en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 692 subscribers, ranking 8 036 in the Technologies & Applications category and 2 171 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 692 subscribers.

According to the latest data from 03 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 143 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 27.84%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.00% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 369 views. Within the first day, a publication typically gains 2 511 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 692
Subscribers
-124 hours
+47 days
+14330 days
Posts Archive
በተቋሙ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የሚተገበሩ ፕሮጀክቶች ይፋ ሆኑ ……////…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግሪድ ማዘመን፣ የዲጂታላዜሽን፣ ታዳሽ ኃይልን የማመንጨት እና የአቅም ግንባታ ሥራዎችን ለማከናወን የሚያስችል የአምስት ዓመት ፕሮጀክት ይፋ ሆነ፡፡  በፕሮጀክቶቹ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር  ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢ/ር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ተቋሙ ለሚተገብራቸው ፕሮጀክቶች የአውሮፓ ህብረትን ጨምሮ ሌሎች አበዳሪ ተቋማት ለሰጡት ትኩረት እና ላሳዩት ፈጣን ምላሽ ምስጋና ሊቸራቸው ይገባል። በፕሮጀክቱ ታዳሽ የሆነና የካርበን ልቀትን ለመቀነስ የሚያስችሉ የኃይል አማራጮች ማልማት እና በተቋሙ ውስጥ ባሉ ሁሉም የቢዝነስ ዘርፎች ዲጂታላይዝድ የሆኑ አሰራሮችን መተግበር እንደሚያካትት አስታውቀዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ተጠሪና የትብብር ኃላፊ ሚስተር ሮቤርቶ ሽሊሮ  በበኩላቸው ኢትዮጵያ የውሃ ኃይል ማመንጫ መሰረተ ልማት በመገንባት ብትታወቅም ያልተነኩ የፀሐይ፣ የንፋስ እና የጅኦተርማል እምቅ ሀብቶች ባለቤት እንደሆነች መገንዘባቸውን አንስተዋል፡፡ ስለሆነም ህብረቱ ከሌሎች አጋሮች ጋር በመሆን የተቋሙን የልማት ሥራዎች ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ፕሮግራም 3 ዳይሬክተርና የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ በበኩላቸው ፕሮጀክቶቹ ተቋሙን ወደ ተሻለ ቁመና ለማድረስ ታስበው የተቀረፁ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ በተቋሙ በአምስት ዓመት የሚተገበሩት ፕሮጀክቶች በአራት ዘርፎች ማለትም የግሪድ ማዘመንና ዕድሳት፣ ዲጅታላዜሽን፣ ታዳሽ ኃይል ልማት እና የአቅም ግንባታ ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆኑንም ነው የገለፁት፡፡  ፕሮጀክቶቹን ለማስፈፀም 270 ሚሊዮን ዩሮ  እንደሚፈልግ የጠቀሱት ሥራ አስኪያጇ የፋይናንስ ምንጩ የፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እና የፈረንሳይ ግምጃ ቤት መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በአምስት ዓመት የሚጠናቀቀው ይህ ፕሮጀክት 22 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ሙሉ በሙሉ የማዘመን ሥራ፣ አዲስ የመቆጣጠሪያ ማዕከል/NlDC/ ግንባታ፣ የትራንስፎርመር ወርክ ሾፕ እድሳት፣ የ1 ሺህ 590 ኪሎ ሜትር የኦፕቲካል ፋይበር መስመር ዝርጋታ እና ደረጃውን የጠበቀ የሥልጠና ማዕከል ግንባታ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ሥራ አስኪያጇ አብራርተዋል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት የተጎዱ የአሸጎዳ የንፋስ ተርባይኖችን በመጠገን ወደ ኦፕሬሽን ለመመለስ መታቀዱንም አመልክተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የዕውቀት ሽግግር ለማድረግ የሚያስችል አውደ ጥናት ተካሄደ ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር የዕውቀት ሽግግር እንዲኖር ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ፡፡ ተቋሙ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣  ኬቲኤች እና ቻልመርስ  ከተሰኙ የሲዊዲን ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር የአንድ ቀን አውደጥናት አዘጋጅቷል። አውደጥናቱ "የውሃ ኃይል ማመንጫዎችና የኦፕሬሽን ዕቅድ ለኢትዮጵያ እንዲሁም ለኢትዮጵያ የኃይል ልማት ዘርፍ አማራጭ መንገዶችና የረዥም ጊዜ ሞዴልና ትንታኔ" በሚሉ ርዕሶች በተዘጋጁ ጥናታዊ ጽሑፎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢትዮ ፓዎር አካዳሚ ተወካይ ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) በአውደ ጥናቱ ላይ እንደተናገሩት ተቋሙ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር ለተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች የዕውቀት ሽግግር እንዲኖር ለማድረግ እየሰራ ይገኛል፡፡ ቀደም ሲል አካዳሚው በስልጠናዎች ላይ ብቻ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር ወንድወሰን ከለውጡ በኋላ ከስልጠናዎች በተጨማሪ ከተቋሙ ሥራ ጋር በተያያዘ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተሠሩ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሑፎችን ወደ ተቋሙ በማምጣት አውደ ጥናቶችን ለማካሄድ አቅዶ እየተሰራ ስለመሆኑም አስታውቀዋል። አውደ ጥናቱ ለሠራተኞች የዕውቀት ሽግግር ለማድረግ ከማገዙም ባለፈ የተቋሙን አሰራሮች ለመፈተሸ የሚስችል ዕድል እንደሚፈጥርም ዶ/ር ወንድወሰን አመልክተዋል። "የውሃ ኃይል ማመንጫዎችና የኦፕሬሽን ዕቅድ ለኢትዮጵያ " በሚል ርዕሰ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት በኢንኮድ ኢንጂነሪንግ ሶሉሽን ኃ/የተ/ ኩባንያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ፍሬሕይወት ግርማ (ዶ/ር) ጥናቱ ወደ ኃይል ማመንጫ ግድቦች የገባውን ውሃ  እንዴት በአግባቡ መጠቀም እንደሚቻል እና በጣቢያዎች የኦፕሬሽን ሥራ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል፡፡ በዚህም የማመንጫ ግድቦችን ውሃ በአግባቡ ለመጠቀም የረጅም ጊዜ  የኦፕሬሽን ሥራ ዕቅድ ሞዴል በመቅረፅ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኬቲኤች ከተሰኘ የሲዊድን ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያካሄደው ጥናት አምስት ዓመታትን የፈጀ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እየተደረገበት ይገኛል። "ለኢትዮጵያ የኃይል ልማት ዘርፍ አማራጭ መንገዶችና የረዥም ጊዜ ሞዴልና ትንታኔ" በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ረዳት ፕሮፌሰር ዳዊት ሀብቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው ጥናቱ በቀጣይ በኢትዮጵያ ሊኖር የሚችለውን የኃይል አቅርቦትና ፍላጎት እንዲሁም የኢነርጂ ልማት ዘርፉ ዕድገት መልካም አጋጣሚዎችና ተግዳሮቶችን ማሳየቱን ተናግረዋል። ይህም ፖሊሲ አውጭዎች እና በዘርፉ የተሰማሩ ተቋማት ይህን ታሳቢ ያደረገ ሥራ እንዲያከናውኑ ግብዓት እንደሚሆን አመልክተዋል። ለአራት ዓመታት ያህል የተካሄደውን ይህን ጥናት የሲዊዲኑ ቻልመርስ ዩኒቨርሲቲ እና  የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በትብብር መደገፋቸውን ጠቅሰዋል። በአውደ ጥናቱ ላይ የተሳተፉ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች በበኩላቸው አውደ ጥናቱ በተቋሙ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በጥናት ላይ ተመስርቶ የመፍትሔ እርምጃዎችን ለመውሰድ እንደሚያስችል ጠቁመው መሠል ፕሮግራሞች በቀጣይ ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል። በአውደ ጥናቱ ላይ ከጀነሬሽን፣ ከትራንስሚሽን፣ ከኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፎች እንዲሁም ከኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ የተውጣጡ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ተሳትፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

ጣቢያው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ5 ሺ 430 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል ……..///……… የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከዕቅዱ በላይ ኃይል ማምረቱን የጣቢያው የኦፕሬሽን ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ደጀኔ ጉታ እንዳስታወቁት ማመንጫ ጣቢያው በ2017 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት 4 ሺ 725 ነጥብ 56 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማመንጨት አቅዶ 5 ሺ 436 ነጥብ 5  ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማምረት ችሏል፡፡ ይህም ከዕቅዱ የ710 ነጥብ 94 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ15 ነጥብ 04 በመቶ እንዲሁም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ189 ነጥብ 65 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ3 ነጥብ 61 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን አቶ ደጀኔ ተናግረዋል፡፡ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማምረት የሚያስችሉ የፍተሻና የክትትል ሥራዎች በየጊዜው መከናወናቸው፣ የኦፕሬሽን ሥራው የተቋሙ ሥራ አመራር ባፀደቀው የኦፕሬሽን ሥራዎች የአሰራር ስርዓት ማኑዋል መሰረት መከናወኑ እና የኃይል መቋረጥ አመላካቾችና ችግሮች (alarms and faults) ሲስተዋሉ ወዲያውኑ እንዲወገዱ መደረጋቸው ጣቢያው ከዕቅዱ በላይ ለማመንጨቱ ምክንያቶች እንደሆኑ ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ መጨረሻ 6 ሺ 141 ነጥብ 49 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን ያስታወሱት አቶ ደጀኔ ባለፉት ዘጠኝ ወራትም ከአጠቃላይ ዕቅዱ የ88 ነጥብ 52 በመቶ አፈጻፀም ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል፡፡ ይህም በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት አመላካች እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡                                                                                                                የጊቤ 3 ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በ18 ማመንጫ ጣቢያዎች ከተመረተው የ21 ሺ 299 ነጥብ 69 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ የ25 ነጥብ 5 በመቶ ድርሻ በመያዝ የታላቁ ህዳሴ ግድበን ተከትሎ በሁለተኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን ከኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የተገኘው መረጃ ያመለክታል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

በፕሮጀክቱ አካባቢ የተራቆቱ ቦታዎችን ወደነበሩበት የመመለስ ሥራ እየተከናወነ ነው ……..///……… በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ የተራቆቱ ቦታዎችን ቀድሞ ወደነበሩበት ተፈጥሯዊ ይዞታ የመመለስ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን በፕሮጀክቱ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዕቅድ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ እንዳስታወቁት ፕሮጀክቱ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳይ ሥራዎችን በአካባቢያዊና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት ምክረ ሃሳብ እና በሳይት የመልሶ ማልማት የአሰራር ሥርዓትና ዕቅድ መሰረት እያከናወነ ነው፡፡ በዚህም ለፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ግብዓት የተቆፈሩ እና ተረፈ ምርቶች ተጠራቅመውባቸው የነበሩ የተለያዩ ቦታዎችን በጥናቱና በአሰራር ስርዓቱ መሰረት ወደ ተፈጥሯዊ ይዞታቸው የመመለስ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ አቶ ግዛቸው እንዳሉት ፕሮጀክቱ ራሱን የቻለ የሥራ ቡድን እና የችግኝ ጣቢያ አቋቁሞ ከግንባታ ሥራው ጎን ለጎን የመልሶ ማልማት ሥራውን የዕለት ተዕለት ተግባራት አድርጎ እየሰራ ይገኛል፡፡ ሥራው ለአካባቢው መልክዓምድር እና ለአየር ንብረቱ ተስማሚ የሆኑ ሀገር በቀል ችግኞችን እና የአፈር መከላትን መከላከል እንደሚያስችል በሳይንሳዊ ዘዴ የተረጋገጠ "ቪቲባር" የተሰኘ ሳርን በመትከል እየተከናወነ ስለመሆኑም አስረድተዋል፡፡ የተለያዩ ማሽነሪዎችና ወርክ ሾፖች የተተከሉበት ቦታን ጨምሮ በፕሮጀክቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ሌሎች ቀሪ ቦታዎችን ወደ ነበሩበት የመመለሱ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቶ ግዛቸው አረጋግጠዋል፡፡ ፕሮጀክቱ የአካባቢ ጥበቃ ሥራን ለማጠናከር በሀገሪቱ በየዓመቱ እየተካሄደ ባለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ በንቃት በመሳተፍ እና በጣቢያው ላይ የሚያለማቸውን ችግኞችና ሳሮችን ለአካባቢው አርሶ አደሮች እና መስተዳደሮች በማቅረብ አሻራዉን እያሳረፈ እንደሚገኝ ሥራ አስኪያጁ ጠቅሰዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በአካባቢው ያለውን የመሰረት ልማት እጥረት ለመቅረፍ በመንገድ፣ በመጠጥ ውሃ፣ በትምህርት፣ በጤና እና በሌሎች ዘርፎች ላይ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ የማህበራዊ  ኃላፊነት ሥራዎችን ማከናወኑን አቶ ግዛቸው አስረድተዋል፡፡ በፕሮጀክቱ ሥራ ተቋራጭ ዊቢውልድ ኩባንያ ኢንቫይሮመንታል ኢንጅነር የሆኑት አቶ ይኸነው ቸኮል በበኩላቸው እየተከናወነ ካለው የሳይት መልሶ ማልማት ሥራ በተጨማሪ አካባቢውን ከከባቢ አየር ብክለት ለመጠበቅ በቆሻሻና ተረፈ ምርት አወጋገድ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ፕሮጀክቱ አካባቢውን ከብክለት ለመጠበቅ የሚያስችሉ የተለያዩ የአሰራር ስርዓቶችን ተግባራዊ ማድረጉንም ተናግረዋል፡፡ በዚህም ከተሸከርካሪና ማሽነሪዎች እጥበትና የሰርቪስ አገልግሎት የሚለቀቁ ዘይቶችና ዘይት ነክ ኬሚካሎች አካባቢውን እንዳይበክሉ ውሃውን ከዘይት የሚለይና የሚያጣራ ማሽን በመጠቀም ውሃው መልሶ ጥቅም ላይ የሚውልበት አሰራር መዘርጋቱን አስረድተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የኮንክሪት ሙሌት በሚከናወንበት ጊዜ የሚፈጠሩ የተረፈ ምርት ቆሻሻዎች አካባቢን የሚበክሉ መሆኑናቸውንና አለመሆናቸውን ናሙና በመውሰድ እንደሚረጋገጥና ጉዳት የሚያደርስ ከሆነም በሳይንሳዊ ዘዴ ተጣርቶ እንደሚለቀቅ ነው የጠቆሙት፡፡ የመልሶ ማልማት ሥራው የአካባቢውን ሥነ ምህዳር ለመጠበቅ እና  በቀጣይ ሰው ሰራሽ ሀይቁ በደለል እንዳይሞላ በማድረግ ግድቡ የሚጠበቅበትን አገልግሎት በአግባቡ እንዲሰጥ ለማድረግ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 15 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ሪጅኑ የኮንዳክተር ገመድ የመቀየር ሥራ እያከናወነ ነው .......///……... በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር ሳቢያ ጉዳት የደረሰበትን የአላማጣ - አሸጎዳ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በአዲስ ኮንዳክተር የመቀየር ሥራ እያከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ህንፃ አረጋዊ እንዳስታወቁት የኮንዳክር ገመድ የመቀየር ሥራው ከ40 በመቶ በላይ ተከናውኗል። የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ በአካባቢው በነበረው የፀጥታ ችግር በመጎዳቱ ምክንያት የኃይል መቆራረጥ በተደጋጋሚ ይከሰት እንደነበር የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ በግሪድ ኔትወርኩ ላይም አሉታዊ ጫና ሲያሳድር መቆየቱን ጠቅሰዋል። ከአላማጣ - አሸጎዳ የተዘረጋው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር 126 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ቢሆንም ከዚህ ውስጥ በአዲስ የኮንዳክተር ገመድ ለመቀየር የታሰበው 30 በመቶውን ብቻ መሆኑን ነው የተናገሩት። መስመሩን ለመቀየር የሚያስፈልጉ 38 ድራም የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ እና የሚዘረጋውን የኮንዳክተር ገመድ የሚያገናኙ 100 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ማገናኛዎች (Mid Span Joint) መረከባቸውን አቶ ህንፃ ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት በአዲስ መልክ የኮንዳክተር ዝርጋታ መከናወን ካለበት 37 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር ውስጥ 15 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር መጠናቀቁንም ነው ሥራ አስኪያጁ የጠቆሙት። እንደ አቶ ህንፃ ገለፃ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሶሶዎቹ የተዘረጉበት አካባቢ በረሃማና የመልክዓ ምድሩ አቀማመጥ አስቸጋሪ መሆን፣ ስርቆት እና የነዳጅ አቅርቦት ችግሮች የኮንዳክተር ገመድ ቆየራ ሥራውን ፈታኝ አድርገውታል። የኮንዳክተር ሽቦ እና የኦ.ፒ.ጂ. ደብሊው ፋይበር መስመር ዝርጋታው ሲጠናቀቅ ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች መረጃዎችን ማግኘት ስለሚቻል በፍጥነት የጥገና ሥራዎችን ለማከናወን ሚናው የጓላ እንደሆነም ነው የተናገሩት። የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ ቅየራ ሥራው በሪጅኑ አቅም እንዲከናወን በመወሰኑ ከፍተኛ ወጪ ማዳን ተችሏል ያሉት አቶ ህንፃ የዝርጋታ ሥራው እንዲሰራ ዕድሉን ላመቻቹ በየደረጃው ለሚገኙ የተቋሙ የሥራ አመራሮች ምስጋናቸውንም አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

#የፈተናጥሪ የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-4ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወሳል፡፡ በዚሁ
+2
#የፈተናጥሪ የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-4ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሰረት ከላይ ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ሚያዚያ 17 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 7፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የመሰብሰብያ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

የጂ አይ ኤስ ብሬከሮች ቅየራ ከኃይል አቅርቦት ጋር ተያይዞ የሚነሱ ቅሬታዎችን ይፈታል ………///………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እያከናወነ ያለው የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የማዘመን ሥራ የጣቢያዎቹን አሰራር በማዘመን በደንበኞች የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት እንደሚያግዝ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ፡፡ በአገልግሎቱ የሻሸመኔ ሪጅን የቴክኒክ ክፍል ኃላፊ አቶ ጅብሪል ሩቤ እንደገለፁት የጂ አይ ኤስ መቆጣጠሪያ ቅየራ መከናወኑ የጣቢያቹን አቅም በማሳደግ ለህብረተሰቡ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል፡፡ በሻሸመኔ ማከፋፈያ ጣቢያ የ33 ኪሎ ቮልት መቆጣጠሪያ ከዚህ በፊት ተቀይሮ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ያስታወሱት አቶ ጅብሪል በአሁኑ ወቅት ደግሞ የ15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመር መቆጣጠሪያዎችን ወደ ጂ አይ ኤስ መቆጣጠሪያ የመቀየር ሥራ እየተከናወን ይገኛል ብለዋል፡፡ በአገልግሎቱ የሲዳማ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ አበበ እድሉ በበኩላቸው የማከፋፈያ ጣቢያ መቆጣጠሪያዎች የአገልግሎት ጊዜ እና የሚሰሩበት ዘዴ በማከፋፈያ ጣቢያዎች ለሚፈጠሩ የኃይል መቆራረጦች አንድ ምክንያት እንደሚጠቀሱ ገልፀዋል፡፡ በሪጅኑ ከሚገኙ አራት ማከፋፈያ ጣቢያዎች መካከል በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በይርጋለም አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ መቆጣጠሪያዎችን በዘመናዊ ዕቃዎች የመቀየር ሥራ ስለመጀመሩ ተናግረዋል፡፡ ቀደም ሲል በአንድ ወጪ መስመር ተደርበው ኃይል ሲያገኙ የነበሩ ከተሞችና አካባቢዎች አሁን በተጀመረው የመቆጣጠሪያ መሳሪያ ቅየራ ሥራ ለየብቻቸው የሚወጡበትን ዕድል እንደሚፈጥርም አቶ አበበ ተናግረዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ የብሬከር ቅየራው ከኃይል አቅርቦት ጋር በተያያዘ ከደንበኞች ሲነሱ የነበሩ ቅሬታዎችን ለመፍታት እና በኃይል መቆራረጥ ምክንያት ሁለቱ ተቋማት ሲያጡት የነበረውን ገቢ በማስተካከል በኩል ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡ የሥራ ኃላፊዎቹ እንደገለፁት ሁለቱ ተቋማት ለህብረተሰቡ ያልተቆራረጠ ኃይል ለማቅረብ በቅንጅት እየሰሩ ናቸው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የትንሳዔ በዓል ያለምንም የኃይል እጥረት ተከብሯል ……....///…….... ትላንት በተከበረው የትንሳዔ በዓል እና በዋዜማው ምንም ዓይነት የኃይል እጥረት አለማጋጠሙን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ፡፡ በማዕከሉ የሪል ታይም ኦፕሬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ጉልላት እንግዳ እንደገለፁት ከበዓሉ ዋዜማ አንስቶ በበዓሉ ዕለት የኃይል እጥረት እና መቋረጥ እንዳያጋጥም ከኃይል ማመንጫ እስከ ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት ተደርጎ የተለያዩ ሥራዎች ሲከናወኑ ነበር። ለበዓሉ ለመጠባበቂያ ከተያዘው ኃይል ውጪ ከ4 ሺህ ስምንት መቶ ሜጋ ዋት በላይ ኃይል ለማቅረብ ዝግጅት ቢደረግም በዋዜማው 4 ሺ 624 ሜጋ ዋት እንዲሁም በበዓሉ ዕለት 3 ሺ 856 ሜጋ ዋት ኃይል ከፍተኛ የኃይል ጭነት መመዝገቡን ገልፀዋል፡፡ የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ለሆኑት የዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎች፣ ትላልቅ ኢንዱስትሪዎች እና ለኤክስፖርት የሚቀርበው ኃይል ሳይቋረጥ ዝግጁ ከተደረገው ኃይል ውስጥ በዋዜማው176 ሜጋ ዋት እንዲሁም በበዓሉ ዕለት 944 ሜጋ ዋት ትርፍ ኃይል እንደነበር አቶ ጉልላት አስረድተዋል። ተቋሙ ያለምንም ችግር የሚፈለገውን ኃይል ማቅረብ መቻሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ አስተማማኝ ኃይል የማቅረብ አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ እያሳደገ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ። በዓሉ የሠላም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ። ኢንጂነር አሸ
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ። በዓሉ የሠላም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ  እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ። ኢንጂነር አሸብር ባልቻ፣ ዋና ሥራ አስፈፃሚ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

ለትንሳዔ በዓል በቂ ያኃይል አቅርቦት እንዲኖር ዝግጅት ተደርጓል ..........///............ ለትንሳኤ በዓል የኃይል አቅርቦት ችግር እንዳያጋጥም በቂ ዝግጅት መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግሪድ ሲስተም ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሚኪያስ ወንድሙ እንዳስታወቁት በዋዜማውና በበዓሉ ዕለት በመላው ሀገሪቱ የሚኖረው የኃይል ፍላጎት 4 ሺህ 800 ሜጋ ዋት ሊደርስ እንደሚችል  ተተንብይዋል፡፡ በመሆነም ይህን ታሳቢ ያደረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መሰራታቸውን እና ሊመጣ የሚችል ተጨማሪ የኃይል ፍላጎትን ለማስተናገድ 400 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለመጠባበቂያነት ዝግጁ መደረጉን ገልፀዋል፡፡ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለኃይል መቋረጥ ምክንያት እንዳይሆኑ የቅድመ መከላከልና የፍተሻ ሥራዎች መከናወኑንም ጠቁመዋል፡፡ ከፍተኛ ጭነት በሚበዛባቸው ሰዓታት በመካከለኛና ዝቅተኛ መስመሮች ላይ ጫና እንዳይፈጠር የኃይል አጠቃቀምን ማስተካከል እንደሚገባ አቶ ሚኪያስ አሳስበዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ ለበዓሉ በቂ ኃይል ዝግጁ በመደረጉ ከተቋሙ በቀጥታ ኃይል የሚያገኙ የዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎች፣ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚዎች እና ኤክስፖርት ላይ ከወትሮ የተለየ አጠቃቀም አይኖርም። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የቀጣይ መቶ ቀናት ዕቅዶቻችንን በሙሉ ልብና ፍላጎት ተረባርበን እናሳካለን ---///--- የቀጣይ መቶ ቀናት ዕቅዳችንን በሙሉ ልብ ተረባርበን በመሥራት ለስኬት እናበቃለን ሲሉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምሥራቅ አንድ ሪጅን አመራሮችና ሠራተኞች ተናገሩ። ሪጅኑ በስሩ የሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞችን ያሳተፈ የ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የመጨረሻ ሩብ ዓመት የመቶ ቀናት ዕቅድ ላይ በድሬድዋ ከተማ ውይይት አካሂዷል፡፡ የምሥራቅ ሪጅን አንድ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሐመድ በመድረኩ ላይ እንደተናገሩት ለውይይት የቀረበውን የመቶ ቀናት ዕቅድ ተፈፃሚ በማድረግ በየደረጃው ያሉ ሁሉም  የሪጅኑ ሠራተኞችና ኃላፊዎች በንቃትና በመሉ የኃላፊነት ስሜት እንዲሁም ቁርጠኝነት በርብርብ እንዲፈፀም አሳስበዋል። በሪጅኑ የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን የሰው ኃይል አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ኃላፊ ወ/ሮ ኤልሳቤት ዳባ በበኩላቸው ለተሰብሳቢዎች ባስተላለፉት መልዕክት  ሁሉም የሰብስቴሽን እና የትራንስሚሽን ኃላፊዎች ዕቅዱን ለማሳካት የሚያስችላቸውን የድርጊት መርኃ ግብር አዘጋጅተው በንቃት እንዲተገብሩ ጠቁመዋል። ዕቅዱ ተዘጋጅቶ መቅረቡ ይበል የሚያሰኝ መሆኑን የገለፁት የመድረኩ ተሳታፊዎች በቀረበው ሰነድ ላይ በቂ ውይይት መደረጉ የጋራ መግባባት ላይ ለመድረስ አስችሏል። ይህም በዘርፉ የተናበበ ዕቅድና የጋራ አፈፃፀም እንዲኖር የሚግዝ መሆኑን አብራርተዋል።  ተሳታፊዎቹ አክለውም የቀረበለቸውን ዕቅድ ለመፈፀምና ከግብ ለማድረስ መሟላት ያለበትን የመስሪያ ቁስና ሠው ኃይል ግብዓቶችን በዝርዝር በመወያየት ለቀጣይ አፈፃፀም ተግተው እንደሚሠሩ የጋራ አቋማቸውን አስታውቀዋል። የምሥራቅ ሪጅን  አንድ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በድሬደዋ በተዘጋጀው የጋራ መድረክ የ2017 ዓ.ም የመጨረሻ ሩብ አመት የመቶ ቀናት ዕቅድ ፀድቋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 10 ቀን 2017 ዓ.ም