en
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Open in Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 323 subscribers, ranking 1 756 in the Transport category and 2 541 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 323 subscribers.

According to the latest data from 16 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 90 over the last 30 days and by 8 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 40.85%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.40% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 439 views. Within the first day, a publication typically gains 2 050 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 17.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 17 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Transport category.

13 319
Subscribers
+824 hours
+217 days
+9030 days
Posts Archive
Notice Of Online Workshop Change! Friday, April 4/2025
Notice Of Online Workshop Change! Friday, April 4/2025

ኢድ ሙባረክ
ኢድ ሙባረክ

Registration Now Open for the 20th ILO Regional Conference!
Registration Now Open for the 20th ILO Regional Conference!

Online Workshop
Online Workshop

Call For Paper
Call For Paper

የጊንጪ - ካቺሴ - ጩሉጤ   የመንገድ  ሥራ ፕሮጀክት ምዕራፍ 1፡ ጊንጭ - ሽኩቴ (ኪ.ሜ 59)   የአስፋልት   ኮንክሪት   መንገድ  ግንባታ    72  በመቶ   ደረሰ አዲስ አበባ፣ መጋቢት  18  ቀን  2017   ዓ.ም (ኢ መ አ) በምዕራብ   ሸዋ   ዞን   ውስጥ   የሚገኙትን   የወረዳና   የቀበሌ  ከተሞችን   የሚያስተሳስረው  የጊንጪ - ካቺሴ - ጩሉጤ  የመንገድ ሥራ ፕሮጀክት  ምዕራፍ 1፡ ጊንጭ - ሽኩቴ (ኪ.ሜ 59)   የአስፋልት ኮንክሪት   መንገድ  ግንባታ  72   በመቶ   ደርሷል፡፡ በአሁናዊው  የፕሮጀክቱ   የግንባታ  እንቅስቃሴም  የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ስራ፣ የሰብቤዝ፣ ቤዝ ኮርስ ፣የስትራክቸር ስራ  እንዲሁም   48 ከ.ሜ  የሚሆን   የአስፋልት   ንጣፍ   ሥራ   እየተከናወነ   ይገኛል፡፡ 62.2  ኪሎ ሜትር   ርዝማኔ   የሚሸፍነው   ይኸው   መንገድ  በወረዳ 19  ሜትር ፣በከተማ  19  ሜትር፣በቀበሌ 14.2 ሜትር ፣ በገጠር  10 ሜትር  የጎን   ስፋት   እንዲኖረው   ተደርጎ   በመገንባት   ላይ   ነው፡፡ በመንገዱ    የግንባታ    ሂደት   የፀጥታ  እና  ያለመረጋጋት  ችግሮች አጋጥመው የነበረ ቢሆንም ኢመአ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ  አካላት  ጋር  ባደረገው ጥረቶች አሁን ላይ የመንገዱ  ግንባታ በእቅዱ መሰረት በመከናወን ላይ ነው። ይህንን  ግንባታ   እያካሄደ    የሚገኘው  ሀገር  በቀሉ የሥራ ተቋራጭ  ገምሹ  በየነ  ጠቅላላ  የሥራ  ተቋራጭ ሲሆን ፎርትረስ ኢንጂነሪንግ ኮንሰልታንትስና አሶሼትስ ሀ.የተ.የግ.ማህበር  የማማከርና  የቁጥጥሩን  ስራ  እያከናወነው  ይገኛል፡፡ ለፕሮጀክቱ   የሚውለው (898,273,177 ) ስምንት  መቶ  ዘጠና  ስምንት  ሚሊዮን  ሁለት  መቶ  ሰባ ሦስት  ሺህ  አንድ  መቶ  ሰባ  ሰባት  ብር   በኢትዮጵያ  መንግስት  የሚሸፈን ነው፡፡ መንገዱ  ቀድሞ  በጣም የተበላሸ  እና  ለትራንስፖርት  አመቺ ያልነበረ  መንገድ   ሲሆን   በአስፋልት  ኮንክሪት  ደረጃ  መገንባቱ  የአካባቢው  ህብረተሰብ  ምቹ የመንገድ   መሰረተ  ልማት  ተጠቃሚ  እንዲሆኑ  የሚያደርግ  ነው፡፡ የጊንጪ - ካቺሴ - ጩሉጤ  መንገድ  በስሩ   የሚገኙትን  ወረዳዎችን፣ ከተሞችን እና ቀበሌዎችን  በቅርበት   ከማገናኘት  ጎን  ለጎን  በአካባቢው  የሚመረቱ   የተለያዩ  የግብርና  ውጤቶች እና የቁም እንስሳት  ለገበያ  ለማውጣት የሚያግዝ ይሆናል ፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የአዲስ - ጊቤ ከባድ ጥገና ፕሮጀክት በተሻለ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2017 (ኢ መ አ):- የአዲስ አበባ - ጅማ ዋና መንገድ አካል የኾነው የአዲስ-ጊቤ አስፋልት መንገድ ከባድ ጥገና ፕሮጀክት በተሻለ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። መንገዱ ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት የሚያስተናግድ በመሆኑና በአገልግሎት ብዛት በመጎዳቱ ምክንያት ነው ከባድ ጥገና እየተደረገለት የሚገኘው። ከዚህም ባሻገር የወጪ ንግድም መተላለፊያ በመኾኑ የመስመሩን ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት በሚመጥን መልኩ መልሶ ግንባታ እየተደረገለት ነው። የከባድ ጥገና ፕሮጀክቱ ለግንባታ አመቺነት ሲባል በሁለት ክፍሎች ተከፋፍሎ እየተከናወነ ይገኛል። ለጥገናው በድምሩ 3 ቢሊዮን ብር የተመደበ ሲኾን፥ ሙሉ ወጪው በፌደራል መንግስት ይሸፈናል። በክፍል - 2 የአዲስ -ጊቤ ወንዝ የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክት 64 ኪሎሜትር የሚሸፍን ኾኖ፥ መነሻውን ሰበታ ከተማ ዲማ ላይ በማድረግ ቆራ ከተማ ድረስ ይዘልቃል። ከባድ ጥገናውን የሚያከናውነው ሀገር-በቀሉ ቤአኤካ ጠቅላላ ንግድ ሥራ አሁን ላይ ከአጠቃላይ ሥራው 46 በመቶውን ማጠናቀቁ ተመልክቷል። በ2018 ዓመት አጋማሽም ሥራውን ሙሉ በሙለ  ለማጠናቀቅ ግብ አስቀምጦ እየሠራ ይገኛል። የፕሮጀክቱ ክፍል - 3 መነሻውን ከቆራ ከተማ በማድረግ እስከ ጊቤ ወንዝ ድረስ እየተከናወነ የሚገኘ ሲኾን፥ 93 ኪሎሜትር ይሸፍናል። ሀገር-በቀሎቹ ቲክስ ኮንስትራክሽን እና ከኤም.ሲ.ጂ ኮንስትራክሽን በጋራ ይሠራሉ። የ9 ኪሎሜትር መልሶ ግንባታ እና የ15 ኪሎሜትር የአስፋልት ኦቨርሌይ ሥራዎች ተሠርቷል። በሁለቱም ፕሮጀክቶች በአሁኑ ወቅት በተጨማሪም የሰብቤዝ፣ ቤዝኮርስ፣ የፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦ እንዲሁም የተበላሹ ቦታዎችን ለይቶ የመቁረጥና በአስፋልት መልሶ የመጠገን ሥራዎች እንዲሁም የአስፋልት ድረባ ሥራ (Asphalt Overlay) በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ በሥራ ተቋራጮቹ የአቅም እና የግብዓት ውስንነቶች እንዲሁም አልፎ አልፎ የሚከሰቱ የፀጥታና ተያያዥ ችግሮች ለመቅረፍ የሚደረገው ጥረት በኢ መ አ በኩል ጥብቅ ክትትሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል። በአጠቃላይ ከባድ ጥገናው ሲጠናቀቅ በአዲስ አበባ-ወልቂጤ-ጅማ ኮሪደር ይስተዋል የነበረውን የትራፊክ እንቅስቃሴ መስተጓጎልና እንግልት ከመቅረፍም ባሻገር ከዚህ ቀደም ለትሽከርካሪ ዕቃ መለዋወጫ የሚወጣውን አላግባብ ወጪ እና የነዳጅ ብክነት ከማስቅረቱም ባለፈ የወጪ ንግዱን በከፍተኛ ኹኔታ ያሳልጣል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የሀሚድ ድልድይ ለትራፊክ አገልግሎት ክፍት ተደረገ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13፣ 2017 (ኢ መ አ):- የወልዲያ - ሮቢት መንገድ ክፍል የኾነው የሀሚድ ወንዝ የብረት ድልድይ ጥገናው መጠናቀቁን ተከትሎ ለትራፊክ አገልግሎት ክፍት ተደርጓል። ድልድዩ ከተፈቀደው ክብደት በላይ በጫነ ከባድ ተሽከርካሪ ጉዳት ደርሶበት እንደነበር ይታወቃል። በወቅቱ ተለዋጭ መንገድ በማዘጋጀት ተሽከርካሪዎች እንዲገለገሉ ማድረግ ተችሏል። የብረት ድልድዩን መልሶ ለመገንባትም በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት እንዲሁም የድልድይ እና ስትራክቸር ዳይሬክቶሬት ባደረጉት ከፍተኛ ርብርብ ድልድዩን በአጭር ጊዜ ውስጥ በመጠገን ለትራንስፖርት እንቅስቃሴ ክፍት ማድረግ ተችሏል። 45 ነጥብ 7 ሜትር ርዝመት ያለው ይኸው ድልድዩ አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ክፍት ተደርጎ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ድልድዩን በዘላቂነት በኮንክሪት ለመገንባት አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ሲኾን፣ በዚህ ዓመት መጨረሻ ግንባታው እንደሚጀመር ይጠበቃል። አሽከርካሪዎች በሕግ በተፈቀደው የጭነት ልክ በመጫን በባለቤትነት ስሜት እንዲገለገሉ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ያሳስባል።

የባቱ - አርሲነገሌ የፍጥነት መንገድ ግንባታ 84 ነጥብ 50 በመቶ ደረሰ የአዲስ አበባ-ሞያሌ-ናይሮቢ-ሞምባሳ የመንገድ ኮሪደር አካል የሆነው የሞጆ-ሐዋሳ ኮንትራት 3 ፡ ባቱ - አርሲነገሌ የፍጥነት መንገድ ግንባታ 84 ነጥብ 50 በመቶ ደርሷል፡፡ 57 ኪሎ ሜትር በሚረዝመው የመንገዱ ግንባታ የእስካሁን ሂደትም የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የውሃ መፋሰሻ ቦዮች (Side Ditches) ፣ የሰብ ቤዝ እና ቤዝ ኮርስ ፣ ሚዛን ጣቢያዎች እና ዞሮ መመለሻ መንገዶች ፣ የስትራክቸር ፣ የመኪና መሸጋገሪያ ፣ የእግረኛ/የእንስሳት መሸጋገሪያ ፣ የወንዝ ድልድዮች ፣ የመንገድ ዳር አጥር ፖሎች የማምረት ፣ የ Intelligent Transport System (ITS) ቱቦ ቀበራ ፣ የአስፋልት ማንጠፍ እንዲሁም በዋናው መንገድ እና አገናኝ መንገዶች ላይ ሌሎች የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። የመንገዱ የአስፋልት ንጣፍ ሥራ በሦስት ደረጃ እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን በእስካሁኑም የመጀመሪያው Dense Bituminous Macadam (DBM) ንጣፍ ስራ 53 ኪሎ ሜትር ፣ የሁለተኛው 52 ኪሎሜትር እንዲሁም የመጨረሻው ደግሞ 35 ኪሎሜትር የሚሆነው ስራ ተገባድዷል። የዚህ ፕሮጀክት ግንባታ ሙሉ በሙሉ ከከተማ ውጪ የሚያልፍ ሲሆን ከከተማዎች ጋር የሚያስተሳስሩ አገናኝ መንገዶች የሚሰሩለት ይሆናል። የፍጥነት መንገዱ በ90 ሜትር የመንገድ ወሰን ውስጥ የሚገኝ ሆኖ ያለው አጠቃላይ የጎን ስፋት 31.6 ሜትር ሲሆን የአገናኝ መንገዶቹ ደግሞ በገጠር 10 ሜትር እና በከተማ ደግሞ 22.5 ሜትር ስፋት ያላቸው ናቸው። መንገዱን ለመገንባት የሚውለው 4.689 (አራት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ብር ) የተሸፈነው በአለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ ነው፡፡ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ዓለም አቀፉ የስራ ተቋራጭ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ ነው፡፡ ኩንሃ ኢንጂነሪንግ እና ኮንሰልቲንግ ከኮሪያ ኤክስፕረስዌይ ኮርፖሬሽን ጋር በትብብር እንዲሁም ሀገር በቀሉ ንዑስ አማካሪ ኢትዮ ኢንፍራ ኢንጂነሪንግ ሃ.የተ.የግ.ኩባንያ የማማከሩንና የቁጥጥሩን ሥራ ያከናውናሉ፡፡ የአዲስ አበባ - ሞጆ - ሞያሌ - ላሙ - ሞምባሳ ትራንስ ኢንተርናሽናል ሀይዌይ አንድ አካል የሆነው ይኸው የመንገድ ኮሪደር -የባቱ ከተማ ፣ የአዳሚ ቱሉ እና አርሲ ነገሌ ወረዳዎች ብሎም ከ17 በላይ ቀበሌዎችን የሚያስተሳስር ነው:: በተጨማሪም በመስመሩ ላይ የሚገኙትን የእርሻና የኢንዱስትሪ እንዲሁም የቱሪስት መስህብ የሆኑ ቦታዎችን ለማገናኘት ያስችላል፡፡ ከዚህም ባሻገር የሞጆ-ሐዋሳ መንገድ 10,000 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የታላቁ የምስራቅ አፍሪካ ኮሪደር የደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ትራንስ አፍሪካን ሃይዌይ አካል በመሆኑ የአህጉራችንን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ትስስር በማጠናከር ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መንገድ ነው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads