en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 696 subscribers, ranking 8 049 in the Technologies & Applications category and 2 173 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 696 subscribers.

According to the latest data from 02 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 141 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 28.59%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.37% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 487 views. Within the first day, a publication typically gains 2 569 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 696
Subscribers
No data24 hours
+147 days
+14130 days
Posts Archive
ከተረዳዳንና ከተባበርን የማይሳካ ነገር እንደማይኖር በኮይሻ አካባቢ የተገኘው ውጤት ማሳያ ነው ...............//.......... ከተረዳዳንና ከተባበርን የማይሳካ ነገር እንደማይኖር በጎፋ ዞን መለኮዛ ወረዳና አካባቢው የተገነቡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ማሳያ ናቸው ሲሉ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ ገለፁ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ዊ ቢውልድ ኩባንያ የጋራ ትብብር በጎፋ ዞን መለኮዛ ወረዳ ባንካ ቀበሌ ባንካ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ላይ የተገነቡ የመማሪያ ክፍሎች በዛሬው እለት ተመርቀዋል። ምርቃቱ ላይ የተገኙት የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ እንደተናገሩት አካባቢው የበርካታ ተፈጥሮ  ፀጋዎች ባለቤት ቢሆንም ባለው የመሰረተ ልማት እጥረት ምክንያት ጥቅም ላይ ሳይውል ቆይቷል። ይሁንና የኮይሻ ፕሮጀክት በአካባቢው ከመጣ በኋላ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የዊ ቢውልድ ኩባንያ ባከናወኗቸው የመሠረተ ልማት ግንባታዎች የአካባቢው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እየተነቃቃ ይገኛል ብለዋል። በዛሬው እለት ለምረቃ የበቁ የመማሪያ ክፍሎች በአካባቢው ያለውን የትምህርት ተደራሽነት በማስፋት በእውቀት የታነፀ ትውልድ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱም ተናግረዋል። እንደ ዋና አስተዳዳሪው ገለፃ ፕሮጀክቱ ከመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች ባለፈ በዞኑ በሚከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎች ላይ ሰብዓዊ ድጋፎችን በማድረግ የማህበረሰብ አለኝታነቱን እያሳየ ይገኛል። ተቋማቱ እያደረጉ ላሉት ሁሉን አቀፍ ድጋፍም አመስግነዋል። "ከተባበርንና በጋራ ከቆምን ሀገር መለወጥ እንደምንችል በአካባቢው ከተገኘው ውጤት ተገንዝበናል" ያሉት ኢንጂነር ዳግማዊ ሀገሪቱ ያላትን ፀጋ ጥቅም ላይ ለማዋል ሁሉም በአንድነትና በትብብር መስራት እንደሚጠበቅበትም አስገንዝበዋል።  በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮይሻ ፕሮጀክት የአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ ፕሮጀክቱ በአካባቢው መተግበር ከጀመረ ወዲህ ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የጤና፣ የውሃ፣ የመንገድ፣ የትምህርት ወዘተ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስታውሰዋል። በጅማ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ በቆዩ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች እየተመራ ለምረቃ የበቁት የትምህርት መማሪያ ክፍሎች ተቋሙ ለማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች የሰጠውን ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል። በትምህርት ቤቱ ላይ ለተገነቡ አራት የመማሪያ ክፍሎች እና አንድ የአስተዳደር ቢሮ 17 ነጥብ 6  ሚሊዮን ብር  ወጭ መደረጉን ጠቁመዋል። የተማሪዎቹ አስተባባሪ አቶ ኤሊያስ ኤካ በበኩላቸው ተማሪዎች በአካባቢው ያለውን የትምህርት ተደራሽነት እጥረት ከግንዛቤ በማስገባት የትምህርቱ አካል የሆነውን የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራ በትምህርት ዘርፍ ላይ ማድረጋቸውን ገልፀዋል። ለመማሪያ ክፋሎቹ ግንባታ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኮይሻ ፕሮጀክት ሥራ ተቋራጩ ዊ ቢውልድ ኩባንያ በገንዘብ፣ በጥሬ ዕቃ እና በሰው ሀይል ድጋፍ ማድረጋቸውን ጠቁመው ለተደረገላቸው ድጋፍም ተቋማቱን አመስግነዋል። በዕለቱ ለትምህርት ቤቱ ግንባታ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላት እውቅና ተሰጥቷል። በምረቃ ሥነ- ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይና የጄነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን እና የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት  ጀማል አባፊጣ(ዶ/ር) ጨምሮ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው የሴኔት አባላት፣ የአካባቢው የመስተዳደር አካላት፣ የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎችና የትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ አካላት ተገኝተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

ተመራቂዎች ያገኙትን ዕውቀት ከልምዳቸው ጋር አቀናጅተው በአግባቡ ሥራ ላይ ማዋል ይጠበቅባቸዋል- ኢንጅነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን ሠራተኞች በትምህርት ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ ሀገራዊ ግደታቸውን በአግባቡ መወጣት እንደሚጠበቅባቸው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጄነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አሳሰቡ። ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ ኪዳን ለተመራቂ የኮይሻ ፕሮጀክት ሠራተኞች የእንኳን ደሥ አላችሁ መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት እንደገለጹት ተቋሙ የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል የመሆን ራዕዩንና የያዘውን የስትራቴጂክ ዕቅድ ለማሳካት ብቃት ያለው የሰው ኃይል ያስፈልጋል። በዚህም ተቋሙ ከአጫጭር ስልጠናዎች በተጨማሪ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችንና የፕሮጀክት ሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲ በተቋሙ የሰው ኃይል ልማት ላይ የበኩሉን አሻራ እያሳረፈ ከሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካከል አንዱ መሆኑን አስታውሰው በአሁኑ ወቅትም ተቋሙ ከዩኒቨርሲቲው ጋር ያለውን ትበብር በማጠናከር የኮይሻ ፕሮጀክት ሠራተኞች ከመደበኛ ሥራቸው ጎን ለጎን የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው  እንዲከታተሉ በማድረግ ማስመረቅ ተችሏል ብለዋል። የትምህርት መርሃ ግብሩ የሥራ ልምድን ከንድፈ-ሀሳብ ባጣመረ መልኩ በመሠጠቱ  ለተቋሙ ብቃት ያለው ሠራተኛ በማፍራት በኩል ከፍተኛ ሚና እንዳለው የተናገሩት ኢንጂነር ኤፍሬም ተማሪዎች ከፕሮጀክቱ ጋር ተያያዥነት ባላቸው ጉዳዮች ላይ የሰሩዋቸው የመመረቂያ ጽሑፎች ለተቋሙ በግብዓትነት እንደሚያገለግሉም አስታውቀዋል ። ዩኒቨርስቲው የተቋሙን ሠራተኞች አቅም ለማሳደግ እያደረገ ላውን ጥረት እና የዛሬ ተመራቂዎች ለስኬት እንዲበቁ ላበረከተው አስተዋፅኦ አመስግነው ተቋሙ በቀጣይ በሰው ኃይል ልማትና በሌሎች መስኮች ከዩኒቨርስቲው ጋር የሚኖረውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ኢንጂነር ኤፍሬም አረጋግጠዋል። በቀጣይ በተለያዩ የሥራ ቦታዎች ያሉ ሠራተኞችን አቅም በማሳደግ ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት የትምህርት እድሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ተመራቂዎቹ በትምህርት ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀት ከልምዳቸው ጋር በማቀናጀት በፕሮጀክቱ ቆይታም ሆነ ወደፊት  በሚሰማሩበት የሥራ መስክ የተጣለባቸውን  ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ  ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው አሳስበዋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው  "በማህበረሰብ ውስጥ ነን" በሚል መርሁ  የማህበረሰብ አገልግሎቶቹን እያከናወነ  እንደሚገኝ ገልፀው ለፕሮጀክቱ ሠራተኞች የተሰጠው የትምህርት ፕሮግራም ዩኒቨርሲቲው የማህበረሰቡ መሆኑን በተግባር ማረጋገጥ የተቻለበት ነው ብለዋል። ኮይሻ ፕሮጀክት የሀገራችን የማንሰራራት ያረጋግጣሉ ብሎ ዩኒቨርሲቲው ከለያቸው ፕሮጀክቶች አንዱ በመሆኑ የሠራተኞቹን አቅም ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በዚህም የፕሮጀክቱን ሠራተኞች ከሥራቸው ጎን ለጎን በሥራ ቦታቸው ላይ ሄዶ በማስተማር ማስመረቅ መቻሉን አስረድተው በዘርፉ ብቃት ያለው ባለሙያ ለማፍራት ዩኒቨርሲቲው ከተቋሙ ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። ከተመራቂ ሠራተኞች መካከል ኤሊያስ ኤካ እና ተወዳጅ በቀለ  እንደተናገሩት ትምህርቱ  በመደበኛ ሥራቸው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሳያሳድርባቸው አጠናቀው በመመረቃቸው ደስታቸውን ገልፀዋል፡፡ በትምህርት ቆይታቸው ለሥራቸው ግብዓት የሚሆኑ ተጨማሪ እውቀቶችን እንዳገኙ የገለፁት ተመራቂዎቹ  የተከታተሉት የትምህርት መስከ በሥራቸው ላይ ውጤታማ  እንዲሆኑ እንደሚረዳቸውም አስረድተዋል፡፡ በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው ትምህርቱን እንዲከታተሉ ተቋሙና ፕሮጀክቱ ላደረጉላቸው ድጋፎች አመስግነው  የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9

የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች የኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ጎበኙ .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ፕሮጀክትን የሥራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል። የሥራ ኃላፊዎቹ የዋናውን ግድብና የኃይል ማመንጫ ቤቱን የግንባታ ሥራ እንዲሁም የግንባታ ግብዓት  ማምረቻ ወርክ ሾፖችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። በጉብኝቱ ፕሮጀክቱ የደረሰበትን ደረጃና የአሰራር ሂደት፣ ፕሮጀክቱ እያከናወነ ስላለው የማህበራዊ አገልግሎት ሥራዎች እንዲሁም ግንባታውን በተያዘለት መርሃ ግብር ለማጠናቀቅ በቀጣይ መከናወን ስለሚኖርባቸው ሥራዎች የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ መብራቱ ተሾመ ለሥራ ኃላፊዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። ሥራ አስኪያጁ በማብራሪያቸው ፕሮጀክቱ በፋይናንስና ችግር ምክንያት ተጓቶ የነበረ ቢሆንም በተቋሙና በመንግስት በተወሰዱ እርምጃዎች አሁን የግንባታ ሥራው በጥሩ ሂደት ላይ ይገኛል ብለዋል። በዚህም በአሁኑ ወቅት የዋናው ግድብ የጥቅጥቅ ኮንክሪት ሙሌት 70 በመቶ፣ የማመንጫ ቤቱ  የመጀመሪያ ደረጃ የአርማታ ኮንክሪት 68 በመቶ እንዲሁም የግድቡ የውሃ ማስተንፈሻ የስትራክቸራል ኮንክሪት ሥራ 30 በመቶ ላይ መድረሱን አብራርተዋል። ግድቡ ሲጠናቀቅ ከሚኖረው 201 ሜትር ከፍታ አሁን ላይ በአማካኝ ከ120 ሜትር በላይ መድረሱን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀም ደግሞ 72 በመቶ ላይ ደርሷል ነው ያሉት። በቀጣይ በኤሌክትሮ ሜካኒካልና ሀይድሮሊክ ስቲል ስትራክቸር ገጠማ ሥራዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራና ይህም የከፍተኛ አመራሩን የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል። እንደ አቶ መብራቱ ገለፃ ጉብኝቱ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ፕሮጀክቱ የደረሰበትን ደረጃ ተመልክተው በቀጣይ ለሚከናወኑ ሥራዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ እና ለችግሮቹ አፍጣኝ እርምጃዎችን እንዲሰጡ ያስችላል። ከጅማ እስከ ጭዳ ባለው መንገድ ላይ የሚስተዋለው ችግር በፕሮጀክቱ ዕቃዎች ማጓጓዝ ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ በመሆኑ ከፍተኛ ሥራ አመራሩ ችግሩ እንዲቀረፍ እያከናወነ ያለውን ሥራ አጠናክሮ እንዲቀጥልም አሳስበዋል። በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የጄነሬሽን ቢዝነስ  ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ ኪዳን እና የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ የፋይናንስ ችግር ገጥሞት  እንደነበር በማስታወስ የግንባታ ሥራውን ለማስቀጠል ተቋሙ አሁን ላይ አብዛኛውን ክፍያዎች በራሱ እየሸፈነ ስለመሆኑም ገልፀዋል። የመስክ ምልከታው  የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ የደረሰበትን ደረጃና ያጋጠሙ ችግሮችን በጋራ ለይቶ ለችግሮቹ ወቅታዊ መፍትሔ በመስጠት የፕሮጀክቱን አፈፃፀም ለማሻሻል እንደሚያግዝ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪም ጉብኝቱ በቀጣይ መከናወን ስለሚኖርባቸው ሥራዎች  አቅጣጫ ለማስቀመጥ የሚያስችል ሲሆን ምልከታው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

በተለያዩ የትምህርት መስኮች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች የምረቃ ሥነ -ሥርዓት እየተካሄደ ነው የጅማ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ከዊ ቢውልድ ኩባንያ ጋር በመተባበር በሁለተኛ ዲግሪ ያስተማራቸውን 37 የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞችን በዛሬው ዕለት እያስመረቀ ነው፡፡ በምረቃ ሥነ -ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይና በተቋሙ የጄኔሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን እና የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣን(ዶ/ር) ጨምሮ ሌሎች የተቋሙ ከፍተኛ  የሥራ ኃላፊዎች፣  የዩኒቨርሲቲው የሴኔት አባላት፣ የኮንታና ጎፋ ዞኖች ዋና አስተዳሪዎችና ሌሎች የአካባቢው የመስተዳድር አካላት የፕሮጀክቱ  የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፣  የተመራቂ ቤተሰቦች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ተቋሙ በኃይል ማመንጫ ጣቢያ እና በፕሮጀክቶች ላይ የሚገኙ ሠራተኞች በየአካባቢያቸው ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር ከመደበኛ ሥራቸው ጎን ለጎን በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው የትምህርት ዕድል የሚያገኙበትን ምቹ ሁኔታ እየፈጠረ ሲሆን በዛሬው ዕለት የሚመረቁ የኮይሻ ፕሮጀክት ሠራተኞችም የዚሁ ተጠቃሚ ናቸው። ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለፕሮጀክቱ ሠራተኞች የተሰጠው የትምህርት እድል በኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመቻቸ ስለመሆኑም ተገልጿል። ከተመራቂዎች መካከል አስሩ በኮንስትራክሽን ኢንጂነሪንግና ማኔጅመንት፣ 14 በፕሮጀክት ማኔጅመንት እና ፋይናንስ እንዲሁም 13 በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን የትምህርት መስክ የተከታተሉ ናቸው። ከዚህ ውስጥ 33 ወንድና ሦስቱ ሴቶች ናቸው። ሠራተኞች በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው ትምህርታቸውን መከታተላቸው በሥራ ቦታዎች ላይ የሠው ኃይል እጥረት እንዳያጋጥም ያግዛል። ከሠራተኞች ምርቃት በተጨማሪ በተመራቂ ሠራተኞች አስተባባሪነት የተገነባ ትምህርት ቤት ምርቃት እንዲሁም የኃይል ልማት ዘርፉን ለማሳደግ በተቋሙና በዩኒቨርሲቲው መካከል ያለው የትብብር ሥራ ተጠናክሮ በሚቀጥልበት መንገድ ላይ ውይይት ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

ኬንያ ከውጭ ከምትገዛው ኤሌክትሪክ 83 በመቶውን የምትገዛው ከኢትዮጵያ ነው ….…///….… ኬንያ ከውጭ ከምትገዛው አጠቃላይ የኃይል አቅርቦቷ ውስጥ 83 በመቶው ከኢትዮጵያ የተገኘ መሆኑን ካፒታል ኤፍ ኤም የተሰኘው የሀገሪቱ ሬዲዮ ገለጸ፡፡ የመረጃ ምንጩ የሀገሪቱን የኢነርጂና ነዳጅ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣን ጠቅሶ እንደዘገበው ኬንያ  እስከ ሰኔ ወር 2017 ዓ.ም. ድረስ ከውጭ ካስገባችው ጠቅላላ የኤሌክትሪክ ኃይል 83 በመቶው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገኘ ነው፡፡ ኬንያ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በፈጠረችው የኃይል ትስስር ከዚህ ቀደም ሀገራዊ የኤሌክትሪከ ፍላጎቷን ለማሟላት ለነዳጅ እና ለሌሎች አማራጭ የኃይል ምንጮች የምታወጣውን ከፍተኛ ወጪ አስቀርቶላታል ፡፡ በዚህም ኬንያ በዓመት 10 ሚሊየን ዶላር ገደማ  ማዳን መቻሏን ሬዲየው አስታውቋል፡፡ የኬንያው ቢዝነስ ዴይሊ አፍሪካ ጋዜጣ በበኩሉ የኢትዮጵያ  የኃይል  አቅርቦት  በኬንያ ሊፈጠር የሚችለውን የኃይል ቀውስ በመከላከል ረገድ ወሳኝ  መሆኑን በመጥቀስ “ኢትዮጵያ ኬንያን ከመብራት መጥፋትና ከፈረቃ ታድጋለች” ሲል ዘግቧል፡፡ ኢትዮጵያ እና ኬንያ ቀደም ሲል በተፈራረሙት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ስምምነት መሰረት ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ በቀን በከፍተኛ ጭነት ሰዓት 200 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለኬንያ እያቀረበች ትገኛለች፡፡ ኢትዮጵያ ቀጣናውን በኃይል ትስስር ለማጠናከር በያዘችው ዕቅድ መሰረት ከኬኒያ በተጨማሪ በአሁኑ ወቅት ከጂቡቲ፣ ሱዳን እና ታንዛኒያ ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ትስስር ፈጥራለች፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከቻይናው የጂሲኤል ኢነርጅ ቴክኖሎጂ ኩባንያ ሊቀመንበር ጋር ተወያየዩ ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የቻይናው ጂሲኤል ኢነርጅ ቴክኖሎጂ ኩባንያ ሊቀመንበር ሚስተር ዡ ጎንግሃን ሁለቱ ተቋማት በትብብር በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡ የሲጂኤል ኢነርጂ ቴክኖሎጂ ኩባንያ ሊቀመንበር ሚስተር ዡ ጎንግሃን ኩባንያቸው በታዳሽ ኃይል ልማትና ኦፕሬተርነት፣ በሲልከን፣ ሊቲየም እና በሌሎች ማዕድናት ምርትና ማቀነባበር ላይ በስፋት እየተሳተፈ ስለመሆኑ ለኢንጂነር አሸብር አስረድተዋል፡፡ ኩባንያቸው በኢትዮጵያም በቅርቡ በድሬደዋ ከተማ አካባቢ በአሉሚኒየም፣ ኮባልትና ኮፐር ማቀነባበር ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳለው ገልፀው ለዚህም አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡ ፋብሪካው በአጭር ጊዜ ውስጥ 4 ሺ ሜጋ ዋት እንዲሁም በሚቀጥሉት አምስትና ስድስት ዓመታት 6 ሺ ሜጋ ዋት ኃይል እንደሚያስፈልገው ጠቅሰው ፋብሪካው ውጤታማ እንዲሆን ተቋሙ ይህን ኃይል ዝግጁ እንዲያደርግላቸውም ሊቀመንበሩ ጠይቀዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ለፋብሪካው ከሚያስፈልገው የኃይል አቅርቦት ባለፈ በተለያዩ የኃይል ልማት ዘርፎች፣ በዳታ ማይኒንግ፣ በኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያ ግንባታ እና በአቅም ግንባታ ጉዳዮች ላይ ለመሳተፍና ከተቋሙ ጋር በትብብር ለመስራት  ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው ተቋሙ ከኩባንያው ጋር በትብብር ለመስራት ፈቃደኛና ደስተኛ እንደሆነ ገልፀው ውይይቱ ፍላጎቶቹን ወደ ተግባር ለመለወጥ እንደሚረዳም ተናግረዋል፡፡ የዳታ ማይኒንግ ለኢትዮጵያ አጠቃላይ ሀገራዊ ምርት (GDP) እያበረከተ ያለው አስተዋጽዖ አነስተኛ በመሆኑ ተቋሙ አሰራሮቹን እንደገና ለማደራጀት እየሰራ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡ የሁለቱን ተቋማት በጋራ የመስራት ፍላጎት ወደ ተግባር ለመለወጥ ሥራውን የሚያስተባብር የቴክኒክ ቡድን እንዲቋቋም ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

አብዛኞቹ ግድቦች በቂ ውሃ ይዘዋል ………///……….. አብዛኞቹ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድቦች በክረምቱ የዝናብ ወቅት በቂ ውሃ መያዛቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግድብ ደህንነት ክትትል እና ቁጥጥር ሥራ አስኪያጅ ገልፀዋል። ሥራ አስኪያጁ አቶ ኤሊያስ ደላሽ እንደተናገሩት የታላቁ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ የተከዜ፣ጊቤ አንድ፣የፊንጫ እና ቆቃ ግድቦች መያዝ የሚጠበቅባቸውን የውሃ መጠን ሙሉ በሙሉ ይዘዋል። ለበለስ ኃይል ማመንጫ ጥቅም ላይ የሚውለው የውሃ ከፍታ ከሚጠበቀው 1787 ሜትር በላይ በሳንቲም ሜትሮች ከፍ ማለቱን ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመርቆ ሙሉ በሙሉ ወደ አገልግሎት መግባቱ ለሌሎች ግድቦች ውሃ የመያዝ ሥራዎችን ያሳለጠ መሆኑን አቶ ኤሊያስ ተናግረዋል። ግድቦቹ ሳይንሳዊ በሆነ ስሌት ዓመቱን በሙሉ ጥቅም ላይ እንደሚውሉም ነው የገለፁት። ኢትዮጵያ ከምታመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል 95 ከመቶ በላይ ከውሃ ኃይል ምንጭ መሆኑ ይታወቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 19 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ! የ2018 የመስቀል በዓል የሰላም እንዲሆንላችሁ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ስም ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡ በዓሉ የሠላም፣ የጤናና የአብሮነት እንዲሆን
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ! የ2018 የመስቀል በዓል የሰላም እንዲሆንላችሁ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ስም ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡ በዓሉ የሠላም፣ የጤናና የአብሮነት እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ፡፡ አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር) ዋና ሥራ አስፈፃሚ

ግድቡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ልማት ወሳኝ ነው …….///…….. ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ልማት ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ተናገሩ፡፡ ፕሬዝዳንቱ በ80ኛው የተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በአዲስ ዓመት ዋዜማ በይፋ መመረቁን አስታውሰዋል፡፡ ግድቡ ከ5 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ የማመንጨት አቅም እንዳለው የገለፁት አምባሳደር ታዬ በማገዶ እጥረት ለሚሰቃዩ የኢትዮጵያ እናቶች ኃይል በማቅረብ እፎይታ ይሰጣል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ይህ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትን ለማሳደግ እንደሚረዳም ለጉባኤው አስገንዝበዋል፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሌላቸው ከ60 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያንን የኃይል ተደራሽ ለማድረግ ታልሞ እየተሰራ ሲሆን የህዳሴ ግድብ ግንባታ የዕቅዱ አንዱ አካል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ታዬ እንደገለፁት ግድቡ ከሀገር ውስጥ ፍጆታ ባሻገር ለቀጣናዊ የኃይል ትስስርም ጉልህ አስተዋጽኦ አለው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የኑክሌር ልማት ፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረሙ …….///…….. በኢትዮጵያ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ልማት ዙሪያ በሩሲያ አቶሚክ ኢነርጂ ኮርፖሬሽን(ሮሳቶም) እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መካከል የድርጊት መርሃ ግብር ተፈረመ። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) እና የሮሳቶም ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሌክሲ ሊካቼቭ ፊርማቸውን ባኖሩበት የፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ተገኝተዋል፡፡  በፊርማ ሥነሰሥርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደተናገሩት በሩሲያ ያደረጉት ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቱን የሚያጠናክር ነው። ኢትዮጵያ ለሁሉን አቀፍ እድገት የሚውል የኑክሌር ልማት ፕሮጀክት ለመጀመር የረጅም ጊዜ ልምድ ካላት ሩሲያ ጋር ተባብራ ለመስራት ያላትን ቁርጠኝነትም ገልፀዋል። የኒውክሌር ኃይል የረጅም ጊዜ ልማትን ለማስጠበቅ፣ የኃይል ምንጮችን ለማብዛት እና የኢትዮጵያን አቅም ለማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በበኩላቸው በሩሲያ እና ኢትዮጵያ መካከል ያለው የሁለትዮሽ ግንኙነት በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ መሆኑን ጠቁመዋል። ሩሲያ በኒክሌየር ቴክኖሎጂ እና በሌሎች መስኮች ያላትን ልምድ ለኢትዮጵያ በማካፈል ለጋራ እድገት በትብብር እንደምትሰራ ጠይቀዋል፡፡ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በበኩላቸው በሩሲያ እና ኢትዮጵያ መካከል ያለው የሁለትዮሽ ግንኙነት በተረጋጋ ሁኔታ እያደገ መሆኑን  ተናግረዋል። የሀገራቱ ግንኙነቶች በዘላቂ ሁኔታ እያደጉ እና የንግድ ትስስሩም እየጨመረ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ የታላቁ የሕዳሴ ግድብን የሚስተካከል ለሰላማዊ ዓላማ ብቻ የሚውል የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ግንባታ በቅርቡ እንደምትጀምር መግለጻቸው ይታወሳል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም