fa
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

رفتن به کانال در Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

کانال ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 331 مشترک است و جایگاه 1 756 را در دسته حمل و نقل و رتبه 2 537 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 331 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 17 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 95 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 18 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 41.14% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.24% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 485 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 032 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 16 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 18 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کرده‌اند.

13 331
مشترکین
+1824 ساعت
+417 روز
+9530 روز
آرشیو پست ها
የጥንቃቄ መልዕክት!!
የጥንቃቄ መልዕክት!!

አመታዊው  የመንገድ ጥናት ኮንፈረንስ ተካሄደ አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 22/2016 ዓ.ም  አመታዊው  የመንገድ ጥናት  ኮንፈረንስ  በኢትዮጵያ  መንገዶች አስተዳደር  የመንገድ  ምርምር  ማዕከል  ለሰባተኛ ጊዜ  "ዘለቄታዊ  የመንገድ  መሠረተ  ልማት  እና አስተዳደር   በምርምር"  በሚል  መሪ  ቃል  ተካሄዷል፡፡ በኮንፈረንሱ  ላይ  የከተማና  መሠረተ  ልማት ሚ/ር ዴኤታ  ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። በዕለቱ የመርሃ-ግብሩ ተጋባዥ እንግዶች  ያለፉት  የመንገድ ዘርፍ ፕሮግራሞች (RSDP) ትግበራና ፈተናዎች እንዲሁም የባለድርሻ አካላት የእውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግርን አስመልክቶ ገለፃ አድርገዋል። ከዚህም ባሻገር በመርሐ-ግብሩ ላይ  በተጋባዥ እንግዶች  እና በተቋሙ  ባለሙያዎች  የተለያዩ  የምርምር  ጥናቶች ቀርበዋል። የኢትዮጵያ የመንገድ መሰረተ ልማት አጀማመር እና ፈተናዎች ፣ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች የጤና እና ደህንነት ግምገማ ፣ የግንባታ ቁሳቁሶች የላቦራቶሪ ሙከራ አፈፃፀም፣የመንገድ ንጣፍ አሰራር ቴክኖሎጂ ፣ ከመሬት በስተጀርባ ያለው የፔኔትሬቲንግ ራዳር (ጂፒአር)ያለበት ደረጃ  እንዲሁም የመሬት መንሸራተትን ለመከላከል የተሰሩ ስራዎቸን በሚመለከቱ ጥናቶች ላይ ገለፃ ተደርጓል። በቀረቡ የጥናትና ምርምር ስራዎች  ዙሪያ በእለቱ የተገኙ ባለድርሻ አካላት ጥያቄዎች ያነሱ ሲሆን የቀረቡ ጥያቄዎችም በምርምሩ  በተሳተፉ  የዘርፉ  ባለሙያዎች  በኩል  ምላሽ  ተሰጥቶባቸዋል። ኢመአ  በመንገድ መሰረተ ልማት ዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመከላከል የሚያስችሉ ምርምሮች እና በዘርፉ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለመተግበር  የሚያስችሉ  እንቅስቃሴዎች  በማድረግ  ረገድ እያከናወነ የሚገኘው ዘርፈብዙ ስራዎቸ ለውጥ ለማምጣት የሚያግዙ መሆናቸውም ተገልጿል ። በተቋሙ የመንገድ ምርምር ማዕከል አማካኝነት እየተደረጉ የሚገኙ በርካታ ምርምሮች የሀገሪቱን  የመንገድ መሰረተ ልማት ለማሻሻልና ለማሳደግ ብሎም በዘርፉ ለውጥ ለማምጣት  ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚኖራቸው በመሆኑ ይህንን መሰል ጥናቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ተብሏል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር አካሄደ አዲስአበባ ፣ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ኢመአ) የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ የሚገኘውን የአንድ ጀንበር አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ ዘመቻን በእንጦጦ የጠፈር ምርምር አካባቢ አካሄደ፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ በሚገኘው የችግኝ ተከላ ዘመቻ ላይ የኢመአ የስራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡ የኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን የአካባቢን የአየር ንብረት ሚዛን የሚጠብቁ እና ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡ አክለውም በመንገድ ግንባታ ሂደት ወቅት የተነሱ ዛፎችን በመተካት ፤ የአካባቢውን ስነ-ምህዳር ለመጠበቅ ሁሉም የተቋሙ ማህበረሰብና ባለድርሻ አካላት የበከላቸውን አስተዋጽኦ ሊወጡ እንደሚገባም ገልፀዋል፡፡ በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ የታቀደውን በአንድ ጀንበር 600 ሚሊዬን ችግኞችን የመትከል መርሃ-ግብር ላይ እንደ ተቋም በመሳተፍ ሀገራዊ ግዴታቸውን በመወጣታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ አክለውም ከመትከል ባሻገር ተገቢውን እንክብካቤ በማድረግ ለመጪው ትውልድ የሚያኮራ ተግባር ማስተላለፍ ይገባልም ብለዋል ፡፡ በተከላው መረሃግብር የተሳተፉ ሰራተኞችም ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መትከላቸውን ጠቅሰው ችግኞቹ ሲፀድቁ እንደሀገር ያለንን የደን ሽፋን ከመጨመር ባሻገር የምግብ ዋስትናችንን የሚያረጋግጡ ይሆናሉ ብለዋል፡፡ ተቋሙ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚተገበረው የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ አካል በመሆን በዋናው መስሪያ ቤት ፣ በሁሉም የመንገድ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤቶች ፣ በዲስትሪክቶች እንዲሁም በመንገድ ምርምርና ማሰልጠኛ ማዕከላት ሰራተኞቹ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ በማድረግ በእቅድ የተያዘው ግብ እንዲሳካ ከፍተኛ ድጋፍና ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል ፤ ይህን ተግባርም አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር አካሄደ አዲስአበባ ፣ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ኢመአ) የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ የሚገኘውን የአንድ ጀንበር አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ ዘመቻን በእንጦጦ የጠፈር ምርምር አካባቢ አካሄደ፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ በሚገኘው የችግኝ ተከላ ዘመቻ ላይ የኢመአ የስራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡ የኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን የአካባቢን የአየር ንብረት ሚዛን የሚጠብቁ እና ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡ አክለውም በመንገድ ግንባታ ሂደት ወቅት የተነሱ ዛፎችን በመተካት ፤ የአካባቢውን ስነ-ምህዳር ለመጠበቅ ሁሉም የተቋሙ ማህበረሰብና ባለድርሻ አካላት የበከላቸውን አስተዋጽኦ ሊወጡ እንደሚገባም ገልፀዋል፡፡ በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ የታቀደውን በአንድ ጀንበር 600 ሚሊዬን ችግኞችን የመትከል መርሃ-ግብር ላይ እንደ ተቋም በመሳተፍ ሀገራዊ ግዴታቸውን በመወጣታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ አክለውም ከመትከል ባሻገር ተገቢውን እንክብካቤ በማድረግ ለመጪው ትውልድ የሚያኮራ ተግባር ማስተላለፍ ይገባልም ብለዋል ፡፡ በተከላው መረሃግብር የተሳተፉ ሰራተኞችም ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መትከላቸውን ጠቅሰው ችግኞቹ ሲፀድቁ እንደሀገር ያለንን የደን ሽፋን ከመጨመር ባሻገር የምግብ ዋስትናችንን የሚያረጋግጡ ይሆናሉ ብለዋል፡፡ ተቋሙ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚተገበረው የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ አካል በመሆን በዋናው መስሪያ ቤት ፣ በሁሉም የመንገድ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤቶች ፣ በዲስትሪክቶች እንዲሁም በመንገድ ምርምርና ማሰልጠኛ ማዕከላት ሰራተኞቹ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ በማድረግ በእቅድ የተያዘው ግብ እንዲሳካ ከፍተኛ ድጋፍና ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል ፤ ይህን ተግባርም አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር አካሄደ አዲስአበባ ፣ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ኢመአ) የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ የሚገኘውን የአንድ ጀንበር አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ ዘመቻን በእንጦጦ የጠፈር ምርምር አካባቢ አካሄደ፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ በሚገኘው የችግኝ ተከላ ዘመቻ ላይ የኢመአ የስራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡ የኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን የአካባቢን የአየር ንብረት ሚዛን የሚጠብቁ እና ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡ አክለውም በመንገድ ግንባታ ሂደት ወቅት የተነሱ ዛፎችን በመተካት ፤ የአካባቢውን ስነ-ምህዳር ለመጠበቅ ሁሉም የተቋሙ ማህበረሰብና ባለድርሻ አካላት የበከላቸውን አስተዋጽኦ ሊወጡ እንደሚገባም ገልፀዋል፡፡ በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ የታቀደውን በአንድ ጀንበር 600 ሚሊዬን ችግኞችን የመትከል መርሃ-ግብር ላይ እንደ ተቋም በመሳተፍ ሀገራዊ ግዴታቸውን በመወጣታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ አክለውም ከመትከል ባሻገር ተገቢውን እንክብካቤ በማድረግ ለመጪው ትውልድ የሚያኮራ ተግባር ማስተላለፍ ይገባልም ብለዋል ፡፡ በተከላው መረሃግብር የተሳተፉ ሰራተኞችም ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መትከላቸውን ጠቅሰው ችግኞቹ ሲፀድቁ እንደሀገር ያለንን የደን ሽፋን ከመጨመር ባሻገር የምግብ ዋስትናችንን የሚያረጋግጡ ይሆናሉ ብለዋል፡፡ ተቋሙ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚተገበረው የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ አካል በመሆን በዋናው መስሪያ ቤት ፣ በሁሉም የመንገድ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤቶች ፣ በዲስትሪክቶች እንዲሁም በመንገድ ምርምርና ማሰልጠኛ ማዕከላት ሰራተኞቹ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ በማድረግ በእቅድ የተያዘው ግብ እንዲሳካ ከፍተኛ ድጋፍና ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል ፤ ይህን ተግባርም አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads