ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 572 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 384 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 165 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 572 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 23 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 0، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -2، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 25.89‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.48‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 026 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 408 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 9.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 24 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 572
المشتركون
-224 ساعات
-37 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
በመንግስትና ግል አጋርነት የሚለሙ ስምንት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ተለይተዋል ……..///…….… በመንግስት እና በግል አጋርነት የሚለሙ ስምንት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች መለየታቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመንግሥት እና የግል አጋርነት መመሪያ ገለፀ። በመምሪያው የፀሐይና ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ሥራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ዘውዴ እንደገለጹት የኃይል ስብጥሩን በማሳደግ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋት በኃይል ማመንጨት ዘርፍ የግል አልሚዎች እንዲሳተፉ የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል፡፡ የግል ዘርፉ ኃይል ማመንጫ ገንብቶና ኃይል አመንጭቶ ለተቋሙ መሸጥ አዲስ አሰራር በመሆኑ የፕሮጀክቶችን አዋጭነት በተመለከተ ተቋሙ የግል ዘርፉን ለማሳተፍና ለማበረታታት ብሎም ፕሮጀክቶቹን ሥራ ላይ ለማዋል የሚያስችል ጥናት በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን መሰራቱን ተናግረዋል፡፡ በዚህም በመንግስትና በግል አጋርነት የሚለሙ ስምንት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች መለየታቸውንና ከእነዚህ ውስጥ የአራቱ ማለትም ጋድ 1 እና 2፣ ዲቼቶ እና ወራንሶ ጥናታቸው መጠናቀቁንም አብራርተዋል፡፡ በጥናት የተለዩትን የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች ለማልማት እ.ኤ.አ በ2019 ግንቦት ወር ጨረታ መውጣቱን  አቶ አሸናፊ አስታወሰዋል፡፡ ይሁንና በወቅቱ የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት ዋስትና በመጠየቁ፣ በውጭ ሀገር ፕሮጀክቱን የተመለከተ የገንዘብ ዝውውር ለማከናወን አካውንት የመክፈት ፈቃድ በመጠየቁ እና ይህንን ለማስፈጸም የሚያስችል አዲስ መመሪያ በማስፈለጉ የግል አልሚዎቹ ወደ ተግባር አለመግባታቸውን ጠቁመዋል፡፡ አሁን ላይ ግን በሀገሪቱ እየተተገበረ በሚገኘው የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ላይ መንግስት ለፕሮጀክቶቹ ትኩረት በመስጠቱ፣ የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት ዋስትና በመተግበሩ እና የውጭ ምንዛሬ አካውንት ለመክፈት አስቻይ ሁኔታ በመኖሩ ፕሮጀክቶቹን ወደ ትግበር እንዲገቡ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ጋድ 2 እና ወራንሶ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በመንግስት እና በግል አጋርነት ለማልማት ጨረታ ወጥቷል ብለዋል፡፡ ሁለቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች 225 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም እንዳላቸውና ፕሮጀክቶቹን ለማጠናቀቅ 200 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የኃይል ስብጥሩን በማሳደግ የኤሌክትሪክ ተደራሽነቱን ከማስፋትም ባሻገር መንግስት ፕሮጀክቱን በራሱ የፋይናንስ አቅም ቢሰራ ሊያወጣ የሚችለውን ፋይናንስ በግል አልሚው በመሸፈን ፕሮጀክቶቹን መተግበር የሚያስችለው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹ በመንግስትና ግል አጋርነት ሲለሙ በተሻለ ጥራትና ጊዜ ለማጠናቀቅ ዕድል ይፈጥራል ያሉት ሥራ አስኪያጁ ከአዋጭነት ጥናቱ ጀምሮ እስከ ፕሮጀክቱ ትግበራ የእውቀት ሽግግር እንዲኖር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ከስምንቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች እስከ 750 ሜጋ ዋት ለማመንጨት ዕቅድ ተይዟል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 14  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

በራስ ኃይል የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አሳሰቡ …….///…… በራስ ኃይል የሚከናወኑ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት ማጠናቀቅ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ፡፡ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ከተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በራስ ኃይል የሚከናወኑ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ያሉበትን ደረጃ ገምግመዋል፡፡ ኢንጂነር አሸብር በዚሁ ወቅት እንዳሉት በተቋሙ የራስ ኃይል የሚከናወኑ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የተቋሙ የመፈጸም አቅም የሚገነባባቸው ከመሆናቸውም በተጨማሪ በጥራትና በጊዜ በማጠናቀቅ በዘርፉ ተወዳዳሪ ለመሆን ዕድል የሚሰጥ ነው ፡፡ የተቋሙ አብዛኛው በጀት በፕሮጀክቶች ላይ እንደሚውል የጠቆሙት ኢንጂነር አሸብር በሥራ ሂደት እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች ላይ ተወያይቶ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ እና አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ውይይቱ ማስፈለጉን ተናግረዋል፡፡ በራስ ኃይል በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እንዲሁም በተቀመጡ ዝርዝር መስፈርቶች መሰረት እንዲጠናቀቁ ለማድረግ በሥራው ላይ የሚሳተፉ አካላት ተቀናጅተው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ውድነህ የማነ በበኩላቸው በተቋሙ በራስ ኃይል መምሪያ አስር የሚሆኑ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፍያ ጣቢያዎች ግንባታ በመካሄድ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ውይይቱ በራስ ኃይል የሚሰሩ ፕሮጀክቶችን አፈጻጸም በመገምገም ከአስተሳሰብ ጀምሮ አሰራሮችን በመለወጥ እንዲሁም ፕሮጀክቶችን አቅዶ ከመፈፀም፣ ከፋይናንስ እና ከዕቃ አቅርቦት በተያያዘ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች በመቅረፍ አፈጻጸማቸውን ለማሻሻል እንደሚያግዝ ገልጸዋል፡፡ ቀደም ሲል የራስ ኃይል ግንባታና ማማከር የሥራ ክፍሎች ለየብቻ የነበሩ መሆኑን ያስታወሱት አቶ ውድነህ በመዋቅሩ ሁለቱ ክፍሎች በአንድ ላይ መሆናቸው ከዲዛይን ጀምሮ የግንባታ ሥራዎች በተቀናጀ መልኩ እንዲከናወኑ ያስችላል ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ የኢንጂነሪንግ ክፍሉ እንደ ተቆጣጣሪ ሳይሆን የኮንስትራክሽን ኃይሉ የሚፈልገውን ቴክኒካዊ ድጋፍ ለመስጠት ዕድል የሚሰጥ በመሆኑ ፕሮጀክቶች በጥራት፣ በጊዜና በተያዘላቸው በጀት ለማጠናቀቅ ይረዳል፡፡ በውይይቱ የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም በመገምገም የሚስተዋሉ ችግሮች ተለይተው የሚፈቱበት ቀጣይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ጠቁመዋል፡፡ ፕሮጀክቶችን በጊዜ ማጠናቀቅ ለተቋም ብሎም ለሀገር የሚኖረውን ሚና ከግምት በማስገባት ሁሉም ተቀናጅቶ መስራት እንደሚኖርበትም አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 13  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ጣቢያው የአካባቢውን የኃይል ፍላጎት ለመመለስ ችሏል ………///………. በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሆለታ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ወደስራ ያስገባቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች የተሟላ ኃይል  ለማቅረብ ምቹ ሁኔታ መፍጠራቸውን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ጥላሁን አዘዘው እንደተናገሩት የሆለታ ማከፋፈያ ጣቢያ ለአቃቂ፣ ሰበታ እና ሱሉልታ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም ለአካባቢው ነዋሪዎችና በኢንቨስትመንት ዘርፍ ለተሰማሩ አምራቾች በተሟላ መልኩ ኃይል በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡ ጣቢያው የተገጠመለት ጂ አይ ኤስ መቆጣጠሪያ፣ የስካዳ ሲስተም እና ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶች ጣቢያው ኃይል ሳይቆራረጥ ደንበኞች ጋር ለማድረስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳበረከቱ የጣቢያው የጥገና ባለሙያ ተዳቻ ገናሌ ተናግረዋል። የጣቢያው መሳሪያዎች የኃይል መቋረጥ ሲኖር ችግሩ የደረሰበት መስመር እና የችግሩን ዓይነት እንዲሁም የችግሩን መጠን በመለየት መረጃን በቀላሉ መልሶ ለመጠገን እንደሚያግዝ አስረድተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 13  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

በአፈጻጸም ላይ የሚታዩ ችግሮችን በመፍታት ፕሮጀክቶችን በታቀደላቸው ጊዜ ማጠናቀቅ ይገባል፤ ……..///….… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ፕሮጀክቶችን በታቀደላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ያለመ ወይይት ከሥራ ተቋራጮችና አማካሪዎች ጋር አካሂዷል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት በሥራ ተቋራጮች የአፈጻጸም ድክመት እንዲሁም ውስጣዊና ውጫዊ ችግሮች ምክንያት በሚጓተቱ ፕሮጀክቶች ምክንያት ተቋሙ ለአላስፈላጊ ወጭና ለተደጋጋሚ የሕዝብ ቅሬታ እየተዳረገ ነው። ተቋሙ ከፕሮጀክቶች አፈጻጸም ጋር በተያያዘ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት እንዲሁም የክትትልና ቁጥጥር ሥርዓቱን በማጠናከር የፕሮጀክቶችን አፈጻጸም ለማሻሻል የመዋቅር ማሻሽያ ጭምር ማድረጉን ጠቁመዋል። በግንባታ ላይ የሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ፕሮጀክቶችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ ተቋሙ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዷለም ሲዓ በበኩላቸው ውይይቱ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም ላይ የሚታዩ ችግሮችን ምንጭ በመለየት መፍትኄዎችን ለማስቀመጥ እና አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ያለመ ነው ብለዋል። ውይይቱ በግንባታ ላይ ያሉትን ፕሮጀክቶች በታቀደላቸው ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ ከማገዙም በተጨማሪ በቀጣይ ግንባታቸው ለሚጀመሩ ፕሮጀክቶች ግብዓት የሚገኝበት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ የእቃ አቅርቦት፣ የጸጥታ ችግር፣ የካሳ ክፍያ፣ ስርቆት እና ከፋይናንስ ጋር የተያያዙ ችግሮች ለፕሮጀክቶች መዘግየት ምክንያት መሆናቸውን ሥራ ተቋራጮቹ በውይይቱ ላይ አንስተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በሰጡት የማጠቃለያ ሃሳብ በሁሉም ወገን ለፕሮጀክቶቹ መዘግየት ምክንያት የሆኑ ችግሮችን በመቅረፍ ቀሪ ሥራዎችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡ ሥራ ተቋራጮች አደረጃጀታቸውን በማጠናከር፣ የሰው ኃይል እና የግብዓት አቅርቦታቸውን በማሻሻል ፕሮጀክቶችን በወቅቱና በተያዘላቸው በጀት ለማጠናቀቅ መስራት እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል፡፡ በቀጣይ መሰል ውይይቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተጠቁሟል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የታዳሽ ኃይል ልማት ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ የሚያስችል ስምምነት ተደርጓል ……..///….… ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ንግድ መድን ኤጀንሲ የታዳሽ ኃይል ልማት ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ የሚያስችላቸውን የመግ
የታዳሽ ኃይል ልማት ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ የሚያስችል ስምምነት ተደርጓል ……..///….… ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ንግድ መድን ኤጀንሲ የታዳሽ ኃይል ልማት ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት አድርገዋል። ስምምነቱ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች የፋይናንስ አቅርቦት ስጋት እንዳያጋጥማቸው ለባለሀብቶች ዋስትና ለመስጠት እና ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በዘርፉ ያላቸውን እምነት ለማሻሻል የሚያስችል እንደሆነ በስምምነቱ ወቅት ተነግሯል። ስምምነቱ የፋይናንስ ስጋቶችን በመቀነስ የአልሚዎችን የክፍያ ደህንነት እና ወሳኝ የሆኑ መንግስታዊ  ተቋማትን ወቅታዊ ክፍያዎች ለማረጋገጥ እንደሚረዳም ተመላክቷል። የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት ስምምነቱ ክፍያዎችን በወቅቱ ከማሳለጥ ባለፈ የፋይናንስ አደጋዎችን ለመቀነስ፣ የኃይል ግዥ ስምምነቶችን ተዓማኒነት ለማረጋገጥ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብድር ብቃትን ለማሻሻል ያግዛል። ከዚህ በተጨማሪ በሀገሪቱ እያደገ ባለው የታዳሽ ሃይል ገበያ ላይ ተጨማሪ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እንደሚረዳ መገለፁን ካፒታል ጋዜጣ በማህበራዊ የትስስር ገፁ ዘግቧል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 12 ቀን 2017 ዓ.ም

የወልቂጤ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን የማዘምን ስራ እየተሰራ ነው ………///………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወልቂጤ ባለ 230  ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያን የማዘመን ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው ሥራ ኃላፊ ሙጀረብ የኑስ ገልፀዋል። ኃላፊው እንደገለፁት በማከፋፈያ ጣቢያው ዘመናዊ የጂአይኤስ መቆጣጠሪያ ቅየራ እና ወረቀት አልባ የኦፕሬሽን ሥራዎች ክትትል ሥራዎች ተጀምረዋል። ማከፋፈያ ጣቢያው ተጨማሪ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚፈልጉ ደንበኞችን ለማስተናገድ የሚያስችል አቅም እንደተፈጠረለት ገልፀዋል። እንደኃላፊው ገለፃ ማከፋፈያ ጣቢያው 360  ሜጋ ዋት የመጫን አቅም ያለው ቢሆንም አሁን ላይ ለደንበኞች እያቀረበ ያለው 158 ሜጋ ዋት ብቻ በመሆኑ ተጨማሪ ደንበኞችን እየጠበቀ ይገኛል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው ከሰኮሩ ማከፋፈያ ጣቢያ በ230 ኪሎ ቮልት ኃይል ተቀብሎ ለሰበታ፣ ለሆሳዕናና ለወሊሶ ማከፉፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም ለጉራጌና አካባቢው ማህበረሰብ ኃይል ያቀርባል። ከዚህ በተጨማሪም ጣቢያው ለሊፍ የተፈጥሮ ውሃና ለዘቢዳር ቢራ ፋብሪካዎች  እንዲሁም ለወልቂጤ ዬኒቨርስቲ ኃይል እያቀረበ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ ጣቢያውን በሙሉ አቅሙ ለመጠቀም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ቢሮ እና ከማዕከላዊ  ጉራጌ ዞን  አስተዳደር ጋር ጋር ምክክር እየተደረገ  እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 10  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የደሴ ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ በተያዘለት መርሃግብር እየተከናወነ ነው ………///………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ በተያዘለት መርሃግብር እየተከናወነ  መሆኑን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ተናገሩ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ዳንኤል ተክለማርያም እንደተናገሩት ተቋሙ ሁለት 63 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች እንዲሁም 6 ባለ 33 ኪሎ ቮልት እና 10 ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ያሉት የማከፋፈያ ጣቢያ በደሴ ከተማ እየገነባ ይገኛል፡፡ 1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር አጠቃላይ በጀት ተይዞለት እየተገነባ ያለውን ፕሮጀክት በተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ እያከናወነው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ግንባታውን እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2019 ለማጠናቀቅ እቅድ ተይዞ እየተሰራ ነው ያሉት አቶ ዳንኤል የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ሲጠናቀቅ ለደሴ ከተማ እና ለአከባቢው አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ያደርጋል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ትራንስፎርመሮችን በቦታቸው የማስቀመጥ ሥራ ተከናውኖ ለመቆጣጠሪያ ክፍል ህንፃ ግንባታ የሚሆን የመሬት ቆረጣ ሥራ በመከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ ዳንኤል ገለጻ የደሴ ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ከፍተኛ የመሬት ቆረጣ የሚፈልግ በመሆኑ የቆረጣ ሥራዉን በፍጥነት ለማከናወን ተጨማሪ ማሽነሪዎችን ወደ ሳይት ለማስገባት ታቅዷል፡፡ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ለደሴ ከተማና አካባቢው የሚኖረውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ ከግምት በማስገባት የመስተዳድር አካላት እና ሕብረተሰቡ ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ እያደረጉ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ ለ94 ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመው ሥራው እየሰፋ ሲሄድ ተጨማሪ የህብረተሰብ ክፍሎችን እንደሚያሳትፍ ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 7  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

ፕሮጀክቱ የወረዳውን የኤሌክትሪክ ኃይል ጥያቄ የሚመልስ ነው ……..///……… የሽግዳን ባለ 230/132/33 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት የሰላማጎ ወረዳና የአካባቢው ነዋሪዎችን የዘመናት የኤሌክትሪክ ኃይል ጥያቄ እንደሚመልስ የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ፡፡ የወረዳው አስተዳዳሪ ዋና አማካሪ አቶ ስምዖን ኤርሚያስ እንደገለፁት የሰላማጎ ወረዳ መቀመጫ በሆነችው ሐና ሙርሲ ከተማ ጨምሮ በወረዳው ሥር የሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ባለመሆናቸው በአካባቢው ማህበረሰብ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ ይገኛል፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል ባለመኖሩ ባለሀብቶች በአካባቢዉ ከማልማት ይልቅ ወደ ሌላ ቦታ እንዲሸሹ እያደረጋቸው እንደሆነና መዋዕለ ነዋያቸውን ለማፍሰስ ፈቃድ የወሰዱ ባለሃብቶችም ወደ ሥራ አለመግባታቸውን ነው የተናገሩት፡፡ የሽግዳን ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ግንባታ ከተጀመረ ወዲህ ባለሃብቶች በአካባቢው ለመሰማራት ጥያቄ ማቅረባቸውን የገለፁት አማካሪው ይህም በቀጣይ አካባቢውን የኢንቨስትመንት እና የቱሪዝም እንቅስቃሴ እንደሚያነቃቃ አመልክተዋል። እንደ አማካሪው ገለፃ የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ለወረዳው ነዋሪዎች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም ባለፈ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በአካባቢው የሚገኙ ወጣቶችን አደራጅቶ በተለያዩ ዘርፎች ለማሰማራት ያግዛል፡፡ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ በመፋጠን ላይ የሚገኝ ሲሆን በሥራው ላይ ችግር እንዳያጋጥም መስመሩ በሚያልፍባቸው አካባቢዎች አደረጃጀት በመፍጠርና በወረዳ ደረጃም አራት የቴክኒክ ቡድኖችን በማዋቀር ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ማህበረሰቡን እስከ አሁን ከነበረበት ጨለማ የሚያወጣ በመሆኑ የአካባቢው ነዋሪ እና ወረዳዉ ለፕሮጀክቱ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አማካሪው አረጋግጠዋል፡፡ የሰላማጎ ወረዳ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ስር ከሚገኙ ስድስት ወረዳዎች መካከል አንዱ ሲሆን የወረዳው መቀመጫ የሆነችው ሐና ሙርሲ ከተማም ከአዲስ አበባ በ880 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 5  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ሁለት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ለማልማት ዝግጅት ተደርጓል ……..///……. በሶማሌ ክልል ጋድ እና በኦሮሚያ ክልል ወራንሶ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በመንግስት እና በግል አጋርነት ለማልማት ጨረታ ወጥቷል፡፡ ሁለቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች 225 ሜጋ ዋት ኃይል በማመንጨት የኃይል ስብጥሩን ለማስፋት እንደሚያስችል ተስፋ ተጥሎበታል፡፡ ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የኃይል አማራጮች አቅም ተጠቅማ የኃይል ፍላጎቷን ለማሟላት የግል አልሚዎች በዘርፉ እንዲሰማሩ የሚያስችል የመንግስትና የግል አጋርነት የሕግ ማዕቀፍ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ ከአሁን ቀደም በመንግሥት እና በግል አጋርነት ማዕቀፍ ከንፋስ ኃይል 300 ሜጋ ዋት ለማመንጨት አሜአ ፓወር ከተሰኘ የተባበሩት አረብ ኤመሬቶች ኩባንያ ስምምነት በመፍጠር ወደ ሥራ መገባቱ ይታወቃል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 04 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

photo content

የቲርጋ ማከፋፈያ ጣቢያን ግንባታ  ለማፋጠን እየተሰራ ነው ………///……… ከአዲስ አበባ በ1 ሺህ 70 ኪሎ ሜትር ርቀት በደቡብ ኦሞ ዞን ኛንጋቶም ወረዳ ላይ እየተገነባ  የሚገኘውን የቲርጋ ባለ 132/33 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራን ለማፋጠን እየተሰራ መሆኑን የብሔሪዊ  የኤሌክትሪክ ግሪድ ደቡባዊ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ገለፀ። የጣቢያው ሳይት ኢንጂነር አቶ ደረጀ ክፍሌ እንደገለፁት የግንባታ ግብዓቶች በቅርበት ባለመገኘታቸውና በአካባቢው ባለው የአየር ፀባይ ምክንያት ሥራዎችን በመርሃ ግብሩ መሰረት ማከናወን አልተቻለም። ሥራ ተቋራጩ ለግንባታ ሥራ የሚያስፈልጉትን ጠጠር ከ150 ኪሎ ሜትር ፣ አሸዋ ከ250 ኪሎ ሜትር እንዲሁም ውሃ ከ80 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እያጓጓዘ እንደሚጠቀም የሳይት ኢንጂነሩ አስረድተዋል። እንደ አቶ ደረጀ ገለፃ በፕሮጀክቱ ቦታ ርቀት ምክንያት የተስተዋለው የግንባታ አቅርቦት ችግር እና በሙቀቱ ምክንያት በማሽነሪዎች ላይ የሚያጋጥሙ ብልሽቶች በሥራው ላይ መስተጓጎል ፈጥረዋል። በአካባቢው ያለው ሙቀት በኮንክሪት መሠረት ሥራዎች እና በማሽነሪዎች ብልሽት ላይ እያሳደረ ያለውን ችግር ለመቅረፍ የምሽት ሥራ መጀመሩን የተናገሩት አቶ ደረጀ ለሥራው የሚያስፈልገውን በቂ የሠው ኃይልም ከሌላ ቦታ በማምጣት የማሟላት ሥራ እየተከናወነ ነው ብለዋል። የፕሮጀክቱ ሥራ ተቋራጭ ሀዮሰንግ ሄቪይ ኢንደስትሪስ ኮርፖሬሽን የጥራት ቁጥጥርና ማረጋገጥ ሥራ አስኪያጅ አቶ አዲስዓለም ማሩ በበኩላቸው የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ቢጓተትም በአሁኑ ወቅት የሠራተኞች መኖሪያ ቤት፣ የመቆጣጠሪያ ክፍሉ እና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች መትከያ የመሰረት ቁፋሮና የኮንክሪት ሙሊት ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ አብራርተዋል። የጣቢያው አጠቃላይ አፈፃፀም 8 ነጥብ 7 እንዲሁም የሲቪል ግንባታ ሥራው 3 በመቶ እንደተከናወ የጠቆሙት አቶ አዲስዓለም ሥራውን ለማፋጠን ተጨማሪ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሙያዎችን የማሳተፍና ተጨማሪ ማሽነሪዎችን ወደ ሳይቱ የማስገባት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። በፕሮጀክቱ የሳይት 2 ሥራ አስኪያጅ አቶ አርጋው ታዲ እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ሲጠናቀቅ በአካባቢው የመስኖ ልማትን ለማስፋፋት፣ በዙሪያው ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችና በግንባታ ላይ ለሚገኘው የስኳር ፋብሪካ ኃይል ለማቅረብ እንዲሁም ከፋብሪካው ተረፈ ምርት የሚመነጨውን ብሔራዊ ግሪድ ለማስገባት ያስችላል። ጣቢያው አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ጥምር ገቢ መስመር፣ አንድ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመር እና አምስት ባለ 33 ኪሎ ኪሎ ወጪ መስመሮች እንደሚኖሩት ተናግረዋል። በግንባታ ግብዓቶች እጥረት ምክንያት በወቅቱ ያልተከናወኑ ሥራዎችን ለማፋጠን ሥራ ተቋራጩ ትኩረት ሠጥቶ እየሰራ እንደሆነም አቶ አርጋው ጠቅሰዋል። የማከፋፈያ ጣቢያው የግንባታ ሥራ ከ8 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የሆነ በጀት ተይዞለት እየተከናወነ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም