es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 560 suscriptores, ocupando la posición 8 357 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 160 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 560 suscriptores.

Según los últimos datos del 25 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 32, y en las últimas 24 horas de -5, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 26.03%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.88% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 052 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 472 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 8.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 26 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 560
Suscriptores
-524 horas
+167 días
+3230 días
Archivo de publicaciones
በተቋማችን የሚገኙ የኃይል ማመንጫዎች፣ ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የግንባታና ኦፕሬሽን እንዲሁም ሌሎች ሥራዎችን የሚመለከቱ የተለያዩ የቪዲዮ ፕሮዳክሽኖችን በተቋማችን ስም በተከፈተ የዩቱዩብ ቻናል ላይ ሲጫኑ ቆይተዋል። በመሆኑም ተቋማችን ሲያከናውናቸው የነበሩትንና እያከናወናቸው የሚገኙ ሥራዎችን በአግባቡ ለመረዳት እና ለብዙኃኑ ተደራሽ ለማድረግ ከዚህ በታች በተቀመጠው https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ማስፈንጠሪያ ወይም ሊንክ በመግባት መረጃዎቹን ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን መረጃውን ለብዙኃኑ ለማድረስ እንዲቻል ቻናሉን ሰብስክራይብ በማድረግ ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲጋብዙ በአክብሮት እንጠይቃለን። ተቋማችን የሚያከናውናቸውን ስራዎች በምስልና ድምፅ ከሚዘጋጁት መረጃዎች በተጨማሪ የፅሁፍ መረጃዎችን ከፈለጉም በተለያዩ የዲጂታል አማራጮች መረጃዎች የሚያገኙ መሆኑን እንገልፃለን። 📡📲💡። 📖 በዲጂታል መጽሔቶቻችንን 👉 https://www.eep.com.et/?page_id=17536 ላይ ያንብቡ። የኢ.ኤ.ኃ. ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 14  ቀን 2017 ዓ.ም

ሪጅኑ አስተማማኝ ኃይል ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎች ማከናወኑን ገለፀ ……..///……. የምስራቅ ሁለት ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ባለፉት ስድስት ወራት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎች ማከናወኑን አስታወቀ። የመምሪያው ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ወርቁ ሙሉ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት በጅግጅጋ፣ ፊቅ፣ ጎዴ፣ ደገሃቡር እና ቀብሪደሃር  የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የአስቸኳይ ጥገና እና የፍተሻ ሥራዎች ተሰርተዋል። ሪጅኑ የኃይል አቅርቦቱን ይበልጥ አስተማማኝ ለማድረግ በጅግጅጋ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ማከናወኑን ጠቁመዋል። በአሁኑ ወቅት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ለጅግጅጋ ከተማና አካባቢው አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ የጠቀሱት ተወካይ ዳይሬክተሩ በጣቢያው ከተሰራው የ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ስዊችጊር የማዘመን ሥራ ባሻገር የትራንስፎርመር አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ጥያቄዎች ለተቋሙ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ መቅረቡን ተናግረዋል። በቀጣይም በጎዴ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የዘመናዊ ስዊችጊር ቅየራ ሥራ ለማከናወን ታቅዶ እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውንም ነው አቶ ወርቁ የገለፁት። እንደ ተወካይ ዳይሬክተሩ ገለፃ ሪጅኑ በስሩ በሚያስተዳድራቸው አምስት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና የማስተላለፊያ መስመሮች በዕቅድ ላይ የተመሰረቱ የጥገና እና የፍተሻ ሥራዎች እያከናወነ ይገኛል። በዚህም በግማሽ በጀት ዓመቱ በአምስቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ 85 ቤዮችን የመጠገን እና የመፈተሽ ሥራ መስራቱን ተናግረዋል፡፡ ሪጅኑ በሚያስተዳድራቸው የማስተላለፊያ መስመሮች ላይ 1 ሺ 643 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ብረቶች ላይ እንዲሁም 719 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የፍተሻና ጥገና ሥራዎች መከናወናቸውንም ነው አቶ ወርቁ ያብራሩት። እንደ ተወካይ ዳይሬክተሩ ገለፃ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት በተከናወኑ የጥገና እና የፍተሻ ሥራዎች በተደጋጋሚ ይከሰት የነበረውን የኃይል መቆራረጥ እንዲቀንስ አስችሏል። በጎዴ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ደረጃውን የጠበቀ የአጥር ግንባታ ሥራ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ የተናገሩት አቶ ወርቁ የአጥር ግንባታው በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ ግመሎች ወደ ጣቢያው እንዳይገቡ ለመከላከል ያለመ መሆኑንም ነው የገለፁት። ባለፉት ስድስት ወራት የጅግጅጋ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽን ሠራተኞች መኖሪያ ቤት ዕድሳት መከናወኑን ጠቅሰው በቀጣይም የቀብሪድሃር እና ደጋሃቡር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽን ሠራተኞች የመኖሪያ ቤት ዕድሳት ለማከናወን የግዥ ሂደቱ መጠናቀቁን አብራርተዋል። ሪጅኑ በጅግጅጋ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ውስጥ በተቋሙ የራስ ኃይል የግንባታ መምሪያ በኩል ጊዜያዊ ተገጣጣሚ የቢሮ ግንባታ ለማከናወን አቅዶ በስፋት እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 14  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

በመንግስትና ግል አጋርነት የሚለሙ ስምንት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ተለይተዋል ……..///…….… በመንግስት እና በግል አጋርነት የሚለሙ ስምንት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች መለየታቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመንግሥት እና የግል አጋርነት መመሪያ ገለፀ። በመምሪያው የፀሐይና ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ሥራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ዘውዴ እንደገለጹት የኃይል ስብጥሩን በማሳደግ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋት በኃይል ማመንጨት ዘርፍ የግል አልሚዎች እንዲሳተፉ የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል፡፡ የግል ዘርፉ ኃይል ማመንጫ ገንብቶና ኃይል አመንጭቶ ለተቋሙ መሸጥ አዲስ አሰራር በመሆኑ የፕሮጀክቶችን አዋጭነት በተመለከተ ተቋሙ የግል ዘርፉን ለማሳተፍና ለማበረታታት ብሎም ፕሮጀክቶቹን ሥራ ላይ ለማዋል የሚያስችል ጥናት በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን መሰራቱን ተናግረዋል፡፡ በዚህም በመንግስትና በግል አጋርነት የሚለሙ ስምንት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች መለየታቸውንና ከእነዚህ ውስጥ የአራቱ ማለትም ጋድ 1 እና 2፣ ዲቼቶ እና ወራንሶ ጥናታቸው መጠናቀቁንም አብራርተዋል፡፡ በጥናት የተለዩትን የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች ለማልማት እ.ኤ.አ በ2019 ግንቦት ወር ጨረታ መውጣቱን  አቶ አሸናፊ አስታወሰዋል፡፡ ይሁንና በወቅቱ የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት ዋስትና በመጠየቁ፣ በውጭ ሀገር ፕሮጀክቱን የተመለከተ የገንዘብ ዝውውር ለማከናወን አካውንት የመክፈት ፈቃድ በመጠየቁ እና ይህንን ለማስፈጸም የሚያስችል አዲስ መመሪያ በማስፈለጉ የግል አልሚዎቹ ወደ ተግባር አለመግባታቸውን ጠቁመዋል፡፡ አሁን ላይ ግን በሀገሪቱ እየተተገበረ በሚገኘው የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ላይ መንግስት ለፕሮጀክቶቹ ትኩረት በመስጠቱ፣ የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት ዋስትና በመተግበሩ እና የውጭ ምንዛሬ አካውንት ለመክፈት አስቻይ ሁኔታ በመኖሩ ፕሮጀክቶቹን ወደ ትግበር እንዲገቡ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ጋድ 2 እና ወራንሶ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በመንግስት እና በግል አጋርነት ለማልማት ጨረታ ወጥቷል ብለዋል፡፡ ሁለቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች 225 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም እንዳላቸውና ፕሮጀክቶቹን ለማጠናቀቅ 200 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የኃይል ስብጥሩን በማሳደግ የኤሌክትሪክ ተደራሽነቱን ከማስፋትም ባሻገር መንግስት ፕሮጀክቱን በራሱ የፋይናንስ አቅም ቢሰራ ሊያወጣ የሚችለውን ፋይናንስ በግል አልሚው በመሸፈን ፕሮጀክቶቹን መተግበር የሚያስችለው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹ በመንግስትና ግል አጋርነት ሲለሙ በተሻለ ጥራትና ጊዜ ለማጠናቀቅ ዕድል ይፈጥራል ያሉት ሥራ አስኪያጁ ከአዋጭነት ጥናቱ ጀምሮ እስከ ፕሮጀክቱ ትግበራ የእውቀት ሽግግር እንዲኖር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ከስምንቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች እስከ 750 ሜጋ ዋት ለማመንጨት ዕቅድ ተይዟል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 14  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

በራስ ኃይል የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አሳሰቡ …….///…… በራስ ኃይል የሚከናወኑ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት ማጠናቀቅ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ፡፡ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ከተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በራስ ኃይል የሚከናወኑ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ያሉበትን ደረጃ ገምግመዋል፡፡ ኢንጂነር አሸብር በዚሁ ወቅት እንዳሉት በተቋሙ የራስ ኃይል የሚከናወኑ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የተቋሙ የመፈጸም አቅም የሚገነባባቸው ከመሆናቸውም በተጨማሪ በጥራትና በጊዜ በማጠናቀቅ በዘርፉ ተወዳዳሪ ለመሆን ዕድል የሚሰጥ ነው ፡፡ የተቋሙ አብዛኛው በጀት በፕሮጀክቶች ላይ እንደሚውል የጠቆሙት ኢንጂነር አሸብር በሥራ ሂደት እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች ላይ ተወያይቶ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ እና አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ውይይቱ ማስፈለጉን ተናግረዋል፡፡ በራስ ኃይል በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እንዲሁም በተቀመጡ ዝርዝር መስፈርቶች መሰረት እንዲጠናቀቁ ለማድረግ በሥራው ላይ የሚሳተፉ አካላት ተቀናጅተው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ውድነህ የማነ በበኩላቸው በተቋሙ በራስ ኃይል መምሪያ አስር የሚሆኑ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፍያ ጣቢያዎች ግንባታ በመካሄድ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ውይይቱ በራስ ኃይል የሚሰሩ ፕሮጀክቶችን አፈጻጸም በመገምገም ከአስተሳሰብ ጀምሮ አሰራሮችን በመለወጥ እንዲሁም ፕሮጀክቶችን አቅዶ ከመፈፀም፣ ከፋይናንስ እና ከዕቃ አቅርቦት በተያያዘ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች በመቅረፍ አፈጻጸማቸውን ለማሻሻል እንደሚያግዝ ገልጸዋል፡፡ ቀደም ሲል የራስ ኃይል ግንባታና ማማከር የሥራ ክፍሎች ለየብቻ የነበሩ መሆኑን ያስታወሱት አቶ ውድነህ በመዋቅሩ ሁለቱ ክፍሎች በአንድ ላይ መሆናቸው ከዲዛይን ጀምሮ የግንባታ ሥራዎች በተቀናጀ መልኩ እንዲከናወኑ ያስችላል ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ የኢንጂነሪንግ ክፍሉ እንደ ተቆጣጣሪ ሳይሆን የኮንስትራክሽን ኃይሉ የሚፈልገውን ቴክኒካዊ ድጋፍ ለመስጠት ዕድል የሚሰጥ በመሆኑ ፕሮጀክቶች በጥራት፣ በጊዜና በተያዘላቸው በጀት ለማጠናቀቅ ይረዳል፡፡ በውይይቱ የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም በመገምገም የሚስተዋሉ ችግሮች ተለይተው የሚፈቱበት ቀጣይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ጠቁመዋል፡፡ ፕሮጀክቶችን በጊዜ ማጠናቀቅ ለተቋም ብሎም ለሀገር የሚኖረውን ሚና ከግምት በማስገባት ሁሉም ተቀናጅቶ መስራት እንደሚኖርበትም አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 13  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ጣቢያው የአካባቢውን የኃይል ፍላጎት ለመመለስ ችሏል ………///………. በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሆለታ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ወደስራ ያስገባቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች የተሟላ ኃይል  ለማቅረብ ምቹ ሁኔታ መፍጠራቸውን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ጥላሁን አዘዘው እንደተናገሩት የሆለታ ማከፋፈያ ጣቢያ ለአቃቂ፣ ሰበታ እና ሱሉልታ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም ለአካባቢው ነዋሪዎችና በኢንቨስትመንት ዘርፍ ለተሰማሩ አምራቾች በተሟላ መልኩ ኃይል በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡ ጣቢያው የተገጠመለት ጂ አይ ኤስ መቆጣጠሪያ፣ የስካዳ ሲስተም እና ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶች ጣቢያው ኃይል ሳይቆራረጥ ደንበኞች ጋር ለማድረስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳበረከቱ የጣቢያው የጥገና ባለሙያ ተዳቻ ገናሌ ተናግረዋል። የጣቢያው መሳሪያዎች የኃይል መቋረጥ ሲኖር ችግሩ የደረሰበት መስመር እና የችግሩን ዓይነት እንዲሁም የችግሩን መጠን በመለየት መረጃን በቀላሉ መልሶ ለመጠገን እንደሚያግዝ አስረድተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 13  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

በአፈጻጸም ላይ የሚታዩ ችግሮችን በመፍታት ፕሮጀክቶችን በታቀደላቸው ጊዜ ማጠናቀቅ ይገባል፤ ……..///….… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ፕሮጀክቶችን በታቀደላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ያለመ ወይይት ከሥራ ተቋራጮችና አማካሪዎች ጋር አካሂዷል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት በሥራ ተቋራጮች የአፈጻጸም ድክመት እንዲሁም ውስጣዊና ውጫዊ ችግሮች ምክንያት በሚጓተቱ ፕሮጀክቶች ምክንያት ተቋሙ ለአላስፈላጊ ወጭና ለተደጋጋሚ የሕዝብ ቅሬታ እየተዳረገ ነው። ተቋሙ ከፕሮጀክቶች አፈጻጸም ጋር በተያያዘ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት እንዲሁም የክትትልና ቁጥጥር ሥርዓቱን በማጠናከር የፕሮጀክቶችን አፈጻጸም ለማሻሻል የመዋቅር ማሻሽያ ጭምር ማድረጉን ጠቁመዋል። በግንባታ ላይ የሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ፕሮጀክቶችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ ተቋሙ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዷለም ሲዓ በበኩላቸው ውይይቱ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም ላይ የሚታዩ ችግሮችን ምንጭ በመለየት መፍትኄዎችን ለማስቀመጥ እና አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ያለመ ነው ብለዋል። ውይይቱ በግንባታ ላይ ያሉትን ፕሮጀክቶች በታቀደላቸው ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ ከማገዙም በተጨማሪ በቀጣይ ግንባታቸው ለሚጀመሩ ፕሮጀክቶች ግብዓት የሚገኝበት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ የእቃ አቅርቦት፣ የጸጥታ ችግር፣ የካሳ ክፍያ፣ ስርቆት እና ከፋይናንስ ጋር የተያያዙ ችግሮች ለፕሮጀክቶች መዘግየት ምክንያት መሆናቸውን ሥራ ተቋራጮቹ በውይይቱ ላይ አንስተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በሰጡት የማጠቃለያ ሃሳብ በሁሉም ወገን ለፕሮጀክቶቹ መዘግየት ምክንያት የሆኑ ችግሮችን በመቅረፍ ቀሪ ሥራዎችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡ ሥራ ተቋራጮች አደረጃጀታቸውን በማጠናከር፣ የሰው ኃይል እና የግብዓት አቅርቦታቸውን በማሻሻል ፕሮጀክቶችን በወቅቱና በተያዘላቸው በጀት ለማጠናቀቅ መስራት እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል፡፡ በቀጣይ መሰል ውይይቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተጠቁሟል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የታዳሽ ኃይል ልማት ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ የሚያስችል ስምምነት ተደርጓል ……..///….… ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ንግድ መድን ኤጀንሲ የታዳሽ ኃይል ልማት ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ የሚያስችላቸውን የመግ
የታዳሽ ኃይል ልማት ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ የሚያስችል ስምምነት ተደርጓል ……..///….… ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ንግድ መድን ኤጀንሲ የታዳሽ ኃይል ልማት ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት አድርገዋል። ስምምነቱ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች የፋይናንስ አቅርቦት ስጋት እንዳያጋጥማቸው ለባለሀብቶች ዋስትና ለመስጠት እና ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በዘርፉ ያላቸውን እምነት ለማሻሻል የሚያስችል እንደሆነ በስምምነቱ ወቅት ተነግሯል። ስምምነቱ የፋይናንስ ስጋቶችን በመቀነስ የአልሚዎችን የክፍያ ደህንነት እና ወሳኝ የሆኑ መንግስታዊ  ተቋማትን ወቅታዊ ክፍያዎች ለማረጋገጥ እንደሚረዳም ተመላክቷል። የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት ስምምነቱ ክፍያዎችን በወቅቱ ከማሳለጥ ባለፈ የፋይናንስ አደጋዎችን ለመቀነስ፣ የኃይል ግዥ ስምምነቶችን ተዓማኒነት ለማረጋገጥ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብድር ብቃትን ለማሻሻል ያግዛል። ከዚህ በተጨማሪ በሀገሪቱ እያደገ ባለው የታዳሽ ሃይል ገበያ ላይ ተጨማሪ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እንደሚረዳ መገለፁን ካፒታል ጋዜጣ በማህበራዊ የትስስር ገፁ ዘግቧል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 12 ቀን 2017 ዓ.ም

የወልቂጤ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን የማዘምን ስራ እየተሰራ ነው ………///………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወልቂጤ ባለ 230  ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያን የማዘመን ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው ሥራ ኃላፊ ሙጀረብ የኑስ ገልፀዋል። ኃላፊው እንደገለፁት በማከፋፈያ ጣቢያው ዘመናዊ የጂአይኤስ መቆጣጠሪያ ቅየራ እና ወረቀት አልባ የኦፕሬሽን ሥራዎች ክትትል ሥራዎች ተጀምረዋል። ማከፋፈያ ጣቢያው ተጨማሪ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚፈልጉ ደንበኞችን ለማስተናገድ የሚያስችል አቅም እንደተፈጠረለት ገልፀዋል። እንደኃላፊው ገለፃ ማከፋፈያ ጣቢያው 360  ሜጋ ዋት የመጫን አቅም ያለው ቢሆንም አሁን ላይ ለደንበኞች እያቀረበ ያለው 158 ሜጋ ዋት ብቻ በመሆኑ ተጨማሪ ደንበኞችን እየጠበቀ ይገኛል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው ከሰኮሩ ማከፋፈያ ጣቢያ በ230 ኪሎ ቮልት ኃይል ተቀብሎ ለሰበታ፣ ለሆሳዕናና ለወሊሶ ማከፉፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም ለጉራጌና አካባቢው ማህበረሰብ ኃይል ያቀርባል። ከዚህ በተጨማሪም ጣቢያው ለሊፍ የተፈጥሮ ውሃና ለዘቢዳር ቢራ ፋብሪካዎች  እንዲሁም ለወልቂጤ ዬኒቨርስቲ ኃይል እያቀረበ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ ጣቢያውን በሙሉ አቅሙ ለመጠቀም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ቢሮ እና ከማዕከላዊ  ጉራጌ ዞን  አስተዳደር ጋር ጋር ምክክር እየተደረገ  እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 10  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የደሴ ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ በተያዘለት መርሃግብር እየተከናወነ ነው ………///………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ በተያዘለት መርሃግብር እየተከናወነ  መሆኑን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ተናገሩ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ዳንኤል ተክለማርያም እንደተናገሩት ተቋሙ ሁለት 63 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች እንዲሁም 6 ባለ 33 ኪሎ ቮልት እና 10 ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ያሉት የማከፋፈያ ጣቢያ በደሴ ከተማ እየገነባ ይገኛል፡፡ 1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር አጠቃላይ በጀት ተይዞለት እየተገነባ ያለውን ፕሮጀክት በተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ እያከናወነው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ግንባታውን እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2019 ለማጠናቀቅ እቅድ ተይዞ እየተሰራ ነው ያሉት አቶ ዳንኤል የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ሲጠናቀቅ ለደሴ ከተማ እና ለአከባቢው አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ያደርጋል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ትራንስፎርመሮችን በቦታቸው የማስቀመጥ ሥራ ተከናውኖ ለመቆጣጠሪያ ክፍል ህንፃ ግንባታ የሚሆን የመሬት ቆረጣ ሥራ በመከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ ዳንኤል ገለጻ የደሴ ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ከፍተኛ የመሬት ቆረጣ የሚፈልግ በመሆኑ የቆረጣ ሥራዉን በፍጥነት ለማከናወን ተጨማሪ ማሽነሪዎችን ወደ ሳይት ለማስገባት ታቅዷል፡፡ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ለደሴ ከተማና አካባቢው የሚኖረውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ ከግምት በማስገባት የመስተዳድር አካላት እና ሕብረተሰቡ ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ እያደረጉ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ ለ94 ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመው ሥራው እየሰፋ ሲሄድ ተጨማሪ የህብረተሰብ ክፍሎችን እንደሚያሳትፍ ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 7  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

ፕሮጀክቱ የወረዳውን የኤሌክትሪክ ኃይል ጥያቄ የሚመልስ ነው ……..///……… የሽግዳን ባለ 230/132/33 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት የሰላማጎ ወረዳና የአካባቢው ነዋሪዎችን የዘመናት የኤሌክትሪክ ኃይል ጥያቄ እንደሚመልስ የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ፡፡ የወረዳው አስተዳዳሪ ዋና አማካሪ አቶ ስምዖን ኤርሚያስ እንደገለፁት የሰላማጎ ወረዳ መቀመጫ በሆነችው ሐና ሙርሲ ከተማ ጨምሮ በወረዳው ሥር የሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ባለመሆናቸው በአካባቢው ማህበረሰብ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ ይገኛል፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል ባለመኖሩ ባለሀብቶች በአካባቢዉ ከማልማት ይልቅ ወደ ሌላ ቦታ እንዲሸሹ እያደረጋቸው እንደሆነና መዋዕለ ነዋያቸውን ለማፍሰስ ፈቃድ የወሰዱ ባለሃብቶችም ወደ ሥራ አለመግባታቸውን ነው የተናገሩት፡፡ የሽግዳን ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ግንባታ ከተጀመረ ወዲህ ባለሃብቶች በአካባቢው ለመሰማራት ጥያቄ ማቅረባቸውን የገለፁት አማካሪው ይህም በቀጣይ አካባቢውን የኢንቨስትመንት እና የቱሪዝም እንቅስቃሴ እንደሚያነቃቃ አመልክተዋል። እንደ አማካሪው ገለፃ የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ለወረዳው ነዋሪዎች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም ባለፈ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በአካባቢው የሚገኙ ወጣቶችን አደራጅቶ በተለያዩ ዘርፎች ለማሰማራት ያግዛል፡፡ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ በመፋጠን ላይ የሚገኝ ሲሆን በሥራው ላይ ችግር እንዳያጋጥም መስመሩ በሚያልፍባቸው አካባቢዎች አደረጃጀት በመፍጠርና በወረዳ ደረጃም አራት የቴክኒክ ቡድኖችን በማዋቀር ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ማህበረሰቡን እስከ አሁን ከነበረበት ጨለማ የሚያወጣ በመሆኑ የአካባቢው ነዋሪ እና ወረዳዉ ለፕሮጀክቱ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አማካሪው አረጋግጠዋል፡፡ የሰላማጎ ወረዳ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ስር ከሚገኙ ስድስት ወረዳዎች መካከል አንዱ ሲሆን የወረዳው መቀመጫ የሆነችው ሐና ሙርሲ ከተማም ከአዲስ አበባ በ880 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 5  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ሁለት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ለማልማት ዝግጅት ተደርጓል ……..///……. በሶማሌ ክልል ጋድ እና በኦሮሚያ ክልል ወራንሶ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በመንግስት እና በግል አጋርነት ለማልማት ጨረታ ወጥቷል፡፡ ሁለቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች 225 ሜጋ ዋት ኃይል በማመንጨት የኃይል ስብጥሩን ለማስፋት እንደሚያስችል ተስፋ ተጥሎበታል፡፡ ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የኃይል አማራጮች አቅም ተጠቅማ የኃይል ፍላጎቷን ለማሟላት የግል አልሚዎች በዘርፉ እንዲሰማሩ የሚያስችል የመንግስትና የግል አጋርነት የሕግ ማዕቀፍ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ ከአሁን ቀደም በመንግሥት እና በግል አጋርነት ማዕቀፍ ከንፋስ ኃይል 300 ሜጋ ዋት ለማመንጨት አሜአ ፓወር ከተሰኘ የተባበሩት አረብ ኤመሬቶች ኩባንያ ስምምነት በመፍጠር ወደ ሥራ መገባቱ ይታወቃል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 04 ቀን 2017 ዓ.ም