en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 679 subscribers, ranking 8 043 in the Technologies & Applications category and 2 176 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 679 subscribers.

According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 111 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.35%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.94% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 974 views. Within the first day, a publication typically gains 2 500 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 679
Subscribers
-124 hours
-157 days
+11130 days
Posts Archive
photo content
+3

photo content
+9

በሀሳብ ልዕልና እንጂ በጠመንጃ ሀገረ መንግስት አይነባም ………..///……….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች የሀሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና በሚል መሪ ሀሳብ በሀገራዊና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በተቋሙ ዋና መስሪያ ወይይት አካሂደዋል፡፡ በውይይቱ ላይ የተቋሙ ሠራተኞች የኑሮ ውድነትን፣ ተንቀሳቅሶ ለመስራት ያለውን የጸጥታ ችግር እና የሠራተኛውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት እየተሰሩ ካሉ ሥራዎች ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን አንስተዋል፡፡ ከኑሮ ውድነት ጋር ተያይዞ ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የተቋሙ የፋይናንስ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደተናገሩት የኑሮ ውድነቱ ከዓለም አቀፋዊ የዋጋ ግሽበት ጋር የሚያያዝ በመሆኑ መንግስት ችግሩን ለመቅረፍ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ ጨምሮ በልማት ትሩፋት ሥራዎች ገበያውን የማረጋገት ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡ ከጸጥታ ጋር ተያይዞ ለተነሱት ጥያቄዎች ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸበር ባልቻ በሰጡት ምላሽ አብዛኛዎቹ የፀጥታ መደፍረስ ችግሮች ከነጠላ ትርክቶች የሚነሱ በመሆኑ ለሀሳብ ልዕልና ቦታ አልተሰጠውም ነበር፡፡ በመሆኑም መንግስት የዜጎችን ሠላምና ደህንነት ለማረጋገጥ ሀገረዊ ምክከር ኮሚሽን ከማቋቋም አንስቶ በጠመንጃ ሳይሆን በሀሳብ ልዕልና እንጂ ላይ የተመሰረተ ሀገረ መንግስት ለመገንባት የተያዩ ጥረቶችን እያደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡ ለተፈጠሩት የጸጥታ ቸግሮች መፍትሄ ለማስገኘት የሚደረገው ጥረት የሁሉንም ተሳትፎ የሚፈልግ በመሆኑ ሁሉም ከመንግስት ጎን እንዲቆም ጠይቀዋል፡፡ የመኖሪያ ቤት ችግርን በተመለከተ ዋና ሥራ አስፈፃሚው በሰጡት ምላሽ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመነጋገር የተጀመሩ ሥራዎች እንዳሉ በመጠቆም ጥያቄው መፍትሔ እስኪያገኝ ድረስ ከሚመለከተው አካላት ጋር በቅርበት መስራቱን እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 09 ቀን 2017 ዓ.ም

ሠራተኛው በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ ግልፅ ግንዛቤ በመጨበጥ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀረበ ……...///…….. የመንግስትን ፖሊስ የሚያስፈጽሙ ሠራተኞች በመላው ሀገሪቱ በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ ግልፅ ግንዛቤ በመጨበጥ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸበር አሸበር ባልቻ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ባካሄዱት ውይይት ማጠቃለያ ላይ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት በኮቪድ፣ በዓለም የኢኮኖሚ ቀውስ፣ በእርስ በእርስ ግጭት እና በመሳሰሉት ችግሮች ውስጥ ሆና ዕድገት አስመዝግባለች፡፡ የተመበዘገበው ዕድገት ትሩፋቶቸና የመጣው ለውጥ ሀገራችን የገጠማትን ተግዳሮቶች አልፋ መሄድ እንደምትችል ከማሳየት ባለፈ ለውጡ በተቋሙ በግልጽ የሚታይ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ የተቋሙ ሠራተኞች ከጨለምተኛ አመለካከት ወጥተው ትክክለኛ መረጃ በመያዝ ለአላስፈላጊ ነጣለ ትርክት ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከለውጡ በፊት ምን ደረጃ ላይ እንደነበር የሚዘጋ አይደለም ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከለውጡ በኋላ በምን ያህል መስዋትነት እና ቁርጠኛ አመራር አሁን ላለበት ደረጃ መብቃቱ ተጨባጭ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ይሁንና ተቋሙ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም እና መዘግየት የሚያጋጥሙትን ከፍተቶች ለማስወገድ የሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች በትኩረት እንዲሰሩ አቅጣጫ መቀመጡን ገልፀዋል፡፡ ስለሆነም ሠራተኞች የሚመለከቷቸውን የብልሹ አሰራር ክፍተቶች የሚያሳዩ ማስረጃዎችን በመያዝ ድርጊቱን እንዲዋጉ ኢንጂነር አሸብር ጠይቀዋል፡፡ በውይይቱ ከሠራተኞች የተነሱትን የተለያዩ ጥያቄዎች ዋና ሥራ አስፈጻሚው እና ሌሎች የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ምላሽ ሰጥተውባቸዋል ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች ካካሄዱት ውይይት ጎን ለጎን የደም ልገሳ አካሂደዋል፡፡ የደም ልገሳ መርሃግብሩ በተለያዩ ምክንያቶች ደም ለሚያስፈልጋቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲውል ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡ መርሃ ግብሩን አስመልክቶ ንግር ያደረጉት በደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት የትምህርት እና የቅስቀሳ ባለሙያ ሲስተር አሰጋሽ ጎሳ እንደተናገሩት ደም በፋብሪካ የማይመረት በመሆኑ በደም አጦት ማንም ሰው ህይወቱን ሊያጣ አይገባም፡፡ ሠራተኛው የወገን ደራሽነቱን ደም በመለገስ በተግባር ማሳየት እንደሚገባው የተናገሩት ባለሙያዋ ደም በለገስ ከኮሌትሮል፣ ከደም ውስጥ የብረት መጠን ክምችት፣ ከካንሰርና ከሌሎች በሽታዎች የመታደግ የጤና ጠቀሜታዎች እንዳሉት አስረድተዋል፡፡ ደም የሚሞት እና የሚያረጅ እንዲሁም የሚተካ በመሆኑ በሚተካ ደም የማይተካ የሰው ህይወት ልናድንበት ይገባል ብለዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 09 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

የተቋሙ ሠራተኞች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት በማካሄድ ላይ ናቸው ........///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች የሀሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና በሚል መሪ ሀሳብ በሀገራዊና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በተቋሙ ዋና መስሪያ ወይይት ማካሄድ ጀምረዋል። የውይይት መድረኩን የከፈቱት የኢንጂነሪንግ ዘርፍ ሥራ አሰፈጻሚ አቶ ውድነህ የማነ የተቋሙ ሠራተኞች መንግስት በሚሰራቸው ሥራዎች ላይ ግልፅ መረጃ ሊኖራቸው ይገባል። በመድረኩ ላይ የህልም ጉልበት ለእምርታዊ  እድገት በሚል በመንግስት የተዘጋጀው ሰነድ በንባብ ቀርቧል። በሰነዱ ላይ የሚደረገው ውይይት እንደቀጠለ ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 09 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የወጣ ወጣት በተአምር ህይወቱ ተርፏል …….///……. በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ የወጣ ወጣት ኃይል እንዲቋረጥ ማድረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታውቋል፡፡ በዘርፉ የደቡብ ሁለት ሪጅን እንደገለፀው ወጣቱ ዛሬ ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ከወላይታ ሶዶ ወደ ሳውላ በሚሄደው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ወጥቶ አልወርድም በማለቱ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሚገኙ ጎፋ ዞን፣ አሪ ዞን፣ ባስኬቶ ዞን እና ኦሞ ዞን ሙሉ በሙሉ እንዲሁም ጋሞ ዞን በከፊል ከሦስት ሰዓታት በላይ ኃይል ተቋርጦ ቆይቷል፡፡ በምን ምክንያት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ እንደወጣ ያልታወቀው ወጣት በአካባቢው ሽማግሌዎችና የመስተዳድር አካላት ቢለመንም ለመውረድ ግን አስቸግሮ እንደነበር መምሪያው ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለሙያዎች ኃይል በማቋረጥ ወጣቱ ሳይጎዳ በገመድ አስረው በማውረድ በተአምር ህይወቱን ታድገዋል፡፡ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የሚያስተላልፉት የቮልቴጅ መጠን ከፍተኛ በመሆኑ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መምሪያው አሳስቧል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 06  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

በማከፋፈያ ጣቢያው መቆጣጠሪያ ላይ የተከናወነው ጥገና ተጠናቋል …….///……… በአዲስ አበባ ጎፋ ማከፋፈያ ጣቢያ ችግር አጋጥሞት የነበረውን የከረንት ትራንስፎርመር መቆጣጠሪያ የመቀየር ሥራ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 3 ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታውቋል፡፡ ችግሩ እስኪቀረፍ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት ስለጠበቁ መምሪያው አመስግኗል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 06  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

በሀረር እና ጅግጅጋ ከተሞችና አካባቢያቸው የተቋረጠው ኃይል ተመልሷል .......///....... ከድሬዳዋ 3 ወደ ሀረር የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የገጠመው
በሀረር እና ጅግጅጋ ከተሞችና አካባቢያቸው የተቋረጠው ኃይል ተመልሷል .......///....... ከድሬዳዋ 3 ወደ ሀረር የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የገጠመው ችግር ተጠግኖ አካባቢዎቹ ዳግም ኃይል ማግኘታቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የምስራቅ አንድ ሪጅን የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታውቋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 06 ቀን 2017 ዓ.ም

ቡድኑ ሁለተኛ ሽንፈት አስተናግዷል ........///...... የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን ከልደታ ክፍለ ከተማ ጋር ባደረገው ጨዋታ አንድ ለባዶ በሆነ ውጤት ተረቷል። ዛሬ ከጠዋቱ 3 ሰዓት በተከናወነው ጨዋታ ሳሮን ሰመረ ብቸኛዋን የማሸነፊያ ጎል ለክለቧ አስቆጥራለች። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በኳስ ቁጥጥር የበላይነት ወስዶ ቢጫወትም ጎልን ከመረብ ማዋሀድ ሳይችል ቀርቷል። በአንፃሩ የመከላከል አጨዋወት ስልት የተከተሉት ልደታዎች ያገኟትን ብቸኛ የግብ አጋጣሚ ወደ ጎል በመቀየር  ሶስት ነጥብ ማግኘት ችለዋል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ4ኛ ሳምንት መርሃ ግብር በመጪው ህዳር 10 ቀን 2017 ዓ.ም ከሀምበርቾ  ክለብ ጋር የሚጫወት ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 06 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

በሀረር እና ጅግጅጋ ከተሞችና አካባቢያቸው የተቋረጠውን ኃይል ለመመለስ ርብርብ እየተደረገ ነው .......///....... ከድሬዳዋ 3 ወደ ሀረር የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በገጠመ ችግር ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የምስራቅ አንድ ሪጅን የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ እንደገለፀው ከድሬደዋ ቁጥር ሦስት ወጥቶ ወደ ሀረር እና ጅግጅጋ ከተሞች በሚሄደው መስመር የታወር መገናኛ (Jumper) ቦታ ላይ ችግር አጋጥሟል። በዚህ የተነሳ ከማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል የሚያገኙት የሀረር እና ጅግጅጋ ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም ከጣቢያዎቹ ኃይል የሚያገኙ የምስራቅ ኢትዮጵያ ከተሞች ኃይል መቋረጡን መምሪያው አስታውቋል። የተቋረጠውን መስመር ለመጠገን የጥገና ባለሙያዎች ርብርብ እያደረጉ በመሆኑ በተጠቀሱት አካባቢዎች ያሉ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ መምሪያው ጠይቋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 06 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ቋሚ ኮሚቴው የይርጋለም ቁጥር አንድና ሁለት የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ጎበኘ ……..///……… በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የይርጋለም ቁጥር አንድ እና ሁለት የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያዎችን ጎብኝቷል። ቋሚ ኮሚቴው ያደረገው ጉብኝት በጣቢያው የታዩ የኦዲት ግኝቶችን መሠረት ያደረገ የእርምት እርምጃ ስለመውስዱ እንዲሁም በኦዲት ግኝቱ ወቅት የተቀመጡ አቅጣጫዎች ተግባራዊ ስለመደረጋቸው በመስክ ተገኝቶ ለመገምገም ያለመ ነው። የቋሚ ኮሚቴው አባላት ስለማከፋፈያ ጣቢያዎቹ አሰራር እና ተቋሙ የኃይል ፍሰቱን የሚቆጣጠርበትን ሥርዓት በተመለከተ በጣቢያው ኃላፊዎች ገለፃ የተደረገላቸው ሲሆን ጣቢያዎቹን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ እና የቡድኑ አስተባባሪ የተከበሩ ወ/ሮ አራሬ ሞሲሳ ከኦዲት ግኝቱ ጋር ተያይዞ የንብረት አያያዝ፣ የካሳ ክፍያ እና ለአካባቢው ማህበረሰብ የተሰጠ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስለመኖሩ እና የማስተካከያ እርምጃዎች ስለመወሰዳቸው በመስክ ምልከታው ወቅት አንስተዋል። ተቋሙ በፕሮጀክቶች ላይ የሚታየውን የፋይናንስና የግብዓት እጥረት በመቅረፍ የሀገር ሀብትን ከብክነት ለመጠበቅ በግኝቶቹ ላይ ማስተካከያና የእርምት እርምጃ መውሰድ እና ሊያሰሩ የሚያስችሉ የአሰራር ስርዓቶችን መዘርጋት እንደሚያስፈልገው ምክትል ሰብሳቢዋ አሳስበዋል። ተቋሙ የፕሮጀክቶች ግንባታ ሥራን በሚመለከት ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ በመስራት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የጀመረውን ቅንጅታዊ አሠራርን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባው አመልክተዋል። ቋሚ ኮሚቴው የሀዋሳ ቁጥር አንድ እና ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያዎችንም ጎብኝቷል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 06 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://
ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 05  ቀን 2017 ዓ.ም