uk
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Відкрити в Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Канал ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 13 323 підписників, посідаючи 1 756 місце в категорії Транспорт та 2 541 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 13 323 підписників.

За останніми даними від 16 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 90, а за останні 24 години на 8, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 40.85%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 15.40% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 439 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 050 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 17.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 17 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Транспорт.

13 323
Підписники
+824 години
+217 днів
+9030 день
Архів дописів
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሰራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሄዱ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24 ፣ 2017 (ኢ መ አ):- የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሰራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል ዛሬ  ለሰባተኛ ዙር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሄዱ። የዋናው መስሪያ ቤቱ ፤ የአለም ገና ማሰለጠኛ እና የምርምር ማዕከላት ሰራተኞች እና  የሥራ ኃላፊዎች በጋራ  በመሆን  በእንጦጦ ኦቭዞርቫቶሪ ማዕከል አካባቢ አሻራቸውን አሳርፈዋል። በተመሳሳይ ተቋሙ በሁሉም የጥገና ዲስትሪክቶች ፥ ሴክሽኖች እና ማሰልጠኛ ማዕከላት እንዲሁም ፕሮጀክት ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች ችግኞችን ተክሏል። ተቋሙ በዛሬው ዕለት በሁሉም አካባቢ የተከለውን 200,000 ችግኝ ጨምሮ በሰባተኛው ዙር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ከ700,000 በላይ ችግኞችን ተክሏል። ኢመአ ባለፋት ሰባት ዓመታት ሀገራዊ  አረንጓዴ አሻራን ለማሳረፍ የተቋሙን መላውን ሰራተኛ በማሳተፍ  ሀላፊነቱን መወጣቱን ቀጥሏል። የተቋሙ ሰራተኞች  አረንጓዴ አሻራን ማሰረፉ ያለው ጥቅም የጎላ መሆኑን ተረድተው ሀገራዊ ባህል ተሳትፎና ንቃታቸው በማደጉ ደስተኞች መሆናቸውን የተቋሙ የስራ ኃላፊዎች ገልፀዋል ። የተከሉትን ችግኞች በቀጣይ መንከባከብ ላይ በትኩረት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። እንደ ተቋም በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች  የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ የሚያደርግ ግብረ -ሀይል በመቋቋሙምም የመጽደቅ ምጣኔው አጥጋቢ ውጤት እንዲገኝ ማስቻሉ ተገልጿል። በተለይም የመንገድ ግንባታን ተከትሎ በደኖች ላይ ጉዳት እንዳይከሰት መጠንቀቅ መቻሉ ፤ የዲዛይን ስራዎችን ታሳቢ አድርጎ ቀድሞ መስራቱ እንዲሁም ተቋራጮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የችግኝ ተከላ መርሃ -ግብርን አጠናክረው መቀጠላቸው በአካባቢ ጥበቃ ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ የሚያሳድር መሆኑ ታውቋል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኢትዮጵያ የገጠር ትስስር ለምግብ ዋስትና መርሃ ግብርን (Rural Connectivity for Food Security Program) አስመልክቶ ውይይት ተካሄደ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24 ፣ 2017 (ኢ መ አ):- የኢትዮጵያ የገጠር ትስስር ለምግብ ዋስትና መርሃ ግብርን አስመልክቶ ሰትሪነግ ኮሚቴ (Rural Connectivity for Food Security Program Stressing Committee) የፕሮግራሙን  2017 ዕቅድ አፈጻጸም  እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አስመልክቶ ውይይት አካሂዷል፡፡ የኢትዮጵያ የገጠር ትስስር ለምግብ ዋስትና መርሃ ግብር ዓላማ የታለሙ ህዝቦችን ለምግብ ገበያ እና አገልግሎት ለአየር ንብረትን የማይበገር መንገዶችን ተደራሽነት ማሳደግ  እና የገጠር መንገዶች አስተዳደር ተቋማዊ አቅምን ማጠናከር ነው። በመርሃ ግብሩ የገጠር መንገዶችን ማሻሻል ፣ ግንባታ እና ጥገና የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችሉ ደረጃ ያላቸው መንገዶችን በመገንባት የገጠር ቀበሌ ማዕከላትን በአቅራቢያው ከሚገኙ ዋና ዋና መንገዶች ጋር በማገናኘት የግብርና እምቅ አካባቢዎችን የሚያገናኙ መንገዶችን መገንባት እንዲሁም በመልክአ ምድራዊ አቀማመጥ ምክንያት ተደራሽነት ለሌላቸው አካባቢዎች የእግረኞች ማቆሚያ ማቋረጫዎች (የመሄጃ ድልድዮች) ግንባታ የማከናወን ተግባራት የሚካሄዱበት ነው፡፡  ከዚህም ባሻገር ለቆላማና አርብቶ አደር ማህበረሰቦች በየወቅቱ በጎርፍ ምክንያት መሻገሪያ ችግር ላለባቸው ልዩ መዋቅሮች የቧንቧ ቱቦዎች፣ የቦክስ  ድልድዮች ወዘተ ግንባታ ማከናወን እና የአየር ንብረት አደጋዎችን ለመቋቋም የሚስችሉ ታሳቢዎችን በማካተት የክልል እና የወረዳ መንገዶችን ለመስራት በማቀድ የትግበራ እና የአስተዳደር ስልቶችን እና ልምዶችን ማሻሻል  የመርሃ ግብሩ የትኩረት መስክ ነው፡፡ በተጨማሪም የአየር ንብረት አደጋዎችን ግምት ውስጥ በማስገባት የገጠር መንገድ ንብረት አስተዳደር ስርዓቶችን ማጠናከር ፤ በገጠር መንገዶች ላይ የመንገድ ደህንነትን ማሳደግ በተለይ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ የመንገድ ተጠቃሚዎችን ፣  እግረኞችን እና ባለ 2/3-ጎማ ተሽከርካሪዎችን ስርዓት መሻሻልን እና  ተቋማዊ የልማት ተግባራትን የማከናወን ተግባራት በመርሃ-ግብሩ ይከናወናሉ፡፡ በፕሮግራሙ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የሚከናወን ሲሆን ፣ በ2017 ዓ.ም ከታዩት መልካም አጋጣሚዎች በመነሳት በፌደራል እና በክልል መንግስታት መንገዶች በጥራት እንዲከናወኑ  ባለሞያዎችን ከሚደግፉ ተቋማት መካከል የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋም የሆነው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ቁርጠኝነቱን አሳይቷል ። በዚህም የገጠር ትስስር ለምግብ ዋስትና መርሃግብር በ2017 ዓ.ም ለሁሉም  የገጠር ማህበረሰቦች መንገዶችን በመሥራት  ከከተማ ጋር  ለማስተሳሰር እና የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማሻሻል ባደረገው የፕሮጀክት ዕቅድ አፈጻጸም   ላይ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ  ግምገማ አካሂዷል ። በሌላ በኩል የቀጣይ 2018 በጀት ዕቅድ ትኩረቶች ቀደም  ሲል የነበሩ መንገዶችን መጠገን ፣ማህበራዊ ፋይዳ ያላቸውን መዳረሻዎችን ማገናኘት፣ ደህንነቱ የተጠበቀ መንገድ እንዲገነባ ማድረግ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን የመንገድ ፕሮግራሙ በ 2018 በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ክረምት ከበጋ አገልግሎት የሚሰጡ የአዳዲስ የ2266 ኪሎሜትር የመንገድ ግንባታ ፣  የ243 የተንጠልጣይ የእግረኛ መሻገሪያ ድልድዮች ግንባታ እንዲሁም  የ3021 ኪሎሜትር በተገነቡ ነባር የገጠር መንገዶች ላይ ጥገና እና በህብረተሰብ ተሳትፎ የ5600 ኪሎሜትር የገጠር መንገድ ለመገንባት ከታሰቡት ዕቅዶች መካከል  ተጠቃሾች ናቸው ። የተሻሻሉ የገጠር መንገዶች ማህበራዊ አገልግሎቶችን የማግኘት አቅማቸውን በማሳደግ በገጠር ነዋሪዎች ላይ አወንታዊ ተፅእኖ የሚኖረው ሲሆን  በሀገር አቀፍ ደረጃ  ትልቅ ሚና  ይኖረዋል ። የፕሮግራሙን ውጤታማነት ለማረጋገጥ  መሻሻል ያለባቸውን ቦታዎች በመለየት  የመደበኛ  ክትትል ስራዎች  እንደሚያስፈልጉ ተመላክቷል ። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

በዋርዴር - ቀብሪደሀር መንገድ ፕሮጀክት አስፋልት የማንጠፍ ሥራ እየተከናወነ ነው አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2017 (ኢ መ አ):- በሶማሌ ክልል የዋርዴር ዞንን ከቀብሪደሀር ዞን ጋር በሚያገናኘው የመንገድ ፕሮጀክት አስፋልት የማንጠፍ ሥራ እየተከናወነለት ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ 138 ነጥብ 94 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ አሁን ላይ የ36 ኪሎሜትር አስፋልት የማልበስ ሥራ ተሠርቷል። ጎን ለጎንም የስትራክቸር፥ የሰብቤዝ፥ ቤዝኮርስ እንዲሁም የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። ከፕሮጀክቱ አጠቃላይ የግንባታ ሥራ አሁን ላይ 69 በመቶው ተጠናቅቋል። የገንዘብ እጥረት፣ የሥራ ተቋራጩ የመፈጸም አቅም እንዲሁም የውኃ እጥረት በግንባታው ወቅት የገጠሙ ተግዳሮቶች ናቸው። ችግሮቹን መቅረፍ የሚያስችሉ የተለያዩ ጥረቶችም በመደረግ ላይ ናቸው። ሀገር - በቀሉ ማክሮ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ ግንባታውን በማከናወን ላይ ይገኛል። ለመንገድ ግንባታው 1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በፌደራል መንግስት ተመድቦለታል። የመንገዱ መገንባት 2 ዞኖችን ጨምሮ 1 ወረዳ እና 7 ቀበሌዎችን በማስተሳሰር የነዋሪውን ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያሳድጋል። በመሥመሩ የሚገኙ አነስተኛ መንደሮች ወደ ከተማነት የሚያድጉበትን ምቹ ዕድል ይፈጥራል። ነባሩ መንገድ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ እና ለመጓዝ ከ4 ሰዓት በላይ የሚወስድ ሲኾን፥ በቀጣይ ግንባታው ሲጠናቀቅ ከዋርዴር ከተማ ተነስቶ ቀብሪደሀር ከተማ ለመድረስ የሚፈጀውን ጊዜ ወደ 2 ሰዓት ያሳጥረዋል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የባሌ ጎባ -በርበሬ-ደሎመና የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 08 ፣ 2017 (ኢ መ አ):-  የባሌ ጎባ -በርበሬ-ደሎመና የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ አፈፃፀም ላይ የሚገኝ ሲሆን አሁናዊ አፈፃፀሙም  44.19 ኪሎ ሜትር (33.21%) ላይ ደርሷል ። መንገዱ የሚሠራው በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ሲሆን ጠቅላላ እርዝመቱ 133.09 ኪ.ሜ ነው ። የጎን ስፋቱ የእግረኛ መንገድን ጨምሮ በወረዳ 22.5ሜ ፣ በቀበሌ 17ሜ. ሲሆን በገጠር ደግሞ የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 10 ሜ. ነው ። የመንገድ ግንባታውን በማከናወን ላይ የሚገኘው አገር በቀሉ ዓለማየሁ ከተማ ኮንስትራክሽን ድርጅት ሲሆን የማማከርና ቁጥጥር ሥራው ደግሞ  ቤስት ኮንሰልቲን ኢንጂነርስ ኃ/የተ/የግ /ማህበር በማካሄድ ላይ ነው ። ለግንባታ የሚውለው 8,400,000,000.00 (ስምንት ቢሊዮን አራት መቶ ሚሊዮን ብር )  በኢትዮጵያ መንግሥት የተሸፈነ ነው ፡፡ በእስከአሁኑ አፈፃፀም ከፕሮጀክቱ አጠቃላይ 133 ኪሎ ሜትር ውስጥ44.19 ኪሎ ሜትር (33.21%) የጠረጋና የሙሌት ሥራዎች የተሠሩ ሲሆን ፣  4 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራም ተከናውኗል ። የዚህ ፕሮጀክት መጠናቀቅ በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን እንደ ስንዴ ፣ ገብስ ፣ጤፍ ፣ በቆሎ ፣ ለውዝ  ፣ ማር እና የተለያዩ ቅመማ ቅመሞችን በቀላሉ ለገበያ ተደራሽ ለማድረግ ያስችላል፡፡ በተጨማሪም የማህረሰቡን ማህበራዊ አገልግሎት ከማሳለጥ ባሻገር አካባቢው የባሌ ተራሮች መገኛ በመሆኑ የአካባቢውን የቱሪስት ፍሰት በመጨመር ረገድም አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል፡፡   ይህ ጎባ ከተማ ላይ ተጀምሮ ደሎ ከተማ ላይ የሚያበቃው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ከ አዲስ አበባ  450 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ነው ። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

መሀንዲሶች መንገድ ከመገንባት በዘለለ ለትውልድ የሚተላለፍ አሻራ ማኖር ይጠበቅባቸዋል - አቶ ዛዲግ አብርሃ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2017 (ኢ መ አ): መሀንዲሶች መንገድ ከመገንባት በዘለለ ለትውልድ የሚተላለፍ አሻራ ማኖር ይጠበቅባቸዋል ሲሉ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናግረዋል። ለኢ መ አ ከፍተኛ አመራሮች በትራንስፎርሜሽን ሊደርሺፕ ዙሪያ እየተሰጠ ያለው ተከታታይ ሥልጠና በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ውሏል። አቶ ዛዲግ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ መሀንዲሶች በሀገረ መንግስት እና በብሔረ መንግስት ግንባታ ቁልፍ ሚና እንዳላቸው ሊገነዘቡ ይገባል። ከዚህም ባለፈ መሀንዲሶች አድማሰ ሰፊ፣ በሥነ ምግባር የታነጹ፣ ከሕዝብ ዘንድ መልካም አመኔታን ያተረፉ እንዲሁም ከአካባቢ አስተሳሰብ ወጥተው በሀገር ደረጃ ማሰብ የሚችሉ መሆን ይገባቸዋል ብለዋል። መንገድ ከመገንባት ባሻገር መሀንዲሶች ለትውልድ ውርስ ሲሰሩ በሕዝብ ዘንድ የሚገባቸውን መልካም ሥም እና ሞገስ ያገኛሉ ብለዋል። የአንዲት ሀገር ዕድል ፈንታ ከሚወስኑት መካከል በመንገዶቿ ስፋት፣ በድልድዮቿ ጥንካሬ እንዲሁም በመሀንዲሶቿ ታታሪነት መኾኑንም አንስተዋል። የመንገድ ግንባታ የፍትህ፣ የፖሊሲ እና የማንነት ጉዳይ ነው ያሉት አቶ ዛዲግ፤ የመንገድ ግንባታዎች እንዲሁም ድልድዮች ብሔራዊ ትዕምርት ሊኾኑ ይገባል ብለዋል። ከዚህም ባሻገር በጥናት ላይ የተመሠረተ የመንገድ ስርአት እንዲኖር ማድረግ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተውበታል። ለማኅበረሰቡም ለዘለቄታው የሚጠቀምበት እና የሀገሪቱን የመንገድ ሀብት በአግባቡ መጠበቅ የሁሉም ሀላፊነት እንደሆነ አቶ ዛዲግ አብርሃ ጨምረው ተናግረዋል ። ለከፍተኛ አመራሮች እና ባለሞያዎች የሚሰጠው የአቅም ግንባታ ሥልጠና በተከታታይነት እየተሰጠ ይገኛል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

ለሀገራችን የመሠረተ ልማት ማንሰራራት በሥነ ምግባር የታነጹ እና በቴክኖሎጂ የታገዙ ማሀንዲሶች ሚና ወሳኝ ነው:- አቶ ዛዲግ አብርሃ አዲስ አባባ፣ ሐምሌ 13፣ 2017 (ኢ መ አ):- ለሀገራችን የመሠረተ ልማት ማንሰራራት በሥነ ምግባር የታነጹ እና በቴክኖሎጂ የታገዙ ማሀንዲሶች ሚና ወሳኝ መኾኑን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናግረዋል። አቶ ዛዲግ ' መንገድ እና የኢትዮጵያ ማንሰራራት' በሚል ርዕስ ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች እና ማሀንዲሶች ሥልጠና እየሰጡ ይገኛሉ። ፕሬዝዳንቱ በወቅቱ እንደገለጹት፤ መሀንዲሶች መንገድ የመሠረት ልማቶች ሁሉ አውራ መኾኑን በመገንዘብ ለሀገራዊ የመንገድ ፕሮግራም ስኬት መትጋት፣ የመንገድ ፕሮጀክቶች በተቀመጠላቸው የጥራት ደረጃ፣ የዋጋ መጠን እና የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ በማድረግ በኩል ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል። ለሀገራዊ ትልም መሳካት መሀንዲሶች ቁልፍ ሚና እንዳላቸው የገለጹት አቶ ዛዲግ፥ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ስንክሳሮችን የሚፈታ ድልድይ እየገነቡ መኾናቸውን መሀንዲሶች መረዳት ይኖርባቸዋል ብለዋል። መሀንዲሶች ሀገር ሲያቀኑ ህፃናት ወደ ትምህርት ቤት ይሄዳሉ፣ ምርት ለገበያ ይቀርባል፣ እናቶች ወደ ሆስፒታል ያመራሉ፣ ግንኙነት ይሳለጣል በድምሩ የብሄረ መንግስት እና የሀገረ መንግስት ግንባታ እውን እንደሚሆን አብራርተዋል። ለአራት ቀናት የሚቆየው ሥልጠናው፣ በሚቀጥሉት ቀናትም የሚካሄድ ይሆናል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

በናዳ ምክንያት ዝግ ኾኖ የቆየው የሳውላ - ላስካ - ሳላይሽ መንገድ ለትራፊክ አገልግሎት ክፍት ኾነ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2017 (ኢ መ አ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በናዳ ምክንያት ዝግ ኾኖ የቆየው የሳውላ - ላስካ - ሳላይሽ መንገድ ለትራፊክ አገልግሎት ክፍት ኾኗል። መንገዱ አካባቢው ላይ በጣለው ከባድ ዝናብ ተከትሎ በተከሰተ ናዳ ለ3 ቀናት ለትራፊክ አገልግሎት ዝግ ኾኖ ቆይቷል። አሁን ላይ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሶዶ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ባደረገው ከፍተኛ ርብርብ ጊዜያዊ የተለዋጭ መንገድ በመገንባት መንገዱን ዳግም ለትራፊክ እንቅስቃሴ ክፍት ማድረግ ተችሏል። በሌላ በኩል ዋናውን መንገድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከናዳ ነጻ ለማድረግ እና ለትራፊክ እንቅስቃሴ ክፍት ለማድረግ ዲስትሪክቱ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል። ጎን ለጎንም አካባቢው ለናዳ የተጋለጠ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ አስፈላጊውን የቅድመ-ጥንቃቄ ሥራዎችን በየጊዜው ያከናውናል። በዚህ አጋጣሚ አሽከርካሪዎች መንገዱ ክፍት እስኪኾን ድረስ ላሳዩት ትዕግስት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እያመሰገነ፣ ወቅቱ ክረምት እንደመኾኑ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ያሳስባል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የመንገድ መሠረተ ልማት ሁሉንም የሀገሪቱ አካባቢዎች በማስተሳሰር እና በማዋሀድ የብሔራዊ ኩራት ምንጭ ሊሆን ይገባል:- አቶ ዛዲግ አብርሃ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2017 (ኢ መ አ):- የመንገድ መሠረተ ልማት ሁሉንም የሀገሪቱ አካባቢዎች በማስተሳሰር እና በማዋሀድ የብሔራዊ ኩራት ምንጭ ሊሆን ይገባል ሲሉ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናገሩ። "መንገድ እና የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል ርዕስ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና መሥሪያ ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በሥልጠናው ላይ የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች፣ የመንገድ ጥገና ዲስትሪክት አመራር እና ባለሞያዎች ተሳታፊ ናቸው። ሥልጠናውን እየሰጡ የሚገኙት የአካዳሚው ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ፤ መንገድ ልብዙ ነገሮች ድልድይ ኾኖ ያስተሳስራል፤ የሀገራትን ዕድገትም ከመንገድ ውጪ ማሰብ አይቻልም ብለዋል። መንገድ የአንድ ሀገር ርዕይ ምልክት ነው፤ የሀገሪቷን መዳረሻ ለማወቅ የገነባቻቸውን መንገዶች መመልከት በቂ ነው ሲሉም ጨምረው ተናግረዋል። በመኾኑም አመራር እና ባለሞያዎች መንገድን ከመገንባት ባሻገር፤ መንገድ ስትራቴጂካዊ የአገር ግንባታ መሣሪያ መሆኑን እና በአንድ ሀገር ኢኮኖሚ፥ ማኅበራዊ፥ ፖለቲካዊ እንዲሁም አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ዘርፈ ብዙ ሚና የሚጫወት መሆኑን ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጥ አድርገው መገንባት ይኖርባቸዋል ብለዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር መሐመድ አብዱራህማን (ኢንጅነር)፤ ሥልጠናው ለተቋሙ ከፍተኛ አመራር እና ባለሞያዎች ከፍተኛ አቅም የሚፈጥር መኾኑን አስረድተዋል። ለአካዳሚው ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃም በወቅቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ሥልጠናው በመላው ሀገሪቱ ለሚገኙ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሙያዎች ለአራት ተከታታይ ቀናት በአካል እና በበይነ-መረብ እንደሚሰጥም ተመላክቷል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

"የአንድ ሀገር እስትንፋስ የመንገድ መሰረተ ልማት ነው" ዛዲግ አብርሃ አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 12 ቀን 2017 ዓ.ም (አፍሌክስ):- የአንድ ሀገር እስትንፋስ የመንገድ መሰረተ ልማት እንደሆነና መንገድ የተገለጠም ያልተገለጠም ኃይል እንዳለው የአፍሌክስ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናገሩ:: ፕሬዝዳንቱ ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ፣ የዲስትሪክት ዳይሬክተሮች እና ባለሙያዎች 'መንገድ እና የኢትዮጵያ ማንሰራራት' በሚል ርዕስ ላይ በሰጡት ስልጠና የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድ አብዱራህማን ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ፣ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከተጣበበ ጊዜያቸው ላይ ቀንሰው ለተቋማቸው አመራሮች ስልጠና ለመስጠት በመምጣታቸው አመስግነው፣ ስልጠናው በአዲሱ በጀት መጀመሪያ ላይ መሰጠቱ ለተቋሙ አመራር እና ባለሙያ ከፍተኛ አቅም እንደሚሆን ተናግረዋል:: ስልጠናው በመላው ሀገሪቱ ለሚገኙ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሙያዎች ለአራት ተከታታይ ቀናት በአካል እና በበይነ-መረብ እንደሚሰጥም ዋና ዳይሬክተሩ ጨምረው ገልጸዋል:: አቶ ዛዲግ መንገድ የአንድ ሀገር እስትንፋስ እና ለቀጣዩ ትውልድ የሚተላለፍ ቋሚ አሻራ ሊሆን የሚችልባቸውን አውዶች በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን ፣ መንገድ ብሔራዊ አንድነትን እያጠናከረ የመንግስትን ቅቡልነት የሚያረጋግጥ የአስተዳደር መሳሪያ እንደሆነ አብነቶችን ጠቅሰው አስረድተዋል:: 'የአንድ ሀገር ዜጎች ነን ብለን እንድናስብ ከሚያደርጉን አዕማዶች ውስጥ መንገድ አንዱ ነው' የሚሉት አቶ ዛዲግ ፣ የመንገድ መሰረተ ልማት የተዘነጉ እና የተረሱ አካባቢዎችን በማስተሳሰርና በማዋሀድ የብሔራዊ ኩራት ምንጭ እየሆነ እንደመጣና የጋራ ዕጣ-ፈንታን የሚያደምቅ የሚታይ ኃይል እንዳለው ተናግረዋል:: አንዳንድ መንገዶች ማንነትን የመገንባት ፣ ትውልድን የማስተሳሰርና ሰላምን የማስፈን ዕድልን እንደሚፈጥሩ ያስታወሱት አቶ ዛዲግ ፣ ሰዎች በሽማግሌ ብቻ ሳይሆን በመንገድም እርቅ እንደሚያወርዱ ከዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችና ከህይወት ልምዳቸው በመነሳት አካፍለዋል:: የስልጠናው ተሳታፊዎች ላነሷቸው ጥያቄዎች እና አስተያየቶች በቂ ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል:: ስልጠናው ለአራት ተከታታይ ቀናት በአካል እና በበይነ-መረብ እንደሚቀጥልም የተገኘው መረጃ ያመለክታል:: ምንጭ https://www.facebook.com/share/1BFqAj9kCz/

የአፍሌክስ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ስለ መንገድ መሰረተ ልማት ምን አሉ? ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ፣ የዲስትሪክት ዳይሬክተሮች እና ባለሙያዎች 'መንገድ እና የኢትዮጵያ ማንሰራራት' በሚል ርዕስ ላይ በሰጡት ስልጠና ስለ መንገድ መሰረተ ልማት ምን አሉ? 🛣️ መንገድ የአንድ ሀገር የደም ዝውውር እና እስትንፋስ ነው ፣ 🛣️ መንገድ የተገለጠም ያልተገለጠም ኃይል ያለው የአንድ ማህበረሰብ ትስስር ማሳያ ነው ፣ 🛣️ መንገድ ስትራቴጂያዊ የሆነ የሀገር የትራንስፎርሜሽን መሳሪያ ነው ፣ 🛣️ መንገድ ካርታ ላይ የተመሰረተ መስመር ብቻ አይደለም:: ይልቁንም የጋራ ማንነትን የሚበይን መሰረተ ልማት ነው ፣ 🛣️ መንገድ የአንድ ሀገር ርዕይ ምልክት ነው:: የሀገሪቷን መዳረሻ ለማወቅ የገነባቻቸውን መንገዶች መመልከት በቂ ነው ፣ 🛣️ መንገድ የሀገራት የኢኮኖሚ መወዳደሪያ ፣ የአቅም ማሳያ መለኪያ እየሆነ ነው ፣ 🛣️ መንገድ ለብዙ ነገሮች ድልድይ ሆኖ ያስተሳስራል:: የሀገራትን ዕድገት ከመንገድ ውጭ ማሰብ አይቻልም ፣ 🛣️ መንገድ ለአንዲት ሀገር ተስፋም ቃልኪዳንም ነው:: ፖሊሲ እና ኢኮኖሚን ያስማማል:: በመንገድ ላይ ያልተመሰረተ ኢኮኖሚ ፈራሽ ነው ፣ 🛣️ መንገድ እና ነፃነት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው:: መንገድ የሌለው ነፃነት የለውም ፣ 🛣️ መንገድ ማን ይምጣ ፣ ማን ይመለስ ፣ ማን ይቅር ፣ ማን በተወለደበት አርጅቶ ይሙት የሚለውን ይበይናል ፣ 🛣️ መንገድ የገበያ ተደራሽነትን ይጨምራል ፣ የትራንስፖርት ወጭን ይቀንሳል ፣ ኢንዱስትሪን ያስፋፋል ፣ የስራ ዕድልን ይፈጥራል ፣ 🛣️ መንገድ ብሔራዊ አንድነትን ያጠናክራል ፣ ቅቡልነት ያለው መንግስት እንዲኖር ያደርጋል ፣ 🛣️ መንገድ የተረጋጋ እና የዳበረ ዴሞክራሲ እንዲኖር ያደርጋል 🛣️ መንገድ ፍትሕ እንዲሳለጥ ፣ ማህበራዊ ችግሮች እንዲፈቱ ፣ አስተዳደራዊ ጉዳዮች እንዲሰምሩ ያደርጋል ፣ 🛣️ መንገድ የደህንነት እና የሰላም መሳሪያ ነው:: የድህረ ቀውስ መፍቻም ነው ፣ ምንጭ https://www.facebook.com/100064912051411/posts/1213789137461477/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v