ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
前往频道在 Telegram
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
显示更多📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览
频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 323 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 756,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 541 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 323 名订阅者。
根据 16 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 90,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 40.85%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.40% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 439 次浏览,首日通常累积 2 050 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 17 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
13 319
订阅者
+824 小时
+217 天
+9030 天
帖子存档
13 323
የጊንጪ - ካቺሴ - ጩሉጤ የመንገድ ሥራ ፕሮጀክት ምዕራፍ 1፡ ጊንጭ - ሽኩቴ (ኪ.ሜ 59) የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ 72 በመቶ ደረሰ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 18 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ መ አ) በምዕራብ ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኙትን የወረዳና የቀበሌ ከተሞችን የሚያስተሳስረው የጊንጪ - ካቺሴ - ጩሉጤ የመንገድ ሥራ ፕሮጀክት ምዕራፍ 1፡ ጊንጭ - ሽኩቴ (ኪ.ሜ 59) የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ 72 በመቶ ደርሷል፡፡
በአሁናዊው የፕሮጀክቱ የግንባታ እንቅስቃሴም የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ስራ፣ የሰብቤዝ፣ ቤዝ ኮርስ ፣የስትራክቸር ስራ እንዲሁም 48 ከ.ሜ የሚሆን የአስፋልት ንጣፍ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
62.2 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ የሚሸፍነው ይኸው መንገድ በወረዳ 19 ሜትር ፣በከተማ 19 ሜትር፣በቀበሌ 14.2 ሜትር ፣ በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ነው፡፡
በመንገዱ የግንባታ ሂደት የፀጥታ እና ያለመረጋጋት ችግሮች አጋጥመው የነበረ ቢሆንም ኢመአ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ባደረገው ጥረቶች አሁን ላይ የመንገዱ ግንባታ በእቅዱ መሰረት በመከናወን ላይ ነው።
ይህንን ግንባታ እያካሄደ የሚገኘው ሀገር በቀሉ የሥራ ተቋራጭ ገምሹ በየነ ጠቅላላ የሥራ ተቋራጭ ሲሆን ፎርትረስ ኢንጂነሪንግ ኮንሰልታንትስና አሶሼትስ ሀ.የተ.የግ.ማህበር የማማከርና የቁጥጥሩን ስራ እያከናወነው ይገኛል፡፡
ለፕሮጀክቱ የሚውለው (898,273,177 ) ስምንት መቶ ዘጠና ስምንት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰባ ሦስት ሺህ አንድ መቶ ሰባ ሰባት ብር በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡
መንገዱ ቀድሞ በጣም የተበላሸ እና ለትራንስፖርት አመቺ ያልነበረ መንገድ ሲሆን በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ መገንባቱ የአካባቢው ህብረተሰብ ምቹ የመንገድ መሰረተ ልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያደርግ ነው፡፡
የጊንጪ - ካቺሴ - ጩሉጤ መንገድ በስሩ የሚገኙትን ወረዳዎችን፣ ከተሞችን እና ቀበሌዎችን በቅርበት ከማገናኘት ጎን ለጎን በአካባቢው የሚመረቱ የተለያዩ የግብርና ውጤቶች እና የቁም እንስሳት ለገበያ ለማውጣት የሚያግዝ ይሆናል ፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 323
የአዲስ - ጊቤ ከባድ ጥገና ፕሮጀክት በተሻለ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2017 (ኢ መ አ):- የአዲስ አበባ - ጅማ ዋና መንገድ አካል የኾነው የአዲስ-ጊቤ አስፋልት መንገድ ከባድ ጥገና ፕሮጀክት በተሻለ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል።
መንገዱ ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት የሚያስተናግድ በመሆኑና በአገልግሎት ብዛት በመጎዳቱ ምክንያት ነው ከባድ ጥገና እየተደረገለት የሚገኘው። ከዚህም ባሻገር የወጪ ንግድም መተላለፊያ በመኾኑ የመስመሩን ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት በሚመጥን መልኩ መልሶ ግንባታ እየተደረገለት ነው።
የከባድ ጥገና ፕሮጀክቱ ለግንባታ አመቺነት ሲባል በሁለት ክፍሎች ተከፋፍሎ እየተከናወነ ይገኛል። ለጥገናው በድምሩ 3 ቢሊዮን ብር የተመደበ ሲኾን፥ ሙሉ ወጪው በፌደራል መንግስት ይሸፈናል።
በክፍል - 2 የአዲስ -ጊቤ ወንዝ የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክት 64 ኪሎሜትር የሚሸፍን ኾኖ፥ መነሻውን ሰበታ ከተማ ዲማ ላይ በማድረግ ቆራ ከተማ ድረስ ይዘልቃል።
ከባድ ጥገናውን የሚያከናውነው ሀገር-በቀሉ ቤአኤካ ጠቅላላ ንግድ ሥራ አሁን ላይ ከአጠቃላይ ሥራው 46 በመቶውን ማጠናቀቁ ተመልክቷል። በ2018 ዓመት አጋማሽም ሥራውን ሙሉ በሙለ ለማጠናቀቅ ግብ አስቀምጦ እየሠራ ይገኛል።
የፕሮጀክቱ ክፍል - 3 መነሻውን ከቆራ ከተማ በማድረግ እስከ ጊቤ ወንዝ ድረስ እየተከናወነ የሚገኘ ሲኾን፥ 93 ኪሎሜትር ይሸፍናል። ሀገር-በቀሎቹ ቲክስ ኮንስትራክሽን እና ከኤም.ሲ.ጂ ኮንስትራክሽን በጋራ ይሠራሉ። የ9 ኪሎሜትር መልሶ ግንባታ እና የ15 ኪሎሜትር የአስፋልት ኦቨርሌይ ሥራዎች ተሠርቷል።
በሁለቱም ፕሮጀክቶች በአሁኑ ወቅት በተጨማሪም የሰብቤዝ፣ ቤዝኮርስ፣ የፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦ እንዲሁም የተበላሹ ቦታዎችን ለይቶ የመቁረጥና በአስፋልት መልሶ የመጠገን ሥራዎች እንዲሁም የአስፋልት ድረባ ሥራ (Asphalt Overlay) በመከናወን ላይ ናቸው፡፡
በሥራ ተቋራጮቹ የአቅም እና የግብዓት ውስንነቶች እንዲሁም አልፎ አልፎ የሚከሰቱ የፀጥታና ተያያዥ ችግሮች ለመቅረፍ የሚደረገው ጥረት በኢ መ አ በኩል ጥብቅ ክትትሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
በአጠቃላይ ከባድ ጥገናው ሲጠናቀቅ በአዲስ አበባ-ወልቂጤ-ጅማ ኮሪደር ይስተዋል የነበረውን የትራፊክ እንቅስቃሴ መስተጓጎልና እንግልት ከመቅረፍም ባሻገር ከዚህ ቀደም ለትሽከርካሪ ዕቃ መለዋወጫ የሚወጣውን አላግባብ ወጪ እና የነዳጅ ብክነት ከማስቅረቱም ባለፈ የወጪ ንግዱን በከፍተኛ ኹኔታ ያሳልጣል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 323
የሀሚድ ድልድይ ለትራፊክ አገልግሎት ክፍት ተደረገ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13፣ 2017 (ኢ መ አ):- የወልዲያ - ሮቢት መንገድ ክፍል የኾነው የሀሚድ ወንዝ የብረት ድልድይ ጥገናው መጠናቀቁን ተከትሎ ለትራፊክ አገልግሎት ክፍት ተደርጓል።
ድልድዩ ከተፈቀደው ክብደት በላይ በጫነ ከባድ ተሽከርካሪ ጉዳት ደርሶበት እንደነበር ይታወቃል። በወቅቱ ተለዋጭ መንገድ በማዘጋጀት ተሽከርካሪዎች እንዲገለገሉ ማድረግ ተችሏል።
የብረት ድልድዩን መልሶ ለመገንባትም በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት እንዲሁም የድልድይ እና ስትራክቸር ዳይሬክቶሬት ባደረጉት ከፍተኛ ርብርብ ድልድዩን በአጭር ጊዜ ውስጥ በመጠገን ለትራንስፖርት እንቅስቃሴ ክፍት ማድረግ ተችሏል።
45 ነጥብ 7 ሜትር ርዝመት ያለው ይኸው ድልድዩ አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ክፍት ተደርጎ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
ድልድዩን በዘላቂነት በኮንክሪት ለመገንባት አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ሲኾን፣ በዚህ ዓመት መጨረሻ ግንባታው እንደሚጀመር ይጠበቃል።
አሽከርካሪዎች በሕግ በተፈቀደው የጭነት ልክ በመጫን በባለቤትነት ስሜት እንዲገለገሉ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ያሳስባል።
13 323
የባቱ - አርሲነገሌ የፍጥነት መንገድ ግንባታ 84 ነጥብ 50 በመቶ ደረሰ
የአዲስ አበባ-ሞያሌ-ናይሮቢ-ሞምባሳ የመንገድ ኮሪደር አካል የሆነው የሞጆ-ሐዋሳ ኮንትራት 3 ፡ ባቱ - አርሲነገሌ የፍጥነት መንገድ ግንባታ 84 ነጥብ 50 በመቶ ደርሷል፡፡
57 ኪሎ ሜትር በሚረዝመው የመንገዱ ግንባታ የእስካሁን ሂደትም የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የውሃ መፋሰሻ ቦዮች (Side Ditches) ፣ የሰብ ቤዝ እና ቤዝ ኮርስ ፣ ሚዛን ጣቢያዎች እና ዞሮ መመለሻ መንገዶች ፣ የስትራክቸር ፣ የመኪና መሸጋገሪያ ፣ የእግረኛ/የእንስሳት መሸጋገሪያ ፣ የወንዝ ድልድዮች ፣ የመንገድ ዳር አጥር ፖሎች የማምረት ፣ የ Intelligent Transport System (ITS) ቱቦ ቀበራ ፣ የአስፋልት ማንጠፍ እንዲሁም በዋናው መንገድ እና አገናኝ መንገዶች ላይ ሌሎች የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
የመንገዱ የአስፋልት ንጣፍ ሥራ በሦስት ደረጃ እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን በእስካሁኑም የመጀመሪያው Dense Bituminous Macadam (DBM) ንጣፍ ስራ 53 ኪሎ ሜትር ፣ የሁለተኛው 52 ኪሎሜትር እንዲሁም የመጨረሻው ደግሞ 35 ኪሎሜትር የሚሆነው ስራ ተገባድዷል።
የዚህ ፕሮጀክት ግንባታ ሙሉ በሙሉ ከከተማ ውጪ የሚያልፍ ሲሆን ከከተማዎች ጋር የሚያስተሳስሩ አገናኝ መንገዶች የሚሰሩለት ይሆናል።
የፍጥነት መንገዱ በ90 ሜትር የመንገድ ወሰን ውስጥ የሚገኝ ሆኖ ያለው አጠቃላይ የጎን ስፋት 31.6 ሜትር ሲሆን የአገናኝ መንገዶቹ ደግሞ በገጠር 10 ሜትር እና በከተማ ደግሞ 22.5 ሜትር ስፋት ያላቸው ናቸው።
መንገዱን ለመገንባት የሚውለው 4.689 (አራት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ብር ) የተሸፈነው በአለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ ነው፡፡ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ዓለም አቀፉ የስራ ተቋራጭ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ ነው፡፡
ኩንሃ ኢንጂነሪንግ እና ኮንሰልቲንግ ከኮሪያ ኤክስፕረስዌይ ኮርፖሬሽን ጋር በትብብር እንዲሁም ሀገር በቀሉ ንዑስ አማካሪ ኢትዮ ኢንፍራ ኢንጂነሪንግ ሃ.የተ.የግ.ኩባንያ የማማከሩንና የቁጥጥሩን ሥራ ያከናውናሉ፡፡
የአዲስ አበባ - ሞጆ - ሞያሌ - ላሙ - ሞምባሳ ትራንስ ኢንተርናሽናል ሀይዌይ አንድ አካል የሆነው ይኸው የመንገድ ኮሪደር -የባቱ ከተማ ፣ የአዳሚ ቱሉ እና አርሲ ነገሌ ወረዳዎች ብሎም ከ17 በላይ ቀበሌዎችን የሚያስተሳስር ነው:: በተጨማሪም በመስመሩ ላይ የሚገኙትን የእርሻና የኢንዱስትሪ እንዲሁም የቱሪስት መስህብ የሆኑ ቦታዎችን ለማገናኘት ያስችላል፡፡
ከዚህም ባሻገር የሞጆ-ሐዋሳ መንገድ 10,000 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የታላቁ የምስራቅ አፍሪካ ኮሪደር የደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ትራንስ አፍሪካን ሃይዌይ አካል በመሆኑ የአህጉራችንን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ትስስር በማጠናከር ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መንገድ ነው፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
