፋና ያለአምላክ ሆነን በባእድ አምላክ የጨለማ ጥላ ድንጉጥ ከመሆን እርሱን በማወቅና በማመን ዋስትናውን ማግኘት አለብን፡፡ የእስራእል መዳን የተቋጠረበት እውቀት እግዚአብሄር ድምጹን ልኮ ህዝቡን ባስተማራቸው ዘመን ሁሉ እርሱን የሚያውቁበትን መንገድ ገልጦላቸው ነበር፡፡ በየዘመናቱ በተነሱት ትውልዶች ውስጥ ግን መለኮታዊውን ትምህርት የሚበርዙ አሳሳቾች መነሳታቸው ስላልቀረ እግዚአብሄር ከነዚያ አሳቾች ህዝቡን ነጻ ያወጣ ዘንድ ነቢያትን አስነስቶ ሰማያዊውን እውቀት ደጋግሞ ልኮአል፡፡ በይሁዳ ነገሥታት በዖዝያንና በኢዮአታም በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ ተነስቶ መለኮታዊውን እውቀት ለህዝቡ ያውጅ ነበር። እግዚአብሔር ተናግሮአልና ሰማያት ስሙ፥ ምድርም አድምጪ… ሲልም ተናግሮአል፡፡(ኢሳ.1:1) ህዝቡም የእግዚአብሄርን ነገር ያስተውል ዘንድ መመልከት የነበረበት፣ እንዲሁም ማወቅና ማመን ያለበት የእግዚአብሄር ነገር ምን እንደነበር ሲያሳይ እንዲህ ይል ነበር፡- • የእግዚአብሄር ምክርና ብርቱ እጅ ከጠላትና ከፈተና ያድናቸው ዘንድ እንዳለው ሊያውቁና ሊያምኑ ይገባል ኢሳ.43:1-3 ”አሁንም ያዕቆብ ሆይ፥ የፈጠረህ፥ እስራኤልም ሆይ፥ የሠራህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ተቤዥቼሃለሁና አትፍራ፤ በስምህም ጠርቼሃለሁ፥ አንተ የእኔ ነህ። በውኃ ውስጥ ባለፍህ ጊዜ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፥ በወንዞችም ውስጥ ባለፍህ ጊዜ አያሰጥሙህም፤ በእሳትም ውስጥ በሄድህ ጊዜ አትቃጠልም፥ ነበልባሉም አይፈጅህም። እኔ የእስራኤል ቅዱስ አምላክህ እግዚአብሔር መድኃኒትህ ነኝ፤ ግብጽን ለአንተ ቤዛ አድርጌ፥ ኢትዮጵያንና ሳባንም ለአንተ ፋንታ ሰጥቻለሁ።” ህዝቡ በዚህ እወቀት ሲገነቡ እርሱ የአባታቸው የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር መድኃኒታቸው መሆኑን ስለሚያምኑ አባቶቻቸውን በረዳበት ክንድ እነርሱም መረዳት እንደሚችሉ ያስተውላሉ፡፡ • እግዚአብሄር ህዝቡን እንደሚወድ ሊያውቁ የተገባ ነው ኢሳ.43:4 ”በዓይኔ ፊት የከበርህና የተመሰገንህ ነህና፥ እኔም ወድጄሃለሁና ስለዚህ ሰዎችን ለአንተ አሕዛብንም ለነፍስህ እሰጣለሁ።” እግዚአብሄር እንደሚወዳቸው እንዲያውቁ የሚያስፈሩና የሚያስደነግጡዋቸው ነገስታቶችን ማርኮ ከእግራቸው በታች ሊያደርግ እንዳለው በማመልከት ተናግሮአቸዋል፡፡ • እግዚአብሄር ከህዝቡ ጋር እንደሆነና ለህዝቡ ምርኮን ሁሉ እንደሚመልስ ሊያውቁ ይገባል ኢሳ.43:5-7 ”እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ ዘርህንም ከምሥራቅ አመጣዋለሁ፥ ከምዕራብም እሰበስብሃለሁ። ሰሜንን፡- መልሰህ አምጣ፥ ደቡብንም፡- አትከልክል፤ ወንዶች ልጆቼን ከሩቅ ሴቶች ልጆቼንም ከምድር ዳርቻ፥ በስሜ የተጠራውን ለክብሬም የፈጠርሁትን፥ የሠራሁትንና ያደረግሁትን ሁሉ አምጣ እለዋለሁ።” ይቀጥላል... ምንጭ፦ tsionvoice.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ምድራቸውን ትወርሳት ዘንድ የምትገባው ስለ ጽድቅህና ስለ ልብህ ቅንነት አይደለም፤ ነገር ግን አምላክህ እግዚአብሔር ከፊትህ በሚያጠፋ
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ምድራቸውን ትወርሳት ዘንድ የምትገባው ስለ ጽድቅህና ስለ ልብህ ቅንነት አይደለም፤ ነገር ግን አምላክህ እግዚአብሔር ከፊትህ በሚያጠፋቸው በእነዚያ አሕዛብ ኃጢአት ምክንያትና ለአባቶችህ ለአብርሃምና ለይስሐቅ ለያዕቆብም የማለላቸውን ቃል ይፈጽም ዘንድ ነው።” ዘዳግም 9፥5 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

የቀጠለ... የእግዚአብሔር መልስ እግዚአብሔር መልሱን የሚያዘገዬው ካለ እርሱ ምንም ማድረግ እንደማንችል ሊያስገነዝበን ሲወድ ነው። “ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉም” (ዮሐ15፡5) ብሏልና። አባታችን ሙሴ እስራኤላውያንን እየመራ ከግብፅ ያወጣቸው ለአገልግሎት ከተጠራ ከአርባ አመት በኋላ 80 ሲሞላው ነበር። አርባ አመት ሙሉ ግን በሲና በርሃ እጅግ አስቸጋሪ በሆነው ሙቀት ውስጥ የዮቶርን በጎች ይጠብቅ ዘንድ ግድ ነበር።(ዘጸ 4፡18) 3. ምንም ላይመልስልን ይችላል፡-  ላቀረብነው ልመና ምንም አይነት ምላሽ ካላገኘን፤ ያ ማለት እኛ ከጠየቅነው ጥያቄ በላይ የተሻለ ነገር አስቦልናል ማለት ነው። እኛ ሰዎች ደካሞች እንደመሆናችን የሚጎዳንና የሚጠቅመንን ለይተን ማወቅ ስለማንችል አጥብቀን የፈለግነው ነገር ምላሹ ከቀረ፤ ሌላ የተሻለ ነገር እግዚአብሔር እያዘጋጀልን እንደሆነ እንመን። በእርግጥ አንዳንድ ጊዜ ሰዎች ሳያውቁት የሚጠፉበትን ነገር ወይም ደግሞ ሌሎችን የሚጎዳ ነገር ሊለምኑ ይችላሉ። በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር በሰዎች ጥፋት ተባባሪ ስለማይሆን “ይህ አይሆንም!” ሊለን ይችላል። የዘብዴዎስ ልጆች እናት ያቀረበችው ልመና ልጆቿን ለመስቀል ሞት የሚያበቃ ስለነበር የተሰጣት ምላሽ “የምትለምኑትን አታውቁም”(ማቴ.20፡22) የሚል ነበር። ይህን ሁሉ የእግዚአብሔር የአሰራር መንገዶች ከተገነዘብን የእርሱን መልስ ስንጠብቅ ምን ምን ማድረግ ይኖርብናል የሚሉትን ነጥቦች ደግሞ እንደሚከተለው እንመልከት፡- 1.በእምነት መኖር እግዚአብሔር አምላክ ሰምቶ እንዳልሰማ አይቶም እንዳላየ ዝም የሚል አምላክ አለመሆኑን ማመን አለብን። እርሱ የሚሰማ የሚመልስም ነው እንጂ። ችግርና መከራ ሲገጥመን እግዚአብሔር እንደሚረዳንና እንዲያውም ለእኛ በጣም ቅርብ የሚሆነው በዚህ ጊዜ መሆኑን ማመን አለብን። ዳንኤል የእግዚአብሔርን መልአክ ያየው እጅግ አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ በወደደቀበት ወቅት በአንበሶች ጉድጓድ ውስጥ ነው። አናንያ፤አዛርያና ሚሳኤልም መልአኩን ያዩት በእሳት ውስጥ ሆነው ነው። እርሱ የእኛ ጭንቀት ተካፋይ ስለመሆኑ ነቢዩ ኢሳይያስ “በጭንቃቸውም ሁሉ እርሱ ተጨነቀ”(ኢሳ63፡9) በማለት ተናግሯል። እኛ ስንጨነቅ፤ በዳር ሆኖ የሚያየን ሳይሆን አብሮን የሚጨነቅ አምላክ እንዳለን ስናስብ ምን ያህል ልባችን በደስታ ይሞላ ይሆን? ስለዚህ የእግዚአብሔርን መልስ ስንጠብቅ በእርሱ ላይ ያለን እምነት የተደላደለና የማይነቃነቅ መሆን ይኖርበታል።(1ቆሮ 5፡58) 2.በተስፋ ክርስትና በተስፋ የሚኖሩት ህይወት ነው። ክርስቲያንም የሚኖረው ከሚታዩት ነገሮች በላይ ስለሆነ በዚህ አለም እያለ በሚያጣቸው፤ ሀላፊ ጠፊ በሆኑ ነገሮች ተስፋ አይቆርጥም። በሥጋዊውም ሆነ በመንፈሳዊ ህይወት የሚያስፈልገንን ነገር ጠይቀን መልሱን የምንጠብቀው በተስፋ ነው። አንዳንድ ጊዜ የወደፊቱ ህይወታችን ድቅድቅ ጨለማ የዋጠው መስሎ የሚታየን ጊዜ ይኖራል። በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር አምላክ የተናገራቸውን የተስፋ ቃላት በህሊናችን መድገም በቃላችን ማስታወስ ይኖርብናል። “በህይወትህ ዕድሜ ሁሉ... አልጥልህም፤አልተውህም”(ኢሳ1፡5) “እኔ ከአንተ ጋር ነኝና...አትፍራ”(ሐዋ.18፡10) እግዚአብሔር አምላክ ለጥቂት ጊዜ የተወን ቢመስልም ለዘለአለሙ ግን ይሰበስበናልና ተስፋችን እርሱ ብቻ ሊሆን ይገባል። እርሱን ተስፋ ያደረገ ሰው ከቶውንም ቢሆን አይወድቅምና። በአንድ ቀን ውስጥ ጨለማና ብርሃን እንደሚፈራረቁ ሁሉ በሰው ልጅ ህይወትም ፈተናና ደስታ ይፈራረቃሉ።ስቅለት እንዳለ ሁሉ ፋሲካም ይኖራል፤ ስለዚህ በስቅለት ያዘነ የተከዘ ሰው በፋሲካው ደግሞ ይደሰታል። በስቅለት ካላለፉ በቀር ስለፋሲካ ማውራት እንደሚከብደው ሁሉ ደስታም ያለ ፈተና ሊመጣ አይችልም። ለዚህ ነው ሐዋሪያው ያዕቆብ በመልእክቱ “ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቁጠሩት”(ያዕ.1፡2) ያለው። ይህ የተስፋ ቃል የተነገረው ጽኑ የሆነው መከራችን አስከትሎ የሚያመጣው በረከት ስላለ ነው። የገጠመን አስጨናቂ ፈተና ደስታን እንደሚያመጣልን ተስፋ የምናደርግ ስንቶቻችን እንሆን? 3.በፍቅር ቀድሞ ስናደርግ እንደነበረው ሰውንም እግዚአብሔርንም መውደድ፤ ለሁሉም የሚገባውን ክብር መስጠት የእርሱን መልስ ስንጠብቅም መቀጠል አለበት። ዮሴፍ ያለ ኃጢአቱ ስለ ታሰረ፤ በእስር ቤት ሆኖ የእግዚአብሔርን መልስ ይጠብቅ ነበር። ነገር ግን በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ እንኳን በእስር ቤት ውስጥ እግዚአብሔርንም ሰውንም በፍቅር ያገለግል ነበር እንጂ ድሮ ያደርግ የነበረውን ነገር አላቋረጠም። ብዙ ሰዎች ግን የጸሎታቸው ምላሽ ሲዘገይ ቀድሞ ያደርጉ የነበሩትን ነገሮች እርግፍ አድረገው ይተዋሉ። በፊት ከቤተ ክርስቲያን የማይለዩት፤ በቀን ሁለት ጊዜ የሚጸልዩት አሁን ጨርሰው ይጠፋሉ፤ ከጸሎትም ይሸሻሉ። ምክንያታቸውን ሲገልጹም እግዚአብሔር እንደረሳቸው፤ ለጸሎታቸውም ምላሽን እንዳጡ ይናገራሉ። እነዚህ ሰዎች የዘነጉት ነገር ቢኖር እግዚአብሔር አምላክ ማንንም እንደማይረሳ ነው። “ሴት ከማህፀንዋ ለተወለደው ሕፃንዋ እስከማትራራ ድረስ ልትረሳ ብትችልም” እርሱ ግን ፈጽሞ ሰው እንደማይረሳ የተናገረ አምላክ ነው።(ኢሳ.49፡15)      ስለዚህ ሰማይና ምድር ቢያልፉም እነርሱ ጸንተው የሚኖሩትን፤ ሦስቱን የክርስትና ሃይማኖት የእምነት ምሰሶዎች “እምነትን፤ ተስፋን፤ ፍቅርን” (1ቆሮ.13፡13) አንግበን፤ ከሁሉም በሚበልጠው በፍቅር ከአምላካችን ጋር ተሳስረን፤  ከፊት ለፊታችን የሚጠብቀንን ሩጫ በትእግስት እንሩጥ። ለአባቶቻችን የተለመነ አምላክ ለእኛም መሻታችን ይፈጽምልናልና እምነታችንን አጽንተን የእርሱን መልስ እንጠብቅ። እርሱን ተስፋ አድርጎ ያፈረ የለምና ተስፋችንንም በእርሱ ላይ እንጣለው። “የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔርም ያለቀ የተቆረጠ ነገርን በምድር መካከል ሁሉ ይፈጽማል”(ኢሳ 10፡23) ከእኛ የራቀ ቢመስለንም ምን ጊዜም ከአጠገባችን መሆኑንም አንዘንጋ። አንድያ ልጁን ሳይሳሳ የሰጠን አምላክ የእኛን ልመና እነዴት አይቀበለን? ምንጭ:- deaconfikreselassie.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ቢሰሙ ቢያገለግሉትም፥ ዕድሜአቸውን በልማት፥ ዘመናቸውንም በተድላ ይፈጽማሉ።” ኢዮብ 36፥11 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ቢሰሙ ቢያገለግሉትም፥ ዕድሜአቸውን በልማት፥ ዘመናቸውንም በተድላ ይፈጽማሉ።” ኢዮብ 36፥11 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ጻድቃንን ትባርካቸዋለህ፤ በሞገስህም እንደ ጋሻ ትከልላቸዋለህ።” መዝሙር 5፥12 (አዲሱ መ.ት) ወደ ቻናሉ
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ጻድቃንን ትባርካቸዋለህ፤ በሞገስህም እንደ ጋሻ ትከልላቸዋለህ።” መዝሙር 5፥12 (አዲሱ መ.ት) ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “በዚያም ቀን፦ እነሆ፥ አምላካችን ይህ ነው፤ ተስፋ አድርገነዋል፥ ያድነንማል፤ እግዚአብሔር ይህ ነው፤ ጠብቀነዋል፤ በማዳኑ ደስ ይለና
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “በዚያም ቀን፦ እነሆ፥ አምላካችን ይህ ነው፤ ተስፋ አድርገነዋል፥ ያድነንማል፤ እግዚአብሔር ይህ ነው፤ ጠብቀነዋል፤ በማዳኑ ደስ ይለናል ሐሤትም እናደርጋለን ይባላል።” ኢሳይያስ 25፥9 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

የእግዚአብሔር መልስ ልዑለ ባህርይ እግዚአብሔር በሰው ልጆች ውስጥ ያለችውን ነፍስ የፈጠረው በአርአያውና በአምሳሉ ነው። የቀሩትን ፍጥረታት “ይሁን” እያለ በቃሉ ብቻ ካለመኖር ወደ መኖር ሲያመጣ፤ የሰውን ልጅ ግን ከምድር አፈር በመውሰድ በእጆቹ ከፈጠረው በኋላ እስትንፋሱን እፍ በማለት ሕያው እንዲሆን አድርጎታል። በዚህም ምክኒያት የሰው ልጅ ከሌሎቹ ፍጥረታት ሁሉ እጅግ የላቀ መሆኑን ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ “ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬያለሁና አመሰግንሃለሁ፤ ሥራህ ድንቅ ነው ነፍሴም እጅግ ታውቀዋለች”(መዝ.139፡14) በማለት ገልጾታል። ጌታችንም በቅዱስ ወንጌል የሰው ልጅ ከፍጥረታት ሁሉ የከበረ መሆኑን ሲገልጽ “የራሳችሁ ፀጉር እንኳን የተቆጠረ ነው”(ሉቃ.12፡7) በማለት እነርሱ የሚችሉትን ብቻ ይስሩ እንጂ ሌላ የሚያሳስባቸውን ነገር ሁሉ በእርሱ ላይ እንዲጥሉ የማጽናኛ ቃል ይነግራቸው ነበር። ሳይታክቱ ዘወትር እርሱን ደጅ እንዲጠኑም “...ለምኑ ይሰጣችኋል፤ ፈልጉ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ ይከፈትላችሁማል”(ማቴ 7፡7) በማለት ያስተምራቸዋል። እውነቱ ይህ ሆኖ ሳለ በዘመናችን የብዙ ሰዎች ጥያቄ ግን “እኔ እግዚአብሔርን ዘወትር ደጅ እጠናለሁ፤ እንደ ቃሉም እሄዳለሁ፤ ነገር ግን ለጠየቅሁት ጥያቄ ሁሉ የእግዚአብሔር መልስ የት አለ? እስከመቼስ ልጠብቀው?” የሚል ነው። የእግዚአብሔር መልስ በዘገየ ቁጥርም እነርሱ አላስፈላጊ ወደ ሆነ ጭንቀትና ፍርሃት ውስጥ ይወድቃሉ። በመሠረቱ የሚፈራና የሚጨነቅ ሰው የእግዚአብሔርን ፍቅርና ቃልኪዳን የረሳ ሰው ስለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም። በዚህ ጽሑፍ የእግዚአብሔር መልስ በምን መልኩ ወደ ህይወታችን ሊመጣ እንደሚችልና እኛም ደግሞ የእርሱን መልስ ስንጠብቅ ምን ማድረግ እንደሚገባን በመጠኑ ለመዳሰስ እንሞክራለን። እግዚአብሔር አምላክ ሥራዎቹን የሚሰራበት ረቂቅ ጥበቡ ብዙ ጊዜ ከሰው አስተሳሰብና አመለካከት ጋር አብሮ ሲሄድ አይታይም። “ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል እንዲሁ መንገዴ ከመንገዳችሁ አሳቤም ከአሳባችሁ ከፍ ያለ ነው”(ኢሳ 55፡8) እንዳለው የእርሱ አሳብ እና የሰው ልጆች አሳብ የሰማይና የምድር ያህል የተራራቀ ነው። ለምሳሌ አንድ ሰው የሚጎዳውን ነገር ዛሬ እንዲሰጠው አጥብቆ ሊለምን ይችላል። እግዚአብሔር ግን እንደሚጎዳው ስለሚያውቅ ያንን አስቀርቶ የሚጠቅመውን ነገር አዘግይቶ አስፈላጊ በሆነ ሰዓት ይሰጠዋል። ለዚህ ነው በመጽሐፍ ቅዱስ ጌታ እግዚአብሔር “…ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም” (ኤር. 29፡11) በማለት የሚናገረው። ስለዚህ አሳባችንን ከእርሱ አሳብ ጋር አንድ እንዲሆን መጸለይ እንጂ እርሱን ወደ እኛ አሳብ ለማምጣት መታገል የለብንም ማለት ነው። እግዚአብሔር አምላክ ገና ሳንለምነው የምንፈልገውን አውቆ የሚሰጠን አምላክ ስለመሆኑና የለመነውንም ነገር እንዳገኘነው እንድንቆጥር እንዲህ በማለት ያስተምረናል “...ስለዚህ እላችኋለሁ፤ የጸለያችሁትን የለመናችሁትንም ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ፤የሆንላችሁማል”(ማር.11፡24) ይህን ሁሉ የተስፋ ቃል በልባችን ውስጥ ካስቀመጥን፤ የእግዚአብሔር መልስ በእነዚህ በሦስት አይነቶች ወደ ህይወታችን ሊመጣ እንደሚችል መገንዘብ እንችላለን፡- 1. በጠየቅነው ዕለት ወይም በፍጥነት፡-  እግዚአብሔር አምላክ ለጠየቅነው ጥያቄ ፈጣን ምላሽ ሊሰጠን ይችላል። ይህ ከሆነ በእርሱ ላይ ያለንን እምነት እንድናጠነክር ፈቃዱ ሆኗል ማለት ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ለጥያቄያቸው ፈጣን ምላሽ የተሰጣቸው ሰዎች አሉ። የመቶ አለቃው ልጁን እንዲፈውስለት ወደ ጌታ ቀርቦ “ጌታ ሆይ...ቃል ብቻ ተናገር ብላቴናዬም ይፈወሳል” (ማቴ.8፡8) ብሎ ሲማጸነው ወዲያውኑ ነበር የመለሰለት። ይህም የሆነበት ምክኒያት የመቶ አለቃው ከመጀመሪያው በጌታ ላይ እምነት ስለነበረው ያንኑ ሊያጠናክርለት ስለፈቀደ ነው። ከጌታ ቀኝ ተሰቅሎ የነበረው ጥጦስም የሆነውን ሁሉ ከተመለከተ በኋላ ክርስቶስ እውነተኛ የባህሪ አምላክ መሆኑን ሲያረጋግጥ “ጌታ ሆይ፡- በመንግስትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ” ብሎ ሲጠይቀው ጊዜ ሳይወስድ ወዲያውኑ ነበር “እውነት እልሀለሁ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትሆናለህ” ያለው(ሉቃ.23፡43) ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን የሰዎችን የአጋንንትንም ልመና በፍጥነት የመለሰበት ጊዜ ነበር። ክርስቶስን አይተው እንዳያጠፋቸው ስለተጨነቁ “ወደ እሪያው መንጋ ስደደን”(ማቴ.8፡31) ብለው ሲለምኑት እንዲገቡ ፈቅዶላቸዋል። በሽተኞችን፤ ታመው የአልጋ ቁራኛ የሆኑትን፤ የተሸከማቸውን አልጋ ተሸክመው እንዲሄዱ አድርጓቸዋል።እኛስ በህይወታችን ስንት ጊዜ እግዚአብሔር በፍጥነት መልሶልን እኛ ግን እረስተነው ይሆን? ብዙ ሰዎች ታመው አልጋ ላይ ሲሆኑ፤ ወይም በጭንቀት ውስጥ ሲወድቁ እግዚአብሔርን ይማጸኑና እርሱም ከበሽታቸው ሲፈውሳቸው፤ ከጭንቀታቸው ሲላቀቁ  ይረሱታል። በእርግጥ የሰው ልጅ ብዙ ጊዜውን የሚያሳልፈው እግዚአብሔር ወደ ፊት የሚሰጠውን ነገር በማሰብ ወይም ደግሞ እርሱ የከለከለውን ነገር በማሰላሰል እንጅ እስካሁን ስለተደረገው ነገር በማመስገን አይደለም። የተደረገልን ነገር በሙሉ በእኛ ኃይልና ብርታት ከመሰለንና ለእርሱ የሚገባውን ድርሻ ለእኛ የምናደርግ መሆናችንን ካወቀ ወይም ደግሞ በእርሱ ላይ ያለንን ትእግስት መፈተን ከፈለገ እግዚአብሔር ጸሎታችን የሚመልስልን በሚከተለው አማራጭ ይሆናል። 2. ከብዙ ጊዜ በኋላ ዘግይቶ ሊመልስልን ይችላል፡-  ይህ የሚሆነው ደግሞ እግዚአብሔር የእኛን ትእግስት መፈተን የፈለገ እንደሆነ ነው። ለአብርሃም “በዘርህ አሕዛብ ይባረካሉ” ካለው በኋላ እጅግ ዘግይቶ በእርጅናው ጊዜ ነው ይስሀቅን የሰጠው። የአባታችን የአብርሃም ትእግስትም በዚህ ተፈትኗል። ይቀጥላል... ምንጭ:- deaconfikreselassie.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures