en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 692 subscribers, ranking 8 036 in the Technologies & Applications category and 2 171 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 692 subscribers.

According to the latest data from 03 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 143 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 27.84%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.00% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 369 views. Within the first day, a publication typically gains 2 511 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 692
Subscribers
-124 hours
+47 days
+14330 days
Posts Archive
photo content
+5

#Vacancy የውጪ ሥራ ቅጥር ማስታወቂያ 🌟 ……///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (ኢኤኃ) በጁኒየር ኤሌክትሪካል መሐንዲስ እና በጁኒየር ሜካኒካል መሐንዲስ የስራ መደቦች ብቁ ሠራተኞችን አወዳ
#Vacancy የውጪ ሥራ ቅጥር ማስታወቂያ 🌟 ……///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (ኢኤኃ) በጁኒየር ኤሌክትሪካል መሐንዲስ እና በጁኒየር ሜካኒካል መሐንዲስ የስራ መደቦች ብቁ ሠራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ አመልካቾች በሚከተሉት ሊንኮች መመዝገብ ትችላላችሁ፡፡ 🔗 Link 1      🔗 Link 2 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 9 ቀን 2017 ዓ.ም

ሪጅኑ ሲያካሂድ የቆየውን የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ አጠናቀቀ ...///... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ ሪጅን አንድ ለሁለት ቀናት በድሬደዋ ሲያካሂድ የቆየውን የ2017 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ በዛሬው እለት አጠናቋል። በመዝጊያ መረኃ ግብሩ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር ሥራ አስፈፃሚ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌትነት መኮንን ማህበሩ ከተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ያደረጋቸው የሁለትዮሽ ህብረት ስምምነት አስመልክቶ ገለፃ አድርገዋል። አቶ ጌትነት እንደተናገሩት ማህበሩ የሠራተኛውን ሁለንተናዊ ጥቅም ለማስጠበቅ የሚያስችሉ በርካታ ጉዳዮች ላይ በመደራደር አመርቂ ስራዎች መሠራታቸውን አመላክተዋል። የሠራተኞች ዝውውር፣ የደረጃ ዕድገት፣ የደሞዝ ማሻሻያ፣ የትራንስፖርትና የቤት አበል፣ የበረሃ አበል፣ የህክምና ወጪን የመሳሰሉ በርካታ ጉዳዮችን በህብረት ስምምነቱ በመደራደር የሰራተኛውን ጥቅም በማረጋጋጥ የተሄደበትን ርቀት ገልፀው የስምምነቱ አጠቃላይ ይዘትና ትግበራ በሚቀጥለው ግንቦት አንድ 2017 ዓ.ም ይፋ እንደሚሆንም አስታውቀዋል። በመድረኩ ሲሳተፉ የቆዩ የሪጂኑ ሠራተኞች እንዲሁም የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ኃለፊዎች፣ የጥገና ቡድን ባለሙያዎች፣ የኦፐሬሽን ባለሙያዎች፣ የቡድን መሪዎች፣ አሽከርካሪዎች እና የጥበቃ ሰራተኞች ላነሷቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ተሰጥቷል። በመርኃግብሩ ማጠቃለያ ሪጅኑ በስሩ ከሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ባለፉት ዘጠኝ ወራት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ሦስት ጣቢያዎችን ጨምሮ የማስተላለፊያ መስመር ሰራተኞች፣ የጥገናና የኦፕሬሽን ሰራተኞች፣ አሽከርካሪዎች እንዲሁም የሪጅኑ የአስተዳደር ሰራተኞችን የዕዉቅና የምስክር ወረቀት አበረክቷል። የምስክር ወረቀት የተበረከተላቸው ጣቢያዎች።፣ የቡድን መሪዎች እና ሰራተኞች በተዘጋጀላቸዉ ሽልማት መደሰታቸውን ገልፀዉ ለቀጣይ የተጠናከረ ስራ መሰረት እንደሚሆናቸው ገልፀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 9 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች በመንግስት የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም ላይ ተወያይተዋል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በመንግስት የ2017 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ላይ በዛሬው ዕለት ተወያይተዋል። በውይይቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ እና የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ም/ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ውድነህ የማነ እንደገለፁት ውይይቱ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ሃገራዊና ዓለም አቀፋዊ አውዱን እንዲገነዘቡ ለማድረግ ያለመ ነው። ውይይቱ በዘጠኝ ወሩ ውስጥ እንደ ሃገር በተመዘገቡ ስኬቶች፣ ባጋጠሙ ችግሮች፣ ለችግሮቹ በተወሰዱ የመፍትሔ እርምጃዎች እና በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር እንዲሁም ተቋሙ ለሀገሪቱ እድገት እያበረከተ ያለውን አስተዋፅኦ በማሳወቅ የቀጣይ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ እንደሚረዳ ተናግረዋል። በዕለቱም ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ አዝማሚያዎችና በኢትዮጵያ የሚኖረው አንደምታ፣ የማክሮ ኢኮኖሚ እና የሪፎርሙ አፈፃፀም ውጤቶችና አዝማሚያዎች፣ የዋና ዋና መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች አፈፃፀም፣ ቀጣይነት ባላቸው የዘላቂ ልማቶች፣ በአስቻይ ሁኔታዎች እና በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን የተመለከተ የመወያያ ሰነድ በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ በኢንጅነር አንዷለም ሲዓ ቀርቧል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው የኢኮኖሚ አዝማሚያ በኢትዮጵያ ላይ የሚያሳድረውን አዎንታዊና አሉታዊ አዝማሚያዎቸ በመለየት የተለያዩ ክንውኖች ሲደረጉ እንደነበር ገልፀዋል። በሀገሪቱ የተደረገው ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢኮኖሚያዊ መረጋጋትትን ማረጋጋጥ፣ ኢንቨስትመንትን ማሻሻል፣ የመንግስት የመፈፀም አቅም ማጎልበት እና ምርታማነትንና ተወዳዳሪነትን ማሳደግ ላይ ትኩረት ያደረገ እንደሆነም  አስረድተዋል። ማሻሻያውን ጨምሮ በተቋማት ላይ እየተከናወኑ ያሉ የለውጥ ሥራዎች ተቋሙን በዕዳ ሽግሽግና በሌሎች የተለያዩ ጉዳዮች ተጠቃሚ ማድረጉን ም/ዋና ሥራ አስፈፃሚው አስታውቀዋል። የኤሌክትሪክ ዘርፉ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት በኩል የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን የተናገሩት ኢንጂነር አንዷለም  በዚህም ተቋሙ በሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ከሚያስገኙ ተቋማት በአምስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን አስታውቀዋል፡፡ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከኤሌክትሪክ ዘርፉ 230 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ መገኘቱንም ጠቁመዋል፡፡ በዘጠኝ ወራት ውስጥ በሃገሪቱ እየተካሄዱ የሚገኙ የዋና ዋና ፕሮጀክቶች አፈፃፀም ውጤታማ እንደነበር የተናገሩት ኢንጅነር አንዷለም በኃይል ማመንጫ ዘርፍም የታላቁ ህዳሴ ግድብ 98 ነጥብ 66፣ ኮይሻ 71 ነጥብ 37፣ አይሻ 84 ነጥብ 8 እንዲሁም አሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት 82 ነጥ 31 በመቶ መድረሳቸውን አብራርተዋል። ሃገሪቱ እያመነጨችው ያለው ኤሌክትሪክ ኃይል ለቤት ውስጥ መብራት ብቻ ሳይሆን ኢንዱስትሪንና ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት እንዲሁም በቀጣናው ላይ ተፅዕኖ ለመፍጠር እንደሚረዳ ተናግረዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ከዋጋ ግሽበትና የኑሮ ውድነት፣ በሀገሪቱ በሚስተዋለው የፀጥታ ችግር፣ ከኮሪደር ልማት አተገባበር፣ ሠራተኛውን ተጠቃሚ ለማድረግ እየከናወኑ ባሉ ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረጉ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን አንስተዋል። ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ማብራሪያ የሰጡት የኮርፖሬት ፋይናንስ እና ሃብት አስተዳደር ዘርፍ ም/ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደተናገሩት በሀገሪቱ እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማቶች ለቀጣይ ትውልድና ለኢኮኖሚው የሚኖረውን ሚና በመገንዘብ ነው እየተከናወነ የሚገኘው። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ  ተወካይ እና የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ም/ዋና አስፈፃሚ ኢንጅነር ውድነህ የማነ በበኩላቸው የኮሪደር ልማቱ ኢንቨስትመንትን፣ ቱሪዝምን እና ታላላቅ አህጉርና ዓለም አቀፍ መድረኮች በሀገሪቱ እንዲካሄዱ እየሳበ ይገኛል ብለዋል። የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት በመንግስት እየተደረገ ካለው ድጎማ ባለፈ ችግሮቹን በዘላቂነት ለመፍታትም የማምረት አቅም ማሳደግ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 9 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

የሪጅኑን የበጀት ዓመት ዕቅድ ለማሳካት ሁሉም መረባረብ አለበት …..///….. በሪጅኑ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የነበሩ ክፍተቶችን በማረም በቀሪ ወራት የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ለማሳካት ሁሉም ሊረባረብ እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ ሪጅን አንድ ዳይሬክተር አሳሰቡ፡፡ ሪጅኑ በስሩ የሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያ የሥራ ኃላፊዎች፣ የኦፕሬሽንና የጥገና ባለሙያዎች በተገኙበት የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በድሬድዋ ከተማ እያካሄደ ነው፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ ሙሐመድ እንደገለፁት ለሁለት ቀናት የሚካሄደው ግምገማ የሪጅኑን የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈፃፀም፣ ያጋጠሙ ችግሮች እና የተወሰዱ የመፍትሄ ርምጃዎች ላይ ውይይት በማድረግ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች ያሉበትን ደረጃ ለማወቅ እና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ያለመ ነው፡፡ ሁሉም የሪጅኑ አመራርና ሠራተኛ በተቋሙ እየተከናወነ ያለውን የሪፎርም ሥራ በሚደግፍ መልኩ የኦፕሬሽን ሥራዎችን በአግባቡ ማከናወን እንዳለበትም ጠቁመዋል፡፡ በግምገማው በተለያየ ጊዜ በችግር መልክ ሲነሱ የቆዩና መፍትሄ ያላገኙ ጉዳዮችን በመለየት በቀጣይ በሚፈቱበት አግባብ ዙሪያም አቅጣጫ እንደሚቀመጥ አመልክተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ሪጅኑ ያቀዳቸውን ተግባራት በሙሉ ለማከናወን ባለፉት ዘጠኝ ወራት ያልተከናወኑ ተግባራትንና በሚቀጥሉት ሦስት ወራት ለማከናወን የታቀዱ ሥራዎችን በማካተት የመቶ ቀን ዕቅድ መዘጋጀቱን የጠቆሙት አቶ ወርዲ አመራሩና ሠራተኛው በዕቅዱ ላይ የጋራ መግባባት ኖሯቸው ወደ ሥራ እንዲገቡ ውይይት እንደሚደረግበትም አብራርተዋል። የሪጅኑ የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም በድሬደዋ ቁጥር ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬተር ባለሙያ አቶ በሱፍቃድ ባዩ ቀርቧል፡፡ አስተማማኝና ያልተቆራረጠ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር በሪጅኑ ሥር ባሉ የማከፋፍያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ጊዜውን የጠበቀ የቅድመ መከላከል፣ የትንበያ፣ የፍተሻ ጥገና ሥራዎች እንዲሁም የማዘመን ሥራዎች በራስ አቅም ጭምር መከናወናቸው በሪፖርቱ በጥንካሬ ተነስቷል፡፡ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ስርቆት እና የማስተላለፊያ መስመሮች በቀለበት አለመያያዛቸው በክፍተት የተጠቀሰ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት ላይ በተሳታፊዎቹ ውይይት እየተደረገበት ይገኛል፡፡ የምስራቅ ሪጅን አንድ በስሩ ዘጠኝ የማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና 1950 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ማስተላለፊያ መስመሮችን ያስተዳድራል፡፡ ግምገማው በነገው ዕለትም የሚቀጥል ይሆናል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ስርቆት የፈፀሙ አካላት በቁጥጥር ሥር ውለዋል ……///…. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኮምቦልቻ 2 ወደ ኮምቦልቻ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ ስርቆት የፈፀሙ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን በደቡብ ወሎ ዞን የቃሉ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ የተፈፀመው ስርቆት ለአንድ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ መውደቅና በኮምቦልቻ፣ በደሴ አቀስታ እና ዓለም ከተሞች እና አካባቢያቸው ለመብራት መቋረጥ ምክንያት ሆኖ ነነበር፡፡ በስርቆቱ የተሳተፉ አራት ግለሰቦችን ማለትም ሁለቱ በስርቆቱ በቀጥታ የተሳተፉ፣ አንድ ገዥ እና ቀሪው የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭ በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያካሄደ እንደሚገኝ የገለፀው ፖሊስ ፅ/ቤቱ ምርመራውን በፍጥነት በማጠናቀቅ ለፍርድ ለማቅረብ እየሰራ መሆኑንም አስታውቋል፡፡ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈፀም ስርቆት የወንጀል ተጠያቂነትን የሚያስከትል መሆኑን በመረዳት በመሰል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካልት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡም ፖሊስ አሳስቧል፡፡ በቀጣይም በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈፀም ስርቆትን ለመከላከል ከማህበረሰቡና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀራርቦ እንደሚሰራ ገልጿል፡፡ የኢነርጂ አዋጅ 810/2006 አንቀጽ 26 በኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ ወይም ማከፋፈያ ተቋማት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም ሰው ከ5 እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ወይም እስከ 50 ሺህ ብር በሚደርስ ገንዘብ ወይም በሁለቱም እንደሚቀጣ ይደነግጋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የህፃናት ማቆያ ማዕከሉ የሠራተኞችን ጫና እያቃለለ ነው ……….///……….. የአዋሽ ሁለት እና ሶስት የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የህፃናት ማቆያ ማዕከል በመከፈቱ በሥራ ላይ የሚገጥማቸውን ጫና እያቃለለ መሆኑን የጣቢያው ሠራተኞች ተናገሩ፡፡ በማዕከሉ ልጆቻቸውን በማቆየት ተጠቃሚ የሆኑ የጣቢያው ሰራተኞች እንደተናገሩት ጣቢያው ከሰኞ እስከ አርብ  ልጆቻቸውን ተቀብሎ በመንከባከቡ የሥራ ጊዜያቸውን ለሥራ ለማዋል አስችሏቸዋል፡፡ ማዕከሉ በጣቢያው ውስጥ መከፈቱ ልጆቻቸውን ያለስጋት እንዲቆዩ እና በቅርበት እንዲንከባከቡ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡ በጣቢያው የንብረት አስተዳደርና አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ኮከቤ ተመስገን በበኩላቸው ሁሉም የጣቢያው ሠራተኞች በእውቀት፣ በቁሳቁስ እና በጉልበታቸው በማገዝ ሥራ እንዲጀምር ማድረጋቸውን ገልፀዋል፡፡ ማዕከሉ ለጊዜው ስድስት ህፃናት ተቀብሎ በአንድ ተንከባካቢ ሰራተኛ ስራውን መጀመሩን አስረድተዋል፡፡ 💡"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠ https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ሪጅኑ ለኦዲት ግኝቶች ፈጣን ምላሽ መስጠት እንዳለበት ተገለፀ፤ ….///…. ሪጅኑ ለኦዲት ግኝቶች ፈጣን ምላሽ በመስጠት ለተቋማዊ ለውጡ ስኬት የበኩሉን ሚና ሊወጣ እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውስጥ ኦዲት ዘርፍ አሳሰበ፡፡ ዘርፉ ከምስራቅ ሪጅን አንድ ለተውጣጡ ባለሙያዎችና የሥራ ኃላፊዎች በተቋማዊ ለውጡ እና በውስጥ ኦዲት ሥራዎች ዙሪያ በድሬድዋ ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ መርጋ ተረፈ እንደገለጹት ስልጠናው ሪጅኑ ሥራውን ግልፅነትንና ተጠያቂነትን ባሰፈነ መልኩ በማከናወን ተቋሙ እየተገበረ ያለውን ተቋማዊ ለውጥ ለማሳካት የሚችሉበትን ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ ነው፡፡ የውስጥ ኦዲት ሥራ የተቋሙን የመልካም አስተዳደር፣ የሥራ ቅልጥፍናና የፋይናንስ ጤንነት እንዲሁም የቁጥጥር ሥርዓቱን በመገምገምና በማሻሻል ተቋማዊ ስኬትን ለማምጣት እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡ ኦዲትን ከፋይናንሽያል ምርመራ ጋር ብቻ የማያያዝ አመለካከት መኖሩን የጠቆሙት አቶ መርጋ ዘርፉ ይሄን አመለካከት ለማስተካከል ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተግባራትን ለማከናወን አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡ ሪጅኑ የሚያከናውኗቸው ሥራዎች በተቋሙ የተቀመጡ ፖሊሲዎችና ደንቦችን የተከተለ እና ከብክነት የፀዱ መሆናቸውን በማረጋገጥ እንዲሁም ለኦዲት ግኝቶች ፈጣን ምላሽ በመስጠት በኩል ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባም ገልፀዋል፡፡ የውስጥ ቁጥጥርን በማጠናከር፣ የስጋት አስተዳደርን በማሻሻል፣ የሕግና ደንብ ተገዢነትን በማረጋገጥ ግልጽነትንና ተጠያቂነትን ማስፈን ለአንድ አካል ብቻ የሚተው ባለመሆኑ የውስጥ ኦዲት ሥራውን በተሳካ ሁኔታ ለማከናወን ሁሉም በእኔነት ስሜት እንዲሰራ አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 7 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ፕሮጀክቱ ከመተግበሩ በፊት ጥናት መካሄዱ ተቀባይነቱ እንዲጎላ አድርጎታል ………///……… የአርባ ምንጭ 2ኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ከመጀመሩ በፊት የአካባቢያዊና ማህበረሰባዊ ጉዳዮች ተፅእኖ ጥናት መከናወኑ ፕሮጀክቱ በማህበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖረው ማድረጉ ተገለፀ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የካሳ ጉዳዮች አስተባባሪ አቶ ኢዘዲን ሸምሱ እንደገለፁት የፕሮጀክቱ ግንባታ ከመጀመሩ በፊት በአካባቢው ሥነ ምህዳርና በማህበረሰቡ ላይ ሊፈጥር የሚችለው አወንታዊና አሉታዊ ተፅዕኖ እና ተፅዕኖዎችን እንዴት ማስቀረት እንደሚቻል ከዞን እስከ ቀበሌ ካሉ የመስተዳድር አካላት እና ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡ ግንባታው የሚካሄድበት ቦታ ለ140 ግለሰቦች ለቤት መስሪያነት በመመራቱና በውስጡም ስምንት መቃብሮች መኖራቸው በጥናቱ ስለተለየ ከዞን መስተዳደር፣  ቤት እንዲሰሩ ከተመሩ ግለሰቦች እና ከሟች ቤተሰቦች ጋር በመነጋገር መፍትሔ መገኘቱን ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የማስተላለፊያ መስመሩ ለማህበራዊ አገልግሎት በተሰጠ ቦታና በዞኑ አስተዳደር ህንፃ ላይ እንደሚያልፍ በጥናቱ በመረጋገጡ የሚዘረጋበት ቦታ እንዲቀየር መደረጉንም አቶ ኢዘዲን ጠቅሰዋል፡፡ በፕሮጀክቱ ላይ የተካሄደው ጥናት በኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ማረጋገጫ ተሰጥቶት እና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ወደ ትግበራ መገባቱንም ተናግረዋል፡፡ በፕሮጀክቱ ላይ ጥናትና ከማህበረሰቡ ጋር ውይይት ሳይደረግ ወደ ሥራ ቢገባ ኖሮ በማህበረሰቡ ተቀባይነት ላያገኝ ይችል ነበር ያሉት አስተባባሪው ይህም በግንባታ ሥራው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሊያሳድር እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ በፕሮጀክቱ አማካሪ ባዮሰን ፓወር ኩባንያ የአርባ ምንጭ 2ኛ ማከፋፈያ ጣቢያ የአካባቢና ማህበረሰባዊ ጉዳዮች እንዲሁም የጤናና የሥራ ላይ ደህንነት ባለሙያ አቶ ቤካን ዳምጠው በበኩላቸው ሥራ ተቋራጩ አካባቢውን የማይበክሉ ማሽነሪዎች እንዲጠቀም እና ለፕሮጀክቱ ግንባታ የዋሉ የተለያዩ ተረፈ ምርቶች በአግባቡ እንዲወገዱ ክትትል እየተደረገ ስለመሆኑም ገልፀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠ https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠ https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 7 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

photo content
+2

ለተቋረጠው ኃይል ጊዜያዊ መፍትሄ ተሰጥቷል .........///....... ትናንት በስርቆት ምክንያት የወደቀው የኮምቦልቻ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር  የብረት ምሰሶ በጊዜያዊነት በእንጨት ምሰሶ መተካቱን  በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ አንድ ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደገለፁት በኮምቦልቻ ከተማ አቅራቢያ በተፈፀመው ዝርፊያ የወደቀውን የብረት ታወር በእንጨት ምሰሶ ሲተካ የተፈታታውን ታወር ደግሞ በማጥበቅና የጎደሉ አካሎችን በማሟላት አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጓል። ለጊዜው በተከናወነው ጥገና  በኮምቦልቻ ከተማና አካባቢው፣ በደሴ ከተማና አካባቢው፣ በአቀስታ ከተማና አካባቢው እንዲሁም በዓለም ከተማና አካባቢው የተቋረጠው ኃይል ማምሻውን መመለሱን ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 7 ቀን 2017 ዓ.ም

ፕሮጀክቱ ከመተግበሩ በፊት ጥናት መካሄዱ ተቀባይነቱ እንዲጎላ አድርጎታል ………///……… የአርባ ምንጭ 2ኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ከመጀመሩ በፊት የአካባቢያዊና ማህበረሰባዊ ጉዳዮች ተፅእኖ ጥናት መከናወኑ ፕሮጀክቱ በማህበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖረው ማድረጉ ተገለፀ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የካሳ ጉዳዮች አስተባባሪ አቶ ኢዘዲን ሸምሱ እንደገለፁት የፕሮጀክቱ ግንባታ ከመጀመሩ በፊት በአካባቢው ሥነ ምህዳርና በማህበረሰቡ ላይ ሊፈጥር የሚችለው አወንታዊና አሉታዊ ተፅዕኖ እና ተፅዕኖዎችን እንዴት ማስቀረት እንደሚቻል ከዞን እስከ ቀበሌ ካሉ የመስተዳድር አካላት እና ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡ ግንባታው የሚካሄድበት ቦታ ለ140 ግለሰቦች ለቤት መስሪያነት በመመራቱና በውስጡም ስምንት መቃብሮች መኖራቸው በጥናቱ ስለተለየ ከዞን መስተዳደር፣  ቤት እንዲሰሩ ከተመሩ ግለሰቦች እና ከሟች ቤተሰቦች ጋር በመነጋገር መፍትሔ መገኘቱን ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የማስተላለፊያ መስመሩ ለማህበራዊ አገልግሎት በተሰጠ ቦታና በዞኑ አስተዳደር ህንፃ ላይ እንደሚያልፍ በጥናቱ በመረጋገጡ የሚዘረጋበት ቦታ እንዲቀየር መደረጉንም አቶ ኢዘዲን ጠቅሰዋል፡፡ በፕሮጀክቱ ላይ የተካሄደው ጥናት በኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ማረጋገጫ ተሰጥቶት እና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ወደ ትግበራ መገባቱንም ተናግረዋል፡፡ በፕሮጀክቱ ላይ ጥናትና ከማህበረሰቡ ጋር ውይይት ሳይደረግ ወደ ሥራ ቢገባ ኖሮ በማህበረሰቡ ተቀባይነት ላያገኝ ይችል ነበር ያሉት አስተባባሪው ይህም በግንባታ ሥራው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሊያሳድር እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ በፕሮጀክቱ አማካሪ ባዮሰን ፓወር ኩባንያ የአርባ ምንጭ 2ኛ ማከፋፈያ ጣቢያ የአካባቢና ማህበረሰባዊ ጉዳዮች እንዲሁም የጤናና የሥራ ላይ ደህንነት ባለሙያ አቶ ቤካን ዳምጠው በበኩላቸው ሥራ ተቋራጩ አካባቢውን የማይበክሉ ማሽነሪዎች እንዲጠቀም እና ለፕሮጀክቱ ግንባታ የዋሉ የተለያዩ ተረፈ ምርቶች በአግባቡ እንዲወገዱ ክትትል እየተደረገ ስለመሆኑም ገልፀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠ https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠ https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 6 ቀን 2017 ዓ.ም