EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 560 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 357,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 160 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 560 名订阅者。
根据 26 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 27,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.05%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.01% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 053 次浏览,首日通常累积 2 491 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 27 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 560
订阅者
-724 小时
+147 天
+2730 天
帖子存档
15 550
ሪጅኑ በሚያከናውናቸው ሥራዎች ላይ እያጋጠሙ የሚገኙ ችግሮችን ለመፍታት እየተሰራ ነው
....//....
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ሪጅን በሚያከናውናቸው የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች ላይ እያጋጠሙ የሚገኙ ችግሮችን ለመፍታት እየተሰራ መሆኑን በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ።
በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች ከሰሜን ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች ጋር ውይይት አካሒደዋል፡፡
ውይይቱ በሪጅኑ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች በሥራው ላይ እያሳደሩት ስለሚገኘው ተፅዕኖ እና ችግሮቹ በሚፈቱበት ዙሪያ ላይ ያለመ መሆኑም ነው የተገለፀው፡፡
የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ሮቤል ገ/ እግዚአብሔር በዚሁ ወቅት እንዳሉት በሰሜኑ የሃገሪቱ ክፍል ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር ሳቢያ ጉዳት ደርሶባቸው ለነበሩ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ዘላቂ መፍትሔ መስጠት ባለመቻሉ በመደበኛ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ ይገኛል።
ሪጅኑ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እንዲያስችለው የመልሶ ግንባታ ሥራዎች በአፋጣኝ መከናወን እንዳለባቸውም ነው ያሳሰቡት፡፡
በሪጅኑ አንዳንድ አካባቢዎች እያጋጠሙ የሚገኙ የኃይል መቆራረጦችን ለመቅረፍ የተበላሹ ብሬከሮችን የመቀየር፣ የጣቢያዎችን አቅም የማሳደግና በዕቅድ ተይዘው የቆዩ ፕሮጀክቶችን ወደ ትግበራ የማስገባት ሥራዎች መሰራት እንዳለባቸውም አስረድተዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ከመለዋወጫ ዕቃዎች፣ ከሥራ ላይ ደህንነትና ከሥራ መሳሪያዎች አቅርቦት፣ ከብሬከር ብልሽት፣ ከጣቢያዎች አቅም ማነስና ከኃይል መዋዠቅ ጋር የተያያዙ ችግሮች እንደሚስተዋሉ በውይይቱ ላይ አንስተዋል::
ከምዘና ሥርዓት፣ ከዕድገትና ዝውውር፣ ከጥቅማ ጥቅም፣ ከሠራተኞች አቅም ግንባታና ከኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ስርቆት ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባም ነው ያስረዱት፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 21 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
+7
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በተከታታይ ሁለት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል
...///...
በድሬዳዋ ስቴዲየም በተከናወነው የ3ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ መድን ጋር ተጫውቶ ነጥብ ተጋርቷል።
ሁለቱ ቡድኖች ትናንት ምሽት 1 ሰዓት ባካሄዱት ጨዋታ ባዶ ለባዶ ተለያይተዋል።
በመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ኢትዮጵያ መድኖች ኳስን ተቆጣጥሮ በመጫወት የተሻለ የተንቀሳቀሱ ሲሆን ኢትዮ-ኤሌክትሪኮች በአንፃሩ ጥንቃቄ የተሞላበት የአጨዋወት ስልት ሲከተሉ ተስተውሏል።
በሁለቱም ቡድኖች በኩል ቀዝቃዛ የጨዋታ እንቅስቃሴ የታየበት ይህ ጨዋታ የረባ የኳስ ሙከራ ሳያስመለክት ተጠናቋል።
የዛሬውን ውጤት ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከሶስት ጨዋታዎች ሁለት ነጥብ መሰብሰብ ችሏል።
በ4ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከባህርዳር ከነማ ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም የሚጫወት ይሆናል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 21 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
የተቋረጠው ኃይል ሙሉ በሙሉ ተገናኝቷል
......///......
በደብረ ብርሃን ቁጥር አንድ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በሁለት የባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ላይ ባጋጠመ ችግር ምክንያት ተቋርጦ የቆየው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ መመለሱን የማዕከላዊ አንድ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ።
በመምሪያው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌትነት ተስፋዬ እንደገለፁት በደብረ ብርሃን ከተማና በዙሪያው በሚገኙ አራት ወረዳዎች ለ24 ሰዓት ተቋርጦ የቆየውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት መልሶ ለማገናኘት የሪጅኑ ጥገና ሠራተኞች ርብርብ ሲያደርጉ ቆይተዋል።
ተቋርጦ የቆየውን የኤሌክትሪክ ኃይል ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ዳግም ማገናኘት ተችሏል ያሉት አቶ ጌትነት በጥገና ሥራው ላይ ርብርብ ሲያደርጉ ለነበሩ የጥገና ሠራተኞች በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 20 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
ዘርፉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ ሥራ ለማከናወን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀራርቦ ይሰራል፤
....//....
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የንብረት አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ዘርፍ በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ ከዘርፉ ሠራተኞችና ከአሽከርካሪዎች ጋር ውይይት አካሂዷል።
የዘርፉ ሥራ አሥፈጻሚ ወ/ሮ ስመኝ አያሌው እንደገለጹት ውይይቱ በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ የዘርፉ ሠራተኞችና የሥራ መሬዎች የጋራ መረዳት ኖሯቸው ተቀናጅተው ለተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ለማድረግ ነው።
በዘርፉ ለሠራተኛው ምቹ የሥራ ከባቢ ከመፍጠር፣ የተቋሙን ንብረቶችን ከማስተዳደር፣ የጥገና ሥራዎችን ከማከናወን እና የሰርቪስ ተሽከርካሪዎችን ከማቅረብ አኳያ በ2016 በጀት ዓመት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አስታውሰዋል።
ኃላፊዋ አክለውም አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን ከማስወገድ፣ የቆዩ የተቋሙ ሠነዶችን ከማደራጀት፣ ምቹ የሥራ ከባቢን ከመፍጠር እና ለሠራተኞች የሰረቪስ አገልግሎት ከመስጠት አንጻር አበረታች ሥራዎች ተከናውነዋል ብለዋል።
ሆኖም በየመጋዘኖቹ ተገዝተው የሚገቡ ብዛት ያላቸው የተለያዩ የሥራ ክፍል ዕቃዎች ቶሎ ያለመውጣት፣ ከፍተኛ የቦታ ጥበት፣ በዕቃ ግምጃ ቤት ቅጥር ግቢ የኢንተርኔት ችግር መኖር፣ የአንዳንድ ዕቃዎች መመዘኛ መስፈርት ማግኘት አለመቻል፣ የስቶር ግንባታው በታቀደለት ጊዜ አለመጠናቀቅ፣ የመለዋወጫ ችግር እና የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ የማስወጣት ሥራ በዕቅዱ መሠረት አለመፈጸም ያጋጠሙ ችግሮች መሆናቸው ተገልጿል።
እንደ ሥራ አስፈጻሚዋ ገለጻ በ2016 በጀት ዓመት የተከናወኑ ሥራዎች ለ2017 በጀት ዓመት እቅድ መደላድል የፈጠረ መሆኑን አስታውሰዋል።
በ2017 በጀት ዓመት የተቋሙን ንብረት አያያዝና አጠቃቀም መመሪያ አውጥቶ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰራ የተናገሩት ወ/ሮ ስመኝ 600 ለሚሆኑ የተቋሙ ተሽከርካሪዎች ጂፒኤስ መገጠሙንና በዚህ ዓመት ሥራ ላይ እንደሚውል ጠቁመዋል።
ሥራ አስፈጻሚዋ አክለውም ተቋሙ ያሉት ተሽከርካሪዎችን በአግባቡ ተጠግነው ሥራ ላይ እንዲውሉ የመካከለኛ ጋራዥ በዚሁ በጀት ዓመት ግንባታው እንደሚጀመር ገልጸዋል።
ከመለዋወጫ እቃ እጥረት፣ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ያለው የይዞታና ንብረቶች ጉዳይ በዘላቂነት ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሠራ ተናግረዋል።
በውይይቱ ላይ የመምሪያ ኃላፊዎች የ2017 በጀት ዓመት ዕቅዳቸውን አቅርበው ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 20 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
ዘርፉ ከሰሜን ሪጅን የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር ውይይት እያካሄደ ይገኛል
....//....
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ከሰሜን ሪጅን የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር በሪጅኑ እየተከናወኑ ስላሉ ሥራዎች እና ተግዳሮቶች ዙሪያ በመቐለ ከተማ ውይይት እያካሄደ ይገኛል።
በውይይቱ ላይ የተገኙት በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንደተናገሩት ውይይቱ ሪጅኑ በሚያከናውናቸው ሥራዎች ላይ እያጋጠሙ ባሉ ችግሮች ላይ ውይይት በማድረግ የቀጣይ የሥራ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው።
ከዚህ በተጨማሪም የሪጅኑ ሠራተኞች በአካባቢው የነበረውን ችግር ተቋቁመው ላከናወኑት ሥራ በዘርፉ እውቅና ለመስጠት ዓላማ ያደረገ እንደሆነም አመላክተዋል።
ከሪጅኑ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር እየተካሄደ ያለው ውይይት ሪጅኑ ድጋፍ የሚፈልግበትን ጉዳዮች ግብዓት በመሰብሰብ በቀጣይ ለጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እንደሚያግዝም አቶ ጋሻው ተናግረዋል።
የሰሜን ሪጅን ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሮቤል ገ/ እግዚአብሔር በበኩላቸው ውይይቱ በሪጅኑ የሚነሱ የተለያዩ ችግሮችን በመውሰድ እልባት ለመስጠት ያስችላል ብለዋል።
መስከረም 20 እና 21 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ውይይት ላይ የሪጅኑ የማከፋፈያ ጣቢያዎች፣ የማስተላለፊያ መስመርና የፋይበር ኦፕቲክስ የኦፕሬሽንና ጥገና ኃላፊዎችና ሠራተኞች እንዲሁም በሪጅኑ ስር የሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊዎች እንደሚሳተፉበት አቶ ሮቤል ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት ውይይቱ ከኃይል ማስተላለፊያ መስመር የኦፕሬሽንና ጥገና ሠራተኞች ጋር በመካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን ከሰዓት በኋላም ከማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና የጥገና ሠራተኞች ጋር የሚቀጥል ይሆናል።
ከውይይቱ በተጨማሪ በሪጅኑ በሚገኙ አንዳንድ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ጉብኝት እንደሚካሄድ ከመርሃ ግብሩ ለመረዳት ተችሏል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 20 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
ማመንጫ ጣቢያው በበጀት ዓመቱ 296 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማመንጨት አቅዷል
……..////…….
የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በተያዘው የ2017 በጀት ዓመት 296 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ማቀዱን የጣቢያው የኦፕሬሽን ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ታረቀኝ ተመስገን እንደገለፁት ጣቢያው በ2016 በጀት ዓመት 175 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማምረት አቅዶ 125 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማመንጨት ችሏል።
የ2017 በጀት ዓመት ዕቅዱን ለማሳካትና መደበኛ የኦፕሬሽን ሥራውን አስተማማኝ ለማድረግ ከፕሮጀክት ቢሮ እና ሥራ ተቋራጩ ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝም አቶ ታረቀኝ ገልፀዋል።
የኃይል ማመንጫ ጣቢያው በግንባታ ሂደት ላይ ሆኖ ኤሌክትሪክ ማመንጨት መጀመሩ ተጨማሪ ኢነርጂ ወደ ብሔራዊ ኃይል ቋት እንዲገባ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል።
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በጣቢያው ከተተከሉት 32 የንፋስ ተርባይኖች ውስጥ በአሁኑ ወቅት 23ቱ ኃይል በማመንጨት ላይ ይገኛሉ።
በተያዘው በጀት ዓመት በፍተሻና ሙከራ ላይ የሚገኙ 8 ተርባይኖችን በመረከብና ወደ ኦፕሬሽን በማስገባት ኃይል የሚያመነጩትን የንፋስ ተርባይኖች ቁጥር ወደ 31 ከፍ ለማድረግ ይሰራልም ብለዋል።
የኃይል ማመንጫው የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራዎች ከፕሮጀክቱ ባለሙያዎች ጋር በጥምረት እየተከናወነ በመሆኑ የዕውቀት ሽግግሩ በከፍተኛ ሁኔታ እያገዛቸው እንደሚገኝ አቶ ታረቀኝ ጠቅሰዋል።
ለጣቢያው የኦፕሬሽን ሠራተኞች እየተገነቡ የሚገኙት መኖሪያ ቤቶች በጥራትና በፍጥነት ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት እንዲጀምሩ ለማድረግ ከፕሮጀክት ቢሮው ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝም ገልፀዋል።
በኃይል ማመንጫው አካባቢ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በአስተዳደር ክፍሉ አማካኝነት ተደጋጋሚ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች መከናወናቸውን አቶ ታረቀኝ ተናግረዋል።
120 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ መንግስትና ከቻይና ኤግዚም ባንክ በተገኘ 270 ሚሊየን ዶላር እየተገነባ የሚገኝ ፕሮጀክት ነው።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 18 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ነጥብ ተጋርቷል
........///.......
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው ጨዋታ ባዶ ለባዶ በሆነ ውጤት ተለያይቷል።
ተመጣጣኝ የኳስ ቁጥጥር በተስተናገደበት በዚህ ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ያገኙትን የግብ ዕድል ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል።
በኢትዮ-ኤሌክትሪክ በኩል ፈቃዱ ዓለሙና አሸናፊ ጥሩነህ ጥሩ የማግባት ዕድል ቢያገኙም በቡናዎች የግብ ዘብ መክኖባቸዋል።
ኢትዮጵያ ቡና በበኩሉ በጋናዊው ተጫዋች ኮንኮኒ ሀፋዝ እና በአንተነህ ተፈራ አማካኝነት ያልተሳኩ የጎል ሙከራዎችን አድርገዋል።
ውጤቱን ተከትሎ በፕሪሚየር ሊጉ ሁለት ጨዋታዎችን ያከናወነው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የመጀመሪያውን አንድ ነጥብ አግኝቷል።
በሶስተኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው ሰኞ መስከረም 20 ቀን 2017 ዓ.ም ከኢትዮጵያ መድን ጋር የሚጫወት ይሆናል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 17 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
የፕሮጀክቱ ሠራተኞች የመስቀል ደመራ በዓልን አከበሩ
……..///………
በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በግንባታ ሥራ ላይ የሚገኙ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች የደመራ በዓልን በድምቀት አክብረዋል።
ትናንት አመሻሽ ላይ በተከናወነው መርሃግብር የፕሮጀክቱ የሥራ ኃላፊዎች እና የፕሮጀክቱ አማካሪ ድርጅት አመራሮች በጋራ ደመራውን ለኩሰዋል።
የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የአስተዳደር እና አገልግሎቶች ሥራ አስኪያጅ አቶ ክብሮም ገ/መድህን እንደገለፁት የፕሮጀክት ሥራዎች 24 ሰዓት የሚከናወኑ በመሆናቸው ሠራተኞች በዓላትን በኘሮጀክት ቦታ በድምቀት በማክበር ቤተሰባዊነት እንዲሰማቸው ማድረግ ያስፈልጋል።
በበዓሉ ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙዩኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍስሐ ጌታቸው በበኩላቸው እንዲህ ዓይነት በዓላትን በሥራ ቦታ ላይ ማክበር ሠራተኞች በዓላትን በደስታ እንዲያሳልፉና ለቀጣይ ስራ እንዲነሳሱ ያደርጋል ብለዋል።
አብዛኞቹ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችና ፕሮጀክቶች ከከተማ የራቁ በመሆናቸው በበዓላት ወቅት መሰል ሁነቶችን ማዘጋጀት ሠራተኞችን ከማነቃቃት አንፃር ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑንም ነው የተናገሩት።
የፕሮጀክቱ አማካሪ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ካርሎስ ማርቲኔዝ በበኩላቸው የደመራ በዓል ለየት ያለ ስሜት የፈጠረባቸው መሆኑን ገልፀው ለሁሉም የፕሮጀክቱ ሠራተኞች እና የስራ ኃላፊዎች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በዕለቱ የተለያዩ የመዝናኛ መርሀግብሮች የተከናወኑ ሲሆን የኮንታ የሙዚቃ ባንድ የተለያዩ ጣዕመ ዜማዎችን በማቅረብ በሺዎች የሚቆጠሩ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች በዓሉን በደስታ እንዲያሳልፉ አድርጓል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 17 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ታዳጊ እግር ኳስ ቡድን ሻምፒዮን ሆነ
........///........
የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከ17 ዓመት በታች ታዳጊ እግር ኳስ ቡድን በሐዋሳ ከተማ በተካሄደው የኢትዮጵያ ሻምፒዮና አሸናፊ በመሆን የዋንጫ እና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸልሟል።
በዛሬው ዕለት ሐዋሳ ስታዲየም በተካሄደው የፍፃሜ ጨዋታ የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ታዳጊ ቡድን የሲዳማ ክልል አቻውን በማሸነፍ የውድድሩ ሻምፒዮን ሆኗል።
ሁለቱ ቡድኖች በመደበኛው 90 ደቂቃ ባዶ ለባዶ የተለያዩ ሲሆን አሸናፊውን ለመለየት በተሰጠው የፍፁም ቅጣት ምት የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ታዳጊ ቡድን 4 ለ 3 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።
የኢትዮ ኤሌክትሪክ ታዳጊ ተጫዋች ተመስገን ማናዬ በኮከብ ተጫዋችነት የተመረጠ ሲሆን የቡድን አጋሩ ሙባረክ አረቦ ደግሞ ኮከብ ግብ አግቢ በመሆን ተሸልሟል።
በተጨማሪም የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ሙሉጌታ በዳዳ ኮከብ አሰልጣኝ እንዲሁም ተስፈኛው ታዳጊ ብሩክ ዘላለም ኮከብ ግብ ጠባቂ በመሆን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ከአቶ ባህሩ ጥላሁን ሽልማታቸውን ተረክበዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
የህብረት ሥራ ማህበሩ በሥራ ላይ ጉዳት ለደረሰባቸው ሠራተኞች የበዓል ስጦታ አበረከተ
.........///.........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ ህብረት ሥራ ማህበር የሥራ አመራር ቦርድ አባለት በሥራ ላይ ጉዳት ደርሶባቸው በደጃዝማች ባልቻ ጠቅላላ ሆስፒታል ህክምናቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ሠራተኞችን በመጠየቅ የበዓል ስጦታ አበርክተዋል፡፡
ስጦታው ከባህር ዳር፣ ከሆለታ ከቡራዩ እና ከደራ አካባቢዎች ጉዳት ደርሶባቸው ለመጡ አራት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች የተበረከተ ሲሆን ለእያንዳንዳቸው የ10 ሺህ ብር የበዓል ስጦታ እናእንኳን አደረሳችሁ ካርድ ተበርክቷል።
የህብረት ሥራ ማህበሩ የሥራ አመራር ቦርድ ሰበሳቢ አቶ አንበሴ ግዛቸው እንደተናገሩት ማህበሩ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በጀት መድቦ የተለያዩ ድጋፎችን እና ተግባሮችን እያከናወነ ይገኛል፡፡
ከእነዚህም ውስጥ የሥራ ላይ ጉዳት ደረሶባቸው ህክምናቸውን ለሚከታተሉት የሁለቱ ተቋም ሠራተኞች ጥየቃ እና የበዓል ስጦታ አንዱ ነው ብለዋል ፡፡
እንደ አቶ አንበሴ ገለፃ የማህበሩ አባል ያልሆኑ የሁለቱ ተቋማት ሠራተኞች አባል በመሆን ማህበሩ የሚሰጠውን አገልግሎት የበለጠ ሊያጠናከሩ ይገባል፡፡
በሥራ አመራር ቦርዱ የማህበራዊ ዘርፍ ሰብሳቢ አቶ ደመላሽ ንጉስ እንደተናገሩት በህክምና ላይ የሚገኙት ሠራተኞች ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የመጡ እንደመሆናቸው የጥየቃ ፕሮግራሙ ቤተሰባዊ ቅርርብ እና ለታካሚዎቹ በጎ ሞራል ለመፍጠር ያግዛል።
የሥራ አመራር ቦርዱ ከ2015 ዓ.ም. ጀምሮ የሥራ ላይ ጉዳት ደርሶባቸው ህክምናቸውን ለሚከታተሉ የሁለቱ ተቋማት ሠራተኞችን የህብረት ሥራ ማህበሩ አባል ቢሆኑም ባይሆኑም በመጠየቅ ያለ አድልኦ ሥጦታው እየሰጠ እንደሚገኝ አቶ ደመላሽ ጠቁመዋል ፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ ህብረት ሥራ ማህበር ሥራ አሰኪያጅ አቶ መዝገበ ታከለ በበኩላቸው ማኅበሩ ለገንዘብ ቁጠባ እና ለብድር ብቻ የተቋቋመ ላለመሆኑ እና በማቋቋሚያ ደንቡ የተሰጠውን ኃላፊነት እየተወጣ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
እንኳን አደረሳችሁ!
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለመስቀል በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡
በዓሉ የሰላም፣ የአብሮነት እና የደስታ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ፡፡
አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር)
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
