en
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Open in Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 475 subscribers, ranking 1 732 in the Transport category and 2 491 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 475 subscribers.

According to the latest data from 29 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 209 over the last 30 days and by 5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 36.12%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.66% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 868 views. Within the first day, a publication typically gains 2 111 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 11.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 30 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Transport category.

13 475
Subscribers
+524 hours
+987 days
+20930 days
Posts Archive
የኮንስትራሽን ዘርፉን  ወደ ከፍታ የሚያሸጋግር የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ኢኒሼቲቭ ይፋ ሆነ አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 5፣ 2017 ዓ.ም (ኢመአ)፡ የኮንስትራሽን ዘርፉን  ወደ ከፍታ ለማሸጋገር በፈረንጆቹ ከ2025 እስከ 2050 ድረስ የሚተገበር የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ኢኒሼቲቭ ይፋ ተደርጓል ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በዚህ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪ እና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ መፍጠር ያስልጋል። በኮንስትራክሽን ኢንደስትሪ ውስጥ ለመቆየት ተወዳዳሪነት እና ብቃት ወሳኝ በመሆኑ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ እና ወጪ ማጠናቀቅ አንዱ መገለጫ ሊሆን ይገባል። አሰራሮችን ማዘመን ፣ቴክኖሎጂን መጠቀም፣ እና ዘመናዊ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ስርዓትን መከተል ለኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ህልውና እና አስተማማኝ እድገት ለማምጣት ወሳኝ ናቸው። የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ለሀገራችን እድገት ጉልህ አስተዋጸኦ ሲያበረክት የቆየ እና በቀጠይም ማሳካት ለሚፈለገው ግብ  የማይተካ ሚና ያለው  ከመሆኑም ባሻገር መንገዶች  ለማህበራዊ አገልግሎቶች ያላቸው ተደራሽነት በጣም ከፍተኛ ነው፡፡ ኢንዱስትሪው የሀገር ሥልጣኔ ማሳያ እንደመሆኑ ሥራዎችን በትብብር ማከናወን እንደሚገባ ተገልጿል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የጥንቃቄ መልዕክት!!
የጥንቃቄ መልዕክት!!

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሰራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሄዱ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24 ፣ 2017 (ኢ መ አ):- የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሰራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል ዛሬ  ለሰባተኛ ዙር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሄዱ። የዋናው መስሪያ ቤቱ ፤ የአለም ገና ማሰለጠኛ እና የምርምር ማዕከላት ሰራተኞች እና  የሥራ ኃላፊዎች በጋራ  በመሆን  በእንጦጦ ኦቭዞርቫቶሪ ማዕከል አካባቢ አሻራቸውን አሳርፈዋል። በተመሳሳይ ተቋሙ በሁሉም የጥገና ዲስትሪክቶች ፥ ሴክሽኖች እና ማሰልጠኛ ማዕከላት እንዲሁም ፕሮጀክት ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች ችግኞችን ተክሏል። ተቋሙ በዛሬው ዕለት በሁሉም አካባቢ የተከለውን 200,000 ችግኝ ጨምሮ በሰባተኛው ዙር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ከ700,000 በላይ ችግኞችን ተክሏል። ኢመአ ባለፋት ሰባት ዓመታት ሀገራዊ  አረንጓዴ አሻራን ለማሳረፍ የተቋሙን መላውን ሰራተኛ በማሳተፍ  ሀላፊነቱን መወጣቱን ቀጥሏል። የተቋሙ ሰራተኞች  አረንጓዴ አሻራን ማሰረፉ ያለው ጥቅም የጎላ መሆኑን ተረድተው ሀገራዊ ባህል ተሳትፎና ንቃታቸው በማደጉ ደስተኞች መሆናቸውን የተቋሙ የስራ ኃላፊዎች ገልፀዋል ። የተከሉትን ችግኞች በቀጣይ መንከባከብ ላይ በትኩረት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። እንደ ተቋም በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች  የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ የሚያደርግ ግብረ -ሀይል በመቋቋሙምም የመጽደቅ ምጣኔው አጥጋቢ ውጤት እንዲገኝ ማስቻሉ ተገልጿል። በተለይም የመንገድ ግንባታን ተከትሎ በደኖች ላይ ጉዳት እንዳይከሰት መጠንቀቅ መቻሉ ፤ የዲዛይን ስራዎችን ታሳቢ አድርጎ ቀድሞ መስራቱ እንዲሁም ተቋራጮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የችግኝ ተከላ መርሃ -ግብርን አጠናክረው መቀጠላቸው በአካባቢ ጥበቃ ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ የሚያሳድር መሆኑ ታውቋል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኢትዮጵያ የገጠር ትስስር ለምግብ ዋስትና መርሃ ግብርን (Rural Connectivity for Food Security Program) አስመልክቶ ውይይት ተካሄደ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24 ፣ 2017 (ኢ መ አ):- የኢትዮጵያ የገጠር ትስስር ለምግብ ዋስትና መርሃ ግብርን አስመልክቶ ሰትሪነግ ኮሚቴ (Rural Connectivity for Food Security Program Stressing Committee) የፕሮግራሙን  2017 ዕቅድ አፈጻጸም  እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አስመልክቶ ውይይት አካሂዷል፡፡ የኢትዮጵያ የገጠር ትስስር ለምግብ ዋስትና መርሃ ግብር ዓላማ የታለሙ ህዝቦችን ለምግብ ገበያ እና አገልግሎት ለአየር ንብረትን የማይበገር መንገዶችን ተደራሽነት ማሳደግ  እና የገጠር መንገዶች አስተዳደር ተቋማዊ አቅምን ማጠናከር ነው። በመርሃ ግብሩ የገጠር መንገዶችን ማሻሻል ፣ ግንባታ እና ጥገና የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችሉ ደረጃ ያላቸው መንገዶችን በመገንባት የገጠር ቀበሌ ማዕከላትን በአቅራቢያው ከሚገኙ ዋና ዋና መንገዶች ጋር በማገናኘት የግብርና እምቅ አካባቢዎችን የሚያገናኙ መንገዶችን መገንባት እንዲሁም በመልክአ ምድራዊ አቀማመጥ ምክንያት ተደራሽነት ለሌላቸው አካባቢዎች የእግረኞች ማቆሚያ ማቋረጫዎች (የመሄጃ ድልድዮች) ግንባታ የማከናወን ተግባራት የሚካሄዱበት ነው፡፡  ከዚህም ባሻገር ለቆላማና አርብቶ አደር ማህበረሰቦች በየወቅቱ በጎርፍ ምክንያት መሻገሪያ ችግር ላለባቸው ልዩ መዋቅሮች የቧንቧ ቱቦዎች፣ የቦክስ  ድልድዮች ወዘተ ግንባታ ማከናወን እና የአየር ንብረት አደጋዎችን ለመቋቋም የሚስችሉ ታሳቢዎችን በማካተት የክልል እና የወረዳ መንገዶችን ለመስራት በማቀድ የትግበራ እና የአስተዳደር ስልቶችን እና ልምዶችን ማሻሻል  የመርሃ ግብሩ የትኩረት መስክ ነው፡፡ በተጨማሪም የአየር ንብረት አደጋዎችን ግምት ውስጥ በማስገባት የገጠር መንገድ ንብረት አስተዳደር ስርዓቶችን ማጠናከር ፤ በገጠር መንገዶች ላይ የመንገድ ደህንነትን ማሳደግ በተለይ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ የመንገድ ተጠቃሚዎችን ፣  እግረኞችን እና ባለ 2/3-ጎማ ተሽከርካሪዎችን ስርዓት መሻሻልን እና  ተቋማዊ የልማት ተግባራትን የማከናወን ተግባራት በመርሃ-ግብሩ ይከናወናሉ፡፡ በፕሮግራሙ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የሚከናወን ሲሆን ፣ በ2017 ዓ.ም ከታዩት መልካም አጋጣሚዎች በመነሳት በፌደራል እና በክልል መንግስታት መንገዶች በጥራት እንዲከናወኑ  ባለሞያዎችን ከሚደግፉ ተቋማት መካከል የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋም የሆነው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ቁርጠኝነቱን አሳይቷል ። በዚህም የገጠር ትስስር ለምግብ ዋስትና መርሃግብር በ2017 ዓ.ም ለሁሉም  የገጠር ማህበረሰቦች መንገዶችን በመሥራት  ከከተማ ጋር  ለማስተሳሰር እና የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማሻሻል ባደረገው የፕሮጀክት ዕቅድ አፈጻጸም   ላይ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ  ግምገማ አካሂዷል ። በሌላ በኩል የቀጣይ 2018 በጀት ዕቅድ ትኩረቶች ቀደም  ሲል የነበሩ መንገዶችን መጠገን ፣ማህበራዊ ፋይዳ ያላቸውን መዳረሻዎችን ማገናኘት፣ ደህንነቱ የተጠበቀ መንገድ እንዲገነባ ማድረግ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን የመንገድ ፕሮግራሙ በ 2018 በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ክረምት ከበጋ አገልግሎት የሚሰጡ የአዳዲስ የ2266 ኪሎሜትር የመንገድ ግንባታ ፣  የ243 የተንጠልጣይ የእግረኛ መሻገሪያ ድልድዮች ግንባታ እንዲሁም  የ3021 ኪሎሜትር በተገነቡ ነባር የገጠር መንገዶች ላይ ጥገና እና በህብረተሰብ ተሳትፎ የ5600 ኪሎሜትር የገጠር መንገድ ለመገንባት ከታሰቡት ዕቅዶች መካከል  ተጠቃሾች ናቸው ። የተሻሻሉ የገጠር መንገዶች ማህበራዊ አገልግሎቶችን የማግኘት አቅማቸውን በማሳደግ በገጠር ነዋሪዎች ላይ አወንታዊ ተፅእኖ የሚኖረው ሲሆን  በሀገር አቀፍ ደረጃ  ትልቅ ሚና  ይኖረዋል ። የፕሮግራሙን ውጤታማነት ለማረጋገጥ  መሻሻል ያለባቸውን ቦታዎች በመለየት  የመደበኛ  ክትትል ስራዎች  እንደሚያስፈልጉ ተመላክቷል ። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

በዋርዴር - ቀብሪደሀር መንገድ ፕሮጀክት አስፋልት የማንጠፍ ሥራ እየተከናወነ ነው አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2017 (ኢ መ አ):- በሶማሌ ክልል የዋርዴር ዞንን ከቀብሪደሀር ዞን ጋር በሚያገናኘው የመንገድ ፕሮጀክት አስፋልት የማንጠፍ ሥራ እየተከናወነለት ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ 138 ነጥብ 94 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ አሁን ላይ የ36 ኪሎሜትር አስፋልት የማልበስ ሥራ ተሠርቷል። ጎን ለጎንም የስትራክቸር፥ የሰብቤዝ፥ ቤዝኮርስ እንዲሁም የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። ከፕሮጀክቱ አጠቃላይ የግንባታ ሥራ አሁን ላይ 69 በመቶው ተጠናቅቋል። የገንዘብ እጥረት፣ የሥራ ተቋራጩ የመፈጸም አቅም እንዲሁም የውኃ እጥረት በግንባታው ወቅት የገጠሙ ተግዳሮቶች ናቸው። ችግሮቹን መቅረፍ የሚያስችሉ የተለያዩ ጥረቶችም በመደረግ ላይ ናቸው። ሀገር - በቀሉ ማክሮ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ ግንባታውን በማከናወን ላይ ይገኛል። ለመንገድ ግንባታው 1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በፌደራል መንግስት ተመድቦለታል። የመንገዱ መገንባት 2 ዞኖችን ጨምሮ 1 ወረዳ እና 7 ቀበሌዎችን በማስተሳሰር የነዋሪውን ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያሳድጋል። በመሥመሩ የሚገኙ አነስተኛ መንደሮች ወደ ከተማነት የሚያድጉበትን ምቹ ዕድል ይፈጥራል። ነባሩ መንገድ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ እና ለመጓዝ ከ4 ሰዓት በላይ የሚወስድ ሲኾን፥ በቀጣይ ግንባታው ሲጠናቀቅ ከዋርዴር ከተማ ተነስቶ ቀብሪደሀር ከተማ ለመድረስ የሚፈጀውን ጊዜ ወደ 2 ሰዓት ያሳጥረዋል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የባሌ ጎባ -በርበሬ-ደሎመና የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 08 ፣ 2017 (ኢ መ አ):-  የባሌ ጎባ -በርበሬ-ደሎመና የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ አፈፃፀም ላይ የሚገኝ ሲሆን አሁናዊ አፈፃፀሙም  44.19 ኪሎ ሜትር (33.21%) ላይ ደርሷል ። መንገዱ የሚሠራው በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ሲሆን ጠቅላላ እርዝመቱ 133.09 ኪ.ሜ ነው ። የጎን ስፋቱ የእግረኛ መንገድን ጨምሮ በወረዳ 22.5ሜ ፣ በቀበሌ 17ሜ. ሲሆን በገጠር ደግሞ የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 10 ሜ. ነው ። የመንገድ ግንባታውን በማከናወን ላይ የሚገኘው አገር በቀሉ ዓለማየሁ ከተማ ኮንስትራክሽን ድርጅት ሲሆን የማማከርና ቁጥጥር ሥራው ደግሞ  ቤስት ኮንሰልቲን ኢንጂነርስ ኃ/የተ/የግ /ማህበር በማካሄድ ላይ ነው ። ለግንባታ የሚውለው 8,400,000,000.00 (ስምንት ቢሊዮን አራት መቶ ሚሊዮን ብር )  በኢትዮጵያ መንግሥት የተሸፈነ ነው ፡፡ በእስከአሁኑ አፈፃፀም ከፕሮጀክቱ አጠቃላይ 133 ኪሎ ሜትር ውስጥ44.19 ኪሎ ሜትር (33.21%) የጠረጋና የሙሌት ሥራዎች የተሠሩ ሲሆን ፣  4 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራም ተከናውኗል ። የዚህ ፕሮጀክት መጠናቀቅ በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን እንደ ስንዴ ፣ ገብስ ፣ጤፍ ፣ በቆሎ ፣ ለውዝ  ፣ ማር እና የተለያዩ ቅመማ ቅመሞችን በቀላሉ ለገበያ ተደራሽ ለማድረግ ያስችላል፡፡ በተጨማሪም የማህረሰቡን ማህበራዊ አገልግሎት ከማሳለጥ ባሻገር አካባቢው የባሌ ተራሮች መገኛ በመሆኑ የአካባቢውን የቱሪስት ፍሰት በመጨመር ረገድም አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል፡፡   ይህ ጎባ ከተማ ላይ ተጀምሮ ደሎ ከተማ ላይ የሚያበቃው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ከ አዲስ አበባ  450 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ነው ። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

መሀንዲሶች መንገድ ከመገንባት በዘለለ ለትውልድ የሚተላለፍ አሻራ ማኖር ይጠበቅባቸዋል - አቶ ዛዲግ አብርሃ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2017 (ኢ መ አ): መሀንዲሶች መንገድ ከመገንባት በዘለለ ለትውልድ የሚተላለፍ አሻራ ማኖር ይጠበቅባቸዋል ሲሉ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናግረዋል። ለኢ መ አ ከፍተኛ አመራሮች በትራንስፎርሜሽን ሊደርሺፕ ዙሪያ እየተሰጠ ያለው ተከታታይ ሥልጠና በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ውሏል። አቶ ዛዲግ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ መሀንዲሶች በሀገረ መንግስት እና በብሔረ መንግስት ግንባታ ቁልፍ ሚና እንዳላቸው ሊገነዘቡ ይገባል። ከዚህም ባለፈ መሀንዲሶች አድማሰ ሰፊ፣ በሥነ ምግባር የታነጹ፣ ከሕዝብ ዘንድ መልካም አመኔታን ያተረፉ እንዲሁም ከአካባቢ አስተሳሰብ ወጥተው በሀገር ደረጃ ማሰብ የሚችሉ መሆን ይገባቸዋል ብለዋል። መንገድ ከመገንባት ባሻገር መሀንዲሶች ለትውልድ ውርስ ሲሰሩ በሕዝብ ዘንድ የሚገባቸውን መልካም ሥም እና ሞገስ ያገኛሉ ብለዋል። የአንዲት ሀገር ዕድል ፈንታ ከሚወስኑት መካከል በመንገዶቿ ስፋት፣ በድልድዮቿ ጥንካሬ እንዲሁም በመሀንዲሶቿ ታታሪነት መኾኑንም አንስተዋል። የመንገድ ግንባታ የፍትህ፣ የፖሊሲ እና የማንነት ጉዳይ ነው ያሉት አቶ ዛዲግ፤ የመንገድ ግንባታዎች እንዲሁም ድልድዮች ብሔራዊ ትዕምርት ሊኾኑ ይገባል ብለዋል። ከዚህም ባሻገር በጥናት ላይ የተመሠረተ የመንገድ ስርአት እንዲኖር ማድረግ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተውበታል። ለማኅበረሰቡም ለዘለቄታው የሚጠቀምበት እና የሀገሪቱን የመንገድ ሀብት በአግባቡ መጠበቅ የሁሉም ሀላፊነት እንደሆነ አቶ ዛዲግ አብርሃ ጨምረው ተናግረዋል ። ለከፍተኛ አመራሮች እና ባለሞያዎች የሚሰጠው የአቅም ግንባታ ሥልጠና በተከታታይነት እየተሰጠ ይገኛል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

ለሀገራችን የመሠረተ ልማት ማንሰራራት በሥነ ምግባር የታነጹ እና በቴክኖሎጂ የታገዙ ማሀንዲሶች ሚና ወሳኝ ነው:- አቶ ዛዲግ አብርሃ አዲስ አባባ፣ ሐምሌ 13፣ 2017 (ኢ መ አ):- ለሀገራችን የመሠረተ ልማት ማንሰራራት በሥነ ምግባር የታነጹ እና በቴክኖሎጂ የታገዙ ማሀንዲሶች ሚና ወሳኝ መኾኑን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናግረዋል። አቶ ዛዲግ ' መንገድ እና የኢትዮጵያ ማንሰራራት' በሚል ርዕስ ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች እና ማሀንዲሶች ሥልጠና እየሰጡ ይገኛሉ። ፕሬዝዳንቱ በወቅቱ እንደገለጹት፤ መሀንዲሶች መንገድ የመሠረት ልማቶች ሁሉ አውራ መኾኑን በመገንዘብ ለሀገራዊ የመንገድ ፕሮግራም ስኬት መትጋት፣ የመንገድ ፕሮጀክቶች በተቀመጠላቸው የጥራት ደረጃ፣ የዋጋ መጠን እና የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ በማድረግ በኩል ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል። ለሀገራዊ ትልም መሳካት መሀንዲሶች ቁልፍ ሚና እንዳላቸው የገለጹት አቶ ዛዲግ፥ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ስንክሳሮችን የሚፈታ ድልድይ እየገነቡ መኾናቸውን መሀንዲሶች መረዳት ይኖርባቸዋል ብለዋል። መሀንዲሶች ሀገር ሲያቀኑ ህፃናት ወደ ትምህርት ቤት ይሄዳሉ፣ ምርት ለገበያ ይቀርባል፣ እናቶች ወደ ሆስፒታል ያመራሉ፣ ግንኙነት ይሳለጣል በድምሩ የብሄረ መንግስት እና የሀገረ መንግስት ግንባታ እውን እንደሚሆን አብራርተዋል። ለአራት ቀናት የሚቆየው ሥልጠናው፣ በሚቀጥሉት ቀናትም የሚካሄድ ይሆናል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

በናዳ ምክንያት ዝግ ኾኖ የቆየው የሳውላ - ላስካ - ሳላይሽ መንገድ ለትራፊክ አገልግሎት ክፍት ኾነ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2017 (ኢ መ አ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በናዳ ምክንያት ዝግ ኾኖ የቆየው የሳውላ - ላስካ - ሳላይሽ መንገድ ለትራፊክ አገልግሎት ክፍት ኾኗል። መንገዱ አካባቢው ላይ በጣለው ከባድ ዝናብ ተከትሎ በተከሰተ ናዳ ለ3 ቀናት ለትራፊክ አገልግሎት ዝግ ኾኖ ቆይቷል። አሁን ላይ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሶዶ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ባደረገው ከፍተኛ ርብርብ ጊዜያዊ የተለዋጭ መንገድ በመገንባት መንገዱን ዳግም ለትራፊክ እንቅስቃሴ ክፍት ማድረግ ተችሏል። በሌላ በኩል ዋናውን መንገድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከናዳ ነጻ ለማድረግ እና ለትራፊክ እንቅስቃሴ ክፍት ለማድረግ ዲስትሪክቱ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል። ጎን ለጎንም አካባቢው ለናዳ የተጋለጠ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ አስፈላጊውን የቅድመ-ጥንቃቄ ሥራዎችን በየጊዜው ያከናውናል። በዚህ አጋጣሚ አሽከርካሪዎች መንገዱ ክፍት እስኪኾን ድረስ ላሳዩት ትዕግስት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እያመሰገነ፣ ወቅቱ ክረምት እንደመኾኑ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ያሳስባል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et