en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 572 subscribers, ranking 8 356 in the Technologies & Applications category and 2 162 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 572 subscribers.

According to the latest data from 24 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 24 over the last 30 days and by 19 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.91%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.83% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 035 views. Within the first day, a publication typically gains 2 465 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 8.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“EEP Communication”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 25 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 572
Subscribers
+1924 hours
+197 days
+2430 days
Posts Archive
የቲርጋ ማከፋፈያ ጣቢያን ግንባታ  ለማፋጠን እየተሰራ ነው ………///……… ከአዲስ አበባ በ1 ሺህ 70 ኪሎ ሜትር ርቀት በደቡብ ኦሞ ዞን ኛንጋቶም ወረዳ ላይ እየተገነባ  የሚገኘውን የቲርጋ ባለ 132/33 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራን ለማፋጠን እየተሰራ መሆኑን የብሔሪዊ  የኤሌክትሪክ ግሪድ ደቡባዊ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ገለፀ። የጣቢያው ሳይት ኢንጂነር አቶ ደረጀ ክፍሌ እንደገለፁት የግንባታ ግብዓቶች በቅርበት ባለመገኘታቸውና በአካባቢው ባለው የአየር ፀባይ ምክንያት ሥራዎችን በመርሃ ግብሩ መሰረት ማከናወን አልተቻለም። ሼል ተቋራጩ ለግንባታ ሼል የሚያስፈልጉትን ጠጠር ከ150 ኪሎ ሜትር ፣ አሸዋ ከ250 ኪሎ ሜትር እንዲሁም ውሃ ከ80 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እያጓጓዘ እንደሚጠቀም የሳይት ኢንጂነሩ አስረድተዋል። እንደ አቶ ደረጀ ገለፃ በፕሮጀክቱ ቦታ ርቀት ምክንያት የተስተዋለው የግንባታ አቅርቦት ችግር እና በሙቀቱ ምክንያት በማሽነሪዎች ላይ የሚያጋጥሙ ብልሽቶች በሥራው ላይ መስተጓጎል ፈጥረዋል። በአካባቢው ያለው ሙቀት በኮንክሪት መሠረት ሥራዎች እና በማሽነሪዎች ብልሽት ላይ እያሳደረ ያለውን ችግር ለመቅረፍ የምሽት ሼል መጀመሩን የተናገሩት አቶ ደረጀ ለሥራው የሚያስፈልገውን በቂ የሠው ኃይልም ከሌላ ቦታ በማምጣት የማሟላት ሼል እየተከናወነ ነው ብለዋል። የፕሮጀክቱ ሼል ተቋራጭ ሀዮሰንግ ሄቪይ ኢንደስትሪስ ኮርፖሬሽን የጥራት ቁጥጥርና ማረጋገጥ ሼል አስኪያጅ አቶ አዲስዓለም ማሩ በበኩላቸው የፕሮጀክቱ የግንባታ ሼል ቢጓተትም በአሁኑ ወቅት የሠራተኞች መኖሪያ ቤት፣ የመቆጣጠሪያ ክፍሉ እና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች መትከያ የመሰረት ቁፋሮና የኮንክሪት ሙሊት ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ አብራርተዋል። የጣቢያው አጠቃላይ አፈፃፀም 8 ነጥብ 7 እንዲሁም የሲቪል ግንባታ ሥራው 3 በመቶ እንደተከናወ የጠቆሙት አቶ አዲስዓለም ሥራውን ለማፋጠን ተጨማሪ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሙያዎችን የማሳተፍና ተጨማሪ ማሽነሪዎችን ወደ ሳይቱ የማስገባት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። በፕሮጀክቱ የሳይት 2 ሼል አስኪያጅ አቶ አርጋው ታዲ እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ሲጠናቀቅ በአካባቢው የመስኖ ልማትን ለማስፋፋት፣ በዙሪያው ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችና በግንባታ ላይ ለሚገኘው የስኳር ፋብሪካ ኃይል ለማቅረብ እንዲሁም ከፋብሪካው ተረፈ ምርት የሚመነጨውን ብሔራዊ ግሪድ ለማስገባት ያስችላል። ጣቢያው አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ጥምር ገቢ መስመር፣ አንድ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመር እና አምስት ባለ 33 ኪሎ ኪሎ ወጪ መስመሮች እንደሚኖሩት ተናግረዋል። በግንባታ ግብዓቶች እጥረት ምክንያት በወቅቱ ያልተከናወኑ ሥራዎችን ለማፋጠን ሼል ተቋራጩ ትኩረት ሠጥቶ እየሰራ እንደሆነም አቶ አርጋው ጠቅሰዋል። የማከፋፈያ ጣቢያው የግንባታ ሼል ከ8 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የሆነ በጀት ተይዞለት እየተከናወነ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

ዘርፉ ያስገነባው የዕቃ መጋዘን የሥራ መገልገያ መሣሪያዎችን በአግባቡ ለማደራጀትና ለመጠበቅ ያግዛል  ---///--- በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ያስገነባው የዕቃ መጋዘን  ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ በዘርፉ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ የሀብት  አስተዳደር ቢሮ ሼል አስኪያጅ አቶ ኪሮስ ነጋሽ እንዳስታወቁት በዋና መስሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባው የዕቃ መጋዘን የሥራ መገልገያ መሣሪያዎችን በአግባቡ ለማደራጀትና ለመጠበቅ እያገዘ ነው፡፡ አዲስ የተገነባው መጋዘን ያለ አግባብ በየቦታው ተቀምጠው የነበሩ ዕቃዎችን በአንድ ላይ በመሰብሰብ ከፀሐይ፣ ከአቧራ እና ከዝናብ ለመከላከል እንደሚያስችልም ነው የጠቀሱት፡፡ እንደ አቶ ኪሮስ ገለፃ የዕቃ ማስቀመጫ መጋዘኑ መገንባት የኃይል ማስተላለፊያ መሾመር ዝርጋታዎችን ለማከናወን የሚረዱ በውጭ ምንዛሬ የተገዙ የተለያዩ መሣሪያችን ደህንነት ለማስጠበቅ፤  ምቹ የአሰራር ሥርዓቶችን ተግባራዊ በማድረግ ቀልጣፋና ዘመናዊ የቁጥጥርና ክትትል ሥራዎች እንዲከናወኑ ያግዛል፡፡ ለአገልግሎት ዝግጁ የተደረገው የዕቃ ማስቀመጫ መጋዘን ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበትም ነው ሼል አስኪያጁ የጠቀሱት፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የከተማዋን የኃይል አቅርቦት ያሳድጋል ………///…….. የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራ ሲጠናቀቅ የከተማዋን የኃይል አቅርቦት አሁን ካለበት ከአራት እጥፍ በላይ እንደሚያሳድገው የብሔራዊ የኤሌክትሪክ ግሪድ ደቡባዊ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አስታወቀ። በፕሮጀክቱ የሳይት አንድ ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዱዓለም መላኩ እንዳስታወቁት ፕሮጀክቱ በአርባ ምንጭ ከተማ አካባቢ ሊገነባ ለታሰበው የተቀናጀ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንደስትሪ ፓርክ እና በ120 ኪሎ ሜትር ውስጥ ለሚገኙ አካባቢዎች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ታስቦ እየተከናወነ ይገኛል። የማከፋፈያ ጣቢያው ሁለት ባለ 125 ፣ ሁለት ባለ 63 እና ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች የተከላና ገጠማ ሥራዎች መጠናቀቃቸውን እና የአስር ባለ 33 እና አምስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ፓኔል የማስቀመጥ ሥራዎች እየተከናወነ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ እንደ አቶ አንዱዓለም ገለፃ የፕሮጀክቱ የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራ 65 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች 15 በመቶ ላይ የደረሰ ሲሆን አጠቃላይ አፈፃፀሙ ደግሞ ከ62 በመቶ በላይ ደርሷል። ከአርባምንጭ 2ኛ ማከፋፈያ ጣቢያ በተጨማሪ በወላይታ ሶዶ ሁለተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ እየተከናወነ ያለው የማስፋፊያ ሥራ አጠቃላይ አፈፃፀሙ 62 በመቶ መድረሱን ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል። በማስፋፊያ ሥራው 250 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮችን የማስቀመጥ ሥራ እንደተከናወነ ገልፀው የሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ወጪ እና ገቢ መስመሮች የስቲል ስትራክቸር ተከላ ሥራ በመከናወን ላይ እንደሆነም አስረድተበዋል፡፡ ለአርባ ምንጭ 2ኛ ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራ ከ37 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ እንዲሁም ለወላይታ ሶዶ 2ኛ ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ሥራ ከ14 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በጀት ተይዞላቸዋል። ከማከፋፈያ ጣቢያዎቹ በተጨማሪ ከወላይታ ሶዶ 2ኛ እስከ አርባ ምንጭ 2ኛ በሚዘረጋው የባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር መስመር ላይ ከሚተከሉ 381 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች መካከል የ255ቱ የመሠረት ቁፋሮ ፣ የ242 የመሠረት ግንባታ እና የ22 ምሰሶዎች የተከላ ሥራ መከናወኑን ጠቅሰዋል። የደቡባዊ ግሪድ ሳይት 1 የአንድ አዲስና የሁለት ነባር ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የማስፋፊያ ሥራ እንዲሁም የ216 ኪሎ ሜትር የባለ 230 እና 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ሥራዎችን ያካትታል። የብሔራዊ የኤሌክትሪክ ግሪድ ደቡባዊ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ ሃዮሰንግ ሄቪይ ኢንደስትሪስ ኮርፖሬሽን በተሰኘ የኮሪያ ኩባንያ በመከናወን ላይ ሲሆን የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀምም ከ60 በመቶ በላይ ደርሷል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

photo content
+8

ፕሮጀክቱ ከኦሞ ኩራዝ ስኳር ፋብሪካዎች የሚመነጨውን ኤሌክትሪክ ለመጠቀም ያስችላል …..….///….…. የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ከኦሞ ኩራዝ ስኳር ፋብሪካዎች ተረፈ ምርት የሚመነጨውን የኤሌክትሪክ ኃይል ለመጠቀም እንደሚያስችል የፕሮጀክቱ እና የኦሞ ኩራዝ ስኳር ፋብሪካ የሥራ ኃላፊዎች አስታወቁ። በፕሮጀክቱ የሳይት ሁለት ሥራ አስኪያጅ አቶ አርጋው ታዲ እንዳስታወቁት ከአምስቱ የኦሞ ስኳር ፋብሪካዎች ተረፈ ምርት የሚመነጨውን ከ180 ሜጋ ዋት በላይ ኤሌክትሪክ ከብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር ለማገናኘት የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የግንባታ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል። ይህም የታዳሽ ኃይል ስብጥርንና የማመንጨት አቅምን በማሳደግ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያስችል ገልፀዋል፡፡ በኦሞ ኩራዝ ቁጥር አንድ እና ሦስት ስኳር ፋብሪካዎች የቴክኒክ መምሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ብርሃኑ ጡቃ በበኩላቸው ፋብሪካዎቹ የተፈጨውን የአገዳ ተረፈ ምርት ወደ ቦይለር በማስገባት ኃይል ያመነጫሉ። በፋብሪካው ላይ የኃይል መቆጣጠሪያውን ጨምሮ ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ከዚህ በፊት ዝግጁ መደረጋቸውን የተናገሩት አቶ ብርሃኑ ፕሮጀክቱ እንደተጠናቀቀ በፋብሪካው ላይ ምንም አይነት ተጨማሪ የግንባታ ሥራ ሳይከናወን ማገናኘት እንደሚያስችል አረጋግጠዋል። የኦሞ ኩራዝ ቁጥር ሦስት ስኳር ፋብሪካ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስኪያጅ ኮሎኔል መላኩ ድጋፌ እንደተናገሩት ፋብሪካው ባሉት ሁለት ተርባይኖች 60 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ቢኖረውም እየተጠቀመበት ያለው ከ19 ሜጋ ዋት የማይበልጠውን እንደሆነ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቀ የሚመነጨውን ኤሌክትሪክ ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት በማስገባት የኃይል ብክነትን ለመቀነስ እና የፋብሪካውን ምርታማነት ለማሳደግ ዕድል ይፈጥራል ነው ያሉት። በፋብሪካዎቹ የሚመነጨው ኃይል ወደ ግሪዱ በሚገባበት ጊዜ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ስኳር ኮርፖሬሽን መካከል ያለውን ግንኙነት እንደሚያጠናክረው የሥራ ኃላፊዎቹ አስታውቀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም

የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ አፈፃፀም 35 በመቶ ደርሷል ……..///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡባዊ የኤሌክትሪክ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል የሆነው የሽግዳን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ አፈፃፀም ከ35 በመቶ በላይ መድረሱን በፕሮጀክቱ የሳይት 2 ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ አርጋው ታዲ እንደገለጹት ሽግዳንና ቲርጋ ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም ከሳውላ እስከ ቲርጋ የሚዘረጋው የ196 ኪሎ ሜትር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ሥራ በሳይት ሁለት ስር የሚከናወኑ ናቸው። ከ27 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በሆነ በጀት የተጀመረው የሽግዳን ማከፋፈያ ጣቢያ ሁለት ባለ 125፣ ሦስት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመሮች እና ሁለት ሻንት ሪያክተሮች እንደሚኖሩት ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል። ማከፋፈያ ጣቢያው አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር ገቢ መስመር፣ አንድ ባለ 132 እና አስራ አምስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንደሚኖሩት ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል፡፡ ሦስት ትራንስፎርመሮች፣ ሁለት ሸንት ሪያክተሮች፣ ብሬከሮችና ለማከፋፈያ ጣቢያው አስፈላጊ የሆኑ ሌሎች ዕቃዎች ሳይት መድረሳቸውንና ቀሪ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች በቅርቡ እንደሚገቡ አስታውቀዋል። ከማከፋፈያ ጣቢያው በተጨማሪ ከሳውላ እስከ ሽግዳን በሚዘረጋው በባለ 230 ጥምር መስመር ላይ ከሚተከሉ 387 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች መካከል የ170ዎቹ የመሠረት ቁፋሮ፣ የ160 የመሠረት ግንባታ እና የ12 ምሰሶዎች የተከላ ሥራ መከናወኑን ገልፀዋል። የማከፋፈያ ጣቢያው ሲጠናቀቅ በሰላማጎ ወረዳና በዙሪያው ለሚገኙ ቀበሌዎች እንዲሁም ለስኳር ፋብሪካዎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እንዲሁም የመስኖ ልማትን ጨምሮ በአካባቢው በሌሎች ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎት ያላቸውን ኢንቨስተሮችን ለመሳብ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለዋል። የፕሮጀክቱ የሲቪል መሃንዲስ አቶ መኮንን ጥላሁን በበኩላቸው የሠራተኞች መኖሪያ ቤት 20 በመቶ፣ የኃይል መቆጣጠሪያ ክፍሉ 40 በመቶ፣ የኬብል ማስተላለፊያ ቱቦዎች ሥራ 5 በመቶ እንዲሁም ጣቢያውን ከጎርፍ አደጋ ለመከላከል የሚያስችሉ የፍሳሽ ማስወገጃ ሥርዓት ሥራዎች 2 በመቶ መከናወኑን አስረድተዋል። ከአምስት የትራንስፎርመርና ሁለት ሸንት ሪያክተር ማስቀመጫ የኮንክሪት መሠረት ሥራዎች መካከል የአምስቱ ሲጠናቀቅ የቀሪዎቹን በአንድ ወር ውስጥ በማጠናቀቅ ትራንስፎርመሮችን የማስቀመጥ ሥራ እንደሚከናወንም ተናግረዋል። እንደ አቶ መኮንን ገለፃ ከ452 የኤሌክትሮ ሜካኒካል ብረቶች መትከያ የኮንክሪት መሠረት ሥራ ውስጥ 300 የሚሆኑት መዘጋጀታቸውንና ቀሪዎቹን በሁለት ወራት ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው። የግንባታ ሥራውን የሚያከናውነው የሃዮሰንግ ሄቪይ ኢንደስትሪስ ኮርፖሬሽን የሳይት ሁለት የግንባታ ሥራ አስከኪያጅ ሚስተር ዳንኤል ኪም የፕሮጀክቱ የግንባታ አፈፃፀም በጥሩ ሂደት ላይ ስለሚገኝ በተያዘለት የጊዜ ገደብና ጥራት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ሽግዳንና ቲርጋ ጨምሮ አርባ ምንጭ 2ኛ ላይ የሚገነቡ ሦስት አዳዲስ ማከፋፈያ ጣቢያዎች፣ ነባሩ ወላይታ ሶዶ ሁለተኛ እና አርባምንጭ አንድ ላይ የሚከናወን የማስፋፊያ ሥራ እንዲሁም የ424 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ሥራዎችን ያጠቃልላል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

የማከፋፈያ ጣቢያው በአካባቢው አስተማማኝ ኃይል እንዲኖር እያደረገ ነው ……..//…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሞጆ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ አስተማማኝ ኃይል እያቀረበላቸው መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና የአንበሳ ቢራ ፋብሪካ የሥራ ኃላፊዎች ተናገሩ። በአገልግሎቱ የሞጆ ደንበኞች አገልግሎት መስጫ ማዕከል ሥራ አስኪያጅ አቶ ወንዱ ደረጀ እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የመሸከም አቅም ደንበኞችን ለመሳብ ድርሻው የጎላ በመሆኑ በሞጆ ማከፋፈያ ጣቢያ ያለው አቅም ለደንበኞች በቀላሉ ኃይል ተደራሽ እንዲያደርጉ ዕድል እየፈጠረ ነው። በማዕከሉ ሥር ከሚገኙ 18 ሺህ 500 ደንበኞች ውስጥ ለ12 ቆዳ ፋብሪካዎች፣ ለኢጀሬና ሞጆ ከተማ፣ አንበሳ ቢራ ፋብሪካ፣ ሸራ እና ቢዩ በሚባሉ አካባቢዎች ለሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች ከጣቢያው በሚያገኙት ኃይል እየሰጡ እንደሆነ ተናግረዋል። እንደ አቶ ወንዱ ገለፃ በጣቢያው ያለውን አስተማማኝ አቅም በመጠቀም ለደንበኞች ተጨማሪ ኃይል ለማቅረብና አዳዲስ ደንበኞችን ለማፍራት እየተሰራ ነው። የአንበሳ ቢራ ፋብሪካ የቴክኒክ ሥራ አስኪያጅ አቶ ምንውየለት መላክ በበኩላቸው የሞጆ ማከፋፈያ ጣቢያ ከዚህ በፊት ይስተዋል የነበረውን የኃይል መቆራረጥ በማስቀረት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የሞጆ ማከፋፈያ ጣቢያ ከመገንባቱ በፊት ፋብሪካው ከዱከም መስመር ኃይል ያገኝ እንደነበር በመግለፅ በወቅቱ በመስመሩ ላይ በነበረው የኃይል ተጠቃሚ መብዛት የተነሳ የኃይል መቆራረጥ ያጋጥመው እንደነበር ሥራ አስኪያጁ አስታውሰዋል። ይሁንና ከሞጆ ማከፋፈያ ጣቢያ በባለ 33 ኪሎ ቮልት ራሱን በቻለ መስመር ኃይል ማግኘት ከጀመረ ወዲህ የኃይል መቆራረጡ መቀረፉን አቶ ምንውየለት ገልፀዋል። ይህም በምርት ሂደት ላይ የሚፈጠሩ ችግሮችን በመቅረፍ፣ ለነዳጅ የሚወጣውን ተጨማሪ ወጪ እና በኃይል መቆራረጥ ምክንያት የሚያጋጥሙ የመሣሪያ ብልሽቶችን በማስቀረት እንዲሁም ከተቋማቱ ጋር የነበረውን አለመግባባት እንዲፈታ በማድረግ የራሱን አስተዋፅዖ አበርክቷል ነው ያሉት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

photo content
+5

የማከፋፈያ ጣቢያውን አቅም  ለመጠቀም እየተሠራ ነው ……..///………. የሞጆ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ያለውን የመሸከም አቅም ሙሉ በሙሉ ጥቅም ላይ ለማዋል እየተሰራ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ ገለፁ። ኃላፊው አቶ ሚናስ ወንድምሞላ እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያው ከቢሾፍቱ ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ በ 230 ኪሎ ቮልት ኃይል ተቀብሎ  ለተለያዩ ከተሞችና ፋብሪካዎች ኃይል እያቀረበ ይገኛል። ጣቢያው አስር ባለ 15 እና አራት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ቢኖሩትም አገልግሎት እየሠጡ የሚገኙት አራት ባለ 33 እና አራት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ብቻ መሆናቸውን ኃላፊው  ገልፀዋል። በ 33 ኪሎ ቮልት ባሉት ወጪ መስመሮች ለአንበሳ ቢራ ፋብሪካ፣ ለኢጀሬ ከተማ፣ ለአረርቲ ከተማና ሴራሚክ ፋብሪካ እንዲሁም በባለ 15 ኪሎ ቮልት መስመሮች ለሞጆና ቢሾፍቱ ከተሞች፣ ለአየር ኃይል እና በአካባቢው ለሚገኙ ቆዳ ፋብሪካዎች አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ ይገኛል ብለዋል። ማከፋፈያ ጣቢያው አንድ ባለ 25 ሜጋ ቮልት አምፔር እና ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው  ትራንስፎርመሮች እንዳሉትም ጠቁመዋል። እንደ አቶ ሚናስ ገለፃ ሦስቱ ትራንስፎርመሮች 100 ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ቢኖራቸውም በአሁኑ ወቅት ለደንበኞች እየቀረበ ያለው ከ25 በመቶ የማይበልጠው ነው። ማከፋፈያ ጣቢያው በአካባቢው ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት እንዳሳደገው የገለፁት ኃላፊው የጣቢያውን አቅም እና ዝግጁ የተደረጉ ሁሉንም ወጭ መስመሮች ጥቅም ላይ ለማዋል በአካባቢው ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ውይይት መደረጉን አንስተዋል። ለአዳማ ከተማ ውሃ አገልግሎት፣ ለሞጆ ደረቅ ወደብ፣ ለሞጆ ከተማ እና በአካባቢ ለሚገኙ ዘጠኝ ፋብሪካዎች ተጨማሪ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችሉ የማሰራጫ መሾመር ዝርጋታ በአገልግሎቱ በኩል መጀመሩን ገልፀዋል። የሞጆ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 26 ቀን 2017 ዓ.ም

ተጨማሪ የኃይል ፍላጎቶችን ለማሟላት እየተሰራ ነው .........///…..... በቢሾፍቱ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ እየቀረቡ ያሉ ተጨማሪ የኃይል ጥያቄዎችን ለመመለሾ እየተሰራ መሆኑን የጣቢያው ሼል አስኪያጅ ገለፁ። ሼል አስኪያጁ  አቶ ሲሳይ አይቸው እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያው ከገላን ማከፋፈያ ጣቢያ በባለ 400 ኪሎ ቮልት ጥምር መሾመር ኃይል ተቀብሎ ለቢሾፍቱ፣ ዱከም ቁጥር 2  እና ለሞጆ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል ያከፋፍላል። ማከፋፈያ ጣቢያው አገልግሎት መስጠት በጀመረበት ወቅት 100 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት የ230/15 ኪሎ ቮልት ፓወር ትራንስፎርመሮች ብቻ እንደነበሩት የጠቆሙት ሼል አስኪያጁ በአካባቢው በባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መሾመር የኃይል ጥያቄ በመቅረቡ 100 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት 230/33 ተጨማሪ ፓወር ትራንስፎርመሮች መተከላቸውን አስታውሰዋል። በአቅም ማሳደግና ማስፋፊያ  ሥራዎች በወቅቱ የነበረውን የኃይል ጥያቄ መመለሾ ቢቻልም በአካባቢው ካለው የኢንዱስትሪ መስፋፋት ጋር ተያይዞ የኃይል ጥያቄው ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ሼል አስኪያጁ ገልጸዋል። እንደ አቶ ሲሳይ ገለጻ ያሉት የ400/230 አውቶ ትራንስፎርመሮች ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ አቅም ቢኖራቸውም የአካባቢው የኃይል ፍላጎት በፍጥነት እየደገ ከመሄዱ ጋር ተያይዞ ለማሳራጫ መስመሮች ኃይል የሚያቀርቡ ሁሉም የፓወር ትራንስፎርመሮች ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ አቅም የላቸውም። በዚህም ጣቢያው በ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ካሉት 22 ወጭ መስመሮች ሁለቱ የ33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች አገልግሎት እየሰጡ አለመሆናቸውን ነው የገለፁት። የኃይል ፍላጎቱ የጣቢያው ግንባታና የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ሲከናወኑ ይመጣል ተብሎ ከታሰበው በላይ በፍጥነት እያደገ በመምጣቱ ተጨማሪ ጥያቄዎችን በወቅቱ ለመመለሾ እንዳላስቻለ አቶ ሲሳይ ተናግረዋል። ስለሆነም እያደገ የመጣውን የኃይል ጥያቄ በጊዜያዊነት ለመመለሾ ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ ለማስቀመጥ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅትም ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያው የሚቀመጥበትን ቦታ የመለየትና ሌሎች የጥናት ሥራዎች እየተከናወኑ ስለመሆናቸው ነው ሼል አስኪያጁ የጠቀሱት። ከህብረተሰቡ እና ከኢንዱስትሪዎች እየቀረቡ ያሉ የኃይል ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመመለሾ የሚያስችል የአቅም ማሳደግና የማስፋፊያ ሥራዎችን ለማከናወን ዕቅድ መያዙንም አብራርተዋል። የቢሾፍቱ ቁጥር 3 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከሐምሌ 2012 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

በመድን ፖሊሲዎች አተገባበር ዙሪያ የግንዛቤ ማሳደጊያ ስልጠና ተሰጠ ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ መድን ድርጅት ጋር በመተባበር በመድን ፖሊሲዎች  አተገባበር ዙሪያ ለአምስት ተከታታይ ቀናት  ሥልጠና  ተሰጥቷል፡፡        በሥልጠናው  ማጠቃላያ ላይ በንብረት አስተዳደርና ጥገና መምሪያ የንብረት ሪስክና ኢንሹራንስ ሼል አስኪያጅ አቶ ሳህሌ ደግፍ እንደተናገሩት ሥልጠናው በኢንሹራንስ ፖሊሲዎች አተገባበር ዙሪያ ቴክኒካዊና ህጋዊ አካሄዶችን ለይቶ ለማወቅ የሚያስችል ነው፡፡ ሥልጠናው በሞተር፣ በማሽነሪ ጉዳት፣ በእሳትና መብረቅ፣ በሠራተኞች የ24 ሰዓት የኢንሹራንስ ሽፋን፣ በገንዘብ እና ገንዘብ ነክ ሾል ላይ ለተሰማሩ ሠራተኞች የእምነት ማጉደል የኢንሹራንስ ፖሊሲዎች እና አተገባበር ትኩረት ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሠልጣኞች ከሥልጠናው ባገኙትን እውቀት በኢንሹራንስ መሸፈን ያለባቸውን እና የሌለባቸውን ንብረቶች በመለየት ተቋሙ ተጠቃሚ የሚሆንበት የውሳኔ ሀሳብ ለማቅረብ ያስችላቸዋል ብለዋል፡፡ የኢንሹራንስ ሽፋን በተሰጣቸው ንብረቶች ላይ ጉዳት ሲደርስ በፖሊሲው መሰረት ለካሳ ክፍያ የሚያስፈለጉ መረጃዎችን በፍጥነት አጠናክረው በማዘጋጀት ለሚመለከተው አካል ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡ በሁለት ዙር ለ10 ቀናት በተሰጠው ሥልጠና ላይ ከተቋሙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች የተወጣጡ ከ50 በላይ ባለሙያዎች እና የሥራ መሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ስልጠናው ከኢትዮያ መድን ድርጅት በመጡ ባለሙያዎች መሰጠቱ ተገልጿል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4