ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
前往频道在 Telegram
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
显示更多📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览
频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 331 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 756,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 537 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 331 名订阅者。
根据 17 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 95,过去 24 小时变化为 18,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 41.14%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.24% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 485 次浏览,首日通常累积 2 032 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 16。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 18 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
13 331
订阅者
+1824 小时
+417 天
+9530 天
帖子存档
13 331
የበለስ - መካነ ብርሃን አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታ 75 ነጥብ 2 በመቶ ደረሰ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2017 (ኢ መ አ):- በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን የደባርቅ እና ጃናሞራ ወረዳዎችን የሚያገናኘው የበለስ - መካነ ብርሃን አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታ አፈጻጸም 75 ነጥብ 2 በመቶ ደርሷል።
አሁን ላይ እየተሠሩ ከሚገኙ ዋና ዋና ሥራዎች መካከል የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የሰቤ ቤዝ፣ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ እንዲሁም የጠጠር ማምረት ሥራዎች ይጠቀሳሉ። በተጨማሪም የአስር አነስተኛ እና ከፍተኛ ድልድዩች ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቋል። ፕሮጀክቱ ባጠረ ጊዜ እንዲጠናቀቅ በኢ መ አ በኩል ጥብቅ ክትትል እየተደረገ ይገኛል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ 36 ነጥብ 42 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ ግንባታው በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ እየተካሄደ ይገኛል። በለስ ኮንሰልቲንግ የግንባታውን ጥራት የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ ይሠራል።
ለግንባታው የተመደበው 1,018,952,362.90 (አንድ ቢሊዮን አስራስምንት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺ ) ብር በፌደራል መንግስት ነው የሚሸፈነው።
የአካባቢው የቀድሞ ገጽታ ምንም ዓይነት የመንገድ መሠረተ ልማት ያልነበረው ሲኾን፥ በኅብረተሰቡ ጥያቄ መሠረት እንዲሁም ቦታው ካለው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አንጻር፣ በመንግስት ተወስኖ አሁን ላይ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል።
በአካባቢው የሚስተዋለውን ተደጋጋሚ የጸጥታ ችግር ተከትሎ የግንባታ ጥሬ እቃ እና ማሽነሪዎች በቀላሉ ማቅረብ አለመቻል እንዲሁም የሥፍራው አስቸጋሪ መልካዓ ምድራዊ አቀማመጥ የፕሮጀክቱ ፈተና መኾናቸው ተመልክቷል።
የመንገዱ መገንባት በተለይም በመንገድ እጦት ተራርቆ የቆየውን የደባርቅ እና ጃናሞራ ሕዝብ በቅርበት እና ደረጃውን በጠበቀ መንገድ የሚያገናኝ ነው። በመንገዱ ክልል እና በዙሪያው የሚገኙ የበለስ፣ ወይና፣ ሚጊራ እና መሰል ከተሞች ዕድገት ያፋጥናል። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ቀድሞ ይወስድ የነበረውን 8 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 1 ሰዓት ያሳጥረዋል።
የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ እንደመኾኑም የቱሪዝም ዘርፉን በማነቃቃት በኩል የጎላ ሚና ይጫወታል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
የኢኮኖሚና የማህበራዊ እድገትን ለማረጋገጥ በሚደረግ ሀገራዊ ጥረት የመንገድ ዘርፍ የሚገኝበትን ደረጃ የተሰጠው ትኩረት ወሳኝ ድርሻ አለው፡፡
ለዚህም ነው የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ትኩረት ለዘርፉ በመስጠት በየበጀት ዓመቱ ከፍተኛ መዋለ ንዋይ በመመደብ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች በመተግበር ላይ የሚገኘው፡፡
ይህንን ተከትሎም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በርካታ የመንገድ ግንባታ እና የጥገና ፕሮጀክቶች እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን፤ እነዚህንም ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እና የጥራት ደረጃ ለማስፈፀም የሚያስችሉትን የቅርብ ክትትል ድጋፍ ያደርጋል፡፡
በዚህ ረገድ በ2017 በጀት ዓመት ይኸው ተግባር የቀጠለ ሲሆን የበጀት ዓመቱን እቅድ ተከትለው በትግበራ ሂደት ላይ የሚገኙት ዋና ዋና ስራዎች እንደሚከተለው ይቀርባሉ፡፡
1. ነባር መንገዶችን ማጠናከር፡- በአገልግሎት ላይ ያሉ መንገዶች የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ የማጠናከርያ ስራዎችን በማከናወን ለትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ የማድረግ ሥራ ነው፡፡ በዚህም መሰረት 15 ኪሎ ሜትር ነባር መንገዶችን በማጠናከር ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡በዚህ ፕሮግራም ውስጥ ያሉ ፕሮጀክቶች ብዛት 4 ሲሆኑ ፡፡
> 1 በግንባታ ላይ ያለ ፣
> 3 ወደ ግንባታ ለመሸጋገር በሂደት ላይ ያሉ ናቸው፡፡
2. የነባር መንገዶች ደረጃ ማሻሻል፡- አገልግሎት ላይ ያሉ ነባር መንገዶችን ደረጃቸውን ከፍ በማድረግና በማሻሻል ከጠጠር ወደ አስፋልት እና በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ማሳደግ ነው፡፡ በዚህም መሰረት 330 ኪሎ ሜትር ነባር መንገዶችን የማሻሻል ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ በዚህ ፕሮግራም ውስጥ ያሉ ፕሮጀክቶች ብዛት 78 ናቸው፡፡
3. የአዳዲስ መንገዶች እና የፍጥነት መንገዶች ግንባታ :- ጨረታ ወጥቶላቸው የተፈረሙና ወደ ስራ የሚገቡ አዳዲስ መንገዶችን እንዲሁም የፍጥነት መንገዶች ማከናወን ያጠቃልላል፡፡ በ2017 የበጀት ዓመት 778 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ የአዳዲስ መንገዶች እና የፍጥነት መንገዶች ግንባታ ይከናወናል፡፡በዚህ ፕሮግራም ውስጥ 232 ፕሮጀክቶች ተካተዋል፡፡
4. የመንገዶች ከባድ ጥገና/Overlay Projects፡- የተበላሹ እና ነባር መንገዶችን በከፍተኛ ደረጃ የመጠገን ስራ የሚሰራበት ነው፡፡
> በ2017 በጀት ዓመት 144 ኪሎ ሜትር የመንገዶች ከባድ ጥገና/Overlay Projects ለማከናወን እቅድ ተይዟል፡፡
5. ወቅታዊ እና መደበኛ የመንገድ ጥገናዎች፡- መንገዶችን በመደበኛነት የመጠገን እና በየጊዜው የመንገዶችን ብልሽት በማየት በወቅታዊነት የሚጠገኑ መንገዶች የሚካተቱበት ነው፡፡ በ2017 በጀት ዓመት በወቅታዊ እና መደበኛ ጥገና 14,412 ኪ.ሜ ጥገና ይከናወናል፡፡
> 67 በመደበኛ ጥገና የሚካሄድላቸው ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡
> 41 ወቅታዊ ጥገና የሚከናወንባቸው ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡
6. የመያዣ እና ማጠናቀቂያ ሥራ ፡- በውሉ መሰረት (guaranty) የሚያዝ በጀት እና የፕሮጀክቱ ፊዚካል ስራ ከተጠናቀቀ በኋላ የተወሰነ ሲቀራቸው ለማጠናቀቅ የሚያዝ በጀት ነው፡፡
> ከነባር መንገዶች ደረጃ ማሻሻል ውስጥ 5 የመያዣ እና ማጠናቀቂያ ሥራ ብቻ የሚቀራቸው ናቸው፡፡
> ከአዳዲስ እና ከፍጥነት መንገዶች ግንባታ ውስጥ 14 የመያዣ እና የማጠናቀቂያ ሥራ ብቻ የሚቀራቸው ናቸው፡፡
7. ቅድመ ዝግጅት፡- በዲዛይን ሂደት ላይ ላሉ ፕሮጀክቶች የሚያዝ በጀት ነው፡፡፡
> ከአዲስ መንገዶች ግንባታና የፍጥነት መንገድ ውስጥ 5 በቅድመ ዝግጅት ላይ ይገኛሉ፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
የቆሼ - ሚቶ - ወራቤ መንገድ ፕሮጀክት አስፋልት ወደ ማንጠፍ ምዕራፍ ተሸጋገረ
ወራቤ፣ መስከረም 15፣ 2017 (ኢ መ አ):- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞንን ከማረቆ ልዮ ወረዳ ጋር የሚያገናኘው የቆሼ - ሚቶ - ወራቤ መንገድ ፕሮጀክት አስፋልት ወደ ማንጠፍ ምዕራፍ ተሸጋግሯል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ 73 ኪሎሜትር የሚሸፍን ኾኖ፣ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው።
አሁን ላይ የ11 ነጥብ 2 ኪሎሜትር አስፋልት ንጣፍ፣ የ68 በመቶ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የ60 በመቶ ሰብቤዝ እንዲሁም የ16 በመቶ የቤዝኮርስ ሥራዎች ተከናውነዋል። በተጨማሪም ግንባታው የትራፊክ እንቅስቃሴውን እንዳያስተጓጉል ለተለዋጭ መንገዱ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል። የኹለት ድልድዮች ግንባታን ጨምሮ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ እንዲሁም የአነስተኛ እና ከፍተኛ ከልቨርቶች ግንባታ ሥራም በፕሮጀክቱ ተካትቷል።
ከፕሮጀክቱ አጠቃላይ ሥራ አሁን ላይ 41 ኪሎሜትሩ ወይንም 56 በመቶው ተጠናቅቋል። የግንባታውን ቀሪ ሥራዎች ባጠረ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።
የመንገድ ግንባታውን ሀገር-በቀሉ የንኮማድ ኮንስትራክሽን የሚያከናውን ሲኾን፥ የጥራት እና ቁጥጥር ሥራውን ሽላዲያ አሶሼትስ ከሂትኮን አማካሪ መሀንዲስ ጋር በጋራ በመኾን ይሠራሉ።
ለግንባታ ሥራው 1,850,695,155.03 (አንድ ቢሊዮን ስምንት መቶ ሐምሳ ሚሊዮን ስድስት መቶ ዘጠና አምስት ሺህ) ብር በፌደራሉ መንግስት ተመድቧል።
የመንገዱ ነባር ገጽታ 63 ኪሎሜትሩ በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲኾን፥ ቀሪው ምንም ዓይነት የመንገድ መሠረተ ልማት አልነበረውም። አሁን ላይ መንገዱ በወረዳ የእግረኛ መንገድን ሳይጨምር 14 ሜትር፣ በገጠር ቀበሌ የመንገድ ትከሻን ሳይጨምር 7ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ በመገንባት ላይ ነው የሚገኘው።
ይኽ ፕሮጀክት የማረቆ እና የስልጤ ሕዝብ ሁለንተናዊ ትስስር ከማጎልበቱም ባለፈ በመንገድ ክልል እና በዙሪያው የሚገኙ የኡዳሳ፣ ጦራ፣ ዳሎቻ እና መሰል ከተሞች ዕድገት የሚያፋጥን ነው።
ከዚህ ቀደም ከቆሼ ከተማ ተነስቶ የስልጤ ዞን መናገሻ ወራቤ ከተማ ለመድረስ የሚፈጀውን 3 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 1ሰዓት በማሳጠር፣ በአካባቢው በስፋት የሚታወቁትን የበርበሬ፣ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ጤፍ እና መሰል የጥራጥሬ እና የአዝርዕት ምርት ውጤቶች በፍጥነት እና በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ያስችላል። ለመኪና መለዋወጫ የሚወጣውን አላስፈላጊ ወጪ እና የነዳጅ ብክነትም የሚያስቀር ነው።
የአባያ ሐይቅ (የስልጤ ሐይቅ)፣ አሹቴ ፏፏቴ እንዲሁም አይናጌ ዋሻ የተሰኙ የቱሪስት መዳረሻ ሥፍራዎችን ለጎብኝዎች ምቹ በማድረግ ረገድም የመንገድ ፕሮጀክቱ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
ነባሩ የአዲስ አበባ - ሞጆ - መቂ መንገድ ከባድ ጥገና በመካሄድ ላይ ይገኛል
አዲስ አበባ ፣ መስከረም 14/2017 ዓ.ም 108 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ነባሩ የአዲስ አበባ - ሞጆ - መቂ መንገድ ከባድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል ፡፡
የዚህ መንገድ አካል የሆነው በቢሾፍቱ በሚገኘው አየር ኃይል መግቢያ እስከ ፈጣን መንገድ መግቢያ ድረስ ያለው 5.3 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው መንገድ በመጠናቀቅ ላይ ነው ፡፡ ከዚህም ባሻገር ከገላን ወደ ሞጆ በሚወስደው መንገድ ላይ አልፎ አልፎ ያጋጠሙ ከባድ ብልሽቶች ጥገና ሲደረግላቸው ቆይቷል ፡፡ በቀጣይም እንደጉዳቱ መጠን እየታየ በሌሎች ቦታዎች ላይም ጥገናው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል ፡፡
አሁን ላይ በዓለምገና ዲስትሪክት አማካኝነት ተገቢው ጥገና እየተካሄደለት የሚገኘው ይኸው መንገድ በዚሁ ዓመት ሙሉ በሙሉ እንደሚጠናቀቅ እና በቀጣይም ተገቢ ክትትል እንደሚደረግለት ተገልጿል፡፡
በመስመሩ በርካታ ከተሞች የሚገኙ ሲሆን ፣ የመንገዱ መጠገን ከዚህ ቀደም የሚስተዋለውን የትራፊክ መጨናነቅ ያቃልላል ተብሎ ይታመናል፡፡
እንደሚታወቀው ለመንገዶች ግንባታ እና ጥገና የሚውለው መዋዕለ ንዋይ ከፍተኛ ከመሆኑ አንፃር ተገቢውን አገልግሎት ይሰጡ ዘንድ ሁሉም ባለንብረትና አሽከርካሪ በህግ በተደነገገው የክብደት መጠን መሰረት በመጫን ግዴታውን ሊወጣ ይገባል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ም/ዋና ዳይሬክተር ሆነው ላለፉት በርካታ ዓመታት ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ የትምጌታ አስራት ከመስከረም 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ሆነው ተሾመዋል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ቤተሰብም ክቡር ሚኒስትር ድኤታ አቶ የትምጌታ አስራት እንኳን ደስ አሎት እያለ መጪው የስራ ጊዜዎ የስኬት እንዲሆንልዎ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
መልዕክት!!
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
+3
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተዘጋጀው "የአፍሪቃ ከተሞች ፎረም" ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 29/2016 ዓ.ም ለተከታታይ ሦስት ቀናቶች በሚቆየው ፎረም ላይ ከ 47 በላይ ሀገራት፣ ከ30 በላይ የአህጉሪቱ ከተማ ከንቲባዎች፣ ተመራማሪዎች እንዲሁም የተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ይሳተፋሉ፡፡ ከ1ሺህ 500 በላይ ተሣታፊዎች በዚሁ መድረክ ላይ እንደሚታደሙ ይታመናል።
በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከናወነው ይኸው መድረክ "ዘላቂ የከተሞች ልማት ለአፍሪካ ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ 2063" በሚል መሪ ቃል ነው በመካሄድ ላይ የሚገኘው። ፎረሙ በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር እና በአፍሪካ ኅብረት አጋርነት የተሰናዳ ሲሆን ፣ ሀገራችን በዲፕሎማሲ፣ በማኅበረ-ኢኮኖሚ እንዲሁም ፖለቲካዊ መስኮች የምታተርፍበት ስለመሆኑም ተገልጿል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
