en
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Open in Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 331 subscribers, ranking 1 756 in the Transport category and 2 537 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 331 subscribers.

According to the latest data from 17 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 95 over the last 30 days and by 18 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 41.14%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.24% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 485 views. Within the first day, a publication typically gains 2 032 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 16.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 18 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Transport category.

13 331
Subscribers
+1824 hours
+417 days
+9530 days
Posts Archive
የበለስ - መካነ ብርሃን አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታ 75 ነጥብ 2 በመቶ ደረሰ አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2017 (ኢ መ አ):- በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን የደባርቅ እና ጃናሞራ ወረዳዎችን የሚያገናኘው የበለስ - መካነ ብርሃን አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታ አፈጻጸም 75 ነጥብ 2 በመቶ ደርሷል። አሁን ላይ እየተሠሩ ከሚገኙ ዋና ዋና ሥራዎች መካከል የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የሰቤ ቤዝ፣ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ እንዲሁም የጠጠር ማምረት ሥራዎች ይጠቀሳሉ። በተጨማሪም የአስር አነስተኛ እና ከፍተኛ ድልድዩች ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቋል። ፕሮጀክቱ ባጠረ ጊዜ እንዲጠናቀቅ በኢ መ አ በኩል ጥብቅ ክትትል እየተደረገ ይገኛል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 36 ነጥብ 42 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ ግንባታው በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ እየተካሄደ ይገኛል። በለስ ኮንሰልቲንግ የግንባታውን ጥራት የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ ይሠራል። ለግንባታው የተመደበው 1,018,952,362.90  (አንድ ቢሊዮን አስራስምንት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺ ) ብር በፌደራል መንግስት ነው የሚሸፈነው። የአካባቢው የቀድሞ ገጽታ ምንም ዓይነት የመንገድ መሠረተ ልማት ያልነበረው ሲኾን፥ በኅብረተሰቡ ጥያቄ መሠረት እንዲሁም ቦታው ካለው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አንጻር፣ በመንግስት ተወስኖ አሁን ላይ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል። በአካባቢው የሚስተዋለውን ተደጋጋሚ የጸጥታ ችግር ተከትሎ የግንባታ ጥሬ እቃ እና ማሽነሪዎች በቀላሉ ማቅረብ አለመቻል እንዲሁም የሥፍራው አስቸጋሪ መልካዓ ምድራዊ አቀማመጥ የፕሮጀክቱ ፈተና መኾናቸው ተመልክቷል። የመንገዱ መገንባት በተለይም በመንገድ እጦት ተራርቆ የቆየውን የደባርቅ እና ጃናሞራ ሕዝብ በቅርበት እና ደረጃውን በጠበቀ መንገድ የሚያገናኝ ነው። በመንገዱ ክልል እና በዙሪያው የሚገኙ የበለስ፣ ወይና፣ ሚጊራ እና መሰል ከተሞች ዕድገት ያፋጥናል። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ቀድሞ ይወስድ የነበረውን 8 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 1 ሰዓት ያሳጥረዋል። የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ እንደመኾኑም የቱሪዝም ዘርፉን በማነቃቃት በኩል የጎላ ሚና ይጫወታል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢኮኖሚና የማህበራዊ እድገትን ለማረጋገጥ በሚደረግ ሀገራዊ ጥረት የመንገድ ዘርፍ የሚገኝበትን ደረጃ የተሰጠው ትኩረት ወሳኝ ድርሻ አለው፡፡ ለዚህም ነው የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ትኩረት ለዘርፉ በመስጠት በየበጀት ዓመቱ ከፍተኛ መዋለ ንዋይ በመመደብ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች በመተግበር ላይ የሚገኘው፡፡ ይህንን ተከትሎም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በርካታ የመንገድ ግንባታ እና የጥገና ፕሮጀክቶች እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን፤ እነዚህንም ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እና የጥራት ደረጃ ለማስፈፀም የሚያስችሉትን የቅርብ ክትትል ድጋፍ ያደርጋል፡፡ በዚህ ረገድ በ2017 በጀት ዓመት ይኸው ተግባር የቀጠለ ሲሆን የበጀት ዓመቱን እቅድ ተከትለው በትግበራ ሂደት ላይ የሚገኙት ዋና ዋና ስራዎች እንደሚከተለው ይቀርባሉ፡፡ 1. ነባር መንገዶችን ማጠናከር፡- በአገልግሎት ላይ ያሉ መንገዶች የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ የማጠናከርያ ስራዎችን በማከናወን ለትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ የማድረግ ሥራ ነው፡፡ በዚህም መሰረት 15 ኪሎ ሜትር ነባር መንገዶችን በማጠናከር ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡በዚህ ፕሮግራም ውስጥ ያሉ ፕሮጀክቶች ብዛት 4 ሲሆኑ ፡፡ > 1 በግንባታ ላይ ያለ ፣ > 3 ወደ ግንባታ ለመሸጋገር በሂደት ላይ ያሉ ናቸው፡፡ 2. የነባር መንገዶች ደረጃ ማሻሻል፡- አገልግሎት ላይ ያሉ ነባር መንገዶችን ደረጃቸውን ከፍ በማድረግና በማሻሻል ከጠጠር ወደ አስፋልት እና በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ማሳደግ ነው፡፡ በዚህም መሰረት 330 ኪሎ ሜትር ነባር መንገዶችን የማሻሻል ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ በዚህ ፕሮግራም ውስጥ ያሉ ፕሮጀክቶች ብዛት 78 ናቸው፡፡ 3. የአዳዲስ መንገዶች እና የፍጥነት መንገዶች ግንባታ :- ጨረታ ወጥቶላቸው የተፈረሙና ወደ ስራ የሚገቡ አዳዲስ መንገዶችን እንዲሁም የፍጥነት መንገዶች ማከናወን ያጠቃልላል፡፡ በ2017 የበጀት ዓመት 778 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ የአዳዲስ መንገዶች እና የፍጥነት መንገዶች ግንባታ ይከናወናል፡፡በዚህ ፕሮግራም ውስጥ 232 ፕሮጀክቶች ተካተዋል፡፡ 4. የመንገዶች ከባድ ጥገና/Overlay Projects፡- የተበላሹ እና ነባር መንገዶችን በከፍተኛ ደረጃ የመጠገን ስራ የሚሰራበት ነው፡፡ > በ2017 በጀት ዓመት 144 ኪሎ ሜትር የመንገዶች ከባድ ጥገና/Overlay Projects ለማከናወን እቅድ ተይዟል፡፡ 5. ወቅታዊ እና መደበኛ የመንገድ ጥገናዎች፡- መንገዶችን በመደበኛነት የመጠገን እና በየጊዜው የመንገዶችን ብልሽት በማየት በወቅታዊነት የሚጠገኑ መንገዶች የሚካተቱበት ነው፡፡ በ2017 በጀት ዓመት በወቅታዊ እና መደበኛ ጥገና 14,412 ኪ.ሜ ጥገና ይከናወናል፡፡ > 67 በመደበኛ ጥገና የሚካሄድላቸው ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡ > 41 ወቅታዊ ጥገና የሚከናወንባቸው ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡ 6. የመያዣ እና ማጠናቀቂያ ሥራ ፡- በውሉ መሰረት (guaranty) የሚያዝ በጀት እና የፕሮጀክቱ ፊዚካል ስራ ከተጠናቀቀ በኋላ የተወሰነ ሲቀራቸው ለማጠናቀቅ የሚያዝ በጀት ነው፡፡ > ከነባር መንገዶች ደረጃ ማሻሻል ውስጥ 5 የመያዣ እና ማጠናቀቂያ ሥራ ብቻ የሚቀራቸው ናቸው፡፡ > ከአዳዲስ እና ከፍጥነት መንገዶች ግንባታ ውስጥ 14 የመያዣ እና የማጠናቀቂያ ሥራ ብቻ የሚቀራቸው ናቸው፡፡ 7. ቅድመ ዝግጅት፡- በዲዛይን ሂደት ላይ ላሉ ፕሮጀክቶች የሚያዝ በጀት ነው፡፡፡ > ከአዲስ መንገዶች ግንባታና የፍጥነት መንገድ ውስጥ 5 በቅድመ ዝግጅት ላይ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

መልካም በዓል! የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

የቆሼ - ሚቶ - ወራቤ መንገድ ፕሮጀክት አስፋልት ወደ ማንጠፍ ምዕራፍ ተሸጋገረ ወራቤ፣ መስከረም 15፣ 2017 (ኢ መ አ):- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞንን ከማረቆ ልዮ ወረዳ ጋር የሚያገናኘው የቆሼ - ሚቶ - ወራቤ መንገድ ፕሮጀክት አስፋልት ወደ ማንጠፍ ምዕራፍ  ተሸጋግሯል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 73 ኪሎሜትር የሚሸፍን ኾኖ፣ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው። አሁን ላይ የ11 ነጥብ 2 ኪሎሜትር አስፋልት ንጣፍ፣ የ68 በመቶ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የ60 በመቶ ሰብቤዝ እንዲሁም የ16 በመቶ የቤዝኮርስ ሥራዎች ተከናውነዋል። በተጨማሪም ግንባታው የትራፊክ እንቅስቃሴውን እንዳያስተጓጉል ለተለዋጭ መንገዱ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል። የኹለት ድልድዮች ግንባታን ጨምሮ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ እንዲሁም የአነስተኛ እና ከፍተኛ ከልቨርቶች ግንባታ ሥራም በፕሮጀክቱ ተካትቷል። ከፕሮጀክቱ አጠቃላይ ሥራ አሁን ላይ 41 ኪሎሜትሩ ወይንም 56 በመቶው ተጠናቅቋል። የግንባታውን ቀሪ ሥራዎች ባጠረ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። የመንገድ ግንባታውን ሀገር-በቀሉ የንኮማድ ኮንስትራክሽን የሚያከናውን ሲኾን፥ የጥራት እና ቁጥጥር ሥራውን ሽላዲያ አሶሼትስ ከሂትኮን አማካሪ መሀንዲስ ጋር በጋራ በመኾን ይሠራሉ። ለግንባታ ሥራው 1,850,695,155.03 (አንድ ቢሊዮን ስምንት መቶ ሐምሳ ሚሊዮን ስድስት መቶ ዘጠና አምስት ሺህ) ብር በፌደራሉ መንግስት ተመድቧል። የመንገዱ ነባር ገጽታ 63 ኪሎሜትሩ በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲኾን፥ ቀሪው ምንም ዓይነት የመንገድ መሠረተ ልማት አልነበረውም። አሁን ላይ መንገዱ በወረዳ የእግረኛ መንገድን ሳይጨምር 14 ሜትር፣ በገጠር ቀበሌ የመንገድ ትከሻን ሳይጨምር 7ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ በመገንባት ላይ ነው የሚገኘው። ይኽ ፕሮጀክት የማረቆ እና የስልጤ ሕዝብ ሁለንተናዊ ትስስር ከማጎልበቱም ባለፈ በመንገድ ክልል እና በዙሪያው የሚገኙ የኡዳሳ፣ ጦራ፣ ዳሎቻ እና መሰል ከተሞች ዕድገት የሚያፋጥን ነው። ከዚህ ቀደም ከቆሼ ከተማ ተነስቶ የስልጤ ዞን መናገሻ ወራቤ ከተማ ለመድረስ የሚፈጀውን 3 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 1ሰዓት በማሳጠር፣ በአካባቢው በስፋት የሚታወቁትን የበርበሬ፣ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ጤፍ እና መሰል የጥራጥሬ እና የአዝርዕት ምርት ውጤቶች በፍጥነት እና በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ያስችላል። ለመኪና መለዋወጫ የሚወጣውን አላስፈላጊ ወጪ እና የነዳጅ ብክነትም የሚያስቀር ነው። የአባያ ሐይቅ (የስልጤ ሐይቅ)፣ አሹቴ ፏፏቴ እንዲሁም አይናጌ ዋሻ የተሰኙ የቱሪስት መዳረሻ ሥፍራዎችን ለጎብኝዎች ምቹ በማድረግ ረገድም የመንገድ ፕሮጀክቱ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ነባሩ የአዲስ አበባ - ሞጆ - መቂ መንገድ ከባድ ጥገና በመካሄድ ላይ ይገኛል አዲስ አበባ ፣ መስከረም 14/2017 ዓ.ም 108 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ነባሩ የአዲስ አበባ - ሞጆ - መቂ መንገድ ከባድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል ፡፡ የዚህ መንገድ አካል የሆነው በቢሾፍቱ በሚገኘው አየር ኃይል መግቢያ እስከ ፈጣን መንገድ መግቢያ ድረስ ያለው 5.3 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው መንገድ በመጠናቀቅ ላይ ነው ፡፡ ከዚህም ባሻገር ከገላን ወደ ሞጆ በሚወስደው መንገድ ላይ አልፎ አልፎ ያጋጠሙ ከባድ ብልሽቶች ጥገና ሲደረግላቸው ቆይቷል ፡፡ በቀጣይም እንደጉዳቱ መጠን እየታየ በሌሎች ቦታዎች ላይም ጥገናው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል ፡፡ አሁን ላይ በዓለምገና ዲስትሪክት አማካኝነት ተገቢው ጥገና እየተካሄደለት የሚገኘው ይኸው መንገድ በዚሁ ዓመት ሙሉ በሙሉ እንደሚጠናቀቅ እና በቀጣይም ተገቢ ክትትል እንደሚደረግለት ተገልጿል፡፡ በመስመሩ በርካታ ከተሞች የሚገኙ ሲሆን ፣ የመንገዱ መጠገን ከዚህ ቀደም የሚስተዋለውን የትራፊክ መጨናነቅ ያቃልላል ተብሎ ይታመናል፡፡ እንደሚታወቀው ለመንገዶች ግንባታ እና ጥገና የሚውለው መዋዕለ ንዋይ ከፍተኛ ከመሆኑ አንፃር ተገቢውን አገልግሎት ይሰጡ ዘንድ ሁሉም ባለንብረትና አሽከርካሪ በህግ በተደነገገው የክብደት መጠን መሰረት በመጫን ግዴታውን ሊወጣ ይገባል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ማሳሰቢያ!!
ማሳሰቢያ!!

መልካም በዓል !

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ም/ዋና ዳይሬክተር ሆነው ላለፉት በርካታ ዓመታት ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ የትምጌታ አስራት ከመስከረም 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒ
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ም/ዋና ዳይሬክተር ሆነው ላለፉት በርካታ ዓመታት ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ የትምጌታ አስራት ከመስከረም 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ሆነው ተሾመዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ቤተሰብም ክቡር ሚኒስትር ድኤታ አቶ የትምጌታ አስራት እንኳን ደስ አሎት እያለ መጪው የስራ ጊዜዎ የስኬት እንዲሆንልዎ  መልካም ምኞቱን ይገልጻል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

መልካም አዲስ ዓመት! ምርጥ መንገዶች ለኢትዮጵያ ብልጽግና!

መልዕክት!! በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግ
መልዕክት!! በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተዘጋጀው "የአፍሪቃ ከተሞች ፎረም" ላይ እየተሳተፈ ይገኛል። አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 29/2016 ዓ.ም ለተከታታይ ሦስት ቀናቶች በሚቆየ
+3
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተዘጋጀው "የአፍሪቃ ከተሞች ፎረም" ላይ እየተሳተፈ ይገኛል። አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 29/2016 ዓ.ም ለተከታታይ ሦስት ቀናቶች በሚቆየው ፎረም ላይ ከ 47 በላይ ሀገራት፣ ከ30 በላይ የአህጉሪቱ ከተማ ከንቲባዎች፣ ተመራማሪዎች እንዲሁም የተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ይሳተፋሉ፡፡ ከ1ሺህ 500 በላይ ተሣታፊዎች በዚሁ መድረክ ላይ እንደሚታደሙ ይታመናል። በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከናወነው ይኸው መድረክ "ዘላቂ የከተሞች ልማት ለአፍሪካ ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ 2063" በሚል መሪ ቃል ነው በመካሄድ ላይ የሚገኘው። ፎረሙ በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር እና በአፍሪካ ኅብረት አጋርነት የተሰናዳ ሲሆን ፣ ሀገራችን በዲፕሎማሲ፣ በማኅበረ-ኢኮኖሚ እንዲሁም ፖለቲካዊ መስኮች የምታተርፍበት ስለመሆኑም ተገልጿል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads