en
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Open in Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 331 subscribers, ranking 1 756 in the Transport category and 2 541 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 331 subscribers.

According to the latest data from 17 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 95 over the last 30 days and by 18 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 41.14%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.24% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 485 views. Within the first day, a publication typically gains 2 032 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 16.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 17 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Transport category.

13 331
Subscribers
+1824 hours
+417 days
+9530 days
Posts Archive
የጋምቤላ - አቦቦ - ጎግ - ዲማ፣ ኮንትራት 2፡ ፑኝውዶ - ጎግ - ጊሎ ወንዝ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመልካም የግንባታ አፈጻጸም ላይ ይገኛል አዲስ አበባ ፣ ጥር 01 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ መ አ) በጋምቤላ ህዝቦች ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በአኝዋሃ ዞን እየተገነባ የሚገኘዉ የጋምቤላ - አቦቦ - ጎግ - ዲማ ፣ ኮንትራት 2 ፑኝውዶ - ጎግ - ጊሎ ወንዝ ኪሎ ሜትር 72 የመንገድ ዲዛይንና ግንባታ ፕሮጀክት በመልካም የግንባታ አፈጻጸም ላይ ይገኛል፡፡ የመንገድ ግንባታዉ ከተጀመረ አራት አመታትን ያስቆጠረ ሲሆን አሁናዊ የግንባታ አፈጻጸሙ 90.1 በመቶ ላይ ደርሷል። በዚህም የግንባታዉ ዋና ዋና ስራዎች እየተገባደዱ ይገኛሉ፡፡ ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ 876 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ከምትገኘዉ ፒኝውዶ ከተማ መነሻዉን በማድረግ ጊሎ ወንዝን ተሻግሮ ፍጻሚዉን ያገኛል፡፡ መንገዱን እየገነባ የሚገኘዉ የሥራ ተቋራጭ ቻይና ሬይል ዌይ ሰቨንዝ ግሩፕ ሲሆን የማማከር እና ቁጥጥር ስራው ደግሞ ኢንጅነር ዘውዴ እስክንድር ኮንሰልቲንግ እና እንስራድ ሲቪል ሲስተምስ ኢንጂነሪንግ በጣምራ እያከናወኑ ይገኛሉ፡፡ መንገዱ የሚገነባበት መልከዓ-ምድራዊ አቀማመጥ 12.5 % ሜዳማ ሲሆን 87.5% ደግሞ ጠመዝማዛ ነው፡፡ የመንገዱ የጎን ስፋት የመንገድ ትከሻን ጨምሮ በገጠር 10 ሜትር ፤ በቀበሌ 12 ሚትር ፤ በወረዳ ከተማ ደግሞ 21.5 ሜትር ተጨማሪ ስፋት እንዲኖረዉ ተደርጎ ነዉ እየተገነባ የሚገኘዉ፡፡ የዚህ መንገድ ግንባታ 60 ሜትር ርዝማኔ ያለዉ የጊሎ ወንዝ ድልድልይ ስራ የሚያካትት ሲሆን ተጨማሪ 110 በላይ ጥቃቅን የፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦዎች ግንባታም የፕሮጀክቱ አካል ናቸዉ፡፡ የመንገዱ የቀድሞ ይዞታ ግማሹ ነባር የጠጠር መንገድ ሲሆን የተቀረዉ ምንም መንገድ ያልነበረበት አዲስ መስመር ነዉ፡፡ ባለፋት አመታት የአካባቢዉ ህብረተሰብ በመንገድ እጦት ምክንያት በርካታ እንግልት ሲያስተናግድ ቆይቷል። ይህ መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ አኝዋሃ ዞን ዉስጥ የሚገኙ ጎግ ወረዳን ጨምሮ በርካታ ከተሞችን እና ቀበሌዎችን በቅርብ ርቀት በማስተሳሰር በአካባቢው ይስተዋል የነበረውን የትራንስፖርት ችግር እንደሚቀርፍም ይታመናል። ከዚህም ባሻገር በመቶ ኪሎ ሜትሮች ተራርቀዉ ይገኙ የነበሩትን የዲማ ወረዳና የዞኑን ዋና ከተማ የሆነችው አቦቦ ከተማን ከክልሉ ዋና ከተማ ጋምቤላ ጋር እንዲሁም ከአጎራባች የጎግ ወረዳ ጋር በቅርበት ያገናኛል፡፡ በተጨማሪም አካባቢው ሰፊ የኢንቨስትመንት እና የማዕድን ሃብትን መገኛ በመሆኑ የመንገዱ መገንባት የሀገራችን የኢንቨስትመንትና ማዕድን ልማት ከማጠናከር አኳያ ትልቅ ጥቅም ይኖረዋል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱን በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ አስፈላጊ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ነው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የመሀልሜዳ - ግሼራቤል -መኮይ-ሚላሚሌ (ሎት 1፡ መሀልሜዳ - ጦርመሳያ) የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ 61 ነጥብ 5 በመቶ ደረሰ አዲስ አበባ ፣ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ መ አ) በሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኙትን የወረዳና የቀበሌ ከተሞችን የሚያስተሳስረው የመሀል ሜዳ - ግሼራቤል - መኮይ- ሚላሚሌ (ሎት 1፡ መሀልሜዳ - ጦርመሳያ) የመንገድ ፕሮጀክት 61.5 በመቶ ደርሷል፡፡ በፕሮጀክቱ የስራ እንቅስቃሴ ላይ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የውሀ ማፋሰሻ ቱቦና ፉካ ቀበራ ፣ የአራት ድልድይ ግንባታ እንዲሁም 18 ኪሎ ሜትር የሚሆን የአስፋልት ንጣፍ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ 65.5 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ የሚሸፍነው ይኸው መንገድ በወረዳ 21 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር ፣ በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ነው፡፡ በመንገዱ የግንባታ ሂደት ያጋጠሙ የወሰን ማስከበር እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ችግሮችን ለመፍታት ኢመአ የተለያዩ ጥረቶችን እያደረገ የሚገኝ ሲሆን ይህም ፕሮጀክቱን በሚፈለገው ፍጥነት እንዲሄድ የሚያስችለው ይሆናል፡፡ ግንባታውን እያካሄደ ያለው ዦንግሚ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ሊሚትድ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥሩን ስራ ኢንፍራስትራክቸር ዴቨሎፕመንት ኮንሰልታንትስ (አይ.ዲ.ሲ.ኦ.ኤን) እያከናወነው ይገኛል፡፡ ለፕሮጀክቱ የሚውለው (1,781,238,954.95) አንድ ቢሊዮን ሰባት መቶ ሰማንያ አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሠላሳ ስምንት ሺ ዘጠኝ መቶ አምሳ አራት ብር ከዘጠና አምስት ሣንቲም በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡ ከዚህ ቀደም መንገዱ በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ካለው ጠቀሜታ አንፃር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እንዲገነባ ተደርጓል፡፡ የዚህ መንገድ መገንባት በመንገድ ኮሪደሩ ስር የሚገኙትን የወጀድ፣ ግራኝ፣ ዳርገኝ፣ ጦር መሳያ ከተሞችን ከመሀል ሜዳ ከተማ ጋር በቅርበት ከማገናኘት ጎን ለጎን የጓሳ ኮሚዩኒቲ ጥብቅ ፓርክን ተደራሽ ለማድረግ ብሎም በአካባቢው የሚመረቱ የተለያዩ የግብርና ምርቶች ለማውጣት የሚያስችል ነው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

Are you following US on YouTube? https://www.youtube.com/@ethioroads?sub_confirmation=1
Anonymous voting

Are You Follow Us in YouTube ? https://www.youtube.com/@ethioroads?sub_confirmation=1
Anonymous voting

በአቦምሳ - አሰኮ - ዲቡ ወንዝ የመንገድ ፕሮጀክት አስፋልት ማንጠፍ ተጀመረ አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢመአ) 60 .91 ኪሎ ሜትር በሚረዝመው የኮንትራት አንድ አቦምሳ - አሰኮ - ዲቡ ወንዝ የመንገድ ፕሮጀክት ላይ የአስፋልት ንጣፍ ተጀምሯል፡፡ መነሻውን አቦምሳ ከተማ አድርጎ ዲቡ ወንዝ ላይ በሚያበቃው በዚህ የመንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ ስራ ጎን ለጎን የአፈር ድልዳሎ፣ የምርጥ ጠጠር፣ የድልድይ ግንባታ ስራዎች በመካሄድ ላይ ናቸው፡፡ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የግንባታ እንቅስቃሴ 36.43 በመቶ የደረሰ ሲሆን ይህንንም በማጠናከር በተቀመጠው እቅድ መሰረት ለማስኬድ በትኩረት እየተሰራ ነው። ፕሮጀክቱ በሚፈለገው ፍጥነት ለማስኬድ ብሎም በግንባታ ሂደቱ ላይ ያጋጠሙ የፀጥታና አለመረጋጋት እንዲሁም የካሳ ክፍያ ችግሮችን ለመፍታት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኩል የቅርብ ድጋፍና ክትትል እየተደረገበት ይገኛል፡፡ የመንገድ ግንባታውን ሐቨሪም ኮንስትራክሽን ጠቅላላ የስራ ተቋራጭ ከአለማየሁ ከተማ ጠቅላላ የስራ ተቋራጭ ጋር በጣምራ እያከናወኑት ይገኛል፡፡ የፕሮጀክቱን የማማከር እና የቁጥጥር ስራ መታፈሪያ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ከኤልዳ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነር ጋር በጋራ በመሆን እየሰሩት ነው፡፡ መንገዱ በወረዳ 19 በቀበሌ 16 ፣ በገጠር 10 ሜትር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ አጠቃላይ የጎን ስፋት ያለው ነው ። ግንባታውን ለማከናወን የሚያስችለውን ሁለት ቢሊዮን ሁለት መቶ ስልሳ ሚሊዮን ስምንት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺህ አርባ ሶስት (2,260,899,043) ብር በኢትዮጵያ መንግስት ተሸፍኗል። የአቦምሳ-አሰኮ-ዲቡ ወንዝ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ በዋናነት በአርሲ ዞን ስር የሚገኙ በርካታ የወረዳ እና የቀበሌ ከተሞችን በቅርበት በማስተሳሰር የኢኮኖሚ ዕድገትን ለመፍጠር የሚያስችል ይሆናል፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው በስፋትየሚገኙትን የጤፍ ፣ የስንዴ ፣ የገብስ ፣ የማሽላ ፣ የበቆሎ ፣ የሽንኩርት እና የጫት ምርቶች ወደ ገበያ አውጥቶ በመሸጥ ነዋሪዎች ከምርታቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከማድረግ አንጻር ጠቀሜታው የላቀ ነው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ውጤታማ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ ዘርፉ የሚገኝበትን ነባራዊ ሁኔታ፣ የዘርፉ ቁልፍ ፈተናዎች እንዲሁም ቀጣይ አቅጣጫዎችን በተመለከተ በዛሬው ዕለት ከባለድርሻ አካላት ጋር በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ምርምር ማዕከል ምክክር ተካሂዷል። የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚንስቴር ዴኤታ አቶ የትምጌታ አሥራት፥ መንግስት ለዘርፉ ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መኾኑን አንስተው፥ ፕሮጀክቶች በተቀመጠላቸው ጊዜ፣ የጥራት ደረጃ እና የዋጋ መጠን አለመጠናቀቅ፣ የጸጥታ ስጋቶች፣ የአንዳድን የሥራ ተቋራጮች የአቅም ማነስ እና ጤናማ ያልኾነ ፉክክር፣ የቴክኖሎጂ እና የብቃት ክፍተት እንዲሁም የፍይናንስ እጥረቶች የዘርፉ ማነቆ መኾናቸውን ገልጸዋል። በመኾኑም የኢንዱስትሪውን ውስብስብ እና አንገብጋቢ ችግሮች ለመፍታት እና ውጤታማ ለማድረግ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የዘርፉ ተዋንያን የነቃ ተሳትፎ አስፈላጊ መኾኑን አጽንዖት ሰጥተውበታል። ከዚህ አንጻር የዛሬው መድረክ በቀጣይ ለሚኖሩ ዕርምጃዎች መደላድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ብልሹ አሠራሮች እና የስነ ምግባር ጉድለቶችን በጋራ መታገል ይገባልም ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በየጊዜው እየተባባሰ የመጣው የግንባታ ጥሬ እቃ ዋጋ መናር፣ የአቅም ማነስ፣ ፍትሃዊ የኾነ የውድድር ከባቢ ማነስ፣ የጸጥታ ችግር እንዲሁም የገንዘብ እጥረት ፈተና እንደኾነባቸው አንስተዋል። ዘርፋን ከተደቀኑበት ችግሮች አላቅቆ ውጤታማ እንዲኾን በዋናነት አስቻይ የሥራ ከባቢዎችን መፍጠር፣ ነባራዊ ሁኔታዎችን ያገናዘበ የፖሊስ ማሻሻያዎችን በየጊዜው መተግበር እና ዘመኑን የዋጀ የቴክኖሎጂ እና ብቁ የሰው ኃይል አቅርቦት ሊኖር ይገባል ብለዋል። በቀጣይም የዘርፉን ችግሮች ለመፍታት ከመንግስት እና ከሁሉም የባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እና በትብብር እንደሚሠሩም ተሳታፊዎቹ አረጋግጠዋል። ሚንስቴር መ/ቤቱ ባሰናዳው በዚሁ መድረክ ላይ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሥራ ተቋራጮች፣ አማካሪ መሀንዲሶች፣ የሙያ ማኅበራት እንዲሁም ሌሎች የዘርፉ ተዋንያን ተሳትፈዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 16፣ 2017 (ኢ መ አ):- የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ቃሊቲ በሚገኘው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ምርምር ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል። የኮንስትራክሽን እመርታ ለሀገር ግንባታ በሚል መሪ ሐሳብ የሚካሄደው መድረኩ፥ የኮንስትራክሽን ዘርፉ የሚገኝበት ነባራዊ ሁኔታ (ደረጃ)፣ የዘርፉ ቁልፍ ፈተናዎች እንዲሁም ቀጣይ አቅጣጫዎችን በተመለከተ ትኩረቱን አድርጓል። የከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ባሰናዳው በዚሁ መድረክ ላይ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የሥራ ተቋራጮች፣ አማካሪ መሀንዲሶች እንዲሁም ሌሎች የዘርፉ ተዋንያን ይሳተፉበታል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads