en
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Open in Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 425 subscribers, ranking 1 737 in the Transport category and 2 513 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 425 subscribers.

According to the latest data from 25 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 161 over the last 30 days and by 25 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 34.12%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 14.76% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 579 views. Within the first day, a publication typically gains 1 981 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 11.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 26 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Transport category.

13 425
Subscribers
+2524 hours
+777 days
+16130 days
Posts Archive
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተዘጋጀው "የአፍሪቃ ከተሞች ፎረም" ላይ እየተሳተፈ ይገኛል። አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 29/2016 ዓ.ም ለተከታታይ ሦስት ቀናቶች በሚቆየ
+3
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተዘጋጀው "የአፍሪቃ ከተሞች ፎረም" ላይ እየተሳተፈ ይገኛል። አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 29/2016 ዓ.ም ለተከታታይ ሦስት ቀናቶች በሚቆየው ፎረም ላይ ከ 47 በላይ ሀገራት፣ ከ30 በላይ የአህጉሪቱ ከተማ ከንቲባዎች፣ ተመራማሪዎች እንዲሁም የተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ይሳተፋሉ፡፡ ከ1ሺህ 500 በላይ ተሣታፊዎች በዚሁ መድረክ ላይ እንደሚታደሙ ይታመናል። በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከናወነው ይኸው መድረክ "ዘላቂ የከተሞች ልማት ለአፍሪካ ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ 2063" በሚል መሪ ቃል ነው በመካሄድ ላይ የሚገኘው። ፎረሙ በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር እና በአፍሪካ ኅብረት አጋርነት የተሰናዳ ሲሆን ፣ ሀገራችን በዲፕሎማሲ፣ በማኅበረ-ኢኮኖሚ እንዲሁም ፖለቲካዊ መስኮች የምታተርፍበት ስለመሆኑም ተገልጿል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የጥንቃቄ መልዕክት!!
የጥንቃቄ መልዕክት!!

አመታዊው  የመንገድ ጥናት ኮንፈረንስ ተካሄደ አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 22/2016 ዓ.ም  አመታዊው  የመንገድ ጥናት  ኮንፈረንስ  በኢትዮጵያ  መንገዶች አስተዳደር  የመንገድ  ምርምር  ማዕከል  ለሰባተኛ ጊዜ  "ዘለቄታዊ  የመንገድ  መሠረተ  ልማት  እና አስተዳደር   በምርምር"  በሚል  መሪ  ቃል  ተካሄዷል፡፡ በኮንፈረንሱ  ላይ  የከተማና  መሠረተ  ልማት ሚ/ር ዴኤታ  ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። በዕለቱ የመርሃ-ግብሩ ተጋባዥ እንግዶች  ያለፉት  የመንገድ ዘርፍ ፕሮግራሞች (RSDP) ትግበራና ፈተናዎች እንዲሁም የባለድርሻ አካላት የእውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግርን አስመልክቶ ገለፃ አድርገዋል። ከዚህም ባሻገር በመርሐ-ግብሩ ላይ  በተጋባዥ እንግዶች  እና በተቋሙ  ባለሙያዎች  የተለያዩ  የምርምር  ጥናቶች ቀርበዋል። የኢትዮጵያ የመንገድ መሰረተ ልማት አጀማመር እና ፈተናዎች ፣ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች የጤና እና ደህንነት ግምገማ ፣ የግንባታ ቁሳቁሶች የላቦራቶሪ ሙከራ አፈፃፀም፣የመንገድ ንጣፍ አሰራር ቴክኖሎጂ ፣ ከመሬት በስተጀርባ ያለው የፔኔትሬቲንግ ራዳር (ጂፒአር)ያለበት ደረጃ  እንዲሁም የመሬት መንሸራተትን ለመከላከል የተሰሩ ስራዎቸን በሚመለከቱ ጥናቶች ላይ ገለፃ ተደርጓል። በቀረቡ የጥናትና ምርምር ስራዎች  ዙሪያ በእለቱ የተገኙ ባለድርሻ አካላት ጥያቄዎች ያነሱ ሲሆን የቀረቡ ጥያቄዎችም በምርምሩ  በተሳተፉ  የዘርፉ  ባለሙያዎች  በኩል  ምላሽ  ተሰጥቶባቸዋል። ኢመአ  በመንገድ መሰረተ ልማት ዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመከላከል የሚያስችሉ ምርምሮች እና በዘርፉ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለመተግበር  የሚያስችሉ  እንቅስቃሴዎች  በማድረግ  ረገድ እያከናወነ የሚገኘው ዘርፈብዙ ስራዎቸ ለውጥ ለማምጣት የሚያግዙ መሆናቸውም ተገልጿል ። በተቋሙ የመንገድ ምርምር ማዕከል አማካኝነት እየተደረጉ የሚገኙ በርካታ ምርምሮች የሀገሪቱን  የመንገድ መሰረተ ልማት ለማሻሻልና ለማሳደግ ብሎም በዘርፉ ለውጥ ለማምጣት  ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚኖራቸው በመሆኑ ይህንን መሰል ጥናቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ተብሏል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር አካሄደ አዲስአበባ ፣ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ኢመአ) የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ የሚገኘውን የአንድ ጀንበር አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ ዘመቻን በእንጦጦ የጠፈር ምርምር አካባቢ አካሄደ፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ በሚገኘው የችግኝ ተከላ ዘመቻ ላይ የኢመአ የስራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡ የኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን የአካባቢን የአየር ንብረት ሚዛን የሚጠብቁ እና ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡ አክለውም በመንገድ ግንባታ ሂደት ወቅት የተነሱ ዛፎችን በመተካት ፤ የአካባቢውን ስነ-ምህዳር ለመጠበቅ ሁሉም የተቋሙ ማህበረሰብና ባለድርሻ አካላት የበከላቸውን አስተዋጽኦ ሊወጡ እንደሚገባም ገልፀዋል፡፡ በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ የታቀደውን በአንድ ጀንበር 600 ሚሊዬን ችግኞችን የመትከል መርሃ-ግብር ላይ እንደ ተቋም በመሳተፍ ሀገራዊ ግዴታቸውን በመወጣታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ አክለውም ከመትከል ባሻገር ተገቢውን እንክብካቤ በማድረግ ለመጪው ትውልድ የሚያኮራ ተግባር ማስተላለፍ ይገባልም ብለዋል ፡፡ በተከላው መረሃግብር የተሳተፉ ሰራተኞችም ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መትከላቸውን ጠቅሰው ችግኞቹ ሲፀድቁ እንደሀገር ያለንን የደን ሽፋን ከመጨመር ባሻገር የምግብ ዋስትናችንን የሚያረጋግጡ ይሆናሉ ብለዋል፡፡ ተቋሙ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚተገበረው የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ አካል በመሆን በዋናው መስሪያ ቤት ፣ በሁሉም የመንገድ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤቶች ፣ በዲስትሪክቶች እንዲሁም በመንገድ ምርምርና ማሰልጠኛ ማዕከላት ሰራተኞቹ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ በማድረግ በእቅድ የተያዘው ግብ እንዲሳካ ከፍተኛ ድጋፍና ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል ፤ ይህን ተግባርም አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር አካሄደ አዲስአበባ ፣ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ኢመአ) የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ የሚገኘውን የአንድ ጀንበር አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ ዘመቻን በእንጦጦ የጠፈር ምርምር አካባቢ አካሄደ፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ በሚገኘው የችግኝ ተከላ ዘመቻ ላይ የኢመአ የስራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡ የኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን የአካባቢን የአየር ንብረት ሚዛን የሚጠብቁ እና ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡ አክለውም በመንገድ ግንባታ ሂደት ወቅት የተነሱ ዛፎችን በመተካት ፤ የአካባቢውን ስነ-ምህዳር ለመጠበቅ ሁሉም የተቋሙ ማህበረሰብና ባለድርሻ አካላት የበከላቸውን አስተዋጽኦ ሊወጡ እንደሚገባም ገልፀዋል፡፡ በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ የታቀደውን በአንድ ጀንበር 600 ሚሊዬን ችግኞችን የመትከል መርሃ-ግብር ላይ እንደ ተቋም በመሳተፍ ሀገራዊ ግዴታቸውን በመወጣታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ አክለውም ከመትከል ባሻገር ተገቢውን እንክብካቤ በማድረግ ለመጪው ትውልድ የሚያኮራ ተግባር ማስተላለፍ ይገባልም ብለዋል ፡፡ በተከላው መረሃግብር የተሳተፉ ሰራተኞችም ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መትከላቸውን ጠቅሰው ችግኞቹ ሲፀድቁ እንደሀገር ያለንን የደን ሽፋን ከመጨመር ባሻገር የምግብ ዋስትናችንን የሚያረጋግጡ ይሆናሉ ብለዋል፡፡ ተቋሙ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚተገበረው የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ አካል በመሆን በዋናው መስሪያ ቤት ፣ በሁሉም የመንገድ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤቶች ፣ በዲስትሪክቶች እንዲሁም በመንገድ ምርምርና ማሰልጠኛ ማዕከላት ሰራተኞቹ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ በማድረግ በእቅድ የተያዘው ግብ እንዲሳካ ከፍተኛ ድጋፍና ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል ፤ ይህን ተግባርም አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር አካሄደ አዲስአበባ ፣ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ኢመአ) የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ የሚገኘውን የአንድ ጀንበር አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ ዘመቻን በእንጦጦ የጠፈር ምርምር አካባቢ አካሄደ፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ በሚገኘው የችግኝ ተከላ ዘመቻ ላይ የኢመአ የስራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡ የኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን የአካባቢን የአየር ንብረት ሚዛን የሚጠብቁ እና ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡ አክለውም በመንገድ ግንባታ ሂደት ወቅት የተነሱ ዛፎችን በመተካት ፤ የአካባቢውን ስነ-ምህዳር ለመጠበቅ ሁሉም የተቋሙ ማህበረሰብና ባለድርሻ አካላት የበከላቸውን አስተዋጽኦ ሊወጡ እንደሚገባም ገልፀዋል፡፡ በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ የታቀደውን በአንድ ጀንበር 600 ሚሊዬን ችግኞችን የመትከል መርሃ-ግብር ላይ እንደ ተቋም በመሳተፍ ሀገራዊ ግዴታቸውን በመወጣታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ አክለውም ከመትከል ባሻገር ተገቢውን እንክብካቤ በማድረግ ለመጪው ትውልድ የሚያኮራ ተግባር ማስተላለፍ ይገባልም ብለዋል ፡፡ በተከላው መረሃግብር የተሳተፉ ሰራተኞችም ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መትከላቸውን ጠቅሰው ችግኞቹ ሲፀድቁ እንደሀገር ያለንን የደን ሽፋን ከመጨመር ባሻገር የምግብ ዋስትናችንን የሚያረጋግጡ ይሆናሉ ብለዋል፡፡ ተቋሙ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚተገበረው የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ አካል በመሆን በዋናው መስሪያ ቤት ፣ በሁሉም የመንገድ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤቶች ፣ በዲስትሪክቶች እንዲሁም በመንገድ ምርምርና ማሰልጠኛ ማዕከላት ሰራተኞቹ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ በማድረግ በእቅድ የተያዘው ግብ እንዲሳካ ከፍተኛ ድጋፍና ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል ፤ ይህን ተግባርም አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads