en
Feedback
Tabor Bible Study (ሐዋሳ ታቦር መካነ ኢየሱስ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት)

Tabor Bible Study (ሐዋሳ ታቦር መካነ ኢየሱስ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት)

Open in Telegram

ሐዋሳ ታቦር መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን መጽሐፍ ቅዱስ የሚጠናበት የቴሌግራም ቻናል

Show more
1 083
Subscribers
No data24 hours
+167 days
+3930 days

Data loading in progress...

Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+13
in 1 channels
August '26
+58
in 1 channels
Get PRO
July '26
+37
in 1 channels
Get PRO
June '26
+54
in 1 channels
Get PRO
May '26
+85
in 2 channels
Get PRO
April '26
+65
in 1 channels
Get PRO
March '26
+79
in 1 channels
Get PRO
February '26
+26
in 2 channels
Get PRO
January '26
+68
in 1 channels
Get PRO
December '25
+50
in 2 channels
Get PRO
November '25
+26
in 2 channels
Get PRO
October '25
+85
in 3 channels
Get PRO
September '25
+71
in 1 channels
Get PRO
August '25
+44
in 2 channels
Get PRO
July '25
+72
in 4 channels
Get PRO
June '25
+122
in 2 channels
Get PRO
May '25
+245
in 2 channels
Get PRO
April '250
in 2 channels
Get PRO
March '25
+91
in 2 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
06 September+1
05 September+1
04 September+1
03 September+1
02 September+2
01 September+7
Channel Posts
የዓመቱ መጨረሻ እሑድ የኑዛዜ ቀን 👉ሕዝ. 34፥5-31 👉ራእ 2፥1-7 👉ማር. 11፥12-14፤ 20-24 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መ
የዓመቱ መጨረሻ እሑድ የኑዛዜ ቀን 👉ሕዝ. 34፥5-31 👉ራእ 2፥1-7 👉ማር. 11፥12-14፤ 20-24 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ጳጉሜ_1 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study

2
ርዕስ፦ የቅዱስ አውግስቲን ኑዛዜ ክፍል፦ 4 ምንጭ፦ @Reading_Life_1 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
112
3
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “አባታችሁ አንዱ እርሱም የሰማዩ ነውና በምድር ላይ ማንንም፦ አባት ብላችሁ አትጥሩ።”                   ማቴዎስ 23፥9 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_30 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
151
4
#ያልተለወጠው_የኦግስቡርግ_የሃይማኖት_መግለጫ ያልተለወጠው የኦግስቡርግ የሃይማኖት መግለጫ                 ክፍል-26 ስለዚህ፣ አስፈላጊ ናቸው ተብለው፣ ወይም ጽድቅን ያስገኛሉ በሚል ዐስተሳሰ የሚቋቋሙ ሥርዓቶች ከወንጌሉ ጋር የሚጋጩ ስለ ሆነ፣ እንደነዚህ ያሉትን የአምልክ ተግባራት ማቋቋምም ሆነ አስፈላጊ እንደ ሆኑ አድርጎ መደንገግ ለጳጳሳት ሕጋዊነት የለውም ማለት ነው:: ምክንያቱም በገላትያ [5፡1]፦ «እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ» ተብሎ እንደ ተጻፈው በሕግ መታሰር ለመጽደቅ አስፈላጊ አይደለም የሚለውን የክርስትናን ነጻነት የሚመለከተውን ትምህርት በአብያተ ክርስቲያናት አጥብቆ መያዝ አስፈላጊ ነው፡፡ ጸጋን የምናገኘው በክርስቶስ በማመን እንጂ አንዳንድ ሥርዓቶችን በመፈጸም ወይም በሰዎች በተቋቋሙ የአምልኮ ተግባራት አማካይነት አይደለም የሚለውን የወንጌልን ዋና አንቀጽ አጥብቆ መያዝ አስፈላጊ ነው፡፡ ስለዚህ፣ አንድ ሰው በአምልኮ ስፍራዎች ስለ እሑድና ተመሳሳይ ሥርዓቶች ማሰብ የሚገባው ምንድን ነው? ለዚህ ጒዳይ የእኛ ሰዎች ሲመልሱ በእነርሱ አማካይነት የኃጢአታችንን ዕዳ ክፍያ ለመፈጸም ወይም የሰው ሕሊና ለአምልኮ ተግባር አስፈላጊ እንደሆኑ አድርጎ እንዲቀበላቸው ለማስገደድ ሳይሆን፣ በቤተ ክርስቲያን ማንኛውም ነገር በሥርዓት እንዲካሄድ ጳጳሳትና ቀሳውስት ሥርዓቶችን ማቋቋማቸው ተገቢ ስለሆነ ነው ይላሉ፡፡ ስለ ሆነም ጳውሎስ ሴቶች በማኅበር ራሳቸውን እንዲሸፍኑ አዘዘ [1ቆሮ 11:5] ደግሞም በቤተ ክርስቲያን የሚተረጉሙ ሥርዓት ባለው መንገድ ሊደመጡ ይገባል ብሎአል [1ቆሮ 14፡30]፡፡ አብያተ ክርስቲያናት ለፍቅርና ለጸጥታ ሲባል ለእነዚህ ሥርዓቶች መታዘዛቸው ደግሞም ሌሎችን እስካላሰናከሉ ድረስ መጠበቃቸው ተገቢ ነው:: ስለ ሆነም፣ በአብያተክርስቲያናት ሁሉም ነገር በማያደናግር መልኩ ሥርዓት ባለው መንገድ መከናወን አለበት፤ ዳሩ ግን ሕሊና እንደ እነዚህ ያሉ ነገሮችን ለድነት አስፈላጊ ናቸው ብሎ በማሰብ፣ ወይም ያለ ማሰናከያ እነርሱን በሚተላለፍበት ጊዜ ኃጢአት አድርጌአለሁ በማለት በማይጨነቅበት መንገድ መሆን አለበት፡፡ ልክ አንዲት ሴት ማንንም በማያስቀይም ሁኔታ ራስዋን ሳትሸፍን ከቤት ብትወጣ ኃጢአት አደረገች ብሎ ማንም እንደማይናገር እንደዚሁ ነው። እሑድን፣ ፋሲካን፣ በዓለ ሃምሳንና የመሳሰሉትን በዓላትና ሥርዓቶች የመጠበቅም ጒዳይ እንደዚሁ ነው፡፡ ምክንያቱም፣ በሰንበት ምትክ እሑድን የማክበር አስፈላጊነት በቤተክርስቲያን ሥልጣን የተቋቋመ ነው ብለው የሚፈርጁ ሰዎች ተሳስተዋል፡፡ ሰንበትን ያስቀረው የእግዚአብሔር ቃል እንጂ ቤተ ክርስቲያን አይደለችም፡፡ ምክንያቱም ወንጌል ከተገለጠ በኋላ ሁሉም የሙሴ ሥነ ሥርዓቶች ሊወገዱ ይችላሉ፡፡ ይሁን እንጂ፣ ሕዝቡ መሰብሰብ የሚችሉበትን ቀን ያውቁ ዘንድ አንድ ቀን መመደብ አስፈላጊ እንደ መሆኑ መጠን ቤተ ክርስቲያን ለዚሁ ዓላማ እሑድን የመደበች ይመስላል፡፡ በዚህ ሁኔታ፣ ሰዎች ለክርስትና ነጻነት አንድ ምሳሌ ሊኖራቸውና ሰንበትንም ሆነ ሌላን ቀን ማክበር አስፈላጊ እንዳልሆነ ሊያውቁ ስለሚችሉ ይህ የሚያስደስት ነገር ነበር፡፡ ይቀጥላል . . . ምንጭ፦ Kolb, R., & Wengert, T. J. (Eds.). (2000). The Book of Concord: The Confessions of the Evangelical Lutheran Church. Fortress Press. ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
158
5
ርዕስ፦ የቅዱስ አውግስቲን ኑዛዜ ክፍል፦ 3 ምንጭ፦ @Reading_Life_1 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
157
6
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “እናንተ ግን፦ መምህር ተብላችሁ አትጠሩ፤ መምህራችሁ አንድ ስለ ሆነ እናንተም ሁላችሁ ወንድማማች ናችሁ።” ማቴዎስ 23፥8 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_29 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
176
7
#ያልተለወጠው_የኦግስቡርግ_የሃይማኖት_መግለጫ ያልተለወጠው የኦግስቡርግ የሃይማኖት መግለጫ                 ክፍል-25 እንደ ገናም፣ የወጎቹ መሥራቾች ኃጢአትን ከምግብ፣ ከቀናትና ከመሳሰሉ ነገሮች ጋር በማያያዛቸውና በቤተ ክርስቲያን ላይ የሕግ እስራትን በመጫናቸው ጽድቅን ለማግኘት እነዚህን ማቋቋም በዘሌዋውያን እንደሚታዩት ያሉ የአምልኮ ተግባራት በክርስቲያኖች መካከል ሊኖሩ ይገባ ይመስል፣ ደግሞም እግዚአብሔር እነዚህን እንዲያቋቁሙ ሐዋርያትንና ጳጳሳትን ያዘዘ ይመስል፣ ይህን ሲያደርጉ ከእግዚአብሔር ትእዛዝ ጋር በተቃረነ መልኩ መንቀሳቀሳቸው ነው፡፡ ምክንያቱም አንዳንዶች በዚህ መንገድ ጽፈዋል ጳጳሳቱም በሙሴ ሕግ ምሳሌነት በተወሰነ ደረጃ የተታለሉ ይመስላሉ፡፡ ከዚህም የሚከተሉት ሽክሞች ተፈጠሩ፡- ሌሎችን ባያስቀይምም እንኳ በበዓላት ቀኖች የጉልበት ሥራ መሥራት ሞት የሚገባው ኃጢአት እንደ ሆነ፣ አንዳንድ ምግቦች ሕሊናን የሚያረክሱ እንደ ሆኑ፣ ጾም ተፈጥሮአዊ ባልሆነ ዳሩ ግን አካላዊ ሥቃይን በሚያስከትልበት ጊዜ እግዚአብሔርን የሚያስደስት ሥራ እንደ ሆነ፣ ቀኖናዊ ሰዓታትን ማስተጓጐል ሞት የሚገባው ኃጢአት እንደ ሆነ፣ ምንም እንኳ ቀኖናዎቹ ራሳቸው የሚናገሩት በደልን ስለ መያዝ ሳይሆን የቤተ ክርስቲያንን ቅጣቶች ስለ መያዝ ቢሆንም፣ ጒዳዩን ከያዘው ሰው ፈቃድ ውጭ በተያዘ ጒዳይ ላይ ኃጢአትን ይቅር ለማለት አይቻልም የሚሉት ናቸው፡፡ ጳጳሳት ሕሊናን ለማጥመድ እንደዚህ ያሉትን ወጎች በቤተ ክርስቲያን ላይ የመጫንን መብት ከወዴት አገኙ? ጴጥሮስ በደቀ መዛሙርት ላይ ቀንበር መጫንን የከለከለበት ሐቅ እያለ፣ እንዲሁም ጳውሎስ ለማፍረስ ያይደለ ነገር ግን ለማነጽ ሥልጣን የተሰጣቸው መሆኑን እየተናገረ፣ እነርሱ በእንደዚህ ያሉ ወጎች አማካይነት ኃጢአትን የሚጨምሩት ለምንድን ነው? የሆነ ሆኖ፤ የእግዚአብሔርን ቊጣ ለማብረድ ወይም ለድነት አስፈላጊ እንደ ሆኑ አድርጎ ወጎችን መመሥረትን የሚከለክሉ ግልጽ የሆኑ ምስክሮች አሉ፡፡ ጳውሎስ በቈላስይስ 2[፡16፣20-23]፦ «እንግዲህ በመብል ወይም በመጠጥ ወይም ስለ በዓል ወይም ስለ ወር መባቻ ወይም ስለ ሰንበት ማንም አይፍረድባችሁ»፤ ደግሞም «ከዓለማዊ ከመጀመሪያ ትምህርት ርቃችሁ ከክርስቶስ ጋር ከሞታችሁ እንደ ሰው ሥርዓትና ትምህርት አትያዝ አትቅመስ፣ አትንካ ለሚሉት ትእዛዛት በዓለም እንደምትኖሩ ስለ ምን ትገዛላችሁ? እነዚህ ሁሉ በመደረግ ሊጠፉ ተወስነዋልና፤ ይህ እንደ ገዛ ፈቃድህ በማምለክና በትሕትና ሥጋንም በመጨቈን ጥበብ ያለው ይመስላል» ይላል፡፡ ቲቶ 1[፡14]፦ «ስለዚህ ምክንያት የአይሁድን ተረትና ከእውነት ፈቀቅ የሚሉትን ሰዎች ትእዛዝ ሳያዳምጡ ...» ይላል፡፡ ክርስቶስ በማቴዎስ 15[፡14] ወጎችን ስለሚፈልጉ ሰዎች፡- «ተዉአቸው፤ ዕውሮችን የሚመሩ ዕውሮች ናቸው» ይላል፡፡ ደግሞም «የሰማዩ አባቴ ያልተከለው ተክል ሁሉ ይነቀላል» [ማቴዎስ 15፡13] በማለት እንዲህ ያሉትን የአምልኮ ተግባራት ይቃወማል፡፡ ጳጳሳት ሕሊናዎችን እንደዚህ ባሉ ወጎች ለመጫን መብት ካላቸው፣ መጽሐፍ ቅዱስ ወጎች መመሥረትን እንደዚህ በተደጋጋሚ የሚከለክለው ለምንድን ነው? ለምንስ የአጋንንት ትምህርቶች ብሎ ይጠራቸዋል? መንፈስ ቅዱስስ ስለ እነርሱ ያስጠነቀቀው በከንቱ ነውን? ይቀጥላል . . . ምንጭ፦ Kolb, R., & Wengert, T. J. (Eds.). (2000). The Book of Concord: The Confessions of the Evangelical Lutheran Church. Fortress Press. ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
175
8
ርዕስ፦ የቅዱስ አውግስቲን ኑዛዜ ክፍል፦ 2 ምንጭ፦ @Reading_Life_1 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
169
9
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “. . . በአንድ በደል ምክንያት ፍርድ ለኵነኔ ወደ ሰው ሁሉ እንደ መጣ፥ እንዲሁም በአንድ ጽድቅ ምክንያት ስጦታው ሕይወትን ለማጽደቅ ወደ ሰው ሁሉ መጣ።” ሮሜ 5፥18 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_28 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
210
10
ርዕስ፦ የቅዱስ አውግስቲን ኑዛዜ ክፍል፦ 1 ምንጭ፦ @Reading_Life_1 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
223
11
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “ስለዚህ ምክንያት ኃጢአት በአንድ ሰው ወደ ዓለም ገባ በኃጢአትም ሞት፥ እንደዚሁም ሁሉ ኃጢአትን ስላደረጉ ሞት ለሰው ሁሉ ደረሰ፤” ሮሜ 5፥12 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_27 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
240
12
ርዕስ፦ መጽሐፍ ቅዱስን እናጥና ጸሐፊ፦ ዮሴፍ ቸርች ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
186
13
No text...
189
14
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “በልቅሶ ወጡ እኔም በማጽናናት አመጣቸዋለሁ፤ በወንዝ ዳር በቅን መንገድ አስኬዳቸዋለሁ፥ በእርሱም አይሰናከሉም፤ እኔ ለእስራኤል አባት ነኝና፥ ኤፍሬምም በኵሬ ነውና።” ኤርምያስ 31፥9 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_26 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
251
15
#አዲስ_ዓመት #New_Year 👉ርዕስ፦ መጽሐፍ ቅዱስን በሚገባ ለመረዳት ✍ጸሐፊ፦ ቲ. ኖርተን ስቴሬት 🗣ትርጉም፦ ተክሉ መንገሻ ይህ መጽሐፍ፣ መጽሐፍ ቅዱስን በሚገባ ለመረዳት በጣም ጠቃሚ መጽሐፍ ስለሆነ በአዲስ ዓመት ቅዱሳት መጻሕፍትን በአዲስ መልኩ ለማጥናት ሁነኛ መጽሐፍ እንደሆነ አምነን እነሆ ብለናችኋል። በውስጡም የሚከተሉትን ጉዳዮች አካቷል፦ መሠረታዊ አሳቦች 👉መጽሐፍ ቅዱስን ማን ሊረዳው ይችላል? 👉ለማጥናት ትክክለኛውን መሣሪያ እንዴት መጠቀም እችላለሁ? 👉ለማጥናት እንዴት መጀመር እችላለሁ? አጠቃላይ መመሪያዎች 👉አገባቡን፣ ቃላትን፣ ሰዋሰውን እና የደራሲውን ዓላማ እንዴት ልረዳው እችላለሁ? 👉ቅድመ ሁኔታውን ማጥናት 👉ቅዱስ ቃሉን በራሱ መተርጎም ልዩ መመሪያዎች 👉ዘይቤያዊ አነጋገር፣ ተምሳሌቶች(Symbols), አምሳያዎች (Types), ምሳሌዎችና ምሳሌያዊ ገለጣዎች 👉የዕብራይስጥ ቋንቋ ፈሊጦች፣ ሥነ-ግጥም መረዳት 👉ትንቢት እና ትምህርተ-ሃይማኖት መረዳት 👉የብሉይና የአዲስ ኪዳናት ግንኙነትን መረዳት በስተመጨረሻም ያጠናነውን ለግል ጥቅም ሥራ ላይ ማዋል እንዴት እንደሚቻል የሚያብራራ ድንቅ መጽሐፍ ነው። ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
196
16
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “እግዚአብሔር . . . ስለ ያዕቆብ ደስ ይበላችሁ ስለ አሕዛብም አለቆች እልል በሉ፤ አውሩ፥ አመስግኑ፦ እግዚአብሔር ሕዝቡን የእስራኤልን ቅሬታ አድኖአል በሉ።” ኤርምያስ 31፥7 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_25 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
284
17
የእለቱ የመልእክትና የወንጌል ክፍል #የመልእክት_ክፍል ኤርምያስ 31 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁷ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፦ ስለ ያዕቆብ ደስ ይበላችሁ ስለ አሕዛብም አለቆች እልል በሉ፤ አውሩ፥ አመስግኑ፦ እግዚአብሔር ሕዝቡን የእስራኤልን ቅሬታ አድኖአል በሉ። ⁸ እነሆ፥ ከሰሜን አገር አመጣቸዋለሁ፥ ከምድርም ዳርቻ እሰበስባቸዋለሁ፥ በመካከላቸውም ዕውሩና አንካሳው ያረገዘችና የወለደችም በአንድነት ታላቅ ጉባኤ ሆነው ወደዚህ ይመለሳሉ። ⁹ በልቅሶ ወጡ እኔም በማጽናናት አመጣቸዋለሁ፤ በወንዝ ዳር በቅን መንገድ አስኬዳቸዋለሁ፥ በእርሱም አይሰናከሉም፤ እኔ ለእስራኤል አባት ነኝና፥ ኤፍሬምም በኵሬ ነውና። ሮሜ 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹² ስለዚህ ምክንያት ኃጢአት በአንድ ሰው ወደ ዓለም ገባ በኃጢአትም ሞት፥ እንደዚሁም ሁሉ ኃጢአትን ስላደረጉ ሞት ለሰው ሁሉ ደረሰ፤ ¹³ ሕግ እስከ መጣ ድረስ ኃጢአት በዓለም ነበረና ነገር ግን ሕግ በሌለበት ጊዜ ኃጢአት አይቈጠርም፤ ¹⁴ ነገር ግን በአዳም መተላለፍ ምሳሌ ኃጢአትን ባልሠሩት ላይ እንኳ፥ ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ ድረስ ሞት ነገሠ፤ አዳም ይመጣ ዘንድ ላለው ለእርሱ አምሳሉ ነውና። ¹⁵ ነገር ግን ስጦታው እንደ በደሉ መጠን እንደዚያው አይደለም፤ በአንድ ሰው በደል ብዙዎቹ ሞተዋልና፥ ነገር ግን የእግዚአብሔር ጸጋና በአንድ ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የሆነው ስጦታ ከዚያ ይልቅ ለብዙዎች በዛ። ¹⁶ አንድ ሰውም ኃጢአትን በማድረጉ እንደ ሆነው መጠን እንደዚያው ስጦታው አይደለም፤ ፍርድ ከአንድ ሰው ለኵነኔ መጥቶአልና፥ ስጦታው ግን በብዙ በደል ለማጽደቅ መጣ። ¹⁷ በአንዱም በደል ሞት በአንዱ በኩል ከነገሠ፥ ይልቁን የጸጋን ብዛትና የጽድቅን ስጦታ ብዛት የሚቀበሉ በአንዱ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በሕይወት ይነግሣሉ። ¹⁸ እንግዲህ በአንድ በደል ምክንያት ፍርድ ለኵነኔ ወደ ሰው ሁሉ እንደ መጣ፥ እንዲሁም በአንድ ጽድቅ ምክንያት ስጦታው ሕይወትን ለማጽደቅ ወደ ሰው ሁሉ መጣ። ¹⁹ በአንዱ ሰው አለመታዘዝ ብዙዎች ኃጢአተኞች እንደ ሆኑ፥ እንዲሁ ደግሞ በአንዱ መታዘዝ ብዙዎች ጻድቃን ይሆናሉ። ²⁰-²¹ በደልም እንዲበዛ ሕግ ጭምር ገባ፤ ዳሩ ግን ኃጢአት በበዛበት፥ ኃጢአት በሞት እንደ ነገሠ፥ እንዲሁ ደግሞ ጸጋ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተነሣ በጽድቅ ምክንያት ለዘላለም ሕይወት ይነግሥ ዘንድ፥ ጸጋ ከመጠን ይልቅ በለጠ። #የወንጌል_ክፍል ማቴዎስ 23 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ለሕዝቡና ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ ብሎ ነገራቸው፦ ² ጻፎችና ፈሪሳውያን በሙሴ ወንበር ተቀምጠዋል። ³ ስለዚህ ያዘዙአችሁን ሁሉ አድርጉ ጠብቁትም፥ ነገር ግን እየተናገሩ አያደርጉትምና እንደ ሥራቸው አታድርጉ። ⁴ ከባድና አስቸጋሪ ሸክም ተብትበው በሰው ትከሻ ይጭናሉ፥ እነርሱ ግን በጣታቸው ስንኳ ሊነኩት አይወዱም። ⁵ ለሰውም እንዲታዩ ሥራቸውን ሁሉ ያደርጋሉ፤ ስለዚህ አሽንክታባቸውን ያሰፋሉ ዘርፉንም ያስረዝማሉ፥ ⁶ በምሳም የከበሬታ ስፍራ፥ በምኵራብም የከበሬታ ወንበር፥ ⁷ በገበያም ሰላምታና፦ መምህር ሆይ መምህር ሆይ ተብለው እንዲጠሩ ይወዳሉ። ⁸ እናንተ ግን፦ መምህር ተብላችሁ አትጠሩ፤ መምህራችሁ አንድ ስለ ሆነ እናንተም ሁላችሁ ወንድማማች ናችሁ። ⁹ አባታችሁ አንዱ እርሱም የሰማዩ ነውና በምድር ላይ ማንንም፦ አባት ብላችሁ አትጥሩ። ¹⁰ ሊቃችሁ አንድ እርሱም ክርስቶስ ነውና፦ ሊቃውንት ተብላችሁ አትጠሩ። ¹¹ ከእናንተም የሚበልጠው አገልጋያችሁ ይሆናል። ¹² ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳል፥ ራሱንም የሚያዋርድ ሁሉ ከፍ ይላል። ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
288
18
ከሥላሴ በኋላ 10ኛ እሑድ እውነተኛና ሐሰተኛ ጽድቅ 👉ኤር. 31፥7-9 👉ሮሜ 5፥12-21 👉ማቴ. 23፥1-12 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀ
ከሥላሴ በኋላ 10ኛ እሑድ እውነተኛና ሐሰተኛ ጽድቅ 👉ኤር. 31፥7-9 👉ሮሜ 5፥12-21 👉ማቴ. 23፥1-12 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_24 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
272
19
https://www.youtube.com/watch?v=CV7uNeLZU9k&list=RDCV7uNeLZU9k&start_radio=1
248
20
.    ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨               የዕለቱ ጥቅስ       ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ “እንዲህም አለ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ነቢይ በገዛ አገሩ ከቶ አይወደድም።” ሉቃስ 4፥24 በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_23 የዕለቱ ንባብ ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
287