uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 560 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 357-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 160-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 560 obunachiga ega bo‘ldi.

26 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 27 ga, so‘nggi 24 soatda esa -7 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 26.05% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.01% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 053 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 491 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 8 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 27 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 560
Obunachilar
-724 soatlar
+147 kunlar
+2730 kunlar
Postlar arxiv
ሪጅኑ በሚያከናውናቸው ሥራዎች ላይ እያጋጠሙ የሚገኙ ችግሮችን ለመፍታት እየተሰራ ነው ....//.... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ሪጅን በሚያከናውናቸው የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች ላይ እያጋጠሙ የሚገኙ ችግሮችን ለመፍታት እየተሰራ መሆኑን በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች ከሰሜን ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች ጋር ውይይት አካሒደዋል፡፡ ውይይቱ በሪጅኑ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች በሥራው ላይ እያሳደሩት ስለሚገኘው ተፅዕኖ እና ችግሮቹ በሚፈቱበት ዙሪያ ላይ ያለመ መሆኑም ነው የተገለፀው፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ሮቤል ገ/ እግዚአብሔር በዚሁ ወቅት እንዳሉት በሰሜኑ የሃገሪቱ ክፍል ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር ሳቢያ ጉዳት ደርሶባቸው ለነበሩ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ዘላቂ መፍትሔ መስጠት ባለመቻሉ በመደበኛ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ ይገኛል። ሪጅኑ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እንዲያስችለው የመልሶ ግንባታ ሥራዎች በአፋጣኝ መከናወን እንዳለባቸውም ነው ያሳሰቡት፡፡ በሪጅኑ አንዳንድ አካባቢዎች እያጋጠሙ የሚገኙ የኃይል መቆራረጦችን ለመቅረፍ የተበላሹ ብሬከሮችን የመቀየር፣ የጣቢያዎችን አቅም የማሳደግና በዕቅድ ተይዘው የቆዩ ፕሮጀክቶችን ወደ ትግበራ የማስገባት ሥራዎች መሰራት እንዳለባቸውም አስረድተዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ከመለዋወጫ ዕቃዎች፣ ከሥራ ላይ ደህንነትና ከሥራ መሳሪያዎች አቅርቦት፣ ከብሬከር ብልሽት፣ ከጣቢያዎች አቅም ማነስና ከኃይል መዋዠቅ ጋር የተያያዙ ችግሮች እንደሚስተዋሉ በውይይቱ ላይ አንስተዋል:: ከምዘና ሥርዓት፣ ከዕድገትና ዝውውር፣ ከጥቅማ ጥቅም፣ ከሠራተኞች አቅም ግንባታና ከኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ስርቆት ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባም ነው ያስረዱት፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በተከታታይ ሁለት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል ...///... በድሬዳዋ ስቴዲየም በተከናወነው የ3ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ መድን ጋር ተጫው
+7
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በተከታታይ ሁለት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል ...///... በድሬዳዋ ስቴዲየም በተከናወነው የ3ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ መድን ጋር ተጫውቶ ነጥብ ተጋርቷል። ሁለቱ ቡድኖች ትናንት ምሽት 1 ሰዓት ባካሄዱት ጨዋታ ባዶ ለባዶ ተለያይተዋል። በመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ኢትዮጵያ መድኖች ኳስን ተቆጣጥሮ በመጫወት የተሻለ የተንቀሳቀሱ ሲሆን ኢትዮ-ኤሌክትሪኮች በአንፃሩ ጥንቃቄ የተሞላበት የአጨዋወት ስልት ሲከተሉ ተስተውሏል። በሁለቱም ቡድኖች በኩል ቀዝቃዛ የጨዋታ እንቅስቃሴ የታየበት ይህ ጨዋታ የረባ የኳስ ሙከራ ሳያስመለክት ተጠናቋል። የዛሬውን ውጤት ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከሶስት ጨዋታዎች ሁለት ነጥብ መሰብሰብ ችሏል። በ4ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከባህርዳር ከነማ ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም የሚጫወት ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 21 ቀን 2017 ዓ.ም

የተቋረጠው ኃይል ሙሉ በሙሉ ተገናኝቷል ......///...... በደብረ ብርሃን ቁጥር አንድ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በሁለት የባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ላይ ባጋጠመ ችግር ምክንያት ተቋርጦ
የተቋረጠው ኃይል ሙሉ በሙሉ ተገናኝቷል ......///...... በደብረ ብርሃን ቁጥር አንድ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በሁለት የባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ላይ ባጋጠመ ችግር ምክንያት ተቋርጦ የቆየው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ መመለሱን የማዕከላዊ አንድ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌትነት ተስፋዬ እንደገለፁት በደብረ ብርሃን ከተማና በዙሪያው በሚገኙ አራት ወረዳዎች ለ24 ሰዓት ተቋርጦ የቆየውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት መልሶ ለማገናኘት የሪጅኑ ጥገና ሠራተኞች ርብርብ ሲያደርጉ ቆይተዋል። ተቋርጦ የቆየውን የኤሌክትሪክ ኃይል ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ዳግም ማገናኘት ተችሏል ያሉት አቶ ጌትነት በጥገና ሥራው ላይ ርብርብ ሲያደርጉ ለነበሩ የጥገና ሠራተኞች በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።   "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 20 ቀን 2017 ዓ.ም

ዘርፉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ ሥራ ለማከናወን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀራርቦ ይሰራል፤ ....//.... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የንብረት አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ዘርፍ በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ ከዘርፉ ሠራተኞችና ከአሽከርካሪዎች ጋር ውይይት አካሂዷል። የዘርፉ ሥራ አሥፈጻሚ ወ/ሮ ስመኝ አያሌው እንደገለጹት ውይይቱ በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ የዘርፉ ሠራተኞችና የሥራ መሬዎች የጋራ መረዳት ኖሯቸው ተቀናጅተው ለተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ለማድረግ ነው። በዘርፉ ለሠራተኛው ምቹ የሥራ ከባቢ ከመፍጠር፣ የተቋሙን ንብረቶችን ከማስተዳደር፣ የጥገና ሥራዎችን ከማከናወን እና የሰርቪስ ተሽከርካሪዎችን ከማቅረብ አኳያ በ2016 በጀት ዓመት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አስታውሰዋል። ኃላፊዋ አክለውም አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን ከማስወገድ፣ የቆዩ የተቋሙ ሠነዶችን ከማደራጀት፣ ምቹ የሥራ ከባቢን ከመፍጠር እና ለሠራተኞች የሰረቪስ አገልግሎት ከመስጠት አንጻር አበረታች ሥራዎች ተከናውነዋል ብለዋል። ሆኖም በየመጋዘኖቹ ተገዝተው የሚገቡ ብዛት ያላቸው የተለያዩ የሥራ ክፍል ዕቃዎች ቶሎ ያለመውጣት፣ ከፍተኛ የቦታ ጥበት፣ በዕቃ ግምጃ ቤት ቅጥር ግቢ የኢንተርኔት ችግር መኖር፣ የአንዳንድ ዕቃዎች መመዘኛ መስፈርት ማግኘት አለመቻል፣ የስቶር ግንባታው በታቀደለት ጊዜ አለመጠናቀቅ፣ የመለዋወጫ ችግር እና የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ የማስወጣት ሥራ በዕቅዱ መሠረት አለመፈጸም ያጋጠሙ ችግሮች መሆናቸው ተገልጿል። እንደ ሥራ አስፈጻሚዋ ገለጻ በ2016 በጀት ዓመት የተከናወኑ ሥራዎች ለ2017 በጀት ዓመት እቅድ መደላድል የፈጠረ መሆኑን አስታውሰዋል። በ2017 በጀት ዓመት የተቋሙን ንብረት አያያዝና አጠቃቀም መመሪያ አውጥቶ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰራ የተናገሩት ወ/ሮ ስመኝ 600 ለሚሆኑ የተቋሙ ተሽከርካሪዎች ጂፒኤስ መገጠሙንና በዚህ ዓመት ሥራ ላይ እንደሚውል ጠቁመዋል። ሥራ አስፈጻሚዋ አክለውም ተቋሙ ያሉት ተሽከርካሪዎችን በአግባቡ ተጠግነው ሥራ ላይ እንዲውሉ የመካከለኛ ጋራዥ በዚሁ በጀት ዓመት ግንባታው እንደሚጀመር ገልጸዋል። ከመለዋወጫ እቃ እጥረት፣ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ያለው የይዞታና ንብረቶች ጉዳይ በዘላቂነት ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሠራ ተናግረዋል። በውይይቱ ላይ የመምሪያ ኃላፊዎች የ2017 በጀት ዓመት ዕቅዳቸውን አቅርበው ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 20 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ዘርፉ ከሰሜን ሪጅን የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር ውይይት እያካሄደ ይገኛል ....//.... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ከሰሜን ሪጅን የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር በሪጅኑ እየተከናወኑ ስላሉ  ሥራዎች እና ተግዳሮቶች ዙሪያ በመቐለ ከተማ ውይይት እያካሄደ ይገኛል። በውይይቱ ላይ የተገኙት በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንደተናገሩት ውይይቱ ሪጅኑ በሚያከናውናቸው ሥራዎች ላይ እያጋጠሙ ባሉ ችግሮች ላይ ውይይት በማድረግ የቀጣይ የሥራ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው። ከዚህ በተጨማሪም የሪጅኑ ሠራተኞች በአካባቢው የነበረውን ችግር ተቋቁመው  ላከናወኑት ሥራ በዘርፉ እውቅና   ለመስጠት ዓላማ ያደረገ እንደሆነም አመላክተዋል። ከሪጅኑ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር እየተካሄደ ያለው ውይይት ሪጅኑ ድጋፍ የሚፈልግበትን ጉዳዮች ግብዓት በመሰብሰብ በቀጣይ ለጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እንደሚያግዝም አቶ ጋሻው ተናግረዋል። የሰሜን ሪጅን ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሮቤል ገ/ እግዚአብሔር በበኩላቸው ውይይቱ በሪጅኑ የሚነሱ የተለያዩ ችግሮችን በመውሰድ እልባት ለመስጠት ያስችላል ብለዋል። መስከረም 20 እና 21 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ውይይት ላይ የሪጅኑ የማከፋፈያ ጣቢያዎች፣  የማስተላለፊያ መስመርና የፋይበር ኦፕቲክስ የኦፕሬሽንና ጥገና ኃላፊዎችና ሠራተኞች እንዲሁም በሪጅኑ ስር የሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊዎች እንደሚሳተፉበት አቶ ሮቤል ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ውይይቱ ከኃይል ማስተላለፊያ መስመር የኦፕሬሽንና ጥገና ሠራተኞች ጋር በመካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን ከሰዓት በኋላም ከማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና የጥገና ሠራተኞች ጋር የሚቀጥል ይሆናል። ከውይይቱ በተጨማሪ በሪጅኑ በሚገኙ አንዳንድ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ጉብኝት እንደሚካሄድ ከመርሃ ግብሩ ለመረዳት ተችሏል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 20 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

ማመንጫ ጣቢያው በበጀት ዓመቱ 296 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማመንጨት አቅዷል ……..////……. የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በተያዘው የ2017 በጀት ዓመት 296 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ማቀዱን የጣቢያው የኦፕሬሽን ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ታረቀኝ ተመስገን እንደገለፁት ጣቢያው በ2016 በጀት ዓመት 175 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማምረት አቅዶ 125 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማመንጨት ችሏል። የ2017 በጀት ዓመት ዕቅዱን ለማሳካትና መደበኛ የኦፕሬሽን ሥራውን አስተማማኝ ለማድረግ ከፕሮጀክት ቢሮ እና ሥራ ተቋራጩ ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝም አቶ ታረቀኝ ገልፀዋል። የኃይል ማመንጫ ጣቢያው በግንባታ ሂደት ላይ ሆኖ ኤሌክትሪክ ማመንጨት መጀመሩ ተጨማሪ ኢነርጂ ወደ ብሔራዊ ኃይል ቋት እንዲገባ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በጣቢያው ከተተከሉት 32 የንፋስ ተርባይኖች ውስጥ በአሁኑ ወቅት 23ቱ ኃይል በማመንጨት ላይ ይገኛሉ። በተያዘው በጀት ዓመት በፍተሻና ሙከራ ላይ የሚገኙ 8 ተርባይኖችን በመረከብና ወደ ኦፕሬሽን በማስገባት ኃይል የሚያመነጩትን የንፋስ ተርባይኖች ቁጥር ወደ 31 ከፍ ለማድረግ ይሰራልም ብለዋል። የኃይል ማመንጫው የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራዎች ከፕሮጀክቱ ባለሙያዎች ጋር በጥምረት እየተከናወነ በመሆኑ የዕውቀት ሽግግሩ በከፍተኛ ሁኔታ እያገዛቸው እንደሚገኝ አቶ ታረቀኝ ጠቅሰዋል። ለጣቢያው የኦፕሬሽን ሠራተኞች እየተገነቡ የሚገኙት መኖሪያ ቤቶች በጥራትና በፍጥነት ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት እንዲጀምሩ ለማድረግ ከፕሮጀክት ቢሮው ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝም ገልፀዋል። በኃይል ማመንጫው አካባቢ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በአስተዳደር ክፍሉ አማካኝነት ተደጋጋሚ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች መከናወናቸውን አቶ ታረቀኝ ተናግረዋል። 120 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ መንግስትና ከቻይና ኤግዚም ባንክ በተገኘ 270 ሚሊየን ዶላር እየተገነባ የሚገኝ ፕሮጀክት ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 18 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ነጥብ ተጋርቷል ........///....... በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው ጨዋታ ባዶ ለባዶ በሆነ ውጤት ተለያይቷል። ተመጣጣኝ የኳስ ቁጥጥር በተስተናገደበት በዚህ ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ያገኙትን የግብ ዕድል ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል። በኢትዮ-ኤሌክትሪክ በኩል ፈቃዱ ዓለሙና አሸናፊ ጥሩነህ ጥሩ የማግባት ዕድል ቢያገኙም በቡናዎች የግብ ዘብ መክኖባቸዋል። ኢትዮጵያ ቡና በበኩሉ በጋናዊው ተጫዋች ኮንኮኒ ሀፋዝ እና በአንተነህ ተፈራ አማካኝነት ያልተሳኩ የጎል ሙከራዎችን አድርገዋል። ውጤቱን ተከትሎ በፕሪሚየር ሊጉ ሁለት ጨዋታዎችን ያከናወነው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የመጀመሪያውን አንድ ነጥብ አግኝቷል። በሶስተኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው ሰኞ መስከረም 20 ቀን 2017 ዓ.ም ከኢትዮጵያ መድን ጋር  የሚጫወት ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 17 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

የፕሮጀክቱ ሠራተኞች የመስቀል ደመራ በዓልን አከበሩ ……..///……… በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በግንባታ ሥራ ላይ የሚገኙ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች የደመራ በዓልን በድምቀት አክብረዋል። ትናንት አመሻሽ ላይ በተከናወነው መርሃግብር የፕሮጀክቱ የሥራ ኃላፊዎች እና የፕሮጀክቱ አማካሪ ድርጅት አመራሮች በጋራ ደመራውን ለኩሰዋል። የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የአስተዳደር እና አገልግሎቶች ሥራ አስኪያጅ አቶ ክብሮም ገ/መድህን እንደገለፁት የፕሮጀክት ሥራዎች 24 ሰዓት የሚከናወኑ በመሆናቸው ሠራተኞች በዓላትን በኘሮጀክት ቦታ በድምቀት በማክበር ቤተሰባዊነት እንዲሰማቸው ማድረግ ያስፈልጋል። በበዓሉ ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙዩኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍስሐ ጌታቸው በበኩላቸው እንዲህ ዓይነት በዓላትን በሥራ ቦታ ላይ ማክበር ሠራተኞች በዓላትን በደስታ እንዲያሳልፉና ለቀጣይ ስራ እንዲነሳሱ ያደርጋል ብለዋል። አብዛኞቹ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችና ፕሮጀክቶች ከከተማ የራቁ በመሆናቸው በበዓላት ወቅት መሰል ሁነቶችን ማዘጋጀት ሠራተኞችን ከማነቃቃት አንፃር ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑንም ነው የተናገሩት። የፕሮጀክቱ አማካሪ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ካርሎስ ማርቲኔዝ በበኩላቸው የደመራ በዓል ለየት ያለ ስሜት የፈጠረባቸው መሆኑን ገልፀው ለሁሉም የፕሮጀክቱ ሠራተኞች እና የስራ ኃላፊዎች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። በዕለቱ የተለያዩ የመዝናኛ መርሀግብሮች የተከናወኑ ሲሆን የኮንታ የሙዚቃ ባንድ የተለያዩ ጣዕመ ዜማዎችን በማቅረብ በሺዎች የሚቆጠሩ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች በዓሉን በደስታ እንዲያሳልፉ አድርጓል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 17 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ታዳጊ እግር ኳስ ቡድን ሻምፒዮን ሆነ ........///........ የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከ17 ዓመት በታች ታዳጊ እግር ኳስ ቡድን በሐዋሳ ከተማ በተካሄደው የኢትዮጵያ ሻምፒዮና አሸናፊ በመሆን የዋንጫ እና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸልሟል። በዛሬው ዕለት ሐዋሳ ስታዲየም በተካሄደው የፍፃሜ ጨዋታ የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ታዳጊ ቡድን የሲዳማ ክልል አቻውን በማሸነፍ የውድድሩ ሻምፒዮን ሆኗል። ሁለቱ ቡድኖች በመደበኛው 90 ደቂቃ ባዶ ለባዶ የተለያዩ ሲሆን አሸናፊውን ለመለየት በተሰጠው የፍፁም ቅጣት ምት የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ታዳጊ ቡድን 4 ለ 3 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል። የኢትዮ ኤሌክትሪክ ታዳጊ ተጫዋች ተመስገን ማናዬ በኮከብ ተጫዋችነት የተመረጠ ሲሆን የቡድን አጋሩ ሙባረክ አረቦ ደግሞ ኮከብ ግብ አግቢ በመሆን ተሸልሟል። በተጨማሪም የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ሙሉጌታ በዳዳ ኮከብ አሰልጣኝ እንዲሁም ተስፈኛው ታዳጊ ብሩክ ዘላለም ኮከብ ግብ ጠባቂ በመሆን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ከአቶ ባህሩ ጥላሁን ሽልማታቸውን ተረክበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

የህብረት ሥራ ማህበሩ በሥራ ላይ ጉዳት ለደረሰባቸው ሠራተኞች የበዓል ስጦታ አበረከተ .........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ ህብረት ሥራ ማህበር የሥራ አመራር ቦርድ አባለት በሥራ ላይ ጉዳት ደርሶባቸው በደጃዝማች ባልቻ ጠቅላላ ሆስፒታል ህክምናቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ሠራተኞችን በመጠየቅ የበዓል ስጦታ አበርክተዋል፡፡ ስጦታው ከባህር ዳር፣ ከሆለታ ከቡራዩ እና ከደራ አካባቢዎች ጉዳት ደርሶባቸው ለመጡ አራት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች የተበረከተ ሲሆን ለእያንዳንዳቸው የ10 ሺህ ብር የበዓል ስጦታ እናእንኳን አደረሳችሁ ካርድ ተበርክቷል። የህብረት ሥራ ማህበሩ የሥራ አመራር ቦርድ ሰበሳቢ አቶ አንበሴ ግዛቸው እንደተናገሩት ማህበሩ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በጀት መድቦ የተለያዩ ድጋፎችን እና ተግባሮችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ የሥራ ላይ ጉዳት ደረሶባቸው ህክምናቸውን ለሚከታተሉት የሁለቱ ተቋም ሠራተኞች ጥየቃ እና የበዓል ስጦታ አንዱ ነው ብለዋል ፡፡ እንደ አቶ አንበሴ ገለፃ የማህበሩ አባል ያልሆኑ የሁለቱ ተቋማት ሠራተኞች አባል በመሆን ማህበሩ የሚሰጠውን አገልግሎት የበለጠ ሊያጠናከሩ ይገባል፡፡ በሥራ አመራር ቦርዱ የማህበራዊ ዘርፍ ሰብሳቢ አቶ ደመላሽ ንጉስ እንደተናገሩት በህክምና ላይ የሚገኙት ሠራተኞች ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የመጡ እንደመሆናቸው የጥየቃ ፕሮግራሙ ቤተሰባዊ ቅርርብ እና ለታካሚዎቹ በጎ ሞራል ለመፍጠር ያግዛል። የሥራ አመራር ቦርዱ ከ2015 ዓ.ም. ጀምሮ የሥራ ላይ ጉዳት ደርሶባቸው ህክምናቸውን ለሚከታተሉ የሁለቱ ተቋማት ሠራተኞችን የህብረት ሥራ ማህበሩ አባል ቢሆኑም ባይሆኑም በመጠየቅ ያለ አድልኦ ሥጦታው እየሰጠ እንደሚገኝ አቶ ደመላሽ ጠቁመዋል ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ ህብረት ሥራ ማህበር ሥራ አሰኪያጅ አቶ መዝገበ ታከለ በበኩላቸው ማኅበሩ ለገንዘብ ቁጠባ እና ለብድር ብቻ የተቋቋመ ላለመሆኑ እና በማቋቋሚያ ደንቡ የተሰጠውን ኃላፊነት እየተወጣ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

እንኳን አደረሳችሁ! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለመስቀል በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡ በዓሉ የሰላም፣ የአብሮነት እና የደስታ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ፡፡ አሸብር ባልቻ (ኢንጂነ
እንኳን አደረሳችሁ! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለመስቀል በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡ በዓሉ የሰላም፣ የአብሮነት እና የደስታ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ፡፡ አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ.ም