uz
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Kanalga Telegram’da o‘tish

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር analitikasi

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 13 331 obunachidan iborat bo'lib, Transport toifasida 1 756-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 541-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 13 331 obunachiga ega bo‘ldi.

16 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 90 ga, so‘nggi 24 soatda esa 8 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 40.85% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.40% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 439 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 050 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 17 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 17 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Transport toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

13 323
Obunachilar
+824 soatlar
+217 kunlar
+9030 kunlar
Postlar arxiv
የጋምቤላ - አቦቦ - ጎግ - ዲማ፣ ኮንትራት 2፡ ፑኝውዶ - ጎግ - ጊሎ ወንዝ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመልካም የግንባታ አፈጻጸም ላይ ይገኛል አዲስ አበባ ፣ ጥር 01 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ መ አ) በጋምቤላ ህዝቦች ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በአኝዋሃ ዞን እየተገነባ የሚገኘዉ የጋምቤላ - አቦቦ - ጎግ - ዲማ ፣ ኮንትራት 2 ፑኝውዶ - ጎግ - ጊሎ ወንዝ ኪሎ ሜትር 72 የመንገድ ዲዛይንና ግንባታ ፕሮጀክት በመልካም የግንባታ አፈጻጸም ላይ ይገኛል፡፡ የመንገድ ግንባታዉ ከተጀመረ አራት አመታትን ያስቆጠረ ሲሆን አሁናዊ የግንባታ አፈጻጸሙ 90.1 በመቶ ላይ ደርሷል። በዚህም የግንባታዉ ዋና ዋና ስራዎች እየተገባደዱ ይገኛሉ፡፡ ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ 876 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ከምትገኘዉ ፒኝውዶ ከተማ መነሻዉን በማድረግ ጊሎ ወንዝን ተሻግሮ ፍጻሚዉን ያገኛል፡፡ መንገዱን እየገነባ የሚገኘዉ የሥራ ተቋራጭ ቻይና ሬይል ዌይ ሰቨንዝ ግሩፕ ሲሆን የማማከር እና ቁጥጥር ስራው ደግሞ ኢንጅነር ዘውዴ እስክንድር ኮንሰልቲንግ እና እንስራድ ሲቪል ሲስተምስ ኢንጂነሪንግ በጣምራ እያከናወኑ ይገኛሉ፡፡ መንገዱ የሚገነባበት መልከዓ-ምድራዊ አቀማመጥ 12.5 % ሜዳማ ሲሆን 87.5% ደግሞ ጠመዝማዛ ነው፡፡ የመንገዱ የጎን ስፋት የመንገድ ትከሻን ጨምሮ በገጠር 10 ሜትር ፤ በቀበሌ 12 ሚትር ፤ በወረዳ ከተማ ደግሞ 21.5 ሜትር ተጨማሪ ስፋት እንዲኖረዉ ተደርጎ ነዉ እየተገነባ የሚገኘዉ፡፡ የዚህ መንገድ ግንባታ 60 ሜትር ርዝማኔ ያለዉ የጊሎ ወንዝ ድልድልይ ስራ የሚያካትት ሲሆን ተጨማሪ 110 በላይ ጥቃቅን የፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦዎች ግንባታም የፕሮጀክቱ አካል ናቸዉ፡፡ የመንገዱ የቀድሞ ይዞታ ግማሹ ነባር የጠጠር መንገድ ሲሆን የተቀረዉ ምንም መንገድ ያልነበረበት አዲስ መስመር ነዉ፡፡ ባለፋት አመታት የአካባቢዉ ህብረተሰብ በመንገድ እጦት ምክንያት በርካታ እንግልት ሲያስተናግድ ቆይቷል። ይህ መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ አኝዋሃ ዞን ዉስጥ የሚገኙ ጎግ ወረዳን ጨምሮ በርካታ ከተሞችን እና ቀበሌዎችን በቅርብ ርቀት በማስተሳሰር በአካባቢው ይስተዋል የነበረውን የትራንስፖርት ችግር እንደሚቀርፍም ይታመናል። ከዚህም ባሻገር በመቶ ኪሎ ሜትሮች ተራርቀዉ ይገኙ የነበሩትን የዲማ ወረዳና የዞኑን ዋና ከተማ የሆነችው አቦቦ ከተማን ከክልሉ ዋና ከተማ ጋምቤላ ጋር እንዲሁም ከአጎራባች የጎግ ወረዳ ጋር በቅርበት ያገናኛል፡፡ በተጨማሪም አካባቢው ሰፊ የኢንቨስትመንት እና የማዕድን ሃብትን መገኛ በመሆኑ የመንገዱ መገንባት የሀገራችን የኢንቨስትመንትና ማዕድን ልማት ከማጠናከር አኳያ ትልቅ ጥቅም ይኖረዋል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱን በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ አስፈላጊ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ነው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የመሀልሜዳ - ግሼራቤል -መኮይ-ሚላሚሌ (ሎት 1፡ መሀልሜዳ - ጦርመሳያ) የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ 61 ነጥብ 5 በመቶ ደረሰ አዲስ አበባ ፣ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ መ አ) በሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኙትን የወረዳና የቀበሌ ከተሞችን የሚያስተሳስረው የመሀል ሜዳ - ግሼራቤል - መኮይ- ሚላሚሌ (ሎት 1፡ መሀልሜዳ - ጦርመሳያ) የመንገድ ፕሮጀክት 61.5 በመቶ ደርሷል፡፡ በፕሮጀክቱ የስራ እንቅስቃሴ ላይ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የውሀ ማፋሰሻ ቱቦና ፉካ ቀበራ ፣ የአራት ድልድይ ግንባታ እንዲሁም 18 ኪሎ ሜትር የሚሆን የአስፋልት ንጣፍ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ 65.5 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ የሚሸፍነው ይኸው መንገድ በወረዳ 21 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር ፣ በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ነው፡፡ በመንገዱ የግንባታ ሂደት ያጋጠሙ የወሰን ማስከበር እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ችግሮችን ለመፍታት ኢመአ የተለያዩ ጥረቶችን እያደረገ የሚገኝ ሲሆን ይህም ፕሮጀክቱን በሚፈለገው ፍጥነት እንዲሄድ የሚያስችለው ይሆናል፡፡ ግንባታውን እያካሄደ ያለው ዦንግሚ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ሊሚትድ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥሩን ስራ ኢንፍራስትራክቸር ዴቨሎፕመንት ኮንሰልታንትስ (አይ.ዲ.ሲ.ኦ.ኤን) እያከናወነው ይገኛል፡፡ ለፕሮጀክቱ የሚውለው (1,781,238,954.95) አንድ ቢሊዮን ሰባት መቶ ሰማንያ አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሠላሳ ስምንት ሺ ዘጠኝ መቶ አምሳ አራት ብር ከዘጠና አምስት ሣንቲም በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡ ከዚህ ቀደም መንገዱ በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ካለው ጠቀሜታ አንፃር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እንዲገነባ ተደርጓል፡፡ የዚህ መንገድ መገንባት በመንገድ ኮሪደሩ ስር የሚገኙትን የወጀድ፣ ግራኝ፣ ዳርገኝ፣ ጦር መሳያ ከተሞችን ከመሀል ሜዳ ከተማ ጋር በቅርበት ከማገናኘት ጎን ለጎን የጓሳ ኮሚዩኒቲ ጥብቅ ፓርክን ተደራሽ ለማድረግ ብሎም በአካባቢው የሚመረቱ የተለያዩ የግብርና ምርቶች ለማውጣት የሚያስችል ነው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

Are you following US on YouTube? https://www.youtube.com/@ethioroads?sub_confirmation=1
Anonymous voting

Are You Follow Us in YouTube ? https://www.youtube.com/@ethioroads?sub_confirmation=1
Anonymous voting

በአቦምሳ - አሰኮ - ዲቡ ወንዝ የመንገድ ፕሮጀክት አስፋልት ማንጠፍ ተጀመረ አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢመአ) 60 .91 ኪሎ ሜትር በሚረዝመው የኮንትራት አንድ አቦምሳ - አሰኮ - ዲቡ ወንዝ የመንገድ ፕሮጀክት ላይ የአስፋልት ንጣፍ ተጀምሯል፡፡ መነሻውን አቦምሳ ከተማ አድርጎ ዲቡ ወንዝ ላይ በሚያበቃው በዚህ የመንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ ስራ ጎን ለጎን የአፈር ድልዳሎ፣ የምርጥ ጠጠር፣ የድልድይ ግንባታ ስራዎች በመካሄድ ላይ ናቸው፡፡ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የግንባታ እንቅስቃሴ 36.43 በመቶ የደረሰ ሲሆን ይህንንም በማጠናከር በተቀመጠው እቅድ መሰረት ለማስኬድ በትኩረት እየተሰራ ነው። ፕሮጀክቱ በሚፈለገው ፍጥነት ለማስኬድ ብሎም በግንባታ ሂደቱ ላይ ያጋጠሙ የፀጥታና አለመረጋጋት እንዲሁም የካሳ ክፍያ ችግሮችን ለመፍታት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኩል የቅርብ ድጋፍና ክትትል እየተደረገበት ይገኛል፡፡ የመንገድ ግንባታውን ሐቨሪም ኮንስትራክሽን ጠቅላላ የስራ ተቋራጭ ከአለማየሁ ከተማ ጠቅላላ የስራ ተቋራጭ ጋር በጣምራ እያከናወኑት ይገኛል፡፡ የፕሮጀክቱን የማማከር እና የቁጥጥር ስራ መታፈሪያ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ከኤልዳ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነር ጋር በጋራ በመሆን እየሰሩት ነው፡፡ መንገዱ በወረዳ 19 በቀበሌ 16 ፣ በገጠር 10 ሜትር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ አጠቃላይ የጎን ስፋት ያለው ነው ። ግንባታውን ለማከናወን የሚያስችለውን ሁለት ቢሊዮን ሁለት መቶ ስልሳ ሚሊዮን ስምንት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺህ አርባ ሶስት (2,260,899,043) ብር በኢትዮጵያ መንግስት ተሸፍኗል። የአቦምሳ-አሰኮ-ዲቡ ወንዝ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ በዋናነት በአርሲ ዞን ስር የሚገኙ በርካታ የወረዳ እና የቀበሌ ከተሞችን በቅርበት በማስተሳሰር የኢኮኖሚ ዕድገትን ለመፍጠር የሚያስችል ይሆናል፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው በስፋትየሚገኙትን የጤፍ ፣ የስንዴ ፣ የገብስ ፣ የማሽላ ፣ የበቆሎ ፣ የሽንኩርት እና የጫት ምርቶች ወደ ገበያ አውጥቶ በመሸጥ ነዋሪዎች ከምርታቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከማድረግ አንጻር ጠቀሜታው የላቀ ነው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ውጤታማ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ ዘርፉ የሚገኝበትን ነባራዊ ሁኔታ፣ የዘርፉ ቁልፍ ፈተናዎች እንዲሁም ቀጣይ አቅጣጫዎችን በተመለከተ በዛሬው ዕለት ከባለድርሻ አካላት ጋር በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ምርምር ማዕከል ምክክር ተካሂዷል። የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚንስቴር ዴኤታ አቶ የትምጌታ አሥራት፥ መንግስት ለዘርፉ ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መኾኑን አንስተው፥ ፕሮጀክቶች በተቀመጠላቸው ጊዜ፣ የጥራት ደረጃ እና የዋጋ መጠን አለመጠናቀቅ፣ የጸጥታ ስጋቶች፣ የአንዳድን የሥራ ተቋራጮች የአቅም ማነስ እና ጤናማ ያልኾነ ፉክክር፣ የቴክኖሎጂ እና የብቃት ክፍተት እንዲሁም የፍይናንስ እጥረቶች የዘርፉ ማነቆ መኾናቸውን ገልጸዋል። በመኾኑም የኢንዱስትሪውን ውስብስብ እና አንገብጋቢ ችግሮች ለመፍታት እና ውጤታማ ለማድረግ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የዘርፉ ተዋንያን የነቃ ተሳትፎ አስፈላጊ መኾኑን አጽንዖት ሰጥተውበታል። ከዚህ አንጻር የዛሬው መድረክ በቀጣይ ለሚኖሩ ዕርምጃዎች መደላድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ብልሹ አሠራሮች እና የስነ ምግባር ጉድለቶችን በጋራ መታገል ይገባልም ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በየጊዜው እየተባባሰ የመጣው የግንባታ ጥሬ እቃ ዋጋ መናር፣ የአቅም ማነስ፣ ፍትሃዊ የኾነ የውድድር ከባቢ ማነስ፣ የጸጥታ ችግር እንዲሁም የገንዘብ እጥረት ፈተና እንደኾነባቸው አንስተዋል። ዘርፋን ከተደቀኑበት ችግሮች አላቅቆ ውጤታማ እንዲኾን በዋናነት አስቻይ የሥራ ከባቢዎችን መፍጠር፣ ነባራዊ ሁኔታዎችን ያገናዘበ የፖሊስ ማሻሻያዎችን በየጊዜው መተግበር እና ዘመኑን የዋጀ የቴክኖሎጂ እና ብቁ የሰው ኃይል አቅርቦት ሊኖር ይገባል ብለዋል። በቀጣይም የዘርፉን ችግሮች ለመፍታት ከመንግስት እና ከሁሉም የባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እና በትብብር እንደሚሠሩም ተሳታፊዎቹ አረጋግጠዋል። ሚንስቴር መ/ቤቱ ባሰናዳው በዚሁ መድረክ ላይ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሥራ ተቋራጮች፣ አማካሪ መሀንዲሶች፣ የሙያ ማኅበራት እንዲሁም ሌሎች የዘርፉ ተዋንያን ተሳትፈዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 16፣ 2017 (ኢ መ አ):- የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ቃሊቲ በሚገኘው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ምርምር ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል። የኮንስትራክሽን እመርታ ለሀገር ግንባታ በሚል መሪ ሐሳብ የሚካሄደው መድረኩ፥ የኮንስትራክሽን ዘርፉ የሚገኝበት ነባራዊ ሁኔታ (ደረጃ)፣ የዘርፉ ቁልፍ ፈተናዎች እንዲሁም ቀጣይ አቅጣጫዎችን በተመለከተ ትኩረቱን አድርጓል። የከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ባሰናዳው በዚሁ መድረክ ላይ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የሥራ ተቋራጮች፣ አማካሪ መሀንዲሶች እንዲሁም ሌሎች የዘርፉ ተዋንያን ይሳተፉበታል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads