en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 679 subscribers, ranking 8 043 in the Technologies & Applications category and 2 176 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 679 subscribers.

According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 111 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.35%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.94% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 974 views. Within the first day, a publication typically gains 2 500 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 679
Subscribers
-124 hours
-157 days
+11130 days
Posts Archive
በማከፋፈያ ጣቢያው መቆጣጠሪያ ላይ የጥገና ሥራ እየተከናወነ ነው …….///……… በአዲስ አበባ ጎፋ ማከፋፈያ ጣቢያ የትራንስፎርመር መቆጣጠሪያ ላይ የገጠመውን ችግር ለማስተካከል የጥገና ሥራ መጀመሩን
በማከፋፈያ ጣቢያው መቆጣጠሪያ ላይ የጥገና ሥራ እየተከናወነ ነው …….///……… በአዲስ አበባ ጎፋ ማከፋፈያ ጣቢያ የትራንስፎርመር መቆጣጠሪያ ላይ የገጠመውን ችግር ለማስተካከል የጥገና ሥራ መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 3 ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ፡፡ መምሪያ እንደገለፀው እየተከናወነ ያለው የጥገና ሥራ ከማከፋፈያ ጣቢያው የሚወጡ መስመሮችን በማቀያየር የሚከናወን በመሆኑ ለኃይል መቆራረጥ ምክንያት ሊሆን ይችላል፡፡ ስለሆነም ከማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል በሚያገኙት በጎፋ ኮንዶሚኒየም፣ ላፍቶ፣ ቫቲካንና ቄራ አካባቢ ኃይል በጊዜያዊነት ሊቋረጥ ስለሚችል ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ መምሪያው ጠይቋል፡፡ በዚህ ሰዓት ከባድ ተሽከርካሪዎች ለመንቀሳቀስ የማይፈቀድላቸው ቢሆንም የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት 12 ነጥብ 5 ቶን የመሸከም አቅም ያለው ክሬን እንዲንቀሳቀስ ፍቃድ ስለሰጠ ተቋሙ አመስግኗል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 05 ቀን 2017 ዓ.ም

ለጥገና ሥራ ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት እሁድ ህዳር 8 ቀን 2017 ዓ.ም በመካኒሳ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ ስለሆነም ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 9
ለጥገና ሥራ ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት እሁድ ህዳር 8 ቀን 2017 ዓ.ም በመካኒሳ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ ስለሆነም ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 9፡00 ሰዓት ድረስ በጎፋ ካምፕ አካባቢ፣ በባቱ ኮንዶሚኒየም አካባቢ፣ በመካኒሳ ቆሬ፣ አረቄ ፋብሪካ እና አቦ ቤተክርስቲያን አካባቢ፣ በቫቲካን ጀርባ፣ በመከላከያ ሚኒስቴር መኖሪያ፣ በላፍቶ እና አካባቢው፣ በለቡ ሙዚቃ ሰፈር እንዲሁም በኃይሌ ጋርመንት እና አካባቢው የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦ ይቆያል፡፡ በተመሳሳይ ቀን እሁድ ህዳር 8 ቀን 2017 ዓ.ም በንፋስ ስልክ ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመሮች ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ ስለሆነም ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ በቄራ፣ በገነት ሆቴል፣ በኦሎምፒያ፣ በመስቀል ፍላወር፣ በወሎ ሰፈር፣ በቦሌ መድኃኔዓለም፣ በዮሴፍ እና አደይ አበባ አካባቢ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦ የሚቆይ ስለሆነ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 05 ቀን 2017 ዓ.ም

ትምህርት ቤቱ በተሻሉ መምህራን ጥራት ያለው ትምህርት እየሰጠ ነው ……….///……… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመልካ ዋከና ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት በተሻሉ መምህራን ጥራት ያለው ትምህርት በመስጠቱ በአካባቢው ማህበረሰብ ተመራጭ እየሆነ መምጣቱን የት/ቤቱ ምክትል ርዕሰ መምህር ገለፁ። ምክትል ርዕሰ መምህሩ ጫላ ደሜ እንደገለፁት ትምህርት ቤቱ የጣቢያው ሠራተኛ ልጆች እንዲማሩ ታስቦ ቢከፈትም በሂደት የአካባቢውን ማህበረሰብ ልጆችን ተጠቃሚ ማድረግ ጀምሯል፡፡ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ለትምህርት ቤቱ የግብዓት ድጋፍ የሚያደርግ ከመሆኑ ባሻገር ለመምህራን የመኖሪያ ቤት፣ የትራንስፖርት፣ መብራትና ውሃ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ጠቁመዋል። የጣቢያው የአስተዳደር፣ ንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ ተሻገር በበኩላቸው እንደተናገሩት ጣቢያው ኃይል ከማመንጨት ባሻገር ትውልድ ቀረጻ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል። ትምህርት ቤቱ የሚተዳደረው በክልሉ ትምህርት ቢሮ በኩል ቢሆንም ጣቢያው ክትትልና የተለያዩ ድጋፎችን እንደሚያደርግ ገልጸዋል። በትምህርት ቤቱ የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ሙዘሚር ሙሐመድ እንዲሁም የ6ኛ ክፍል ተማሪ የሆኑት ተማሪ ፈትያ ጀማል እና ተማሪ ሮቤ አለሙ ቱሉ እንደገለጹት የትምህርት ቤቱ መከፈት ከቤተሰብ ሳትርቅ የመማር እድል ፈጥሮላቸዋል። ጣቢያው የከፈተው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ለአካባቢው ልጆች የመማር ተስፋ መፈንጠቁን ገልጿል። ጣቢያው ትምህርት ቤቱን ከመክፈት በተጨማሪ ተማሪዎች ሲታመሙ በጣቢያው ክሊኒክ የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ትምህርት ቤቱ በአሁኑ ወቅት ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል 876 ተማሪዎችን ተቀብሎ እያስተማረ መሆኑን ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 05 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

በቅየሳ ሥራ ለረጅም ዓመታት ላገለገሉ ሴት ሠራተኞች ዕውቅና ተሠጠ ………///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ ዘርፍ ለ36 ዓመታት በቅየሳ ሥራ ላይ ላገለገሉ ሦስት ሴት ሠራተኞች በዛሬው ዕለት ዕውቅና ሰጥቷል። የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ውድነህ የማነ በዕውቅና መርሀግብሩ ላይ እንደተናገሩት የቅየሳ ሥራ ተቋሙ ለሚያከናውናቸው የመሠረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች ቀዳሚውን ድርሻ ይይዛል። ሠራተኞቹ አሁን የደረስንበት ቴክኖሎጂ ላይ ሳንደርስና ሴትነታቸው ሳይበግራቸው ለተቋሙ ላበረከቱት አስቸዋጽዖ አመስግነው በቀጣይ ጊዜ  ልምዳቸውን ለሌሎች በማካፈል ለተቋሙ የሚያደርጉትን አስተዋፅዖ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። ሠራተኞቹ ለረጅም ዓመታት በአንድ መደብ መስራታቸው ከራሳቸው ይልቅ ለተቋሙ ቅድሚያ መስጠታቸውን የሚያሳይ በመሆኑ ሌሎች ሠራተኞችም ይህን አርዓያ ተከትለው ለተቋሙ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል። በዘርፉ የቴክኒካል ድጋፍ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አብዱልአሊም አህመድ በበኩላቸው ዕውቅናው ሠራተኞቹ ለሥራ አመቺ ያልሆኑ አስቸጋሪ የሥራ ሁኔታዎችን ተቋቁመው ያገለገሉበትን ዘመን ታሳቢ ያደረገ ነው። በዛሬው ዕለት የተሰጠው ዕውቅና ሌሎች ሠራተኞች የፈጠራ ችሎታቸውን አዳብረው ለተቋሙ ስኬት በርትተው እንዲሰሩ ተነሳሽነትን እንደሚፈጥርም ተናግረዋል። በቀጣይ ዘርፉን ለማሳደግ ጥረት ለሚያደርጉ ሠራተኞች የሚሠጠው  እውቅና ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት በተቋሙ የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ ዕውቅና የተሠጣቸው ሠራተኞች ሴቶች በማንኛውም ዘርፍ እንደሚችሉና ውጤታማ እንደሚሆኑ በተግባር አሳይተውናል በማለት ገልፀዋል። ዘርፉ ለሴት ሠራተኞች ለሠጠው ዕውቅና አመስግነው ሌሎች የሥራ ክፍሎች ይህን አርዓያ እንዲከተሉ እና ለሴቶች ምቹ የሥራ ከባቢ ለመፍጠር የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳሰበዋል። በዕለቱ ዕውቅና ከተሰጣቸው ሠራተኞች መካከል ተቋሙን ከ1981 ዓ.ም ጀምር በቅየሳ ሥራ ያገለገሉት ወ/ሮ አባይነሽ ፅጌ እንደተናገሩት በአንድ መደብ ላይ ለረጅም ዓመታት ማገልገል የራስን ልምድ ከማዳበሩም ባለፈ ለተቋሙ ውጤታማነት ከፍተኛ ፉይዳ ይኖረዋል። የቅየሳ ሥራ ተቋሙ ለሚያከናውናቸው ሥራዎች "የጀርባ አጥንት" ነው የሚሉት ወ/ሮ አባይነሽ ተቋሙም ሥራው ለዘርፉ የሚኖረውን ፋይዳ በመገንዘብ ለሠጣቸው እውቅና አመስግነው ዕውቅናው በቀሪ ጊዜያቸው ለሚያከናውኑት ሥራ  ስንቅ እንደሚሆናቸው ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 04 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሹፌር 4ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት ጥቅ
+6
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሹፌር 4ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ በመንገድ ትራንስፖርት በሚፈቅደው ህግ እና ደንብ መሰረት 74 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጣችሁ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 14 ለተግባር ፈተና ያለፋችሁ በመሆኑ ህዳር 11 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 የታደሰ መንጃ ፈቃድ በመያዝ ኮተቤ ብረታብረት ፊትለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት ተሽከርካሪ ጥገና አስተዳደር ቢሮ የተግባር ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና አንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 04 ቀን 2017 ዓ.ም

ፕሮጀክቱ ለአካባቢው ወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጥሯል .......//........ የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ለአካባቢው ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩን የሳይት ሥራ አስኪያጁ ተናገሩ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ 190 ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ፈጥሯል። የአካባቢው ወጣቶች በፕሮጀክቱ በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ የተናገሩት አቶ ቴዎድሮስ ይህም ወጣቶቹ በተፈጠረላቸው የሥራ ዕድል ተጠቅመው ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን እንዲያስተዳድሩ ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ በሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ተመርቆ ሥራ አጥ ሆኖ መቆየቱን የጠቀሰው ወጣት ጌታቸው ገብሬ አሁን ላይ በፕሮጀክቱ የዕቃ ግምጃ ቤት ሠራተኛ ሆኖ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግሯል። በፕሮጀክቱ በተፈጠረለት የሥራ ዕድል ከሥራ አጥነት ወጥቶ ራሱንና ቤተሰቡን እያስተዳደረ መሆኑንም ጠቁሟል። ከዕቃ ግምጃ ቤት ሥራው ጎን ለጎን ከሰለጠነበት ሙያ ጋር ተያያዥ በሆኑ ስራዎች ላይ እንዲሳተፍ ዕድል እንደፈጠረለት የተናገረው ወጣት ጌታቸው በቀጣይ በሙያው ተቀጥሮ በመሰል ፕሮጀክቶች ላይ በመሳተፍ ሀገሩን እንደሚያገለግል እምነት እንዳለው ገልጿል። ሌላኛዋ የሥራ ዕድሉ ተጠቃሚ ወጣት ትህትና ብርሃኑ በበኩሏ በፕሮጀክቱ የሥራ ሰዓት ተቆጣጣሪ በመሆን እየሰራች መሆኑን ገልጻለች። የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱ በአካባቢው መጀመር በፈጠረላት የሥራ ዕድል የተሻለ ገቢ ለማግኘት እንደረዳት እና ሌሎች የአካባቢው ወጣቶችም የዚሁ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግራለች፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 04 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

የውጤት ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጋቢት 11 ቀን 2016 ዓ.ም በሎየር 1ኛ የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት
+1
የውጤት ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጋቢት 11 ቀን 2016 ዓ.ም በሎየር 1ኛ የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል ከተ.ቁ 1 እስከ 11 ያላችሁ በተሰጠው የጽሁፍ እና የቃል ፈተና አብላጫ ውጤት ያመጣችሁ በመሆኑ ከህዳር 09 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው ዋና መ/ቤት የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 04 ቀን 2017 ዓ.ም

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሹፌር 3ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት ጥቅ
+3
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሹፌር 3ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ በመንገድ ትራንስፖርት በሚፈቅደው ህግ እና ደንብ መሰረት 74 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጣችሁ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 17 ለተግባር ፈተና ያለፋችሁ በመሆኑ ህዳር 10 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 የታደሰ መንጃ ፈቃድ በመያዝ ኮተቤ ብረታብረት ፊትለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት ተሽከርካሪ ጥገና አስተዳደር ቢሮ የተግባር ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 03 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

የአይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ግንባታን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ………///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአይሻ 3 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ግንባታን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር ገለጹ፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ ሞገስ መኮንን እንደገለጹት የአይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ 120 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዲኖረው ታስቦ እየተገነባ ያለ ፕሮጀክት ሲሆን በአሁኑ ጊዜ አፈጻጸሙ 83 ነጥብ 8 በመቶ ደርሷል፡፡ ግንባታው ደረጃ በደረጃ እየተሠራ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሞገስ ፕሮጀክቱ 80 ሜጋ ዋት ኃይል ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት እያስገባ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ቀሪውን 40 ሜጋ ዋት ኃይል የሚያመነጩ ተርባይኖችን የመትከል ሥራ ለማከናወን የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ተርባይኖችን የመትከል ሥራው በፋይናንስ አቅርቦት ምክንያት መዘግየቱን ያስታወሱት ዳይሬክተሩ አሁን ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አበዳሪዎችን ሳይጠብቅ በራሱ ፋይናንስ ግንባታውን ለማጠናቀቅ ወስኖ ወደ ሥራ መግባቱን አብራርተዋል፡፡ በኢትዮጵያ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ታሪክ የአዳማ አንድ እና ሁለት እንዲሁም የአሸጎዳ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ጨምሮ የአይሻ ሦስት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አራተኛው ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 03 ቀን 2017 ዓ.ም

ጣቢያው ለረጅም ዓመት አስተማማኝ ኃይል እያመረተ እንዲቆይ የጥገና ክፍሉ ሚና ከፍተኛ ነው ……//….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለረጅም ዓመት አስተማማኝ ኃይል እያመረተ እንዲቆይ የጥገና ክፍሉ ሚና ከፍተኛ መሆኑን የጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ ገለፁ፡፡ ኃላፊው አቶ መንበሩ ደምሴ እንደገለጹት የጥገና ክፍሉ በራስ አቅም ወቅቱን የጠበቀ ትልልቅ የጥገና ሥራዎችን በማከናወኑ ጣቢያው ላለፉት 37 ዓመታት አስተማማኝ ኃይል በማምረት ላይ ይገኛል፡፡ በጣቢያው ላይ የመልሶ ግንባታ ሥራ ካለመሰራቱ ጋር ተያይዞ በኦፕሬሽንና በጥገና ክፍሉ ላይ ጫና መፍጠሩን የተናገሩት አቶ መንበሩ በማመንጫ ጣቢያው በየቀኑ፣ በየሳምንቱና በየወሩ የቅድመ መከላከል፣ የትንበያ እና የፍተሻ ጥገና ሥራዎች በማከናወን ጣቢያው ዛሬም ድረስ ኃይል ማምረቱ ሳይቋረጥ መቀጠሉን ገልጸዋል፡፡ የጥገና ሥራዎችን በአግባቡ ለማከናወንም ለባለሙያዎቹ አጫጭር የሥራ ላይ ሥልጠናዎችን እንደሚሰጡና እርስ በእርስ የሚማማሩበት ሥርዓት መዘርጋቱን ጠቁመዋል፡፡ በጣቢያው ከ3 ዓመት በላይ የሠራችው የጥገና ባለሙያ ስናፍቅሽ ጴጥሮስ ተርባይኖች እንዳይቆሙ ዕቃዎች ላይ ማሻሽያ በመስራት ጭምር በራስ አቅም በርካታ የጥገና ሥራዎችን እየሰሩ መሆኑን ተናግራለች፡፡ የጥገናና የኦፕሬሽን ክፍሉ ጥንካሪ ጣቢያው ለረጅም ዓመት ኃይል በአስተማማኝነት እንዲያመርት ማስቻሉንም ጠቁማለች፡፡ በጣቢያው የጥገና ባለሙያ ጥላሁን አጥሌ በበኩሉ የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራዎች የጣቢያውን የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት ለመጨመር በሚያስችል መልኩ እየተከናወኑ መሆኑን ገልጿል፡፡ በጣቢያው ከ30 ዓመት በላይ ልምድ ያላቸው የጥገና ሠራተኞች ልምዳቸውን እያካፈሉ ከኦፕሬሽን ክፍሉ ጋር በመናበብ ጣቢያው ችግር ሳይገጥመውና ሳይቆም በርካታ የቅድመ መከላከል የጥገና ሥራዎች እንደሚሰሩ ተናግሯል፡፡ በመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የኦፕሬሽን ክፍል ኃላፊ አቶ ተክሉ ጎንፋ ክፍሉ በኃይል ማመንጫ ጣቢያው የማዘመን ሥራ ባለመሰራቱና ማንዋል በመሆኑ የኦፕሬሽን ሥራውን ከማዕከል ሆኖ ለመቆጣጠር ፈታኝ እንዳደረገው ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 03 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

ለፕሮጀክቱ የሚውሉ ግብዓቶች በሳይቱ በራስ አቅም እየተመረቱ ነው ………///…….. በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሞጆ ከተማ አቅራቢያ በመገንባት ላይ ለሚገኘው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግብዓቶች በራስ አቅም በሳይቱ ላይ እየተመረቱ መሆኑን በፕሮጀክቱ የኤሌክትሮ ሜካኒካል የሳይት መሐንዲስ ገለፁ፡፡ መሐንዲሱ አቶ ቢኒያም ሀብታሙ እንደተናገሩት በሳይቱ ለአንከር ቦልት ስራ የሚውል ቴምፕሌት እየተዘጋጀ ነው፡፡ በፕሮጀክቱ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሠራተኛ ብርቱካን አብዱ በበኩሏ በሳይቱ በራስ አቅም በሚሰራው የአንከር ቮልት ተከላ ሥራ ላይ እየተሳተፈች መሆኗን ገልፃለች፡፡ ከአሁን ቀደም በውጭ ባለሙያዎች ይከናወኑ የነበሩ ሥራዎችን በሳይቱ በራስ አቅም መስራት መቻሉ ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪና የጊዜ ብክነት እንዳዳነው ተናግራለች፡፡ እንደ ብርቱካን ገለጻ በሳይቱ በራስ አቅም የሚከናወኑ ሥራዎች ባለሙያዎች ዕውቀታቸውን እንዲያዳብሩ እድል ከመፍጠሩ በሻገር ተቋሙ ያሉትን ባለሙያዎች በመጠቀም ትልልቅ ዕቃዎችን እንዲሰራ መተማመንን የሚፈጥር ነው፡፡ የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው በበኩላቸው በሳይቱ ለፕሮጀክቱ አስፈላጊ የሆኑ የግንባታ ግብዓቶችን በራስ አቅም ማምረት መጀመሩ ለሌሎች ፕሮጀክቶች ትልቅ ማሳያ እንደሚሆን ተናግረዋል። የተጀመሩት ሥራዎች ፕሮጀክቱ በግብዓት አቅርቦት ችግር ምክንያት እንዳይጓተት ሚናቸው የጎላ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ቴዎድሮስ በቀጣይ የባለሙያዎችን አቅም በማጎልበት ሌሎች የግንባታ ግብዓቶችን ለመስራት ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በፕሮጀክቱ ላይ በራስ አቅም እየተሰሩ ላሉት ሲቪል ሥራዎች የሚያግዙ ከ50 ሺ በላይ ብሎኬቶች በራስ አቅም በሳይቱ ማምረት መቻሉን ቀደም ሲል መዘገባችን ይታወሳል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 02 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የዋንጫ አሸናፊ ሆኗል ………///…….. በቢሾፍቱ ከተማ በተካሄደው 11ኛው የኢትዮጵያ የ30 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በሁለቱም ፆታ አሸናፊ ሆኗል። በወንዶች በተካሄደው ውድድር የኢትዮ-ኤሌክትሪክ አትሌት ኃይለ ማርያም ኪሮስ 1ኛ በመውጣት የወርቅ ተሸላሚ ሲሆን የቡድን አጋሩ አትሌት ባየልኝ ተሻገር ውድድሩን በሶስተኛነት አጠናቋል፡፡ በተመሳሳይ የሴቶች የሩጫ ውድድር አትሌት ጽጌ ኃይለ ሥላሴ 2ኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ ባለቤት ሆናለች፡፡ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በአጠቃላይ ነጥብ አንደኛ በመሆን የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶለታል። በዚህ ውድድር ከሶስት ክልሎች፣ከአንድ ከተማ አስተዳደር እና ከ15 ክለቦች የተውጣጡ 522 አትሌቶች ተሳትፊ ሆነዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 01 ቀን 2017 ዓ.ም